Al EHSAN አል_ኢህሳን
185 subscribers
402 photos
43 videos
2 files
606 links
የቻናሉ አላማ
1 ባለን አቅም እስልምናን በአግባቡ ለኡማው ማድረስ
2 ሙስሊሞችን በድናቸውም ይሁን በዱኒያ እውቀታቸው የነቁ እንድሆኑ መገፋፋት
3 ለወጣቶች ምክር
4 በልዩ መልኩ ሴቶችን ማንቃትና ሌሎቹም አለማዊና መንፈሳዊ ት/ቶች ይገኙበታል።

ውድና የተከበራቹ የአል ኢህሳን ቻናል ቤተሰቦች ሆይ ውብና ማራኪ የሆኑ ሀሳብ አስተያያታቹ እንዳይለይን

ለአስተያት @S1u9l
አሁኑኑ ይቀላቀሉን
👇
Download Telegram
👆👆👆👆👆👆👆👆
እንደዚህ አይነት ሱራ(ስዕል) ያለበትን ነገር መግዛትም ይሁን መጠቀም በዲናችን በጥብቅ የተከለከለ ነገር(ሀራም) ነው ለልጅም ብሆን ያው ነው አይፈቀድም
🔅ስዕል ያለበትን ቤት መላኢካ አይገባም ተብሎዋል በሀድስ
🔅ታድያ ከቤታችን መላኢካዎች እንዲሸሹ ነው የምንፈልገው? መላኢካዎች ካልቀረቡን ልቀርበን የምችለው ማን እንደሆነ ግልፅ ነው
🔅 ነብዩ ለአልይ ስዕልን ካገኘሀው ቀደሀው ብሆን እንጂ እንዳተወው ነበርኮ ያሉት እኛ ግን በገዛ ገንዘባችን ገዝተን የነብዩን መመሪያ መጣስ፣መላኢካዎችን ከቤታችን ማባረር ሆነ ተግባራችን
🔅የቂያማ ቀን አላህ ዘንድ በጣም የተጠሉ ሰዎች ማለት ህይወት ያለበትን ስዕል የምስሉ ሰዎች እንደሆኑ ተነግሯል ሆኖም እኛ ምርታቸውን እየገዛን እናስተዋውቅላቸዋለን አላህን ልንፈራ ይገባል በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እዚህ ተግባር ውስጥ ያለን ሰዎች በግዜ ተውበት አድርገን ወደ አላህ እንመለስ @ለብዙ ስህተት የምንዳረገው ድንኑን ምያስተምር ጠፍቶ ሳይሆን ከኡለማዎች ጠጋ ብለን ለመማር ያለን ፈላጎት የወረደ በመሆኑ ነው የምንሰራውን መልካል ስራ በሌላ በኩል እራሳችን መልሰን የምናበላሸው
አላህ ማስተዋሉን ይወፍቀን

https://t.me/B1e9h
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
" የ2 ሰዎችን አስክሬን እየፈለግን ነው " - የዞኑ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ

በሀላባ ዞን ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ የጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሰዎች ህይወት ጠፍቷል።

ከሰው ህይወት መጥፋት ባለፈ በአዝእርትና በብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።

ይህ ሁሉ ጉዳት የደረሰው በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲሆን ከዝናቡ ጋር በተያያዘ የተከሰተው የመሬት መሰንጠቅ በህብረተሰቡ ዘንድ ድንጋጤ  መፍጠሩ ተነግሯል።

በጉዳዩ ላይ ቃላቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊው አቶ ሸምሰዲን ጉታጎ ፥ " ሁኔታዉ እጅግ አስደንጋጭ ነው " ብለዋል።

በጎርፍ አደጋው የ5 ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ሲሉ ገልጸዋል።

" አሁንም በጎርፍ ተወስደዉ ከሞቱት 5 ወገኖች መካከል የሁለቱን  አስክሬን ማግኘት አልቻልንም " ብለዋል።

የአስከሬን ፍለጋው ሻላ ሀይቅ ውስጥ እየተካሄደ መሆኑን እና የኦሮሚያ የጸጥታ ኃይሎች በተለይ ዋናተኞች እያገዟቸዉ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጨማሪም አደጋው በርካታ የግለሰብ ቤቶችን እንዲሁም ዌራ ወረዳ ያለን ሆስፒታልን ሙሉ በሙሉ ከስራ ዉጭ እንዳደረገው ገልጸዋል።

በዞኑ በበርካታ ቦታዎች ላይ የተፈጠረው የመሬት መሰንጠቅም በህብረተሰቡ ዘንድ ድንጋጤ መፍጠሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
Al EHSAN አል_ኢህሳን
" የ2 ሰዎችን አስክሬን እየፈለግን ነው " - የዞኑ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ በሀላባ ዞን ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ የጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሰዎች ህይወት ጠፍቷል። ከሰው ህይወት መጥፋት ባለፈ በአዝእርትና በብረት ላይ ጉዳት አድርሷል። ይህ ሁሉ ጉዳት የደረሰው በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲሆን ከዝናቡ ጋር በተያያዘ የተከሰተው የመሬት መሰንጠቅ በህብረተሰቡ ዘንድ ድንጋጤ  መፍጠሩ ተነግሯል። በጉዳዩ…
👉ሰዎች ሆይ! ወደ አላህ እንመለስ
የእኛ ትልቁ ችግራችን ከሌሎች አለመማር ነው በሌሎች የሙስሊም ሀገራት ላይ የምደርሰው እልቂት ለማሳሌ፦
ዱባይ ቱርክ፣ሰዑዲ፣ሱዳን፣ሶማሊ በመሬት መንቀጥቀጥ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ ፣አውሎ ንፋስ መከሰት፣ በጦርነት መብዛት የምደርስባቸው መከራ ለኛ ለሙስሊሞች ትልቅ የማስጠንቀቂያ ደውል ነበር ከተማርንበት
ግን ችግሩ እኛን በቀጥታ እስካነካን ድረስ እኛን አይመለከትም አይነት ነገር ነው ምላሻችን
የሰሞኑን ጎርፍ ተመልከቱ አድስ አበባ 4 ሰው ጎረቤት አላባ 5 ሰው በጎርፍ ተወሰደ እየተባለ ነው ሀላባ ለይ የመሬት መሰንጠቅ ጭምር ነው የተከሰተው ከዚህ በላይ ምን ይሁን የምያስደነግጠን ሰዎች?
አሁንም እድሉ ያለን እኛ በግዜ ወደ አላህ እንመለስ ለማንም ሳይሆን ለራሳችን ስንል መጥፋት የአንድ ቀን ክስተት ነው ሁለተኛ ዬለውም

https://t.me/B1e9h
እያስተዋልን ወገኖቼ!

በጎረቤት ሀገር #ኬንያ ለሳምንታት በዘለቀ ከባድ ዝናብ እና ጎርፍ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 228 መድረሱን የኬንያ የሀገሪር ውስጥ ሚኒስቴር አሳውቋል።

ደብዛቸው የጠፋ በርካታ ሰዎች እንዳሉም ተነግሯል።
https://t.me/B1e9h
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጫት ከሌሎች ዘርፎች የተሻለ ትርፍ እንዳለው ይታወቃል። የጫት ንግድ ማለት ለወገን ገዳይ መርዝ እየሰጡ በምትኩ ገንዘባቸውን መውሰድ ነው። ይሄ ንግድ በወገን ህይወት ላይ መጫወት ያለበት እርኩስ ንግድ ነው። ትርፉ ሳያማልላችሁ ኣኺራችሁን በማስቀደም እንዲህ አይነት ውሳኔ የወሰናችሁ ጀግኖች ኒያችሁን፣ ልፋታችሁን አላህ ይቀበላችሁ። ለሌሎች ምሳሌ ያድርጋችሁ። ለዱንያም ለኣኺራም የሚጠቅማችሁ የተሻለ ሐላል ሪዝቅ ይስጣችሁ። የበዛ፣ የጣፈጠ በሆነ የጀነት ሲሳይ ያንበሻብሻችሁ። በዚህ ውሳኔ ላይ ድርሻ ያላችሁን ሁሉ አላህ እጥፍ ድርብ አድርጎ ይመንዳችሁ።
በነገራችን ላይ
ጫት በመብላትም፣ በማብላትም፣ በማጓጓዝም፣ በመነገድም፣ ለጫት ንግድ በማከራየትም የተሰማራችሁ ሁሉ ወንጀል ላይ ናችሁ። አላህን ፈርታችሁ ከድርጊታችሁ ታቀቡ።

https://t.me/B1e9h
"ሁሉም ሰው በፖለቲካ ተጠምዷል። ፖለቲከኞች ሲቀሩ። እነሱ ግን በንግድ ነው የተጠመዱት።"
* ዐብዱል መሊክ አልኢብቢ *
·
·
መሪር ሐቅ!! አብዛኞቻችን የፖለቲካው ማእበል ወስዶን ከዚያ ከዚህ እያላጋን ነው። አንዳንዱማ ከሃይማኖቱ በላይ ዘሩን እያስቀደመ የቆሻሻ ፖለቲካ ጎርፍ ወስዶታል።
ፖለቲከኞቹስ? አብዛኞቹ የሞቀ ንግድ ላይ ናቸው። እንጀራቸውን ሊያበስሉ ተፍ ተፍ እያሉ ነው። ከመንግሥት በተቃዋሚ ስም፣ ከህዝብ በነፃነት ትግል ስም፣ ከውጭ በሰብአዊ መብት ቅስቀሳ ስም ከያቅጣጫው ይዘርፋሉ። ለምስኪን ተፈናቃዮች የተሰበሰበን እርዳታ ይነጥቃሉ።
በነሱ የፖለቲካ ጦስ የሚሞተው፣ የሚፈናቀለው፣ የሚጎዳው ግን ፖለቲከኞቹ ሳይሆኑ ህዝቡ ነው። ለዘመናት ተዋልዶ፣ ተጋምዶ የኖረ ህዝብ የፖለቲከኞች ድግምት ከተደገመበት በኋላ ፍፁም በማይታሰብ መልኩ አንዱ ሌላውን ያርዳል፤ ይሰቅላል፤ ያቃጥላል፤ ይወግራል፤ በጅምላ ያፈናቅላል። ፖለቲከኞቹ ግን በህዝብ እልቂት ገበያቸው ይደራል። በህዝብ መፈናቀል ንግዳቸው ይደምቃል። በኛ ስም በጮሁ ቁጥር ለኛ የተቆረቆሩ እየመሰለን ጆሯችንን እንሰጣቸዋለን። "ማንም በክፉ አይንካቸው" እንላለን። ፎቷቸውን አሳትመን እንለብሳለን፤ እንለጥፋለን፤ እንሰቅላለን። ግና ህዝብ እየከሳ እነሱ ይደልባሉ። ህዝብ እየተፈናቀለ እነሱ ለአይን ከሚያሳሳ ሰገነት መግለጫ ይሰጣሉ። የህዝብ ልጅ ወደ ትግል፣ የነሱ ልጆች ወደ ውድ ትምህርት ተቋማት። ህዝብ ወደ ታች እነሱ ወደ ላይ።

(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 9/2011)

https://t.me/B1e9h
የሴት ልጅ መስተካከል የማህበረሰብ መስተካከል ነው!!

📌 ሸይኽ ፈውዛን ሀፊዘሁሏሁ እንዲህ ይላሉ:
ሴትን ልጅ በተጨባጭ ካየናት ለማህበረሰቡ እንደ መርህ ልታገለግል የምትችል አካል ነች እሷ ቀጥ ካለች ከተስተካከለች ማህበረሰቡ ይስተካከላል እሷ ከተበላሸች ማህበረሰቡ ይበላሻል።

ምንጭ: (التعليق القويم على كتاب إقتضاء الصراط المستقيم )

📌 ይህን ያሉበትን ምክንያት ካየን ልጆችን አንፃ ምታሳድገው አብራቸው ምትውለው ሴት ልጅ ነች ከአላህ በታች የነገው ትውልድ እጣ ፋንታ የወደቀው በሴት ልጅ እጅ ነው  እና የሴት ልጅ ስነ-ምግባሯ ተበላሸ ማለት ዲንን ሀገርን የሚረከበው ትውልድ ተበላሸ ማለት ነው ስለዚህ ሴት ልጅ እራሷን ችላ የቆመች አንድ መድረሳ ነች ማለት እንችላለን ይህ መድረሳ የተበላሸ ከሆነ ላሸክ ከዚህ መድረሳ ተመርቀው ሚወጡትም ተማሪዎች የተበላሹ ስለመሆናቸው የቀደምቶችንም ታሪክ መለስ ብለን ካየን አሁን ላይ አኢማዎች ብለን ምንጠራቸው የመልካም እናቶች ውጤት ናቸው እነ ኢማሙ አቡ ሐኒፋን እነ ኢማሙ ሻፊኢን እነ ኢማሙ አህመድን እነ ኢማሙል ቡኻሪን ይመስል ሌሎችም
📌 እና ሴት ልጅ የያዛችው(የተሸከመችው) ሀላፊነት ከባድ ነው ሀገርን አለምን ነው መገንባት የያዘችው ነገር ግን አንዳንድ ዘምነናል የሚሉ የተፈጠሩበትን አላማ የዘነጉ ፌሚኒዝም በሚለው ልክፍት የተለከፋ ሴት ልጅ እቤቷ ቁጭ ብላ ልጆቻን መንከባከቧ ማነፃ እንደ ሗላ ቀርነት የሚያዩ አካላቶች አሉ ይህ ከእስላም አስተምህሮ ፍፁም የማይገናኝ አስተሳሰብ ነው ሗላ ቀር ማለት የተፈጠረለትን አላማ የዘነጋ ሰው ነው እና እህቶች ያለባችሁን ትልቅ ሀላፊነት በማወቅ ሀላፊነታቹን በተገቢው መልኩ ልትወጡ እና አላህንም በዚህ ነገር ላይ እንዲያግዛቹ ልጠይቁት ይገባል።

አቡ ዐብዱ-ር'ረሕማን


https://t.me/B1e9h
መራር እውነታ!
ጓደኛህ ማነው?
~
ጓደኛህ ወደ ተሻለ የምትወስደው ወይም ወደተሻለ የሚወስድህ ይሁን። ካልሆነ ግን ወይ ያጠፋሀል። ወይ ታጠፋዋለህ። ወይ ተያይዛችሁ ትጠፋላችሁ።
ሰው ውሎውን ይመስላል። ውሎህ የት ነው? ከማን ጋር? ሰዎች ጠጪ የሚሆኑት በጓደኛ ሰበብ ነው። ቃሚ፣ አጫሽ የሚሆኑትም በጓደኛ ተፅእኖ ነው። ያለ ምክንያት አይደለም "ጓደኛህን ንገረኝና ማንነትህን ልንገርህ" የሚባለው።
ከመጥፎ ሱስ መውጣት፣ ባህሪህን መግራት ትፈልጋለህ? ከልብህ ከሆነ ውሎህን አስተካክል። ልጅህ ከመጥፎ አዝማሚያ እንዲመለስ፣ መስመር እንዲይዝልህ ትፈልጋለህ? ሰበብ ሳታደርስ ጠዋት ማታ አትጨቃጨቅ። ይልቁንም ውሎው ላይ አጥብቀህ ስራ። ካልሆኑ ጓደኞች ጋር ገጥሞ ከሆነ የምትችለውን ሁሉ መስዋእትነት ከፍለህ ለየው።
ለብዙዎች በዲንም ይሁን በዱንያ መቃናት መልካም ጓደኛ ትልቅ ድርሻ አለው። እስኪ በህይወት ጉዟችሁ ላይ አነሰም በዛ ላገኛችሁ ስኬት ወይም መልካም ለውጥ አስተዋፅኦ ያላቸውን ጓደኞቻችሁን ለአፍታ አስቧቸው። በተቻለ መጠን ውለታ መላሽ ሁኑ። እሱ ቢቀር አመስጋኝ ሁኑ። ከዚያም በላይ በዱዓእ አስታውሷቸው።
ጓደኝነት ኣኺራን ከነጭራሹ ሊያጨልም፣ ኩ. ፍ. ር ላይ ሊጥል ይችላል። በጓደኛ ሰበብ ስንቶች ለተረዱት እውነት እጅ መስጠት አቅቷቸዋል?! በጓደኛ ሰበብ ስንቶች ውስጣቸው እያወቀ እምነት ቀይረዋል? ስንት ወንዶች ሴት ተከትለው፤ ስንት ሴቶችም ወንድ ተከትለው ዘላለማዊ ህይወታቸውን አጨልመዋል?! የተሰጠን እድል ከእጃችን ሳያፈተልክ፣ ነፍሳችን ሳትሾልክ በፊት ሳይመሽ እናስብበት። እንወስን በጊዜ። ነገ ፀፀት እንዳይበላን። ጌታችን እንዲህ ይላል:-
{ وَیَوۡمَ یَعَضُّ ٱلظَّالِمُ عَلَىٰ یَدَیۡهِ یَقُولُ یَـٰلَیۡتَنِی ٱتَّخَذۡتُ مَعَ ٱلرَّسُولِ سَبِیلࣰا (27) یَـٰوَیۡلَتَىٰ لَیۡتَنِی لَمۡ أَتَّخِذۡ فُلَانًا خَلِیلࣰا (28) لَّقَدۡ أَضَلَّنِی عَنِ ٱلذِّكۡرِ بَعۡدَ إِذۡ جَاۤءَنِیۗ وَكَانَ ٱلشَّیۡطَـٰنُ لِلۡإِنسَـٰنِ خَذُولࣰا (29) }
{በዳይም፡ «ምነው ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በሆነ ዋ ምኞቴ!» እያለ (በጸጸት) ሁለት እጆቹን የሚነክስበትን ቀን (አስታውስ)። «ዋ ጥፋቴ! ምነው እገሌን ወዳጅ አድርጌ ባልያዝኩ ኖሮ። (የእምነት ቃልን) ከመጣልኝ በኋላ ከማስታወስ በእርግጥ አሳሳተኝ» (ይላል)። ሰይጣንም ለሰው በጣም ለውርደት አጋላጭ ነው።} [አልፉርቃን፡ 27-29]

(ኢብኑ ሙነወር፣ ግንቦት 2/2016)

https://t.me/B1e9h
Forwarded from ተውሒድ የሁሉም ነብያቶች ጥሪ ነው። (Bint Mohammed አላህ ከዐርሹ በላይ ነው።)
አሠላምአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ

ውድና የተከበራችሁ እህት ወንድሞች ይች እህታችን ስሟ ተምሬ አራጋው ጎቸል ትባላለች ከፓስፖርቱላይ እንዳለው በጠለብ ከአራትና አምስት ወር በፊት ሳኡድ ጂዳ ከተማ ገብታ ነበር እናም አሰሪዋ መንገድ ላይ ጥላታለች አሉን። አእምሮዋም ትክክል አይደለም ቪዶወውላይ እንደምታዩት።የቀረጿትም ልጆች ልንወስዳት ስንል ሴትየዋ እምቢአለችን አሉ በሰአቱ ዘወር ብለው ሲመለሱም ከቦታው እንዳላገኙዋት ነው የተናገሩት እና ጂዳ አካባቢ ያላችሁ በተለይ እባካችሁ ይችን እህታችንን ያያት ካለ እንድትተባበሩን በአክብሮት እንጠይቃለን።

አላህ ሁላችንም ይጠብቀን እሷንም ያስገኛት!!

እኔ የሰፈሯ ልጂ ነኝ ካገኛችኋት

0532053175 Bint Mohammed በዚህ ቁጥር በዋሳብም ወይም በመስመር ያገገኙኛል ይደውሉ የሠማችሁም አደራ ሸር አድርጉልኝ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በሱፊያው ዓለም በርካታ የሚመለኩ ቀብሮች አሉ። ቀብሮቹ ዘንድ በመሄድ ልጅ፣ ዝናብ እና የተለያዩ ሐጃዎችን ይማፀናሉ። የሞተ ሰው እንኳን የነሱን ጉዳይ ሊፈፅም ከራሱ፣ ከተሰራለት ዶሪሕ እንኳ መከላከል አይችልም። ይሄው ይሄ "ወሃቢ" የሆነ ጎርፍ ዶሪሑን ነቅሎ እየወሰደው ነው።
{ أَیُشۡرِكُونَ مَا لَا یَخۡلُقُ شَیۡـࣰٔا وَهُمۡ یُخۡلَقُونَ (191) وَلَا یَسۡتَطِیعُونَ لَهُمۡ نَصۡرࣰا وَلَاۤ أَنفُسَهُمۡ یَنصُرُونَ (192) }
"ምንንም የማይፈጥሩትንና እነርሱም የሚፈጠሩትን (በአላህ) ያጋራሉን? ለእነርሱም መርዳትን የማይችሉትን ነፍሶቻቸውንም የማይረዱትን (ያጋራሉን)?" [አልአዕራፍ፡ 191-192


https://t.me/B1e9h
ስለ የታላቁ ነጃሺ ዜሮ ዜሮ (00) መንደር አጭር ማብራሪያ
(Grand Al Najashi 00 Village Project)

📎የፖሮጀክቱ ሰያሜ ፡ የታላቁ ነጃሺ 00 መንደር
📎 የሚሰራበት ቦታ፦ ትግራይ ክልል፣ ውቅሮ ነጃሺ
📎የዜሮ ዜሮ [00] መጠሪያ ሃሳብ የሸክ ሃጂ ኢበራሂም ቱፋ ሲሆን የታሪኩ መነሻና መገኛ ስፍራ (ትግራይ፣ ነጃሺ) ያመላክታል።

®የዚህ ፕሮጀከት የበላይ መሪ ሸክ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ (የኢትዮጵያ እሰልምና ጉዳይች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት)

የፕሮጀክቱ አጋር ተቋማት።

©የትግራይ ክልል እሰልምና ጉዳዮች ጠቅላይ መክርቤት
©የአልነጃሺ መልሶ ግንባታና ልማት ኢኒሼቲቭ( Al-Nejashi Reconstruction and Development initiative (ARDI)

የፖሮጅክቱ ዓላማ

📎በኢትዮጵያ ብሎም የአለም ትልቁ የሙሰሊሞች የታሪክ ቅርሰ የሆነው፤ ለሙሰሊሞች በከባዱ ፈተና ወቅት ከለላ(መጠጊያ) የሆኑት ንጉስ ነጃሺ መካነ ቀርስ አሻራ ያለበት ቦታ በትግራይ ክልል በነጋሺ ከተማ ክብራቸውና ታሪካችው የሚመጥን አለም አቀፍ የቱሪሰት መዳረሻ ቦታ አንዲሆን ሁሉም አቀፍ መንደር (ቪሌጅ) ለመገንባት ያለም ነወ፡፡

የሚገነበው መንደር Educational, health and Development facilities የሚያካትት ሲሆን በውስጡ የተለያዩ ንኡስ ፕሮጀክቶች የሚኖሩት ሲሆን በዋናነት:-

📌መስጂድ እና መድረሳ
📌ሙዚየም
📌ሐላል ሆቴል እና ሎጅ
📌የስፖርት ማዘውተሪያዎች
📌ኢስላሚክ የጥናትና ምርምር ተቋም
📌የቴከኒከና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች
📌ሆስፒታል
እና ሌሎች
Mohammedawel Hagos

https://t.me/B1e9h
በኮንትራት ለስራ የሄዳችሁ ወገኖች
~
ከአሰሪያችሁ ጋር ለምሳሌ የሁለት አመት የስራ ውል (ኮንትራት) ገብታችሁ የተቀጠራችሁ ወገኖች ቃላችሁን ጠብቁ። የተሻለ ደመወዝ ፍለጋ በሚል ምክንያት አትጥፉ። ማንም ቢሆን ወጭ አውጥቶ ቃል አስገብቶ ካገሩ ያስመጣው ሰራተኛ ቃሉን አፍርሶ ጥሎት ቢጠፋ ደስ አይለውም። ራሳችሁ ላይ እንዲሆን የማትፈልጉትን ነገር ሌሎች ላይ አታድርጉ። ቃል ያስጠይቃል። አላህ እንዲህ ይላል፦
{ وَأَوۡفُوا۟ بِٱلۡعَهۡدِۖ إِنَّ ٱلۡعَهۡدَ كَانَ مَسۡـُٔولࣰا }
"በቃል ኪዳናችሁም ሙሉ፡፡ ቃል ኪዳን የሚጠየቁበት ነውና። [አልኢስራእ: 34]

አስገዳጅ ሁኔታ ካልገጠመ በስተቀር።

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ከኢማሙ አህመድ ጋር

ኢማሙ አህመድ ከኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ከትልልቅ ተማሪዎች አንዱ ነው። ኢማሙ አህመድ ኡስታዛቸውን በጣም ይወዷቸው ነበር በሰዎች እና በልጆቻቸውም አጠገብ ያወድሷቸው ነበር ስለ ጀግንነታቸውም ያነሱ ነበር።ከዚህ የተነሳ የኢማሙ አህመድ ልጃቸው ሁልጊዜ ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይን ለማየት ዒባዳቸው እንዴት እንደሆነ ለማየት ትጓጓ ነበር።

        ከእለታት አንድ ቀን ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ወደ ኢማሙ አህመድ ቤት እንግድነት ሄደው አደሩ ።የኢማሙ አህመድ ልጅ ሁኔታቸውን በማየት ነበር እና ከኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ የማይጠበቅ 3 ነገራቶችን ተመለከተች።

1ኛ  ምግብ ቀረበላቸው እና ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ምግቡን አብዝተው በሉ ሆዳቸው እሰከሚሞላ ድረስ።

2ኛ   ከበሉ በኋላ ገብተው ተኙ ሰላተ ለይል ሳይሰግዱ አደሩ።

3ኛ  የሱብሂ አዛን ሲደረግ ውዱእ ሰያደርጉ ወደ መስገጃ ቦታ ሄደው ሰገዱ።

ከእነዚህ ክስተቶች የተነሳ ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይን በጠበቀቻቸው መንገድ ስላላገኘቻቸው በጣም ደነገጠች ፈዘዘችም መታገስ አቃታት ።
አባቷን እንዲህ ብላ ጠየቀች፦ እንዴት ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይን በመሰለ ትልቅ ዓሊም እነዚህ ነገሮች ይታያሉ?
ኢማሙ አህመድም ይህን ጉዳይ ከራሳቸው መስማት አለብኝ ብለው ሄደው ስለ ሁሉም ነገር ጠየቋቸው።

ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይም እንዲህ ብለው መለሱላቸው፦

1ኛ  ምግቡን ሆዴ እስከሚሞላ የበላሁት ምግብህ ከሀላል መሆኑን ስላወኩኝ እና የደጋግ ሰዎች ምግባቸው መዳኒት መሆኑን ስላወኩኝ ነው።የበላውት ስለራበኝ ሳይሆን ለመዳኒትነት ነው የበላውት።

2ኛ ስለመተኛቴ ደሞ ወሏሂ አይኖቼ ሳይተኙ ነው ያደሩት ምክንያቱም ፊቅሃዊ በሆነ በአንድ መስአላ( በአንድ ሀዲስ)  ላይ እያስተነተንኩኝ ነው ያደርኩት በአንዷ ሀዲስ ውስጥ 72 ለሙስሊሞች የሚጠቅሙ ነገራቶችን አውጥቼበታለው በእውቀት ፍለጋ ቢዚ መሆን ከሌሊት ሰላት ስለሚበልጥ ነው።

3ኛ  ውዱእ ሳላደርግ የሰገድኩት ስላልተኛውኝ ውዱእ አልፈታውም።

ባላወቅነው ነገር ሰውን ከመፈረጅ እንጠንቀቅ

قصة الإمام الشافعي مع الإمام
أحمد

كان الإمام أحمد من أبرز طلاب الإمام الشَّافعي وكان يحبُّه حباً كبيراً، وكان دائم الثناء عليه أمام النَّاس وأمام أبنائه، فلمَّا قام الإمام أحمد باستضافة الإمام الشَّافعي في بيته، كانت ابنة الإمام أحمد متشوِّقة إلى رؤية الشَّافعي وعبادته.[٣] ولمَّا وُضع الطعام أكثر الشَّافعي من تناول الطَّعام، ثمَّ نام إلى الفجر ولم يقم الَّليل، وقام فصلَّى بهم الفجر بدون وضوء، فذُهلت ابنة الإمام أحمد لما رأته، ولم تطق صبراً، فسألت أباها عن ذلك إذ كيف يمكن أن يصدر هذا من إمامٍ بوزن الشافعي؟.[٣] فدخل الإمام أحمد إلى الشَّافعي وسأله عن تلك الأمور، فقال له الإمام الشافعي: أمَّا الطعام فما أكثرت منه إلَّا لأنِّي أعلم أنَّ طعامك حلالٌ، وطعام الصَّالحين شفاءٌ، فما أكلت جوعاً إنَّما أكلت تداوياً، وأمَّا نومي بعد الطعام وعدم قيامي لليل فوالله ما نامت عيني وإنَّما كنت أتفَّكر في مسائلَ من الفقه، فاستنبطت اثنتين وسبعين مسألةً ينتفع بها المسلمون، أمَّا صلاتي بكم الفجر بدون وضوء، فما نمت حتى أتوضأ، إنَّما كنت مستيقظاً طول الَّليل.

https://t.me/B1e9h
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Palestine

ዛሬ አይርላንድ ፣ ኖርዌይ እንዲሁም ስፔን ለፍልስጤም የነጻ ሀገርነት እውቅና እንደሚሰጡ በይፋ አስታወቁ።

" የዛሬው ቀን ለፍልስጤም እጅግ ታሪካዊ ቀን ነው " ተብሏል።

የአየርላንድ ጠ/ሚኒስትር ሲሞን ሃሪስ " ዛሬ አየርላንድ ፣ ኖርዌይ እና ስፔን ለፍልስጤም የነጻ ሀገርነት እውቅና ሰጥተናል። ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ እያንዳንዳችን ማንኛውንም አይነት ብሔራዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ፥ " #በሚቀጥሉት_ሳምንታት ተጨማሪ ሀገራት ይህን ጠቃሚ እርምጃ ለመውሰድ ከእኛ ጋር እንደሚተባበሩ እርግጠኛ ነኝ " ሲሉ አክለዋል።

የአይርላንድ መንግሥት ይህ የሀገርነት እውቅና የሁለት ሀገር መፍትሄን እንደሚደግፍና ለቀጠናው ዘላቂ ሰላም አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል።

የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ እና የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ኢስፔን ባርት ኢይድ ሀገራቸው ከግንቦት 28 (እ.ኤ.አ) ጀምሮ ለፍልስጤም ግዛት እውቅና እንደሚሰጡ በይፋ አሳውቀዋል።

የስፔኑ ጠ/ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ፥ " ምንም እንኳን ከአሸባሪው ቡድን #ሃማስ ጋር የሚደረገው ውጊያ ህጋዊ ቢሆንም ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ለፍልስጤም የሰላም ፕሮጀክት የላቸውም " ብለዋል።

የኖርዌይ ጠ/ ሚኒስትር ጆናስ ጋህር ስቶር በበኩላቸው ፥ " እውቅና ከሌለ (የፍልስጤም) በመካከለኛው ምስራቅ ምንም ሰላም ሊኖር አይችልም " ብለዋል።

" ሽብር የተፈፀመው በሃማስና የሁለት ሀገር መፍትሄን በማይቀበሉ እንዲሁም የእስራኤልን መንግሥት በማይደግፉ ታጣቂ ቡድኖች ነው። " ሲሉ አክለዋል።

" ፍልስጤም ነጻ አገር የመሆን መሠረታዊ መብት አላት " ብለዋል።

የፍልስጤም #የነጻ_ሀገርነት እውቅና መስጠት በይፋ ከተሰማ በኃላ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር #በኖርዌይ እና #በአይርላንድ የሚገኙ አምባሳደሮችን በአስቸኳይ ወደ እስራኤል እንዲመለሱ አዘዋል።

ሚኒስትሩ፤ " የዛሬው ውሳኔ ሽብርተኝነት እንደሚከፍል ለፍልስጤማውያን እና ለዓለም መልእክት ያስተላለፈ ነው " ብለዋል።

መረጃው የስካይ ኒውስ ነው።

More - @thiqahEth
ያልገባኝ ነገር ይህ ነው።

እንደምንሞት በርግጠኝነት እናውቃለን ነገር ግን ከሞት በኋላ ላለው ህይወት አልተዘጋጀንም በጤና ነው ወይ ቤተሰብ!!!?