Al EHSAN አል_ኢህሳን
176 subscribers
409 photos
44 videos
2 files
629 links
የቻናሉ አላማ
1 ባለን አቅም እስልምናን በአግባቡ ለኡማው ማድረስ
2 ሙስሊሞችን በድናቸውም ይሁን በዱኒያ እውቀታቸው የነቁ እንድሆኑ መገፋፋት
3 ለወጣቶች ምክር
4 በልዩ መልኩ ሴቶችን ማንቃትና ሌሎቹም አለማዊና መንፈሳዊ ት/ቶች ይገኙበታል።

ውድና የተከበራቹ የአል ኢህሳን ቻናል ቤተሰቦች ሆይ ውብና ማራኪ የሆኑ ሀሳብ አስተያያታቹ እንዳይለይን

ለአስተያት @S1u9l
አሁኑኑ ይቀላቀሉን
👇
Download Telegram
የትናንቱን ወንጀላችንን ሳንረሳ፣ የምሽቱ ኃጢታችን ሳይደርቅ ዛሬም በማለዳ ተነስተን ሌላ የምንጀምረው ነገርስ።

አላህ ሆይ!አልፋታ ብሎ ዕድሜ ልካችንን የሚከታተለንን ጥፋታችንን ቁረጥ።

ኃጢአቱ አብሮት ያልተነሳ ሰው ምንኛ ታደለ!ለንፁህ ተውበት አድለን - ያ ረብ።

https://t.me/B1e9h
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ሙስሊም ነበርን" በሚል በፕሮቴስታንቱ አለም የሚገኙ ስመ ሙስሊሞች ምዕመኑን እንዴት እንደሚያታልሉት ከዚህ መመልከት ይቻላል። ትውልደ ሶማሌ የሆነችው ይህች ሴት በGMM ቲቪ የራሷ ፕሮግራም ያላት ሲሆን ሶማሌውን ለማክፈር ሆርን ኦፍ አፊሪካ ከአሜሪካ ከነ ቤተሰቧ አምጥቶ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እያሰራት ይገኛል። ከስሟ ውጭ ግን ስለ እስልምና ምንም የምታቀው ነገር የላትም። በተለያዩ መድረኮች ግን "ሙስሊም ናት፣ የሸይኽ ቤተሰብ ናት" እየተባለች ተጋብዛ ምዕመኑን በሀሰት ትርክት ታታልለዋለች፥ ያሳዝናል..!
መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ!
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇

https://t.me/B1e9h
ብዕረ ሐኒፍ #3
🔖ሟች እና አልቃሽ

☞የሟችና አልቃሽ አስገራሚ ገፅታ!

በበስራ ከተማ ኗሪ የሆነ አላህን በጣም የሚያመልክ ሰው ወደ ሞት እየተቃረበ መጣ።
በዙሪያው ያሉ ቤተሰቦቹ ማልቀስ ጀመሩ።
ከዛም ይህ ሞት የተጣደው ሰው ለቤተሰቦቹ "ቁጭ አድርጉኝ" አላቸው።  ደግፈው አስቀመጡት።
ከዛ ወደ አባቱ ዞረና "አባቴ ለምንድነው ምታለቅሰው?" አለው።  አባትም" አንተን ማጣቴ ካንተ ቡሃላ ብቸኛ መሆኔ ነው ያስለቀሰኝ።" አለው።

ወደ እናቱም ዞረና "እናቴ ምንድነው ያስለቀሰሽ?" አላት።

እሷም "የልጅ ማጣት መሪር ሀዘን ነው ያስለቀሰኝ።" አለችው።

ወደ ሚስቱም ዞረና "ምንድነው የሚያስለቅስሽ?" አላት እሷም "ያንተን መልካም ነገር ስለማጣ ወደ ሌላ ሰው ስለምከጅል ሸክም ስለምሆን።" አለችው።

ወደ ልጆቹም ዞረና "ምንድነው የሚያስለቅሳቹ?" አላቸው። እነሱም "ከአንተ በኋላ ወደ የቲምነት፣ ወደ ውርደትና ደጋፊ ወደ ማጣት ስለምንጓዝ" አሉ።

ይሁን ሁሉ ከሰማ በኋላ ሟቹ በጣም አለቀሰ።
ቤተሰቦቹም  "ለምን ታለቅሳለህ?" አሉት።
እሱም "ሁላቹም ለኔ ብላቹህ ሳይሆን ለራሳቹህ ጥቅም ነው የምታለቅሱት። ይህን ስላየሁ አለቅሳለሁ።" አለ።

"ከናንተ ውስጥ ለጉዜዬ መርዘም ለስንቄ ማነስ የሚያለቅስልኝ የለም?
ከናንተ ውስጥ ከዚህ በኋላ መኝታዬ ለብቻዬ አፈር ለመሆኑ የሚያለቅስ የለም?
ከእናንተ ውሰጥ ከዚህ  በኋላ አስደንጋጭ ሂሳብ ስለሚጠብቀኝ የሚያለቅስ ሰው የለም?
ከእናንተ ውስጥ የአለማት ጌታ ፊት መቆሜን አስታውሶ የሚያለቅስልኝ የለም? አለና በፊት ለፊቱ ተደፋ።  ቢያንቀሳቅሱትም ህይወቱ አልፋለች። ሞቷል።

سَفَري بَعيدٌ وَزادي لَنْ يُبَلِّغَنـي
*وَقُوَّتي ضَعُفَتْ والمـوتُ يَطلُبُنـي

وَلي بَقايــا ذُنوبٍ لَسْتُ أَعْلَمُها
*الله يَعْلَمُهــا في السِّرِ والعَلَنِ.

ጉዞዬ ሩቅ ነው ስንቄም አያደርሰኝ
ሀይሌም ተዳከመ ሞትም ፈላለገኝ
የማላቃት ወንጀል አለች አሰፍስፋ
አላህ የሚያውቃት በምስጥር በይፋ

በዐብዱረዛቅ አል–ሐበሺይ

https://t.me/B1e9h
☀️እህቴ ሆይ እስቲ አንዴ ከሂወትሽ ትንሽን ደቂቃ ቀንሰሽ እህህ ብለሽ ስሚኝ ምናልባት ይጠቅምሽ ይሆናል...

قال الرسول ﷺ: "الحياء شعبة من الإيمان"
💫 ነቢዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ :- "ሀያዕ ( ማፈር ) ከኢማን ቅርንጫፎች ውስጥ ነው "

💫 ውዷ እህቴ ሀያዕ ማድረግ ለሴት ልጅ  ክብር ነው እንደውም ውበቷም ጭምር ነው ።

💫 አንዳንድ እህቶች አሉ አለባበሳቸው፣ አረማመዳቸው፣ አነጋገራቸው ሀታ ካፊሮች የሚሻሏዋቸው አላህን እንፍራ ዛሬ እንደዚ እንድትመፃደቂ እንደዚ እንድትሆኚ የሚያደርጉሽ ነገሮች ሁሉ ያልፋሉ ይጠፋሉ ግና ለሚያልፍ ነገር ለሚጠፋ ነገር ብለን የነገው አኼራችንን የንገው የዘላለማዊ ሂወታችንን አናበላሻት ...

💫 ውዷ እህቴ ዛሬ ባንቺ ንግግር፣ ባንቺ አረማመድ፣ ባንቺ አወራር ተማርከው የሚያሞግሱሽ እና የሚያደንቁሽ ነገ ከእሳት ነገ ከቀብር ጭንቀት አያድኑሽም ካንቺ ቅጣት ቅንጣትን አይጋሩልሽም ሁሉም ነፍሴ ነፍሴ ነው ሚለው ስለዚህ ዛሬ ስሜትሽን ነፍስያሽን አሸንፈሽ ለነገው ሀገርሽ ብትለፊ መልካም ነው።

💫 ወላሂ ይደንቁኛል እነዚያ ኒቃብን ለብሰው፣ ጅልባብን ለብሳ ንግግሯን፣ ሳቋን፣ ከሩቅ የምትሰሟት ያረህማን ቢያንስ ለለበስነው ልብስ ክብር ይኑረን የሰው ልጅ ያው ሰው ነው ምንም አያመጣም ነገር ግን አላህን እንፍራ የለበስነው ልብስ አይደለም ኒቃብ፣ እና ጅልባብ ሀታ ጭንቅላትሽ ግማሽ ላይ ጣል ምታደርጊያት እስከርብ አንቺን  ከመሸፈኑ ባሻገር ኢስላም የሚል ትልቅ ባንዲራን ነው ይዘሽ ምትጓዢው ባንቺ አንዲት ስህተት ጥርሳችው የወለቀለትን፣ ደማቸው የፈሰሰለትን፣ እርቧችው ሆዳቸው ላይ ዲንጋይ ያሰሩለትን የኛ ነቢይ አለይሂሙ ሰላቱ ወሰላም  ይዘውት የመጡትን ዲን ሰሀቦች አጥንታቸውን ከስክሰው ለኛ ያስረከቡትን ዲን ባንቺ ስህተት ታሰድቢዋለሽ ቢላህ አለይኩም እህቶቼ ሁሉም ነገር ያልፋል ይሄዳል ምንም ማንም ሚቀር የለም አላህ ሱብሀነሁ ወተዐላ ሲቀር ስለዚህ ለሚያልፍ ነገር የማያልፍን ድርጊት አትስሪ ይቅርብሽ ዲንሽን አጥብቀሽ ያዢ ዲንሽ ነው ላንቺ የሚሆንሽ ስሜትሽ ነፍሲያሽን አትከተዪ።

💥 አፍወን አረዘምኩት አሁን ላይ የምናየው የምንሰማው ቢፃፍ ቢፃፍ አያልቅም አላህ ሁላችንንም ከመጥፎ ነገር ይጠብቀን ።

منقول

https://t.me/B1e9h
ጌታዬ ሆይ! እስረኛህና ኸዳሚህ አድርገህ አኑረኝ፡፡ በግልጋሎትህ እስከዘላለሙ አሰማራኝ፡፡ ካንተ ጉያ የማልጠፋ፣ ከመንገድህ የማልርቅ፣ ከትዕዛዝህ የማልወጣ አድርገኝ። ቤትህን የማዘወትር፣ በቁርኣንህ የማተኩር፣ አንተን ፈርቼ የማድር ባርያህ አድርገኝ። ዘወትር ስላንተ የማስተማርና ወዳንተ የማመላክት እሆን ዘንድ አግዘኝ። ሀሳቤን ሰብስብልኝ ቃላቴን አሳምርልኝ።


https://t.me/B1e9h
እዝነት እና መተዛዘን
ኢብኑ/ሙነወር
👆👆👆👆👆👆
ይደመጥ ወሳኝ የሆነ ወቅታዊ ሙሓዶራ
“እዝነት እና መተዛዘን”
ግንቦት 20/2016 በሜክሲኮ ጀርመን ግቢ ተባረክ መስጂድ የቀረበ ሙሓዶራ

https://t.me/B1e9h
👇👇👇


በጣም የሚገርም ወንድማማችነት

ሰለፎች ዘንድ
👇


ከቀደምት ሰለፎች መካከል አንድ ሰው ወደ ጓደኛው ቤት ይሄዳል።
ጓደኛውም ምነው በዚህ ሰአት መጣህ? ይለዋል። "እሱም አራት መቶ ዲርሃም አለብኝና ክፈልልኝ" ይለዋል ።
ጓደኛውም ቤቱ ይገባና አራት መቶ ዲርሀም መዝኖ ይሰጠዋል።
ከዘም ወደ ቤቱ ገብቶ ማልቀስ ይጀምራል ሚስቱም ማልቀሱን ስታይ ገንዘቡን የሚትፈልገው ከሆነና መስጠት የማትችል ከሆነ ለምን የለኝም ብለህ ምክንያት አታቀርብም ነበር? አሁን ማልቀስህ ምን ያደርግልሃል ? አለችው

እሱም በጣም የሚገርምና ልብን የሚነካ ንግግር ተናገራት 👇

👉እኔ እኮ የማለቅሰው ወንድሜ ቤቴ ድረስ መጥቶ ቸግሮት ችግሩን እስኪነግረኝ ድረስ ወንድሜ የሚኖርበትን ሁኔታ ባለማወቄ ነው ኣላት

📚 አት-ተብሲራ 2/263
ዛሬ እኛና እነሱ ዬት ነው ያለነው ሰዎች? እኛም አሁን ከነሱ ጀነት ለመግባት እናስባለን? አላህ በእዝነቱ ይድረስልን እንጂ ከባድ ነው

https://t.me/B1e9h
አንዘርቱኩሙ ናር
አህመድ አደም
አዋጅ አዋጅ አዋጅ

ወላሂ አው ጀሃነም በጣም ያስፈራል አላህ ሁላችንም ጀሃነም ከመውረድ ይጠብቀን አደራ ሁላችንም እናድምጠው እንዳታልፍ

ሸይሃችን አህመድ አደም አላህ ይጠብቅልን

https://t.me/B1e9h
☞  ተራራን  መውጣት የፈራ, ሁሌ በሸለቆ  ውስጥ  ይኖራል❗️

☞ አኬራን የዘነጋ ሰው , በዱንያ ፍቅር እንደተጠማ ይሞታል !

☞" በኢልም ጥላ ስር ጥቂት ሰዓታትን መታገስ ያቃተው ሰው እድሜ ልኩን በጃሂልነት ጥላ ሰር ይኖራል❗️"

https://t.me/B1e9h
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ይህንን የሸይኹን መልዕክት በምገባ አድምጡት በተለይ እህቶች

ሸይኽ አብዱረዛቅ አልበድር

https://t.me/B1e9h
​​አስባቹታል ግን‼️

#ፍቅር በነፃ
#አየር በነፃ
#ንስሀ በነፃ
#የዘላለም_ህይወት በነፃ
------------------------------
#መጠጥ በክፍያ
#ዝሙት በክፍያ
#ጭፈራ_ቤት በክፍያ
#ሺሻ_ጫት በክፍያ

‼️እንዴት ከፍለን ገሀነም እንገባለን
እናስብ ወገን!!!

https://t.me/B1e9h
ጥብቅ ማሳሰቢያ ኡዲህያ ለምታርዱ በሙሉ👇



ዛሬ ዕሮብ ዙል-ቀዕደ ቀን 28 ነው ።
ይህ ማለት ደግሞ ምናልባት ወሩ በ29 ካለቀ የወሩ መጨረሻ ነገ ሐሙስ ሊሆን ይችላልነ

የወሩ መጨረሻ ነገ ሐሙስ ከሆነ ደግሞ ቀጥሎ የምጠቅሳቸውን ነገሮችን ኡዱሒያ ለሚያደርግ ሰው ማስወገድ ስለማይፈቀድለት ከአሁኑ ቅድመ ጥንቃቄ ማደረግ ይኖርበታል 👇

1 ፀጉር መቁረጥ
2 ቀድሞ ቀመስን ማሳጠር
3 ጥፍሩን መቁረጥ
4 የብብትና የብሊት ፀጉርን ማስወገድ የፈለገ ሰው ከነገ ከሐሙስ ማሳለፍ የለበትም

👉ነብዩ ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም እንዲህ ብሏሉ 👇

የዙል-ሒጃ ወር የመጀመሪያዎቹ አስር ቀናት ስገቡ ከእናንተ አንዳቹ ኡዱሒያን ማድረግ ከፈለገ ከፀጉሩም ይሁን ከሰውነቱ ምንም ነገር እንዳይነካ።

አደራ ይህንን አሳሳቢና አስቸኳይ መልዕክት ለሁሉም ሙስሊሞች በማሰራጨት ሙስሊሞችን ከስህተት እንታደግ

https://t.me/B1e9h
የዘንድሮ ወርቃማዎቹ የዙል-ሒጃ የመጀመሪያ ቀናት መቼ ይጀምራሉ?

ዛሬ ዕለተ ረቡዕ በኢትዮጵያ አቆጣጠርግንቦት 28, 2016 E.C. ነው። በኢስላማዊ ካላንደር (በሂጅሪያ) አቆጣጠር ደግሞ ዙል-ቂዕዳህ 28, 1445 H.C. ነው። በፈረንጆቹ ጁን 05, 2024 G.C. ነው።

የዙል-ቂዕዳህ ወር በ29 ቀናት ከተጠናቀቀ ከነገ በኋላ ጁሙዓህ ግንቦት 30, 2016 ይጀመራሉ። የዙል-ቂዕዳህ ጨረቃ 30 ከሞላች ግን ወርቃማዎቹ የዙል-ሒጃ 10 ቀናት ቅዳሜ ሰኔ 01, 2016 E.C. ይጀመራሉ። በኸይር ለማሳለፍ ከወዲሁ ዝግጁ እንሁን።

https://t.me/B1e9h
አስርቱ የዙልሒጃ ቀናት ||
ኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ

NesihaTv

https://youtu.be/tKFIPtXKcno

https://t.me/B1e9h
➡️ ሶስት ትላልቅ ወንዞች

ኢብኑል ቀይም ረሂመሁላሁ እንዲህ ይላል :-
" ለወንጀለኞች በዱንያ ላይ ከወንጀላቸው የሚፀዱባቸው ሶስት ትላልቅ ወንዞች አሏቸው
እነዚህ ወንዞች ካላፀዱአቸው የቂያማ ቀን በጀሀነም ወንዝ ነው የሚፀዱት


1. የተውበተ አንነሱሁ ወንዝ
2. ሀጢያትን የምታብሰው የመልካም ስራ ወንዝ
3. ወንጀልን የሚያጥብ የሙሲባ ወንዝ
አላህ ለባሪያው መልካም ከሻለት ከእነዚህ ወንዞች በአንደኛው ያስገባዋል ንፁህ የተጥራራ ሆኖ ወደ ቂያማ ከወረደ አራተኛ ማፅጃ አያስፈልገውም "

መዳሪጁ ሳሊኪን ( 1/64)

https://t.me/B1e9h
በሃገረ ሳዑዲ ዐረቢያ የወርሃ ዙል-ሒጃህ ጨረቃ ዛሬ ሐሙስ ስለታየች ነገ ጁሙዓህ ግንቦት 30, 2016 E.C. የዙል-ሒጃህ ወር የመጀመሪያው ቀን ይሆንና ወርቃማዎቹ የዙል-ሒጃህ 10 ቀናት ከነገ ይጀምራሉ። ስለሆነም ቅዳሜ ጁን 15, 2024 (ሰኔ 08, 2016 E.C.) የዕለተ ዐረፋህ ቀን ሲሆን እሁድ ጁን 16 (ሰኔ 09) ዒደ-ል-አዽሓህ ይሆናል። አላህ በሰላም ያድርሰን

እነዚህን ወርቃማ ቀናቶች በዒባዳህ ለማሳለፍ ከወዲሁ ዝግጅት አድርጉ። ቀናቶቹን ከምታሳልፉባቸው ዒባዳዎች መካከል፤ ጾም፣ ዚክር፣ ቁርኣን መቅራት፣ ሶደቃ፣ ለቻለ ሰው ሐጅና መሰል በጎ ተግባራትን ማከናወን ይገኙበታል። አላህ ያበርታን።

ሌሎችንም አስታውሱ!


https://t.me/B1e9h
👉  የዒደል አድሓ ተክቢር

     የዒደል አድሓ ተክቢራ ዙል ሒጃ ከገባበት ቀን ( የዙል ቂዕዳ ወር አልቆ የዙል ሒጃ ጨረቃ ከታየበት ጊዜ ) ጀምሮ እስከ አያሙ ተሽሪቅ መጨረሻ ድረስ ይፈቀዳል ። ይህ ልቅ የሆነው ተክቢራ ( በማንኛውም ሳአተ የሚባለው ) ሲሆን የተገደበው ወይም ከሶላት በኋላ የሚባለው ደግሞ የዙል ሒጃ 9ኛ ቀን ፈጅር ሶላት ላይ ተጀምሮ የመጨረሻው አያመ ተሽሪቅ ዐስር ሶያት ላይ ያበቃል ። ወሩ የዚክርና የመልካም ስራ ስለሆነ ከተክቢራ እንዳንዘናጋ እንጠቀምበት ።

https://t.me/B1e9h
ይህ ምልክት ነመስቲ ይባላል ። የሂንዱስ እምነት ተከታዮች የሰላምታ ምልክት ነው ።
ሂንዱሶች በአላህ መኖር የማያምኑ ከሀዲያን ናቸው ። በዚህ ምልክት የሚፈልጉበት መልእክት በውስጤ ያለው አምላክ ባንተ ውስጥ ያለውን አምላክ ሰላም ይለዋል የሚል ነው ።
የሁለቱ መዳፎች መጣመር በኔና ባንተ ውስጥ ያሉት አምላኮች ተጣምረዋል አንድ ሆነዋል የሚል እምነት አላቸው ። ይህ ኩፍር መሆኑ ግልፅና የኢስላምን አስተምሮ የሚፃረር የወሕደቲል ውጁድ ዐቂዳ ነው ። እኛ ሙስሊሞች ከእንደዚህ አይነት ምልክት የተብቃቃን ነን ።
አላህን ስንለምን ሁለቱ መዳፎቻችንን ዘርግተን ገጥመን በዚህ መልኩ " 🤲 " ነው መሆን ያለበት ። ለዚህም የሚከተለው የአላህ መልእክተኛ ንግግር መረጃችን ነው ።
قال النبيﷺ :
« اذا سألتُم الله فأسألوهُ بِبُطونِ أكفِّكُم ولا تَسألوهُ بظهورها »
الالباني صحيح أبي داود

https://t.me/B1e9h
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ስለ አስሩ የዙል ሒጃህ ቀናት አጭር ማስታወሻ!

ከነሲሓ ቲቪ

ሼር በማድረግ ሌሎች እንዲጠቀሙበት ያስተላልፉ!

https://t.me/B1e9h
ለነገህ ምን አዘጋጅተሃል?

አዎ ለቀብር ጨለማ !!
ለቂያማ ጭንቀት !!
በሲራጥ ለማለፍ !!
አላህ ፊት ቁመን ስንጠየቅ ላለው ጭንቀት !!
በጥቅሉ ከሞት በሗላ ላለው ሂወታችን  ምን አዘጋጅተናል?

አላህ (ሱብሓነሁ ወተዐላ) እንድህ ይላል:-

{ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَلْتَنظُرْ نَفْسٌ مَّا قَدَّمَتْ لِغَدٍ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ }

« እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ማንኛይቱም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡ » [ሐሽር (18)]

https://t.me/B1e9h