Al EHSAN አል_ኢህሳን
176 subscribers
409 photos
44 videos
2 files
629 links
የቻናሉ አላማ
1 ባለን አቅም እስልምናን በአግባቡ ለኡማው ማድረስ
2 ሙስሊሞችን በድናቸውም ይሁን በዱኒያ እውቀታቸው የነቁ እንድሆኑ መገፋፋት
3 ለወጣቶች ምክር
4 በልዩ መልኩ ሴቶችን ማንቃትና ሌሎቹም አለማዊና መንፈሳዊ ት/ቶች ይገኙበታል።

ውድና የተከበራቹ የአል ኢህሳን ቻናል ቤተሰቦች ሆይ ውብና ማራኪ የሆኑ ሀሳብ አስተያያታቹ እንዳይለይን

ለአስተያት @S1u9l
አሁኑኑ ይቀላቀሉን
👇
Download Telegram
ሲሳያችን ከሐላል ወይስ ከሐራም
በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
👆👆👆
🔖 ሲሳያችን ከሐላል ወይስ ከሐራም

https://t.me/B1e9h
ከፈተናዎች መውጫ #1
ኢብኑ/ሙነወር
“ከፈተናዎች መውጫ”
ክፍል - 1
ሚያዚያ 14/2016 ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቀረበ

https://t.me/B1e9h
ከፈተናዎች መውጫ #2
ኢብኑ/ሙነወር
“ከፈተናዎች መውጫ”
ክፍል - 2
ሚያዚያ 14/2016 ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቀረበ

https://t.me/B1e9h
ሰለፊያ እውነታና ተግባር
ኢብኑ/ሙነወር
ሰለፊያ፡ እውነታና ጥንቃቄ
ኢብኑ ሙነወር

https://t.me/B1e9h
#አላህ የመልካም ሰሪዎችን ምንዳ በከንቱ አያስቀርም

#አባት ከአምስት #ሴት ልጆቹ ጋር ይኖራል ለትዳርም ስለደረሱ አባት ከታላቋ ጀምሮ በቅደም ተከተላቸው እንዲያገቡለት ይፈልጋል።

ታላቋ ግን አባቷን መንከባከብ በመፈለግ ማግባት አልፈቀደችም ታላቋ ብቻ ስትቀር አራቱ ልጆቹ አገቡ።እሷም አባቷ አጀሉ ደርሶ እስኪሞት ድረስ ተንከባከበችው ። አባት ከሞተ በኃላ ግን ይቺ ሴት ብቻዋን ቀረች ። የአባታቸውንም ኑዛዜ አገኙ እሱም " አደራ ራሷን መስዋዕት ያደረገችው እህታችሁ ሳታገባ ቤቱን እንዳትካፈሉ " የሚል ነበር...

ነገርግን አራቱ እህቶች የትልቅ እህታቸውን ጉዳይ ቦታ ሳይሰጡ ተሽጦ መከፋፈልን ፈለጉ ።

ትልቋ እህታቸው ቤቱን እንደሚሸጡት ስትረዳ ለመግዛት ለተስማማው ሰው በመደወል ከምትኖርበት ቤት ውጭ ሌላ እንደሌላትና ያለውን ሁኔታ አስረድታ ነገሮችን እስክታስተካክል ድረስ ጊዜ እንዲሰጣት አስፈቀደች ። ቤቱን የሚገዛውም ሰውም ፍቃደኝነቱን ገለፀላት። ቤቱ ተሽጦ ለአምስቱ እህቶች ተከፋፈለ።

ከተከፋፈለ በኃላ አራቱ ወደ ትዳራቸው ተመለሱ ታላቋ እህታቸው ከቤት ቀረች። ይቺ ሴት ወላጇን በመንከባከብ ባሳለፈችው ጊዜ አላህ ልፋቷን በዱንያም ከንቱ እንደማያስቀርባት ተማምና በአላህ ተስፋ አድርጋለች።

ወራት አለፉ ቤቱን ከገዛው ሰው ስልክ ተደወለላት ቤቱን እንድትለቅ መልክት እንደሚያስተላልፍ በመገመት በፍራቻ '#ይቅርታ እስካሁን ቤት አላገኘውም' አለችው። እሱም ችግር የለም! የደወልኩም ለሱ ሳይሆን ቤቱን '#መህር' አድርጌ እንድታገቢኝ ልጠይቅሽ ነው ፍቃድሽ ከሆነ ባልሽ እሆናለው ፍቃደኛ ካልሆንሽም ችግር የለም! ቤቱ ግን ያንቺ ነው አላት ። #አጂብ

ይህን ስትሰማ አለቀስች 😭😭
ተስማማችም አላህም የመልካም ሰሪዎችን ምንዳ ከንቱ አያስቀርምና በመልካም ተካሰች ። አባቷን በተንከባከበችበት ቤት ትዳር ይዛ ባሏን መንከባከብ ጀመርች 💍

ያ አላህ ! በየቤቱ ያንተን ተስፋ ብቻ የሚጠባበቁ እህቶች አሉና መልካምን ትዳር ወፍቃቸው🤲🤲🤲

ከአረብኛ የተተረጎመ

https://t.me/B1e9h
ዛሬ የመጽሐፍ ቀን ነው አሉ መሰል። አላማዬ ስለቀኑ ሳይሆን ኢስላማዊ መጽሐፍ ስለሚያቃጥሉት ጉዶች ነው።
ያቃጠሏቸውና ለማቃጠል ያዘጋጇቸው እንዲሁም በውሃ ሊዘፈዝፏቸው ያሰቧቸው መጽሐፍት "መንዙማ" የሚለው የሳዳት ከማል መፅሐፍ፣ "መውሊድ!፣ ኢብኑ ተይሚይያህ… ወዘተ የሚሉትን የኢብኑ ሙነወርን መጽሐፍቶች ነው። ለማቃጠል ያነሳሳቸው ከመጽሐፍቶቹ ጸሐፊዎች ጋር አለመግባባታቸው እንጂ መጽሐፍቶቹ ውስጥ ለመቃጠል የሚዳርግ መጥፎ መልዕክት ኖሮ አይደለም።

ይህን የፈጸሙት ሰዎች ሙስሊሞች ናቸው። ከሙስሊምም አልፈው ብቸኛና እውነተኛ "ሰለፊይ" ነን ብለው የሚሞግቱ ናቸው። እኔ እነዚህን ፌክ ሰለፊያ ነው የምላቸው። እነዚህ ትክክለኛውን የሰለፎች ጎዳና እና ትክክለኛ ሰለፊዮችን የሚያሰድቡና መንገዱን ሌሎች እንዲጠሉት የሚያደርጉ፣ የሚያወሩትንና የሚተገብሩትን የማያውቁ ጉዶች እንጂ ሰለፊይ ናቸው ማለት ይከብደኛል።

"መውሊድ" የሚለውን መጽሐፍ መውሊድ አክባሪ የሆኑ አሕባሾችና መሰል ቡድኖች እንኳ አቃጥለው ጀብዱ እንደሠራ ሰው አላሳዩንም። "መንዙማ" የሚለውን መጽሐፍ መንዙማ ወዳጆች አቃጥለው አላሳዩንም። ታዲያ መውሊድና መንዙማን እቃወማለሁ የሚል ሰው ደራሲውን በመጥላት ብቻ ተነሳስቶ መውሊድና መንዙማ የሚቃወሙ መጽሐፍትን ያቃጥላልን? እኔ እንዲህ አይነት ሰለፊይ ነኝ ባይ ሰምቼም አይቼም አላውቅም።
እነዚህ ስሜታቸውን ያላሸነፉ በእውር ድንበር የሚጓዙ ያልተገራ አንደበት ያላቸው ናቸው፤ አላህ ይምራቸው። ምክንያቱም ባቃጠሏቸው መጽሐፍቶች ውስጥ ያለን ሐዲሥና ቁርኣን አቃጥለዋል።

ሐሰን ታጁን ጠላሁ ብዬ የተረጎመውን የኢማሙ ነወዊይ ሪያዱ-ስ'ሷሊሒን ወይም የኢብኑ ሐጀርን ቡሉጙ-ል-መራም ወይም የሸይኽ ፈውዛንን አል-ኢርሻድ… በእሳት አላቃጥልም።

በዚህ አካሄዳቸው ሳዳትና ኢብኑ ሙነወር አላህ አግርቶላቸው ቁርኣንን ቢተረጉሙም ሊያቃጥሉት ነው ማለት ነው።
አሁን ይሄ እብደት ምን አይነት ሰለፊይነት ነው? ወላሂ ትክክለኛ የደጋግ ሰለፎች መንገድ ከነዚህ ስሜት ከጋለባቸው ሰዎች አካሄድ የጠራ ነው።
አላህ ወደ ትክክለኛው ሐዲድ ይመልሳቸው። ሚዛናዊነትን ያላብሳቸው፣ ካሉበት ጡዘትና እልህ ያብርዳቸው። እኛንም ወደ ቀጥተኛው ጎዳና ይምራን።

https://t.me/B1e9h
☀️ قَالَ رَسُولُ اللهﷺ :


(أكثِروا الصَّلاةَ عليَّ يومَ الجمُعةِ و ليلةَ الجمُعةِ ، فمَن صلَّى عليَّ صلاةً صلَّى الله عليهِ عَشرًا)


📚 صحيح الجامع

✔️ የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:

በጁሙዓ ቀንና ለሊት በኔ ላይ ሶለዋት ማውረድን አብዙ, ምክኒያቱም በኔ ላይ አንድ ሶለዋትን ያወረደ ሰው አላህ በርሱ ላይ አስር ሶለዋትን ያወርዳል።



https://t.me/B1e9h
🔹 የነቢዩላህ ዘከሪያ ዱዓ🔹
ነቢዩላህ ዘከሪያ አሏህ ወራሽ ልጅን እንዲሰጣቸው ዱዓ ባደረጉበት ሰዓት ላይ የተጠቀሙት ቃል ይደንቀኛል።

رَبِّ لَا تَذَرْنِي فَرْدًا
«ጌታዬ ሆይ! ብቻዬን አትተወኝ፡፡"

ይህን ካሉ በኃላ የዱዓቸውን መደምደሚያ እንዲህ አስከተሉ፦

وَأَنتَ خَيْرُ الْوَارِثِينَ
"አንተም ከወራሾች ሁሉ በላጭ ነህ"

ኢማም አሉሲይ በዚህ አንቀፅ ተፍሲር ላይ እንዲህ አሉ:-
"የእሳቸው ንግግር ሲብራራ "ጌታዬ ሆይ! ወራሽ ልጅን ስጠኝ። ውሳኔህ ሆኖ የሚወርሰኝን ልጅ ባትሰጠኝም፤ አንተ ምድርና ሰማያትን የምትወርስ፤ ከወራሾች ሁሉ በላጭ ነህ።" ማለት ነው።
ይህም ረቂቅ የሆነን የዱዓ አደብ ይዟል። ለምኜህ የምፈልገውን ባትሰጠኝ፤ ጉዳዬን ላንተ ጥያለሁ። አንተ በቂዬ ነህ። ካንተ መልካም የሆነን ምትክ እንጂ አላገኝም። ይህ የኢስላም አስኳል ነው። ይህ የኢማን መቅኔ ነው።


https://t.me/B1e9h
Forwarded from "ኡማ ቲቪ " Tv
እኚህ ሰው abdulmunaf yunusa sarina ይባላሉ ፡ እና በጠዋት ይነሱና በመኪና ለመጓዝ አስቸጋሪ የሆኑ ቦታ ላይ ያላቸውን የሩዝ እርሻ ለመጎብኘት ሞተር ሳይክላቸውን ይዘው ይወጣሉ ።
.....
በመንገዳቸውም ላይ የሚያገኟቸውን ሰወች ሰላም እያሉ ፡ በአካባቢው ያሉትን ገበሬዎች ፡ እርሻው እንዴት ሆነላችሁ ፡ ቤተሰብስ ሰላም ነው ወይ ብለው እየጠየቁ ፡ የታመመ ፡ ያዘነ ፡ ወይም የወለደች ሴት ካለች ገባ ብለው ጠይቀው ነው ወደ ስራቸው የሚሄዱት ።
.....
እና አሁን ደግሞ እኚህ ለመኪና አስቸጋሪ ቦታ በሞተር እየሄዱ ስራቸውን እየሰሩ ያሉት ፡ ኩራት የሚባል ጫፋቸው ሳይደርስ የወለደና የታመመን ሰው የሚጠይቁና የሚረዱ ሰው ማን ናቸው የሚለውን እንይ ።
......
abdulmunaf yunusa sarina በነዳጅ ዘይት እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ተሰማርተው እየሰሩ ያሉ ናይጄሪያዊ ቢሊየነር ናቸው ። በአሁኑ ወቅት ፡ በመላ ናይጄሪያ ከ50 በላይ የነዳጅ ማደያዎች እንዲሁም በካኑ ግዛት ያለው ግዙፍ ዩኒቨርስቲ የሳቸው ነው ። ይህ ብቻ አይደለም ። አዝማን የሚባል አየር መንገድ የግል ንብረታቸው ነው ። በስሩም ሁለት ቦይንግ 747 አንድ ኤርባስ እና ሌሎች አውሮፕላኖች አላቸው ። አጠቃላይ የሀብታቸው መጠንም ወደ 3 ቢሊየን ዶላር ይጠጋል
...
ይህ ሁሉ ግን ለሳቸው ምንም አይደለም ። ይህ ሁሉ ንብረት እያላቸው ኩራት ጫፋቸው ደርሶ አያውቅም ። አሁንም በሞተር ይጓዛሉ ። አሁንም የታመመ ይጠይቃሉ ። ህይወታቸው ይሄ ነው ።
....
ሚሊየን ብሮች ያልቀየሩት ምርጥ ስብእና
©Wasihun tasefaya
መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ!
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/+UAKV32q7U2HKzEMf
እስኪ ዛሬ ለኔም ለእናንተም ኻሰተን ለእህቶቻችን ማነቀቃያ ትሆን ዘንድ በዘመናችን ካሉ ድንቅ የሴት ሸይኻህ በወፍ በረር አንዷን ልጠቁማቹ

ስሟ ሸይኻህ ዱክቱራህ ካሚለህ ቢንት መሃመድ ቢን ጃሲም ቢን ዐሊይ አል ጁሃሪል ከዋሪ ትባላለች ዱክቱራህ ካሚለቱል ከዋሪ በሚባለው በስፋት ትታወቃለች ኳታራዊ ነች እጅግ ድንቅ የሆነች የእውቀት ባለቤት ነች ፊቂህ ነህው ኡሱሉል ፊቂህ ተፍሲር እና ሌሎችም ፈኖች ላይ ያላት ተመኩን ዐጂብ ነው

የተለያዩ 17 በዑሉሙ ተፍሲር ፣ ዐቂዳህ ፣ ፊቂህ ፣ ኡሱሉል ፊቂህ ፣ ቀዋኢዱል ፊቂሂያህ ፣ ሲራህ ፣ ሉገህ ፣ መንጢቅ ፣ በላጋህ በመሳሰሉት ፈኖች ላይ ወሳኝ ኪታቦች ተእሊቃቶች እና ኢኽቲሳራቶች አሉዋት ከነሱም ውስጥ በከፊሉ

1ኛ፦ አል ሙኽተሰሩ ሚን ሸርሂል ሙምቲዕ፦ ይህ ኪታብ የኢብኑ ዑሰይሚኑን የዘመኑ የፊቂህ ኢንሳይክሎፒድያ ሚባለውን ግዙፉን ሸርህ አል ሙምቲዕን ያሰጠረችበት ኪታብ ነው የተለያዩ ፈዋኢዶችንም ጨምራበታለች በጃሚአዎች ውስጥ እንደ ዋና ማስተያያ ይወሰዳል ሸይኹ ከመዝሃባቸው ሃናቢላ ወጥተው ተርጂህ ሲያረጉ እሷ የተለያዩ ከመዝሃቡ ፈዋኢዶች ትጨምራለች

2፦ ተፍሲሩ ገሪቢል ቁርአን
3፦ አል ፈዋኢዱል መስጡራህ ፊ ሀሊ አልፋዚ ኪታቢ ኢዕላሚ ሱነቲል መንሹራህ(2 ሙጀለድ)
4፦ አልወሲጥ ፊ ነህው
5፦ አተጥቢቁል ኢዕራቢይ
6፦ አፍናኑ ሲያገቲ ፊ ሀሊ አልፋዚ ዱሩሱል በላገቲ
7፦ አደውኡል ባሂር ፊ ሀሊ አልፋዚ ረውደቱ ናዚር ወጀነቱል ሙናዚር
8፦ አል ዐዝቡል መዒን ፊ ሃሊ አልፋዚ ሚንሃጁ ሳሊኪን
9፦ ሸርህ ኪታቡ ተህቢሪ ፊ ዒልሚ ተፍሲር(2 ሙጀለድ)
10፦ ሸርህ ቀዋኢዱል ፊቂሂያህ
11፦ ቀድሙል ዐሊም ወተሰልሱሉል ሃዋዲስ በይነ ሸይኺል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ወልፈላሲፋህ መዐ በያኒ መን አኽጠአ ፊል መስአለቲ ሚነ ሳቢቂን ወልሙዐሲሪን

12፦ አል ተስሂሉል ሙቅኒዕ ፊ ሃሊ አልፋዚ ረውዲል ሙረቢዕ (4 ሙጀለድ)
14፦ አል ኹላሰቱ ፊ ኡሱሉል ፊቂህ
15፦ አል ሙጅላ ፊ ሸርሂ ቀዋኢዱል ሙስላ ፊ አስማኢላሁል ሁስና
16፦ ሸርሁ ኑኒየቲ ሸይኽ ዐኢድ ዐዒድአል ቀርኒ
17፦ አህካሙ ሰላቲል ኹሱፍ

ቡግየቱል ሙቅተሲዲ ሸርህ ቢዳየቱል ሙጅተሂድን ተዕሊቅ እና ተህቂቅ አርጋዋለች
አትደነቁምን? አትገረሙምን ?
©Abdulhafiz_Mitiku
መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ!

https://t.me/B1e9h
ከስደተኛ ሴት

እየተበደሉ ብዙ እየተከፉ መኖርን በሀሴት፡
ተምረህ ተለወጥ ከስደተኛ ሴት....፡

......ያች ስደተኛ....

ስራ እየበዛባት አይወልቅም ቀሚሷ፡
ግን ስትነጋገር ፈገግ ይላል ጥርሷ፡
ለብሶተኛ ወንድ ዐርዐያህ ነች እሷ፡

እባክህ ወንድ ሆይ፤
ተበደልኩኝ ብለህ አሏህን አታማር....
ህመም መደበቅን፤
ስቃይ መሸከምን ከሴት ልጆች ተማር


Nuredin

https://t.me/B1e9h
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ፀሐይና ጨረቃ ዘላለም ቢኖሩ ከዘመኑ ጋር አይሄዱም እናዘምናቸው ተብሎ ይታሰባል? በጭራሽ!
ኢስላምም እንዲሁ ነው። እስከ እለተ ቂያማ በሚኖር ህዝብ ልክ የተሰፋ የዘመነ ዲን ነው

ሂጃብ ማለት ፀጉር መሸፈኛ ብጣሽ ጨርቅ ሳይሆን ሴቶች ውበታቸውን ለባዕድ ወንዶች ላለማሳየት የሚሰተሩበት፣ የሚሸፈኑበት፣ የሚከለሉበት ተግባር ነው።  ተግባሩ ከራስ እስከ ጥፍር በሰፊ ልብስ መሸፈንን፣ ተግባሩ ባዕድ ወንዶች ባሉበት አለመገኘትን/አለመቀላቀልን፣ ተግባሩ በሚዲያ አለመታየትን፣ ወዘተ ያካተተ የአላህ ትዕዛዝ ነው

ስለሂጃብ ምንነት ያልገባቸው ወይም ሊነግዱበት የፈለጉ ሰዎች ሚስ ሂጃብ የሚል ፀረ-ሂጃብ እንቅስቃሴ ጀምረዋል። የእንቅስቃሴው promoter ደግሞ ሚንበር ቲቪ ነው። ለኢስላም በኢስላም ስም የተቋቋመ አንድ ሚዲያ በዚህ መልኩ ኢስላምን የሚሸረሽር ተግባር ላይ ተሰማርቶ እንደማየት የሚያሳዝን ተግባር የለም ሚዲያውን በቅርብ ለሚያቀው ብዙ የከፍ ተግባትን ሲሰራ ነበር ዛሬ ደሞ ኢሄው በሴት ሀያእነት ስለ ሒጅብ ሊያስተምሩን ሚስ ሒጃብ መጡ!!

ምንኛ የከፋ ንግድ ነው!
ሰወቹን በቅርበት ለሚያቃቸው ጥቅም ያስገኝ እንጂ ሌላም ነገር ቃላቸውን አሳምረው መምጣታቸው አይቀርም ሀራም ሀራም ነው ኸምርን ስም ብቀይርት ያው አስካሪ መጠጥ ነው!!

https://t.me/B1e9h
ከፍ በል በኢስላም!
~
አለባበሳችንን፣ አነጋገራችንን፣ የፀጉር ቁርጣችንን፣ የሜካፕ አጠቃቀም፣ የልብስ ምርጫችንን፣ ... ለመወሰን በወቅታዊ ፋሽን መሸነፍ አይገባም። ሸሪዐው ሲያዝ አሻፈረኝ ብለን የዘመኑ ፋሽን ሲሆን የምንንበረከክ ልፍስፍሶች መሆን የለብንም። እኛ በኢስላማዊ እሴቶቻችን ፈፅሞ የማንሸማቀቅ ኩሩዎች እንጂ የተሸነፈ ስነ ልቦና የያዙ ደካሞች ልንሆን አይገባም። ደግሞም ለራሳችንም ዋጋ መስጠት መልካም ነው። አላህ በኢስላም ካከበረን በኋላ፣ 0ቅልን ያክል ኒዕማ ከሰጠን በኋላ ከሰውነት ወለል ወርደን የልብስ መስቀያ፣ የፋሽን ማሳያ አሻንጉሊት ልንሆን አይገባም።
IbnuMunewor

https://t.me/B1e9h
የሸዋል ወር ሊያልቅ 6 ወይም 7
ቀን ብቻ ስለቀረው ስድስቱን የሸዋል ፆም ያላጠናቃችሁ ወንድምና እህቶች ሳያመልጣችሁ ተሽቀዳደሙ ባረከሏሁ ፊኩም።

https://t.me/B1e9h
'ተጽእኖ  መፍጠር' የሚለው በህይዎታችን ላይ ተጽእኖ እንዳይፈጥርብን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን !
ሶሻል ሚዲያ በባህሪው የምናስተላልፈውን ነገር ሰዎች ግብረ-መልስ የሚሰጡበት  ላይክ፣ኮመንት፣ፎሎው የሚያደርጉቡት ፕላት ፎርም ስለሆነ ተጽእኖው ከፍተኛ ነው ። ዛሬ  አብሃኞቻችን ሌሎች ተጽእኖ ለመፍጠር እንጨነቃለን፣እንጠበባለን ። ሳናስበውም በራስ ፍቅር መውደቅ  እና ከፍ ሲልም ሳይታወቀን በራስ አምልኮ እንጠመዳለን ። ራሳችንን ለመሸጥ በምናደርገው ግፊያ  ራሳችንን እናጣለን !
መጥፎ በሆኑ ነገሮች ተጽእኖ መፍጠር እና ለሌሎች መጥፎ አርአያ መሆን ከባድ የሆነ ክስረት የመሆኑን ያህል መልካም ስራ እየሰራንም በዚሁ መፈተናችን አይቀርም ። ምን ጊዜም እንደ ሙስሊም ራስን መለስ ብሎ መቃኘት፣ሁሉን ነገር አላህ በሚወደው መልኩ ማድረግ፣ነፍስን መርመር ያስፈልጋል ።
ብዙ ሰው ስለተከተለን ታላቅ ደረጃ ላይ የደረስን፣ወይም  ደግሞ ሪአክሽኑ ሲያንስ የወደቅን የሚመስለን ከሆነ ከባድ የስነ-ልቦና ስብራት ያጋጥመናል ።
ሁሌም ቢሆን አላህን ማስታወስ፣ያገኘነውንም ተጽእኖ ፈጣሪነት በቻልነው ሁሉ ወደ እሱ ማስጠጋት በሱው መንገድ መትጋት ያስፈልጋል ።
በተለይ ከኸይር ስራ ከኢባዳ ጋር የተያያዙ ነገሮቻችን በሶሻል ሚዲያ ውሏችን እና አካሄዳችን ላይ ተጽእኖ እንዳይፈጥሩ መጠንቀቁ  መልካም ነው ።፡ በማንኛውም መልኩ ሁልጊዜ ከራስ ጋር ሂሳብ ማድረጉ ተገቢ ነው ብየ አስባለሁ !
ወሏሁ አእለም ! ሁላችንንም አላህ ቅኑን መንገድ ይምራን !
©አብዱረሂም አህመድ

https://t.me/B1e9h
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
~
﴿إذا سَبَّكَ رجلٌ بِما يَعلَمُ مِنكَ، فلا تَسُبَّهُ بِما تَعلَمُ مِنهُ، فيَكونُ أجرُ ذلكَ لكَ ووبالُهُ عليهِ﴾

ሰውዬው ስለአንተ በሚያውቀው ጉዳይ አንስቶ ክብርህን ለማጉደፍ ከሰደበህ(ከወነጀለህ) ፤ አንተ መልስህ ስለሱ ባወከው ነገር ላይ አትስደበው(አትወንጅለው)
በተሰደብክበት ነገር ላንተ ምንዳ ሲኖርህ ውንጀላው ደግሞ ወደራሱ ይሆናል።”


📚ሶሂህ አልጃሚ: 594

https://t.me/B1e9h