Al EHSAN አል_ኢህሳን
193 subscribers
412 photos
44 videos
2 files
642 links
የቻናሉ አላማ
1 ባለን አቅም እስልምናን በአግባቡ ለኡማው ማድረስ
2 ሙስሊሞችን በድናቸውም ይሁን በዱኒያ እውቀታቸው የነቁ እንድሆኑ መገፋፋት
3 ለወጣቶች ምክር
4 በልዩ መልኩ ሴቶችን ማንቃትና ሌሎቹም አለማዊና መንፈሳዊ ት/ቶች ይገኙበታል።

ውድና የተከበራቹ የአል ኢህሳን ቻናል ቤተሰቦች ሆይ ውብና ማራኪ የሆኑ ሀሳብ አስተያያታቹ እንዳይለይን

ለአስተያት @S1u9l
አሁኑኑ ይቀላቀሉን
👇
Download Telegram
ኢማም አቡ ሃቲም ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ👇


" ከንግድ ሁሉ ትርፋማው፦ አለህን ማውሳት ነው።

" ከንግድ ሁሉ ኪሳራው ፦ ሰውን ማውሳት ነው።


📚 በህጀቱል መጃሊስ 86

👉ልብ በሉ! ሸይኹ ለምን ይህን ያለ ይመስላቹሃል? ምኖደውን ሰው/አሰሪያችንን/አንድ ታወቂ ሰውን ብዙ ግዜ እናወሰዋለን ነገር ግን እኛ ለሱ ትዝም አንለውም ብንለውም ምንም አያደርግልንም
★አላህ ግን ባወሳቹኝ ቁጥር አወሳቹሃለው ብሎናል ከዚህም አልፎ በጀማዓ ስናወሳው ከመላኢካዎች እንደምያወሳን ነግሮናል
ታድያ ማነው ያተረፈው ማነው የከሰረው?

https://t.me/B1e9h
ነጋዴ ትርፍ በሚታፈስበት ወቅት ከተዘናጋ መቼ ሊያተርፍ ነው⁉️
በነዚህ ቀናቸውም ሌሊታቸውም በተባረኩ የዙልሒጃ ወርቃማ ቀናት እንጠቀምባቸው። ጾም መጾም፣ ሶደቃ መሰደቅ፣ ዚክር ማብዛት፣ ቁርኣን መቅራት… ኸይር ነገር ላይ ሁሉ እንበርታ። አላህ ያግራልን!

https://t.me/B1e9h
የቀለበት አደራረግ

ሴት ልጅ የወርቅም ይሁን የብር ቀለበት በፈለገችው ጣት ላይ ማድረግ ትችላለች። ነገር ግን ቤት ውስጥም ይሁን ከቤት ውጪ ስትሆን ጌጧን ባዕድ/አጅነቢይ ወንድ እንዳያይ ጌጡን መሸፈን ግዴታ ይሆንባታል። ይህም የቁርኣን ህግና ትእዛዝ ነው።

ወንድ ልጅ ግን የወርቅ ቀለብት ማድረግ አይችልም።
ከወርቅና ከብረት ውጪ ካሉ ነገሮች የተሰራ (የብርም ይሁን ሌላ) ቀለበት ሲያደርግ በመጨረሻው ትንሹ ወይም ከሱ ቀጥሎ ባለው ጣት እንጂ በመሃለኛው ረጅሙ ጣት፣ ከሱ ቀጥሎ ባለው ሌባ (አመልካች) ጣትና አውራ ጣት ላይ ለወንድ ልጅ ቀለበት ማድረግ አይቻልም።
በተለይ በመሃለኛው ረጅሙ ጣትና ቀጥሎ ባለው አመልካች ጣት ላይ ቀለበት ማድረግን ነቢዩ صلى الله عليه وسلم
በግልጽ ከልክለዋል።
ከመሆኑም ጋር ብዙ ወንዶች በነዚህ ጣቶች ቀለበት ሲያደርጉ ይታያል።
ዲናችንን እንወቅ! እውቀት ብርሃን ነው፤ አላዋቂነት ጨለማ ነው።

ኡስታዝ አሕመድ ኣደም

https://t.me/B1e9h
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በከዓባ ዙሪያ “ጠዋፍ” የመራችው ህጻኗ ልጅ

በሳዑዲ አረቢያ መካ የሃጅ ስነስርዓት በሚረግበት ሰዓት በከዓባ ዙሪያ “ጠዋፍ” የመራችው ህጻኗ ልጅ የበርካቶችን ቀልብ ስባለች።

ከእሲያ የሄደችው ህጻኗ ልጅ በአባቷ ትክሻ ላይ ሆና ጠዋፍ ስትመራ የነበረ ሲሆን፤ ሃጃጆችም ልጅ ሲከተሉ ነበር።

https://t.me/B1e9h
👌🟩አስቸኳይ መልእክት ለአረፋ ወደ ገጠር ተጓዦች በሙሉ


بسم اللّه الرحمن الرحيم. الحمد للّه رب العالمين، والصلاة والسلام على أشرف الأنبياء والمرسلين، نبيّنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين، ومن تبعهم بإحسان إلى يوم الدين.
اما بعد
ለዒድ አል አድሃ)(አረፋ) ገጠር እናትና አባቶቻችሁ ጋር ለመሄድ ያሰባቹ ውድ እህትና ወንድሞች ጥቂት ማስታወሻዎቼ ለናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
1 ስትሄድ እነሱን በቻልከው መጠን አስደስተህ ለመመለስ ሞክር ልብ በል የምታስደስታቸው ዱንያዊ ቁሳቁስ ስለያዝክ ብቻ አይደለም
የመጀመሪያ የሄድክ ቀን እነሱን አንጀታቸው የሚያርስ ቃላቶችን ተጠቅመህ አስደስታቸው አብሽር በላቸው ችግርህ; ጭንቀትህ አትንገራቸው  ከጎናቸው አትራቅ ገላቸውን እግራቸውን እጠባቸው ቀጣይ አረፋ ኢንሻአሏህ ሃጅ አስደርጋቸዋለሁ በላቸው ባትወስዳቸው እንደወሰድካቸው ይሰማቸዋል ደስታቸው ይፋፋል ደሞም አላህ ያሳካልህ ይሆናል ከልብህ በላቸው።

2 ከሽርክና ቢዳዓ ደጋግመህ አስጠንቅቃቸው ልብ በል አሁን ዱንያው ቁሳቁስ በመግዛት ብቻ የሚደሰቱት ሁሉ ጊዜያዊ ነው ተውሂድን እንዲረዱ ካላስረዳሃቸው ዘላለማዊ ደስታን ያጣሉ እና ይህ ላንተ ፀፀት ነው የመጀመሪው ሃቃቸው ያለብህም ይህን በማስረዳት ነው በሚገባቸው ቋንቋ ከሽርክ የሚያስጠነቅቁ ሙሃደራዎችን በሚሞር ጭነህ ከሬዲዮ ጋር ይዘህላቸው ሂድ።

☘️3.ለዝየራ ብለህ የምትሄድም ሆነ እዚህ የምትቀመጥ እባክህ ባለህ ነገር አትሰስትባቸው 1000 ብር ካለህ ጫቱን ተወውና 800 ለነሱ ስጣቸው ወላሂ አትጠራጠር
800000000.......  አድርጎ አሏህ ይተካልሃል

🔻አስበህ ታውቃለህ ግን እናትህ እኮ አንተ እዚህ በስልክ ካርድ የምታጠፋው 50 ብር ለማግኘት ነው ሰው ቤት እንሰት ስትፍቅ የምትውለው
አባትህ እኮ ያ በካርድ የምታወጣው 100 ለማግኘት ነው ጠዋት 2:00 ወጥቶ 11:00 ድረስ ሰው ጓሮ የሚያርሰው እና እጁ የተሰነጣጠቀው
እና ትንሽ አታስብም ኪስህ ውስጥ 1000 ይዘህ 500 ለጫት ስታወጣው‼️‼️‼️
ወላሂ እንባ እየተናነቀኝ ነው ይህን መልእክት ያካፈልኩህ


አንተ እዚ ሰው ለመጋበዝ ትሽቀዳደማለህ እሷ እዛ ተርባ ለ 50 ብር ወገቧ ሰው ቤት እንሰት እየፋቀች ተጣሞ ወላሂ ልብ ይነካል
እስቲ ይህን መልእክቴ ካነበብክ በኋላ ወደራስህ ተመለስ
አባትህ እስክታድግ ለዚህ አብቅቶሃል በተራህ አሳድገወኸ እናትህ እስከዚህ እየሸናህባት አሳድጋሃለች አሁን እስቲ በተራዋ አሳድጋት ከኪሱ ብር አይለይ እቤቱ ከቦርሳዋ አንተ እያለህ ብር አትጣ እሷ በቃ  ሰው ቤት መንከራተት ይብቃት።


4.እህቴ ሆይ ለበአል ለዝየራ ብለሽ ወላጆችሽ ጋር ሄደሽ በበአሉ እራሱ አንቺ ቁጭ ብለሽ እሷ እናትሽ ሁሉንም ሰርታ አቀራርባልሽ ቁጭ ብለሽ የምትበዪ ከሆነ ወሏሂ ሰጋሁልሽ !! እሺ መቼ ነው ከድካሟ የምታርፈው?? ስለዚህ ነቃ በይ እስከትመለሺ ድረስ እሷን በክብር ቁጭ አድርገሽ ጎንዋን አሳርፊላት ኻድሚያት አለሁልሽ በያት አብሽር በያት ገላዋን እጠብያት ልብሷን እጠቢላት ፀጉርዋን አበጥሪላት ፏ አድርገሽ ሙሽራ አስመስለሽ ቁጭ አድረገሻት አዘዥኝ በያት ከዛም በመቀጠል ወናውና አንገብጋቢው አንቺም ከቢዳዓና ከሽርክ አስጠንቅቂያት።

5. ለአረፋ ቤተሰብ ዝየራ ብላችሁ እዚም እዛም ቤት ስትዞሩ ውላቹ አድራችሁ የራሳቹ እቤት የሆነች ደቂቃ ብቻ ገባ ወጣ የምትሉ ደሞ በጣም የሚገርም ነገር ነው ለምንድነው የሄድኩት ብላችሁ እስቲ እራሳችሁን ጠይቁ
ኡሚና ባባ እኮ አይናችሁን ትኩር ብለው ጠግበው ሊያዩዋችሁ እንኳን ሳያገኟቹ በ3 ተኛ ወይም በ4ተኛ ቀን ልትሰናበታቸው አጠገባቸው ትሄዳላቹ ይህ ከሆነ
ወላሂ በጣም ልብ የሚሰብር ነገር ነው
ስለዚህ ወንድሜ ልትዘይራቸው ሄድክ አይደል በቃ ካጠገባቸው አትራቅ አጫውታቸው ;አማክራቸው  የቀጣዩ አረፋ እኮ ልታገኛቸውም ላታገኛቸውም ትችላለህ አሏህ ሃያታቸው ከመልካም ስራ ጋር ያርዝመው እንጂ አስበኸዋል እና ቆም ብለህ አስብበት።


6.ሲያማክሩህ ከልብህ ሆነህ አውራቸው ስልክ እየጎረጎርክ አታውራቸው ;አታመናጭቃቸው ;አትገላምጣቸው።

☘️6. እህቴ ሆይ ለዝየራ ብለሽ ሄደሽ የወንጀል በር መክፈቻ ከመሆን ተጠንቀቂ እራስሽን ገላልጠሽ አትሂጂ የሰፈር ልጅ ነው በሚል እዚና እዚያ ከአጅ ነቢ ጋር አትጃጃይ ይባስ ብሎ ውሎሽም አዳርሽም የሰፈር ልጆች ናቸው ብሎ ከነሱ ጋር ማድረግስ ምን ይሉት ቂልነት እንደሆነ አይገባኝም ።

☘️7.ስትሄዱ ጊዜ መኪና ውስጥ አላህን ልትፈሩ ይገባል ያ ሁሉ መንገድ በተክቢራ በአዝካር በቂርአት እንደዚሁም ሙሃደራ ቁርአን በማድመጥ ልታሳልፈው ልታሳልፊው ይገባል ።
አስተውለሃል በዛ ሁኔታ ሆነህ አላህን ብትገናኘው??
በተቃራኒው ደሞ እየቃምክ በዘፈን ሰክረህ ከአጅ ነቢ ጋር እየተጃጃልክ ያ አጅሬው ሞት ከተፍ ቢል ??ስለዚህ ቆም ብለህ አስብ!
አሏህ እንዲህ ይላል

وَمَا تَدْرِي نَفْسٌ مَّاذَا تَكْسِبُ غَدًا ۖ وَمَا تَدْرِي نَفْسٌ بِأَيِّ أَرْضٍ تَمُوتُ ۚ

"ማንኛይቱ ነፍስም ነገ የምትሠራውን አታውቅም፡፡ ማንኛይቱ ነፍስም በየትኛው ምድር እንደምትሞት አታውቅም"።


☘️8.እህት ሚስት ያለህ ሆይ ለብቻዋ አትልቀቃት አንድ መህረም ከሷ ጋር አድርግላት።

☘️9. ከሄዳችሁ በኋላ መጥፎ ነገር ስታዩ ለመከልከል ሞክሩ ምክንያቱም ገጠራማው ማህበረሰብ ላይ ወላጆቻችን  አብዘሃኛው በለማወቅ ነውና የሚፈፅሙት።

🌿10.በቻልከው መጠን ኸይር የተባለ ነገር ሁሉ አድርገህላቸው ምርቃታቸው ለመቀበል ታገል ምርቃታቸው ጠብ አይልምና በግልፅ ታየዋለህ

🌲11.ተሳስተህም እንኳን ሚያስከፋቸው ነገር ላለማድረግ ጥረት አድርግ ወላሂ ወቢላህ ወተሏህ የበደልካቸው እንደህ
ሆነ እርግማናቸው ያጠፋሃል ፊ ዱንያ ወል አኺራህ የሰው በታች ያደርገሃል ሲቀጥል ጀነት በማን እግር ስር ነች??? መልሱን ተውቁታላችሁ አይደል?? አሁንም አትጠራጠር ምታመናጭቃቸው ከሆነ ምትገላምጣቸው ከሆነ ምትበድላቸው ከሆነ አንተ በቀን የፈለግከውን አማርጠህ እየበላህ እነሱ ተርበው እንደሆነ ወላሂ ለራስህ ፍራ !!!

☘️12.እህት ወንድሞች ኖሯቹህ ለነሱ ልብስ እንደዚሁም ሌላ ቁራቁስ የምትገዙ ምን አይነት ልብስና እቃ መግዛት እንዳለባችሁ እወቁ ! ታናሽ እህት ካለህ ለሷ ጥብቅ ያለ ጉርድ ቀሚስ የምትገዛላት ከሆነ ታናሽ ወኔድም ኖሮህ ለሱ ቡጭቅጥቅ ያለ የምእራባውያን ልብስ የምትገዛለት ከሆነ ወደ ጥፋት ልትመራቸው እንደወረድክ አስበው ስለዚህ መፍትሄው ልንገርህ
እህት ካለችህ ጅልባብ ግዛላት ከውስጥ የሚለበስ ግዛላት ጫማ ግዛላት ወንድም ካለህ ጀለቢያ ቀሚስ ጥምጣም ኪታብ እና ሰፋ ያለ ሱሪ ጃኬት ግዛለት


☘️13.የመጨረሻው ጥቆማዬ
ለምንድነው የምሄደው ብላችሁ ኒያችሁን አሳምሩ።

አሏህ ይበልጥ አዋቂ ነው።

ታናሹ ወንድማችሁ አቡሰልማን (አብዱል ዓሊም )ነኝ
እናንተም ባነበባችሁት እኔም በፃፍኩት ተጠቃሚ ያድርገን
ዙል ሂጃ 4/1445
ሰኔ 4/10/2016

وصلى الله على نبينا محمد وآله وصحبه وسلم


https://t.me/B1e9h
🔪
    የኡዱሕያ መስፈርቶች!!

1ኛው, ከቤት እንስሳ መሆን አለበት።
እነርሱም
          
  ግመል
            
  ከብት
            
   በግ

         እና

  ፍየል
   

2ኛው, በሸሪዐ ለተገደበው እድሜ መድረስ አለበት።
        
🍖 ግመል ከሆነ   👉👉  5 ዓመት
        
🍖  ከብት  ከሆነ  👉👉  2 ዓመት
         
🍖  ፍየል  ከሆነ   👉👉  1 ዓመት
          
🍖  በግ    ከሆነ   👉👉 6 ወር የሞላው         


3ኛው, ከነውር (ከዓይብ) የጠራ መሆን አለበት።
      
🛑 ግልፅ  ከሆነ መታወር
       
🛑 ግልፅ  ከሆነ በሽታ
        
🛑 ግልፅ  ከሆነ አንካሳነት
          
🛑 መቅኔ የሌለበት ከሆነ ከሲታማነት


  አንድ ሰው ኡዱሒያ ማረድ ከፈለገ በሚያርደው እንስሳ ላይ ከተጠቀሱ ነውሮች መጥራት አለበት።



🛖ቅርጫ ማድረግ የፈለገ ሰው……

    በግ ወይም  ፍየል ከሆነ ለ1 ሰው ብቻ
    በሬ  ለ7ወይም ግመል ከሆነ ለ10 ሰው መካፈል ይቻላል።

https://t.me/B1e9h
ከሰለፎች መካከል የዐረፋህ ቀን ሲደርስ ዱዓእ አደርግበታለሁ ብለው ወሳኝ ጉዳያቸውን ቋጥረው የሚይዙ ነበሩ። አላህ ካደረሰን ይህ ድንቅ ቀን የፊታችን ቅዳሜ ነው። በተለይ ከሰዓት በኋላ በተለይም ከዐስር በኋላ ሁሉንም ጉዳያችንን ትተን ከወዲሁ ጊዚያችንን በማመቻቸት ወሳኝ ጉዳዮቻችንን ይዘን ለአላህ «ያ ረብ!» ለማለት እንዘጋጅ።

ከአላህ ውጭ ለማንም የማንነግራቸው፣ ብንነግራቸውም ሰዎች በአግባቡ የማይረዱን፣ ውስጣችንን የሚያብሰለስሉን ስንትና ስንት የታፈኑ እምቅ ስሜቶችና ጭንቀቶች አሉብን አይደል! በተለይ ደግሞ ሙእሚን ዱንያን እንደምንም ቢያልፋትም አኺራው ወሳኝ ነውና ሁሉንም ጉዳያችንን ለርሱ ለማመልከት እንዘጋጅ። አላህ ያግራልን።

https://t.me/B1e9h
ውድ ተከታታዮቻችን😍

እንኳን ለኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሰዎ!

በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንልዎ ከልብ እንመኛለን!

ኢድ ሙባረክ!

https://t.me/B1e9h
Audio
የዒድ አል-አዽሐህ አከባበር ስርዓት
በኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ

https://t.me/B1e9h
የእኛ የሙስሊሞች ዒዶች…

የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል: - "የዓረፋ እና የእርዱ  እለት እንዲሁም የተሽሪቅ (ከዙል‐ሒጃ ወር 11ኛው፣ 12ኛው እና 13ኛው) ቀናት የእኛ የሙስሊሞች ዒዶች ናቸው፤ እነሱም የመብላት እና የመጠጣት ቀናት ናቸው።" ( አቡዳውድ ዘግበውታል አልባኒም ሰሂህ ብለውታል)

በዚህ ሐዲስ ውስጥ እነዚህ አምስት ቀናት ማለትም  ከዙል‐ሒጃ ወር 9ኛ፣ 10ኛው፣ 11ኛው፣ 12ኛው እና 13ኛው ቀናት ለሙስሊሞች ከሐጅ ስርአት ጋር ተያይዞ አላህ ለዚህ ቀጥተኛ እምነት ስለመራቸው በልዩ ሁኔታ እንዲደሰቱባቸው፣ የተለያዩ አላህና መልእክተኛው የደነገጓቸውን የአምልኮ አይነቶች በመፈፀም አላህን ሊገዙባቸው፣ እርሱን ሊያመሰግኑባቸው እና ሊያልቁባቸው የተለዩ የዒድ ቀናት መሆናቸውን እንረዳለን። ስለሆነም ዘጠነኛውን ቀን ሐጅ ላይ ላልሆነ ሰው መፆሙ ሲበረታታ፤ አስረኛውን ቀን መፆም ለሁሉም የተከለከለ ይሆናል። ከዚያ በኃላ ያሉትን የተሽሪቅ ቀናት ሐጅ ላይ ላልሆነ ሰው መጾሙ የማይፈቀድ መሆኑን ዑለማዎች ገልፀዋል።

አላህን እርሱ በሚፈልገው መልኩ በመልእክተኛው መንገድ ከሚገዙት ያድርገን!

ጣሀ አህመድ


https://t.me/B1e9h
          🔷   አያሙ ተሽሪቅ

    ከዒደል አድሓ ( የውሙ ነሕር ) ቀጥለው የሚመጡት ሶስት ቀኖች አያሙ ተሽሪቅ በመባል ይታወቃሉ ። እነዚህ ቀኖች ሙስሊሞች እየበሉና እየጠጡ አላህን የሚገዙባቸው ቀኖች ናቸው በእነዚህ ቀኖች በፆም አላህን መገዛት ክከልክል ነው ።  ይህን አሰመልክቶ የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም – እንዲህ ይልሉ : –

عن نبيشة الهذلي أن النبي–  صلى الله عليه وسلم – قال :
(أيام التشريق أيام أكل وشرب وذكر الله) أخرجه مسلم
" አያሙ ተሽሪቅ የመብያና የመጠጫ እንዲሁም አላህ የሚታወስባቸው ቀኖች ናቸው ። "
وفي رواية للإمام أحمد
(من كان صائماً فليفطر فإنها أيام أكل وشرب) .
صحيح مسلم.
" ፆመኛ የሆነ ሰው ያፍጥር እነዚህ ቀኖች የመብያና የመጠጫ ቀኖች ናቸው ። "

   ከእነዚህ ሐዲሶች የምንረዳው በእነዚህ ቀኖች መፆም ክልክል መሆኑ ነው ። ምናልባት ሐጅ ላይ ሆኖ ሀድይ የሌለው ከሆነ አስር ቀን መፆም ይኖርበታል ። ሶስቱን ቀኖች እዛው ፆሞ ሰባቱን ቀኖች ወደ ቤተሰቦቹ ሲመለስ ይፆማል ። ሶስቱን ቀኖች በአያሙ ተሽሪቅም ቢሆን መፆም ይችላል ቀደም ብሎ ካልፆመ ። ከዚህ ውጪ ሌላ ሰው በእነዚህ ቀኖች መፆም አይችልም ። መብላትና መጠጣት ሙባሕ የነበረ ሲሆን በእነዚህ ቀኖች ግን መሰራት ያለበት ዒባዳ ይሆናል ። በመሆኑ ከእርዱ ቀን ማግስት ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት  ድረስ በዒድ ይካተታሉ መፆም አይፈቀድም ። በእነዚህ ቀኖች አላህን መዘከር በጣም ትልቅ የዒባዳ አካል ነው ። አላህ ያግራልን ።

https://t.me/B1e9h
«አባት የመጀመርያም የመጨረሻም የሆነ ብቸኛ ልጁን ሊድር ድል ያለ ሰርግ ደግሶ ዘመድ አዝማድ እና ወዳጆቹን ጠርቶ የምሳ ግብዣውን እየተዟዟረ ይመለከታል።

‹‹ማን ቀረ ማን መጣ›› የሚለውን በትኩረት እየተመለከተ ሳለ የቅርብ የግድግዳ ጎረቤቱን ከእይታው ያጣዋል። ግራ በመጋባት እየተዟዟረ ቢመለከትም ጎረቤቱንም ሆነ የጎረቤቱን ልጆች ሊያይ አልቻለም።

‹‹የልብ ወዳጄ በዛሬ ቀን እንዴት ከጎኔ ይጠፋል›› እያለ በንዴት ስሜት በመብሰልሰል ላይ ሳለ ድንገት የጎረቤቱ ልጅ ብቅ አለ ና በፍጥነት ትንሽ ምግብ ቀማምሶ ትቶ ወጣ።

ይህን ትዕይንት የተመለከተው ደጋሽ በንዴት ተብከነከነ። የአባቱ በደስታው ግዜ አለመገኘት ሳያንሰው ልጁ መጥቶ በምግቡ አላግጦ መውጣቱ አበሳጨው።

በዚህ መሀል የሙሽራው አጃቢዎች ሙሽራውን ይዘው ወደ ሙሽሪት ቤት ጉዞ ሊጀምሩ መኪናቸውን ማንቀሳቀስ ሲጀምሩ ምግቡን ቀማምሶ በፍጥነት የወጣው የጎረቤቱ ልጅ ሙሽራውን ለማጀብ ከግቢ መኪናውን ይዞ ይወጣል።

አባት ተበሳጨ፣ ንዴቱን መቆጣጠር ቢያቅተው በቁጣ መንፈስ ተሞልቶ ወደ ጎረቤቱ ልጅ በመሄድ፦‹‹አባትህ ጎረቤቴ ሁኖ ደስታዬ ላይ አልተገኘም፣ ታላላቅ ወንድሞችህም እንደዝያው፤:ታድያ አንተ ምን አስበህ ነው በምግብ አላግጠህ ትተህ የወጣኸው?  አሁን ተመለስ ያንተን አጃቢነት አንፈልግም›› ብሎ መለሰው። ልጁም እቤቱ ገባ፤ ሰርገኛዎችም ሙሽራውን ይዘው ወደ ሙሽሪት ቤት አቀኑ።

በመጨረሻም አጃቢዎች ሙሽሮችን ይዘው ወደ ቤት በመግባት የደስታቸው ተካፋይ ከሆኑ በኋላ ቀኑ ሲጨልም ሁሉም ተበታትኖ ሰርግ ቤቱ በሙሽሪት እና በሙሽራው ጭር አለ።

አባት አሁንም በጎረቤቶቹ ንዴት እየተብሰለሰለ ነው። ድንገት ከመሸ ያለ ወትሮው የጎረቤቱ ጊቢ ተከፈተ። የሙሽራው አባት እየተመለከተ ነው።

የጎረቤቱ ልጆች በትከሻቸው አስክሬን ተሸክመው ከቤታቸው ሲወጡም ተመለከተ። ፍፁም ዝግታ እና እርጋታም በሚስተዋልበት እርምጃ ልጆቹም ይራመዱ ጀመር።

የሙሽራው አባት ጠጋ አለ። ፦‹‹ምንድነው? የማንን አስክሬን ነው የተሸከማችሁት ›› ሲልም ጠየቃቸው።

‹‹አባታችን ጠዋት ሙቶ ነው፤ ሲሞትም በሱ ለቅሶ ምክንያት ያንተ ደስታ እንዳይጓደል መሞቱን ከሰርግህ በፊት ለማንም እንዳንናገር እና ድምፅ አውጥተን እንዳናለቅስ ተናዞልን ነበር። ለዝያ ነው ድግሱ ላይ መገኘት ያልቻልነው። ›› በማለት ጀናዛ የተሸከሙ ልጆች ጉዳያቸውን አስረዱ።

ደጋሽ ተፀፀተ፦‹‹ወላሂ እኔ በሱ ቦታ ብሆን ይህን የማድረግ አቅም አይኖረኝም ነበር›› ሲልም የፀፀት እንባ ያነባ ጀመር።

በህይወታችን ችላ ያሉ እየመሰሉ በቁስላቸው ደስታችንን ላለማበላሸት ሲሉ ከአከባቢያችን የሚርቁ ሰዎችን አላህ ይዘንላቸው።»

ሰፍዋን

https://t.me/B1e9h
በከባድ ሙቀት ህይወታቸው ያለፈ ሀጃጆች ቁጥር ከ1 ሺህ ተሻገረ‼️

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተለያዩ ሀገራትን ዲፕሎማቶችን ዋቢ አድርጎ ይፋ ባደረገው አሃዝ እስከዛሬ ድረስ 1081 ሃጃጆች ህይወታቸው ማለፉ ተረጋግጧል።

እስካሁን በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት የ10 ሀገራት ዜጎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፥ 658ቱ ግብጻውያን ናቸው።

የሱዳን፣ ሴኔጋል፣ ቱኒዚያ፣ ህንድ፣ ዮርዳኖስ፣ ማሌዥያና ኢራን ዜግነት ያላቸው ሃጃጆችም ህይወታቸው ማለፉን ነው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ያስነበበው።

https://t.me/B1e9h
✍️ ብዕረ ሐኒፍ #4
🔖ኃላፊነት አለብን!

ከሺህ አራት መቶ አመታት በፊት ዓለም ሁለንተናዊ ጽልመት ያካበባት ድቅድቅ ጨለማ ነበርች።መላ ፍጥረታትን ካነበሩበት አስገኝቶ እንደምንጣፍ በዘረጋት ምድሩን ላይ ያኖራቸው ቸር እና ኃያል ጌታ ተትቶ፤የማይጠቅሙ እና የማይጎዱ ግዕዞች የሚመለኩበት ፣ ጉልበተኛው ደካማውን የሚበዘብዝበት እና የሚረግጥበት ፣ የሴት ልጅ ሰዋዊ ማንንነት እንኳን ተረስቶ ከነ ሕይወቷ የምትቀበርበት ፣ የጎሳ እና የዘር ጠብ አይሎ የተከበረው የሰው ልጅ ደም እንደዋዛ የሚፈስባት ዓለም።

አዛኙ ጌታችን አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሰዎች እስከ አፍንጫቸው ከተዘፈቁበት ድርብርብ የጨለማ አዘቅት በእዝነቱ ሊያወጣቸው በፈለገ ጊዜ ፤ የፍጥረታት እንቁ ፣ የሰው ልጅ ሁሉ ዓይነታ የነብያት እና መልዕክተኞች መደምደሚያ የሆኑትን ሙሐመድ ኢብኑ ዐብደላህ ኢብኑ ዐብዱል ሙጠሊብን ﷺ ለመላው ዓለም የመጨረሻው ነብይ እና መልዕክተኛ አድርጎ ላካቸው።

ረሱሉላህ ﷺ ከአላህ ዘንድ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ፣ ህዝባቸውን ከገባበት የመሐይምነት ጨለማ ለማውጣት ሌት ተቀን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ወገባቸውን አስረው ለፉ ፤ ለህዝባቸው መዳን ሲሉ በርካታ መከራ እና ግፍ አዩ ፤ ከባባድ የበደል እና የጭቆና ጊዜያትን አሳለፉ ፣ በገዛ ቤጸባቸው ተገፉ ፣ ዕምብርታቸው ከተቀበረባት የሚወዷት አገር ተሰደዱ።

በርካታ ውጣ ውረዶች ከሞሏቸው ሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ፤ የጌታቸውን መልዕክት አድርሰው ፣ ሰዎች በቡድን በቡድን ወደ እስልምና ሲጎርፉ ተመልክተው ፣ በአላህ እርዳታ ዳዕዋቸው ፣ ልፋታቸው እና ጥረታቸው ፍሬ እንዳፈራ ያስተዋሉ ጊዜ በመሰናበቻው ሐጃቸው ላይ ለባልደረቦቻቸው "የጌታዬን አደራ አድርሻለሁን?" ብለው ጠየቁ። ሰሐቦቻቸውም "አዎን አድርሰዋል" አሉ።እሳቸውም "አላህ ሆይ መስክር !" አሉ።

የነብዩ ባልደረባ እንዲሆኑ አላህ የመረጣቸው ሰሐቦችም ከነብያቸው የተረከቡትን አደራ ጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ አስተላለፉ ፣ በኢስላም ዳዕዋ አገራትን ከፈቱ ፣ በርካቶችን ከጨለማ ወደ ብርሃን አወጡ።ከሰሐቦች ይህን ትልቅ አደራ የተቀበሉት ሰለፎቻችንም ዲኑን በማስተማር እና በማሰራጨት ለቀጣዩ ትውልድ የማሸጋገር ኃላፊነታቸውን ተወጡ።እንዲህ እንዲህ እያለ በየዘመኑ የነበሩ ዑለማዎች እና ደጋግ የአላህ ባሮች ዲኑን ለማስጠበቅ እና ለቀጣዩ ትውልድ ለማሸጋገር ከባባድ መስዕዋትነትን ከፍለው የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማበርከት እስልምናን ከትውልድ ትውልድ እንዲሸጋገር አደርጉ።

ዛሬም የዚህን ዘመን የዲን ኃላፊነት መሸከም በዚሁ ዘመን እየኖርን ያለነው ሙስሊም ማህበረሰቦች ኃላፊነት ነውና እንደየ አቅማችን እና ችሎታችን የበኩላችንን አስተዋጻኦ ለዲኑ ማበርከት የእያንዳንዳችን ግዴታ ነው። በመማር ፣ በማስተማር ፣ ኢስላማዊ የትምህርት ማዕከላትን በማቋቋም ፣ ኢስላማዊ የዳዕዋ እና የትምህርት ስራዎችን በሀሳብ ፣ በጉልበት ፣ በቁሳቁስ እና በገንዘብ በመደገፍ ያለብንን ኃላፊነት መወጣት ይኖርብናል!

አላህ ባለን አቅም እና በተሰማራንበት የስራ ዘርፍ ያለብንን የዲን ኃላፊነት የምንወጣ ባሮች ያድርገን! አሚን!

https://t.me/B1e9h
ባለ ትዳሮች ሆይ ይህ ተራ ወሬ ነው!

🔅ባልና ሚስት በጸብም ይሁን በሰላም በተለያዩ ምክንያቶች ለምንም ያክል ጊዜ ተራርቀው ቢኖሩ ባል በራሱ ወይም በወከለው ሰው ኒካሕ እስካላወረደ ወይም ሚስት በፍርድ ቤት እስካልተፈታች ድረስ በአካል ተራርቀው ስለቆዩ ብቻ ኒካሕ ፈጽሞ አይወርድም።
ይህ ከመሆኑ ጋር ብዙ ሰዎች "3 ወር፣ 6 ወር ወዘተ ተራርቃችሁ ስለቆያችሁ ኒካሕ እንደ አዲስ እሰሩ ተባልን..." ይላሉ!
ይህን አላህም ይሁን መልእክተኛው እንዲሁም የፊቅህ ሊቃውንት (ዑለማኦች) አላሉም።

🔅ስለዚህም ባልና ሚስት በስራም ይሁን በሌላ ምክንያት፤ በስምምነትም ይሁን በጸብ ለወራትም ይሁን ለዓመታት ተራርቀው ቢቆዩ በመራራቃቸው ወይም ተለያይተው በማሳለፋቸው ብቻ ኒካሕ እንደማይወርድ አውቀው ዳግም ኒካሕ ማሰር ሳያስፈልጋቸው ህይወታቸውን አብረው መቀጠል ይችላሉ።

💥የአላዋቂዎች ወሬ እንዳያደናብረን ዲናችንን አስቀድመን እንወቅ! እንማር።

ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም


https://t.me/B1e9h
'
ኢብኑ አቢ ለይላ እና ሁለቱ ሴቶች (የሴቶች ሴራ)


አንዲት አሮጊትና ወጣት ሴት ተካሰዉ በዘመኑ ታዋቂ ወደነበረዉ ቃዲ ኢብኑ አቢ ለይላ ይሄዳሉ

ዳኛዉ መጀመሪያ ማን ይናገር አለ አሮጊቷ አንቺ ተናገሪ አለች ወጣቷም የሁለታችንም እኔ እናገራለሁ ከተሳሳትኩ ትመልሰኛለች አለች


ከዚያም አንተ ቃዲ ሆይ! ይህች አጠገቤ ያለችዉ አሮጊት አክስቴ ነች አባቴ ሲሞት የቲም አድርጎ እሷ ጋ ተወኝ እሷም ባማረ አስተዳደግ አሳደገችኝ በዚህም እንደ እናቴ ስለሆነች እናቴ በማለት ነዉ የምጠራት አለች

ዳኛዉም ከዚያስ አላት

እድሜዬ ለትዳር ሲደርስ የአጎቴ ልጅ ለትዳር  ጠየቀኝ አክስቴም በትዳር አጣመረችን

በጣም እንዋደድ ነበር እኔ ለሱ እሱም ለኔ ብቻ እንደተፈጠርን ከአለም ሌላ እንደሌለን እናስብ ነበር።

ከሶስት አመታት በፍቅር የተሞላ ትዳር በኋላ  የባሌን መልካምነት ስትመለከት ሃብቱም እየሰፋ ሲመጣ ለልጇ ተመኘችዉ

ከዚያም ያማረ ልብስ አልብሳ አስዉባ ወደ ባሌ አስገባቻት እሱም ሲያያት ወደዳት አክስቴም ይህችን ልጄን  እንዳጋባህ  አንድ መስፈርት አለኝ አለችዉ ምን እንደሆነ ሲጠይቃት የመጀመሪያዋ ሚስትህን (የወንድሜን ልጅ)  ሃላፊነት በእጄ ልታረግና ፍቿን እኔ ልሰጣት አለችዉ

እሱም ተስማማ በሰርጉ ቀይ ወደኔ መጥታ ባልሽ ልጄን አግብቷታል ያንቺም ጉዳይ በእጄ አድርጎታል አናም ተፈትተሻል አለችኝ በሌሊትና በረፋድ ፈት ሆንኩ

ከአጭር ጊዜ በኋላ ለረዥም አመታት ሌላ ቦታ የቆየዉ ባሏ ከመንገድ ተመለሰ ታዋቂ ነጋዴ ነበር (ገጣሚም ነዉ ተብሏል)  ስለኛ ሲጠይቃትም እኔ አግብቼ እንደተፋታሁ ልጁም እንዳገባች ነገረችዉ እሱም የመዘየር ሃቅ  አለብኝ በማለት ሊጠይቀኝ መጣ

በዚህ ጊዜ የአክስቴ ባል ሆይ! ታገባኛለህን? አልኩት እሱም መስማማቱን ገለፀልኝ

ነገር ግን አንድ መስፈርት አለኝ እሱም የሚስትህን ጉዳይ  በኔ እጅ ልታደርግ  አልኩት እሱም ተስማማ

ከዚያም ለአክስቴ ባልሽ ያንቺን ጉዳይ በእጄ አድርጎታልና ከርሱ አፋትቼሻለሁ በማለት መልእክት ላኩላት። ከዚያም አገባሁት አክስቴም ፈት ሆነች
አንተ ቃዲ ሆይ!  አላህ እድሜህን ያስረዝመዉና  በዚህ መልኩ አንድ እኩል ሆንን አለች

በዚህ ጊዜ ቃዲዉ በሚሰማዉ ነገር ደንግጦ በመቆም ያአላህ! አለ  እሷም ገና ታሪኩ አልጀመረም ተቀመጥ አለችዉ

እሺ ቀጥይ አላት

ባሌ ከትንሽ የትዳር ቆይታ በኋላ ሞተ እኔም ንብረቱን ወረስኩ

ታዲያ በዚህ ጊዜ አክስቴ መጥታ ለብዙ ዘመናት ለንግድ ሲሄድ ርቀቱን የታገስኩ ልጁን ያሳደግኩ እኔ ነኝ ከዚህ ሃብት ሃቅ አለኝ ብላ ዉርስ ጠየቀች  እኔም እኔ የባሌ ሃብትና ሃቄ ነዉ  አንቺ ከዉርሱ ምን አገባሽ አልኳት

ኢዳዬ ከተጠናቀቀ በኋላ አክስቴ ልጇንና በዉርስ ጉዳች እንዲያሸማግለን የድሮ ባሌን የአሁን የአክስቴ ልጅ ባል ይዛ መጣች።

ወጣቷ ትረካዋን ትቀጥላለች

ከዚያም የድሮ ባሌ ሲመለከተኝ ያሳለፍናቸዉን ጊዜያት አስታወሰ ድጋሚም ከጀለኝ

እኔም ትመልሰኛለህን? አልኩት  መስማማቱን ገለፀልኝ እኔም ግን አንድ መስፈርት አለኝ እሱም የአክስቴን ልጅ ጉዳይ በእጄ ልታደርግ አልኩት። በመስፈርቴ ተስማማ ለአክሰቴ ልጅ ተፈትተሻል አልኳት።

በዚህ ጊዜ ቃዲዉ ኢብኑ አቢ ለይላ እጁን ጭንቅላቱ ላይ አድርጎ ጥያቄዉ የታለ 😳 አለ

አክስትም ተነስታ አንተ ቃዲ ሆይ!  ይህ እንደ ሸሪዓ ሃራም አይደለምን? እኔና ልጄ ፈት ሆነን ይህች ሴት ሁለት ባልና ዉርስ የምትወስድ? አለችዉ

ቃዲዉም በዚህ ዉስጥ ሃራም ነገር አላየሁበትም አንድ ወንድ ሁለት ጊዜ አግብቶ ሁለት ጊዜ መፍታቱና ዉክልና መስጠቱ ምኑ ላይ ነዉ ሃራምነቱ? አለ 

ከዚያም በዘመኑ ከአባሲያዎች የነበረዉ ዋሊ መንሱር ጋር ሄዶ ታሪኩን አጫወተዉ

መንሱርም ከሳቁ ብዛት እግሩን ከመሬት ያማታ ነበር ከዚያም እንዲህ አለ "ቃተለላሁል አጁዝ ለወንድሙ ጉድጓድ የቆፈረ ራሱ ይወድቅበታል ይህችን ግን ባህር ላይ ወደቀች

https://t.me/B1e9h
📨20(ሐያ)ወንድማዊ ምክር ለውዷ እህቴ

①,በተውሒድ ላይ አደራ! ሽርክን እና ቢደዓን በያይነታቸው ራቂ!!
②,, ሁሌ ቤት ውስጥ መቀመጥ ምርጫሽ ይሁን።ወጣ ወጣ አትበይ!!
③,,ተቅዋን(አላህን መፍራት) የውስጥ መዋቢያሽ ካደረግሽ ሀያእን ደሞ ውጫዊ መዋቢያሽ አድርጊው!!
④,,ከ ወንዶች እና ከካፊር ሴቶች ጋ ያለሽ ግንኝነት በጣም አስፈላጊ ሆኖ እስካላገኘሽው ድረስ ራቂ!!
⑤,,ሒጃብሽ ሰፋ ያለና ረዘም ያለ ይሁን!!
⑥,,አካሄድሽ ረጋ ያለና አደብ የተላበሰ ይሁን!!
⑦,,በየቀኑ ብታጠፊ በየቀኑ ወደ አላህ ተመለሺ!!
⑧,,በአለባበስሽና በሥነምግባርሽ ለሌሎች ሴቶችና ለሴት ልጆችሽ ምሳሌ ሁኚ!!
⑨,,ያልተፈቀደልሽን ባዕድ ወንድም ሆነ ሊያገባሽ የሚፈቀድለትን የቅርብ ዘመድ አትጨብጭ!!
10,,ከላይ አላህን ሳይታዘዙ፤ ዉስጤ ንፁህ ነው አላህን ፈራለሁ ማለት ቅጥፈት ነው!!
①①,ከባዕድ ወንድ ጋር ስታወሪ መቅለስለስ፤ በሽ?ታ ያለበትን በሽታውን መቀስቀስ ነውና አደብ ይኑርሽ በንግግርሽ…!!
①②,መስመር እየሳቱ የሚመስሉ የስልክ ወሬዎችንና ቻቶችን ከወድሁ ቁረጪ!!
①③,እየተኳኳሉና እየዘለሉ አላህን እና መልዕክተኛዉን እወዳለሁ ማለት ዉሸት ነውና… ነሽዳ እና መሰል ኮተቶችን ራቂ!!
①④,ሒጃብና ኒቃብ እየለበሱ መጥፎ መሥራት የኢስላምን ንጽሕት ሙስሊምን ሥም ጭምር ማጠልሸት ነውና… በቻልሽው አቅም አደብ ይኑርሽ!!
①⑤,በሐራም መንገድ ገንዘብም ሆነ ትዳር ባገኙት አትቅኚ ፍፃሜው አያምርም እና!!
①⑥,- ፀጉርሽን አትጎዝጉዢ(ከፍ አድርገሽ አትሰሪው) አትቀጥይውም፣ሽቶም ሆነ ዶድራንት ተቀብተሽ አትውጪ!!
①⑦,ስትስቂ በስሱ፤ ሰታወሪ ድምጽሽ ዝቅ ይበል!!
①⑧,በሥራ ቦታ እና በት/ት ቤት  ከሰዎች ጋር ባለሽ ግንኙነት ቀይ መስመር ይኑርሽ!!
①⑨,, ከእህቶችሽ ጋር ተግባቢ እና ትህትና ያለሽ ሁኚ!!
20,,የሸሪዓ እውቀትን በመፈለግ ላይ አደራ እስካሁን ለጠቀስኩት ምክሮች መሰረቱ ነውና!!
منقول
https://t.me/B1e9h
«ለአላህ ብቻ ብሎ በኢኽላስ የሚሰራ ሰው ልክ በአሸዋ መንገድ ላይ እንደሚሄድ ሰው ነው። የእርምጃው ድምፅ አይሰማም፣ ፋናው ግን ይታያል።»

ኸይር ሥራችን ትንሽ ነው፤ ለዚችሁ ስራችን ኢኽላስ ይኑረን፣ ትንሹን ያበዛዋልና!
ኢኽላስ ከሌለው ከንቱ ድካም ነው።

https://t.me/B1e9h
ከዘረፋ ወደ ታላቅ ኢማምነት
❴በአንዲት የቁርአን አንቀፅ በመስራት የተገኘ ታላቅ ክብር❵

ከታቢዒዮች መካከል ታላቅ መሪ የሆኑት ፉዶይል -አላህ ይዘንላቸውና- ጸጸት ከማድረጋቸው በፊት ግማሽ የሆነውን ህይዎታቸውን ያሳለፉት በዘረፋ ተግባር ወይም በሽፍትነት ነው፡፡ አርባ አመት እስኪሞላቸው ድረስ የአካባቢው ህብረተሰብ በጣም ይሰጋቸው ነበር፡፡ “ሲየር አዕላም አን’ኑበላእ” በተባለው ኪታብ ዘህብይ -ረሂመሁሏህ- የእርሳቸውን የጸጸት ታሪክ እንደሚከተለው ይገልጹታል፡፡ ለጸጸት ምክንያት የሆነቻቸው አንዲትን ሴት በማፍቀራቸው ምክንያት እንደሆነ ይወሳል፡፡ ወደሴትዮዋ ቤት ለመድረስ አጥር ላይ
ሲወጡ በአጋጣሚ የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ የሚቀራ ሰው አደመጡ
፡፡
۞ أَلَمْ يَأْنِ لِلَّذِينَ آمَنُوا أَن تَخْشَعَ قُلُوبُهُمْ لِذِكْرِ اللَّهِ
“ለነዚያ ለአመኑት ለአላህ ተግሳጽና ከቁርኣንም ለወረደው ልቦቻቸው ሊፈሩ….
አልቀረበምን?”

📚 [ ሱረቱ አል-ሐዲድ - 16 ]

“ጌታየ ሆይ አዎ ቀርቧል” የሚል መልስ ሰጡ፡፡ ከዚያም ካሰቡት አላማ ተጸጽተው ተመለሱ፡፡ ያኔ እርሳቸው በተጸጸቱበት ወቅት መንገደኞች “እንለፍ አንለፍ? ፉዶይል ቢዘርፈንስ?” በማለት ጭንቀት ውስጥ እንደነበሩ በታሪክ ተዘግቧል፡፡
ፉዶይል የሚከተለውን ተናገሩ፡- ((አስተነተንኩ፣ ሙስሊሞች እኔን ይሰጋሉ፣ እኔ ግን በሌሊት ወንጀል ለመፈጸም እንቀሳቀሳለሁ፣ እኔን ወደዚህ አላህ አላመጣኝም ጸጸትን ለእኔ ሽቶልኝ እንጅ፤ አላህ ሆይ! እኔ ወደአንተ ተጸጽቻለሁ፤ በህይዎት እስካለሁ ድረስ ካዕባን መጎራበት ለእኔ ከጸጸቴ መካከል አንዱ ነው፡፡))
📖 ሲየር አዕላም አን ኑበላእ፡ 8/423

ፉዶይል ከዚህ ዓለም በሞት እስኪሰናበቱ ድረስ መካ ውስጥ አላህን ይገዙ ነበር፡፡ ከመካ ዑለሞች የሐዲስ የተለያዩ የፊቅህ እውቀቶችን ቀስመዋል፤ ሐዲስ ሀፍዘዋል፡፡ ለዚህ ነው ሙስሊሞች የተፍሲር፣ የሐዲስና የፊቅህ መጽሐፎችን ገልጠው ሲያነቡ የዚህን ታላቅ ኢማም ስም ዘወትር የሚያስተውሉት፡፡ አንዲት አንቀጽ የፉዶይልን ህይዎት ከከባድ አመጸኝነት ወደ ደጋግ የአላህ ባሪያነት ቀየረች ፤ የኢማሞች ሁሉ ኢማም አደረገች፡፡

https://t.me/B1e9h
ዩሱፍ ጉድጓድ ውስጥ ጠብቋል፣
ኢብራሂም እሳት ውስጥ ጠብቋል፣
አዩብ ህመሙ እስኪሻለው ድረስ ጠብቋል፣
ዩኑስ በዓሳ ነባሪው ሆድ ውስጥ ጠብቋል።

በመጨረሻም ለሁሉም የመጣውን ፈረጃ እናውቃለን።

አላህ እንድትጠብቅ ካደረገህ ታድለሃልና አሁንም ሳትቸኩል ታገስ።

https://t.me/B1e9h