𝐑𝐢𝐨 𝐢𝐬𝐥𝐚𝐦𝐢𝐜✌️
21.8K subscribers
433 photos
192 videos
8 files
476 links
Download Telegram
'
ብቸኛው ህልሜ ከ አልጋዬ ስነሳ ከሁለት ሰቶች ጋር መንቃት ነው!!
፡
አንደኛዋ "ደህና አደርክ ውዴ" ስትለኝ ሌላኛዋ ደግሞ....
....................................................................................
እላዬ ላይ እየዘለለች "ተነስ አባዬ " እንድትለኝ እፈልጋለው 🥰

@alahu_akber1
የጅማሪዎች ውብ መሆን
ኖርማል ነው ‥. ምክኒያቱም
ጅማሪ ላይ መጥቶ Hi እኔ ውሻ ነኝ
የሚልህ ሰው አይኖርም ።

@alahu_akber1
'
•••✿ ❒ የነብዩሏህ ኑህ ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••

#ክፍል 1

አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ ከነዝያ ህዝቦች ወደ ቀጥተኛው መንገድ ይመራቸው ዘንድ ኑህ የተባሉ መልዕክተኛን አስነሳ።

ኑህም ህዝባቸውን ሰበሰቡ'ና፦" እኔ ለእናንተ ታማኝ መልዕክተኛ ነኝ፡፡

አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ(ክፍያ) አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም" ብለው ህዝባቸውን ተጣሩ።

ይህን ሲሰሙ አስተባበሉት ምንም ሊያምኑለት አላቻሉም።እንዲያውም ያፌዙበት ጀመር። ኑህ ዐ ሰ ያለመሰላቸት ዘወትር ጥሪም ያደርግላቸውም ነበር።

የህዝቦቹ ማፊዝ እና ማላገጥ በበዛበትም ግዜ፦" ወገኖቼ ሆይ! ምንም መሳሳት የለብኝም፡፡ ግን እኔ ከዓለማት ጌታ መልእክተኛ ነኝ፡፡

የጌታዬን መልክቶች አደርስላችኋለሁ፡፡ ለእናንተም እመክራችኋለሁ፡፡ ከአላህም በኩል የማታውቁትን ዐውቃለሁ።" አላቸው።

የኑህን ዐ ሰ ንግግር በሰሙ ግዜ በጣም በመገረም፦" አንተ ኑህ!!! አንተ እኮ እንደኛው ሰው ነህ እንዴት ነው መልዕክተኛ ነኝ ምትለው? በዛ ላይ ጥቂት ተከታዮች አሉህ ሁሉም ግን ድሀ እና ኮሳሳ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ናቸው።

ደግሞም በሀብትም ሆነ በክብር ከኛ ጋር አትመጣጠኑም" ብለውም አስተባበሉ።

ያም አላንስ ብሏቸው እርስ በርስ በሚፈፅሙት የሀውልት አምልኮ እንዲፀኑ ይመካከሩም ጀመር።

ኑህም የህዝቡ ሁኔታ ተስፋ ሲያስቆርጠው በመለማመጥ መልኩ፦አላህን ልትፈሩና ይታዘንላችሁም ዘንድ ከእናንተው (ጎሳ) በኾነ ሰው ላይ እንዲያስጠነቅቃችሁ ከጌታችሁ ግሳጼ ቢመጣላችሁ ትደነቃላችሁን" እያለ ቢያግባባቸውም ክህደታቸው ይበልጥ እየጨመረ እንጂ ምንም አይቀንስም ነበር።

ምንም እንኳን ኑህ ዐ ሰ የህዝቡ ነገር ተስፋ ቢያስቆርጣቸውም ተልዕኮዋቸውን በሚገባ በማድረስ ላይ ቀጥለዋል።

እናም ሁሌ ቀን እና ማታ ህዝባቸውን ስለ አላህ ሲያስታውሷቸው ህዝባቸው የነቢያቸውን ዳዕዋ ከመስማት ጆሮዋቸውን መያዝ ጀመሩ።ጆሮዋቸውን ይዘው መስማት እንቢ ሲሉ ኑህ ዐ ሰ በምልክት ይነግሯቸው ነበር። ኑህም በምልክት ሲነግሯቸው ህዥቡ ግን አይኖቻቸውን በልብሶቻቸው ይሸፍኑ ነበር።

ምንም ተስፋ አልቆርጥ ብሎ መቆም መቀመጥ ሲከለክላቸው፦"ድሆች እና ዝቅተኛ ሰዎች ያንተ ተከታይ ሆነው ሳለ እኛም ከነሱ ጋር እንድንከተልህ ትሻለህን!!! ይልቁንስ እኛ እንድንከተልህ ከፈለግክ እነዚህን ተራ ሰዎች ከጎንህ አርቃቸው።" አሉት።

ኑህ'ም ዐ ሰ፦"እነሱ የሚሰሩትን አላህ ነው ሚያውቀው። እኔ ላባርራቸው አልችልም።

እንዴትስ ረዳቶቼን፣አክባሪዎቼን አባርር ትሉኛላችሁ!!! ቆይ ባባርራቸውስ እኔን ከአላህ ማን ያተርፈኛል? አታስተውሉምን?" ብሎ ጠንከር አለባቸው።

ኑህ ዐ ሰ መልካም ነብይ ነበሩ። ሀብታም፣ድሀ ደከማ፣ጠንካራ፣ትልቅ፣ትንሽ ስይሉ ለሁሉም በክብር የተላኩትን ዳዕዋ አደረሱ።

ምንም እንኳም ለ950 አመታት ዳዕዋ ቢያደርጉም ዳዕዋቸውን ከ80 በላይ ሰው ሊቀበላቸው ባለመቻሉ ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ለጌታቸው ስሞታ ለማቅረብ ተገደዱ።

እንዲህም ሲሉ ለአላህ ነገሩት፦"ጌታዬ! ህዝቦቼ እኮ አስተባበሉኝ። በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን(አድን)፡፡"

ከዚህ በኋላ የኑህ ዐ ሰ የዳዕዋ ጥሪ ዛቻ አዘል መሆን ጀመረ።እነሱም ለኑህ ዐ ሰ ዛች ግድ አልነበራቸውም ይልቁኑ፦"የምትዝትብንን አምጣ እውነተኛ ከሆንክ" እያሉ ሲሳለቁበትም ጀመር።

ኑህም፦"ይህ እኮ በኔ ቁጥጥር ውስጥ አይደለም። ያ የአላህ ስልጣን ነው" ይላቸዋል።

አሁን ነገሩ መቋጫው ተቃርቧል አላህም አስፈሪ ወህይ እንዲህ ሲል ወደ ኑህ አወረደ፦" ከሕዝቦችህ በእርግጥ ካመኑት በስተቀር (ወደፊት ከአሁን በኋላ) አያምኑም፡፡ ይሠሩትም በነበሩት (ክህደት) አትዘን"

በመቀጠልም አላህ ኑህን ዐ ሰ የዘንባባ ችግኝ እንዲተክል አዘዘው።ያች ዛፍ ለማፍራት ስትበቃ የአላህ ቅጣትም በነዚያ ህዝቦች ላይ እንደሚፈፀም ቃል ገባለት።

የአላህ የተለምዶ እዝነቱ ይታወቀ ነው። ትልልቅ ሰዎች ባጠፉት ህፃናትን አይቀጣም'ና ህፃናት የቅጣቱ ሰለባ እንዳይሆኑ ቅጣቱ ከመፈፀሙ ከ40 አመታት በፊት የሴቶቹ ማህፀን ፅንስ መሸከም እንዳይችል አደረገው።

ለ40 አመት ያህል ምንም አይነት ህፃን ሳይወለድ ቀረ።በዚያ ዘመም ኑህ ዐ ሰ የታዘዘውን ዛፍ እንክብካቤ ሲያደርግ እነዚህ አመፀኛ ህዝቦች እንዲህ በማለት ይሳለቁበት ነበር፦"አንተ ኑህ ነቢይ ነኝ እያልክ ዘራፍ ብለህ አላዋጣ ሲልህ ወደ ግብርና ገባህ እንዴ!!!" ድንጋይም ይወረውሩባቸው ነበር።

የተተከለው ዛፍ 50 አመት ሲሞላው አላህም ለኑህ ዐ ሰ ወህይ በማውረድ ዛፎችን እንዲቆጣቸው አዘዛቸው።

ኑህም ዐ ሰ ዛፎቹን ከቆረጠ በኋላ አላህም ትልቅ መርከብ እንዲሰራ አዘዘው።ጂብሪልም መርከብ እንዴት እንደሚሰራ ሊያሳየው ከሰባት ሰማያት ወረደ።

አላህም እንዲህ ሲል ወህይ አወረደ፦

"የመርከቧ ርዝመት 1200 ክንድ

የጎን ስፋት 800 ክንድ

ከፍታው ደግሞ 80 ክንድ የሆነችን መርከብ ስራ"

በተንጣለለ አሸዋማ እና በረሀማ ቦታ ላይ ኑህ መርከቧን መስራት ጀመሩ።ህዝቦቹም ከአጠገቡ ሲያልፉ፦"አንተ ኑህ ከነብይነት አናፂነት ይሻላል ብለህ ነው?" እያሉ ያፌዙበታል።

ከፊሎቹ ደግሞ፦"አንተ ኑህ መርከብ እኮ ለባህር ነው ሚሰራው አንተ እልም ያለ በረሀ ላይ ትሰራለህ እንዴ!" ይሏቸዋል።

ኑህም ለስለስ ባለ አንደበት፦"ዛሬ በኛ ላይ ብትሳለቁብን ነገ እኛም በእናንተ ላይ እንሳለቅባችኋለን" ይላቸው ነበር።

የመርከቧ ስራ ከተጠናቀቀ በኋላ አላህ ኑህን ያመኑበትን ሁሉ መርከቧ ላይ እንዲጭን እና ከእያንዳንዱ እንስሳት እና የዱር አራዊት አንድ ወንድ አንድ ሴት በመርከቧ እንዲጭን አዘዘ።የምዕመናኑ ቁጥር 80 ብቻ ነበር።

ለኑህም ዐ ሰ ሁለት ሚስቶች ነበሩት አንደኛዋ ሙስሊም ስትሆን ሁለተኛዋ አመፀኛ ካፊር ናት።እሱም ሙስሊሟን መርከብ ላይ ጫናት።

መርከቧ ውስጥ ሁሉም ቦታውን ከያዘ በኋላ ፀሀይ ብርሀኗን ተነጠቀች ምድር በአስፈሪ ፅልመት ተዋጠች።

ሰማይም ዶፍ ዝናብን ማንቧቧት ጀመረ...በከርሰ ምድርም ታምቆ የነበረው ውሀ ምድሪቱን እየሰነጠቀ ለጉድ መፍለቅ ጀመረ።

ከሰማይ የወረደው ውሀ እና ከምድር የወጣው ውሀ ሲገናኝ ምድር ከአቅሟ በላይ መጥለቅለቅ ጀመረች።ያን ግዜ መርከቧ ቀስ እያለች መንሳፈፍ ጀመረች።

ክፍል 2 ይቀጥላል....

#share
@alahu_akber1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
'
ያረብ ይሄን የላጤ ሂወት በቃ በለን 😭

@alahu_akber1
'
•••✿ ❒ የነብዩሏህ ኑህ ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••

#ክፍል 2

ከሰማይ የወረደው ውሀ እና ከምድር የወጣው ውሀ ሲገናኝ ምድር ከአቅሟ በላይ መጥለቅለቅ ጀመረች።ያን ግዜ መርከቧ ቀስ እያለች መንሳፈፍ ጀመረች።

ውሀው በየሰዐቱ እየጨመረ ነው አጋጣሚ ኑህ ዐ ሰ ሁኔታውን ለማጣራት ወደ ምድር ሲመለከቱ የአብራካቸው ክፋይ የሆነው ልጃቸው አንዴ ሲወድቅ አንዴ ሲነሳ ውሀው ሲያንከራትተው ተመለከቱት።

እንዲህም ሲሉ ተጣሩ፦"ልጄ ና ከኛ ጋር ተሳፈር ከካሀዲያን ህዝብም አትሁን"

ልጁ ግን በትዕቢት የተሞላ ነው'ና፦"ከውሀው ይጠብቀኝ ዘንድ ወደ ተራራ እወጣለሁ" ብሎ መለሰላቸው።

እሳቸውም፦" ዛሬ ከአላህ ትዕዛዝ ምንም ጠባቂ የለም (እርሱ) ያዘነለት ካልሆነ በቀር" ብለው ንግግራቸውን ሳይጨርሱ እንደ ትልቅ ተራራ ያለ ማዕበል መጣና ልጁን ጠራርጎ ወሰደው።

ኑህም ልጄ እያሉ ወደ አላህ ሲጮሁ አላህም፦" ኑሕ ሆይ! እርሱ ከቤተሰብህ አይደለም፤ እርሱ መልካም ያልሆነ ሥራ ነው፤ በርሱ ዕውቀት የሌለህንም ነገር አትጠይቀኝ፤ እኔ ከሚሳሳቱት ሰዎች እንዳትሆን እገስጽሀለሁ" አለው።ወዲያውኑ ኑህ ተፀፀተና ተመለሰ፡፡አለም ጌታዬ ሆይ በሱ እውቀት የለለኝን ነገር የምጠይቅህ ከመሆን ኤኔ በንተ አጠበቃለሁ ዓለ፡፡ ለኔም በትመረኝ እና በታዝነልኝ ከከሳረመዎች እሆናለሁ ዓለ፡፡

ውሀውም ምድርን ለ40 ቀናት ያህል ካጥለቀለቀ በኋላ ምንም አይነት ነፍስ ያለው ነገር ከምድረ ገፅ ጠፋ።

እብኑ አባስ በወሩት ሀዲስ ኑህ እና ተከታዬቹ በመርከቧዎ ውስጥ ለ6ወራት ቆይተዋል፡፡ በቡዙ ዘገባወች እንደተጠቀሰው ኑህ እና አማኞቹ ከመርከቢቱ የወረዱት በአሹራ እለት ነው፡፡በሙሀረም በ10ኛው ቀን ማለት ነው፡፡በቡዙ ዘገባወች እንደተጠቀሰው ነቢያችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይህነን አሏህ ሙሳን ዐ ሰ ከመስመጥ ያደነበትን አና ኑህን አለይሂሰላም ከመጥለቅለቅ ያደነበትን ያአሹራ እለት በፆም አክበረዋል፡፡

መጥለቅለቁ በአሏህ ሲበሀነሁ ወተዓላ በወረደ ትዕዛዝ ተጠናቀቀ፡፡

ያን ግዜ አላህም ምድርን፦"ምድር ሆይ! ውሃሽን ዋጪ፡፡ ሰማይም ሆይ (ዝናብሽን) ያዢ፡፡" ብሎ ምድርን ከመጥለቅለቅ አስቆመ።ቅጣቱም ተጠናቀቀ፤

ምድር ትንሽ ጠፈፍ ማለት ስትጀመር ኑህን እና ተከታዮቹን የተሸከመችው መርከብ በሰላም ጁዲይ በተባለ ተራራ ላይ አረፈች።

ከዚያነም፡አሏህ ሱ ወ እንዲህ ዓለው ኑህ ሆይ ከኛ በሆነ ሰላም በንተ ለይ እና አንተምጋ ባሉት ህዝቦች፣ ትውልድ ላይ በሆኑ በረከቶችን የተጎናጠፉክ ሁነህ ውረድ፡፡

ከነሱ ዘሮች የሆኑ ህዝቦችም በቅርቢቱ አለም በርግጥ እናስመቻችዋለን።ከዝህ ብሇላ መልሰው ወደ ክህደት ለሚገቡ ደግሞ ከዚያም ከኛ የሆነ አሳማሚ ቅጣት ይነካችዋል ተባለ፡፡

ኑህ በመርከቢቷዋ በቆየበት ቆይታ ውሃው ቶሎ እንዲሰርግ ይፈልግ ነበር፣ በዚሂም ግዜ እርግበን አዲስ ነገር ታመላክተው ዘንድ ይልካት ነበር፣

ምነም ነገር ሰትይዝ ተመለስ ነበር፡፡

ከእለታት አንድ ቀን የዘይቱን ቅረጫፉ አመጣቺለት፣ በዚህም ወሃው የሰረገና አተክልቶች መብቀል እንደጀመረ አወቀ፡፡

እንደገና መልሶ ሲልካት በግሮቿዋ ላይ የጭቃ ቅሬት የዛ ተመለሰች፡፡ ፉቺው በመሬት ላይ አረፈች ማለት ነው፡፡

የበዚህም መጥለቅለቁ እንዳበቃ አወቀ፡፡

ይህ እኛ ዘንድ በታረክ መዛግብት ውስጥ ይገኛል፡፡ከዚህ ተነስተው ነው ሌሎች የሰላም እርግብ የሚሉት፡፡
በግሮቻ የምታዝለውም የዘይቱን ቀንዘል ያነን የሚጦቅም ነው፡፡

ኑህ ዐ ሰ ከአደም ልጆች መካከል እነዚያ ከሱጋ የቀሩት ብቻ እንጂ ሌሎች የሌሉ ሲሆን ወረድ፡፡በምደር ላይ የሉ ሰወች ሁሉ አለቀዋል፡፡በረግጥ መደር እንዳዐሁኑ ግዜ የሰው ልጆች አልተሰረጬባትም፡፡
በተወሰነች ስፉራ በአረብ ደሴት ፣ በፊሊስጢን፣ና በዙሯዋ ብቻ ነበር የሰው ልጆች ሰፈረውባት የነበረው እነኝህ ክልል ብቻ ነበሩ፡፡የተቀሩ ምድሮች የሰው ልጆች፡አልነበሩባትም፡፡ግን የተጥለቀለቀቺው ምደር ሁላ ነበር፡፡

ከዚያን አሏህ ከኑህ ዐ ሰ ጋ የነበረትን ህዝቦች በሙሉ መሀን አደረጋቸው፡፡ መውለድ የማይቺሉ፤ ለኑህ ና ለባለቤቱ በስተቀር ለሌሎች ልጅ ሊወለድ አልቻለም፡፡ከመደር ላይ ከዘለቀው ከኑህ ዝሪያ በስተቀር ሌላ አልቀረም ፡፡

ከዚህም የተነሳ ኑህ ዐ ሰ ሁለተኛው አደም በመባል ይጠራል፡፡ሁለተኛ የሰው ልጅች አባት በመባል ተሰይሞል፡፡

በመጨረሻም አላህ ኑህን ዐ ሰ፦"ኑህ ሆይ! እኔ ፍጥረታትን የፈጠርኩት እንዲገዙኝ ነው።እኔ ያዘዝኳቸውንም እንዲታዘዙኝ ነው።ነገር ግን አመፁኝ፤ከኔ ሌላ የሆነንም አካል ጌታ አድርገው ያዙ። ያን ግዜ ቁጣዬም እነሱ ላይ ተፈፃሚ ሆነ በውሀም አጥለቀለቅኳቸው" ብሎ ወህይ አወረደለት።

አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ የ ኑህን (ዐ ሰ) ህዝብ በውሀ ካጥለቀለቀ በኋላ በምድር ላይ ከ ኑህ(ዐ ሰ) ጋር አብረው ከዳኑት ምዕመናን ውጭ ምንም አይነት የሰው ልጅ አልቀረም ነበር።ኑህ ከወሃው መጥለቅለቅ ቡሇላ 350ዓመት ኖረ፡፡

አሏህ ሱበሃነሁ ወተዓላ እንደጠቀሰው፤ለ350አመታት አሏህን ተገዢና አመስጋኝ ሆኖ ነው የኖረው፡፡

እብኑ ማጀህ በዘገቡት ሀዲስ፣ ነቢዩ (ሰዐወ) የኑህን ፆምን ሲገልፁ ኑህ ዐ ሰ ከኢድ ቀናት ውጭ ያሉትን የዓመቱ ቀናትን ሁሉ የፆሙ ነበር በለዋል፡፡በኢድ ለት ያፈጥራል እንጂ በተቀሩት ቀናት ሁሉ በፆም ላይ ነው፡፡ ኑህ ዐ ሰ የሆን ዓመት ከቆየ ቡሇላ ሞቴ፡፡

ስለሱ ከተዘገቡ ዘገባወች አመዛኙ መካ እንደተቀበረ የሚናገረው ነው፡፡በዐንዳድ ዘገባዎች ደግሞ ሉብናን ሊባኖስ ሀገር በሚገኘው ከርከር በቃ በተባለ ስፉራ የተቀበረ መሆኑን ተነግሯል፡፡ይህም ዘገባ ሚዛን ያለው ነው፡፡ኑህ አለይሂሰላም 3ልጆች ነበሩት ፣ ሳም ፣ሃም ና ያፌስ!!

በሳም ልጆች ውስጥ፦ነጭ ነት ና ትነሽ ጡቁረነት ነበረበት፡፡ ወደ ጠይምነተም የሚያመዝን መልክም አለ፣ነጭነትም ቀይነትም ነበረበት፡፡

በሀም ልጆች ዉስጥ ደግሞ፦ጡቅረት የሚሃይል ሲሆን፣ ጢቂትነጭነት ይገኝበታል፡፡አብዛኛቸው ግን ጡቅረት አለበት፤
የያፌስልጆች ደግሞ፦ነጭነት ና ቀይነት የለባቸው ናቸው፡፡አረቦች እና ኢስሪዒላዊያን የሳም ዝሪያወች ናቸው፡፡

አፍሪካዊያን ደግሞ፦ የሃም ዝሪያ ናቸው፡፡ቱርኮች ፣ምስረቅ ኢሲያወች ና አውሮፓዊያኖች ደግሞ የያፌስ ዝሪያወች ናቸው፡፡

•••✿ ❒ ተ_ፈ_ፀ_መ ❒✿•••

በቀጣይ #ነብዩሏህ ሁድ(ዐ.ሰ) ታሪክ እንጀምራለን 🥰
#share
@alahu_akber1
'
ትልቁ ክስረት ምን እንደሆነ ታውቃላቹ ??
ጀነት ስፋቷ ከምድር በላይ ሆኖ እኛ እዛ ውስጥ ቦታ ቦታ ሳይኖረን ሲቀር ነው 🥀

@alahu_akber1
'
•••✿❒ ነብዩሏህ ሁድ ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••

ይህ በእንዲህ እንዳለ ኑህ ዐ ሰ እና በዘመኑ የነበሩት ሰዎች ከሞቱ በኋላ አንዱ አንዱን ሲተካ ምድር ዳግም በሰዎች ትሞላ ጀመር።

ያ ዘመን ካለፈ በኋላ የነበሩ ህዝቦችም ማንም አምልኮ ከምያውቀው በላይ ጣኦትን ማምለክ ተያያዙት።የህዝቡ መለያ ስማቸውም (ዓድ) ይባላል።

በመጀመርያ የዓድን ህዝቦች ላስተዋውቃችሁ...

የዓድ ህዝቦች በዐረቢያ ምድር በየመን ግዛት አህቃፍ በሚባል አካባቢ ኢረም በተባለች ከተማ የሚኖሩ በጣም ትላልቅ ቁመና ያላቸው ህዝቦች ሲሆኑ፤አላህ ስፍር ቁጥር የሌለውን የፀጋ አይነት ያትረፈረፈባቸው ህዝቦች ናቸው።

ከፀጋዎቻቸውም የሚኖሩበት ምድር በጣም ለቡቃያ አመቺ እና ለም አፈር ያለበት አካባቢ ነው።

ሰውነታቸውም በጣም ግዙፎች እና ረጃጅሞችም ነበሩ።

ከሰውነታቸው መግዘፍ የተነሳ አንድን የቴምር ዘንባባ በሁለት ጣታቸው ይነቅሉ ነበር።(የተምር ዛፎች ምን ያህል ግዙፍ እንደሆኑ ዐረብ ሀገር ያላችሁ ውዶች ታውቁታላችሁ)

ነገር ግን አላህ ለዋለላቸው እንዲህ አይነት ኒዕማ ምላሻቸው ምስጋና ሳይሆን ድንበር ያለፈ አመፅ እና መኩራራት ነበር።

የኑህ ህዝቦች ያደርጉት የነበረውን የጣኦት አምልኮ አሟሙቀው ጀመሩት።ያም አላንስ ብሏቸው ምድርን በተለያዩ የወንጀል አይነቶች ይሞሏትም ጀመር።

ነገር ግን ለቅጣት የማይቸኩለው አላህ በእዝነት አዘል ጥበቡ ከመጥፎ ከልክሎ ወደ መልካም የሚመራቸውን (ሁድ) የተባለውን መልዕክተኛ ከመሀከላቸው ላከላቸው።

ሁድ ዐ ሰ መልካም፣ቁጥብ፣የተረጋጉ እና አንደበተ ርቱዕ እና ዐረብኛ ቋንቋን ለመጀመርያ ግዜ የተናገሩ ሰው ናቸው።አላህም እሳቸውን ወደ ህዝባቸው በመሄድ የጌታቸውን ተልዕኮ እንዲያደርሱ አዘዛቸው።

ሁድ'ም ዐ ሰ የጌታቸውን ትዕዛዝ በመቀበል ወደ ዝባቸው ሄደው፦"እኔ ከጌታችሁ የተላክሁ ነብይ ስሆን፤በዚህ አለምም አላህ የሚባል ጌታ አላ።ከሱ ሌላ አምላክ የለም እነዚህ ከተለያዩ ድንጋይ እና እንጨት ጠርባችሁ ምታመልኳቸው ጣኦታት መጥቀምም መጉዳትም የማይችሉ ደካማ ሲሆኑ ከናንተ ጥበቃን ይሻሉ እንጂ እራሳቸውንም አይጠብቁም።

እኔን የታዘዘኝ ከሞት በኋላ ጀነት ይገባል እኔንም ያስተባበለኝ ጀሀነም መቀመጫው ስትሆን መቀመጫነቷስ ምንኛ ከፋ።" ብለው ማስጠንቀቅ ጀመሩ።

እነሱም ነቢያቸው በሚናገረው ግራ በመጋባት፦"እንዴት ነው አማልክቶቻችንን ትተን አንድን ፈጣሪ ብቻ ምንገዛው!!! ይህ ሰውዬ ምን አይነት ቂልነት ነው ይዞብን የመጣው" ይሉ ነበር።

ሁድ ዐ ሰ ህዝቦቹ የሚያሳዩት የመልስ ምት ለቅፅበት እንኳን ተስፋ አላስቆረጣቸውም ነበር። ይልቁኑ፦"እኔ ከናንተ ዘንድ የፈጣሪያችሁን ጥሪ ለማድረስ ከመሀከላችሁ የተመረጥኩ ስሆን፤የተላክሁበትንም ተልዕኮ ያለመሰላቸት በተደጋጋሚ ወደ እናንተ አደርሳለሁ።

እስቲ ፀሀይን እና ጨረቃን ተመልከቱ...ማን ነው የሚያፈራርቃቸው!!!

ማን ነው'ስ የፈጠራቸው!!!

ምድርንና ሰማይንም ተመልከቱ ማን ነው ምድርን አንጥፎ ሰማይን ያለ መሶሶ ያንጣለለው!!!

ተዉ ህዝቦቼ ጌታችሁን አምልኩት።ተጠንቀቁ እናንተ ከሞታችሁ በኋላ ትቀሰቀሱ'ና በሰራችሁት ትተሳሰባላችሁ።መልካም የሰራ ለነፍሱ ነው መጥፎ የሰራም ከከሳሪዎችም ይሆናል" እያሉ ይጠሯቸው ነበር።

ይህን የነቢያቸውን ጥሪ በሰሙ ግዜ፦"ይህን ሰው ከአማልክቶቻችን አንዱ በመጥፎ ተመልክቶታል(አብዷል)" በማለትም ይተቹት ጀመር።

አንዳንዴም፦"ይሄ ሂሳብ፣ጀነት፣ጀሀነም፣መቀስቀስ....ምናምን ምትለው ምን ማለት ነው?" እያሉም ይከራከሩታል።

የዓድ ህዝቦችም በምድር ላይ ያለ አግባብ ኮሩ፡፡ «ከእኛ ይበልጥ በኀይል ብርቱ ማን ነው?» አሉም፡፡ ያ የፈጠራቸው አላህ እርሱ በኀይል ከእነርሱ ይበልጥ የበረታ መኾኑን አያዩምን? በተዓምራታችንም ይክዱ ነበሩ። (ሱረቱል ፉሲለት)

ሁድ ዐ ሰ የህዝቡ ሁኔታ ተስፋ ሲያስቆርጠው፦"እናንተ ከምትሰሩት ሁሉ እኔ ነፃ መሆኔን ምስካሪ ሁኑ" እያለ የሱን ጥሪ ባለመቀበላቸው በዱንያ የሚወርድባቸውንም ቅጣት ያበስራቸውም ጀመር።

እነሱም፦"ምንድነው ዝም ብለህ ቅጣት ቅጣት...እያልክ ምታስፈራራን!!! እንደውም እስቲ ቅጣት ምትለውን አምጣው" እያሉ ሲያሾፉ

ሁድም ዐ ሰ፦"ይህ የማስጠንቅቃችሁ ቅጣት በናንተ ላይ ተፈፃሚ ይሆናል። አትጠራጠሩ" አሏቸው። በመጨረሻም ሁድ ዐ ሰ በህዝባቸው ላይ ዱዓ ማድረግ ጀመሩ።

ከዚያም አላህ የቅጣቱን አርጩሜ በህዝቡ ላይ ሊያወርድ መጀመርያ ለረጅም አመታት ዝናብ በማቋረጥ ምድሪቱን አድርቆ እንስሳቶቻቸውን አጠፋባቸው።

ሁድም ዐ ሰ፦"ከዚህ ሁሉ እንግልት ሊያድናችሁ እሚችለው በጌታችሁ ማመን ብቻ ነው" አላቸው።

እነሱም፦"በረሀብ እና በጥማት እንሞታታለን እንጂ ከጣኦቶቻችን ሌላ ማንንም አንለምንም" በማለት ጣኦታት ዘንድ እየሄዱ ኡኡኡ... ይሉ ጀመር።

ጣኦቶቻቸው ዘንድ ሄደው እሪ ብለው ሲወጡ ሰማይን በደመና ተሞልቶ አገኙት።በጣምም ተደሰቱ አማልክቱ ፀሎቶቻቸውንም እንደሰሙ አመኑ ጥሩ ዝናብ ሊዘንብልን ነው በማለትም ተመፃደቁ።

ያን ግዜ ሁድ ዐ ሰ፦"ይህ እኮ አምጣልን ያላችሁት የቅጣት ደመና ነው እንጂ እናንተ እንደምትሉት ዝናብ አይደለም" አላቸው።

ከዚያም ከፍተኛ ጉልበት የለው ንፋስ ከተማቸውን ያናውጥላቸው ጀመር።ቀስ በቀስ ንፋሱ አስፈሪ ድምፅን እየቀላቀለ በክፍተኛ ጩሀት ህዝቡን ወደ ሰማይ ማፈናጠር ጀመረ።

በዚህ ሁኔታ ለ 7 ሌሊቶች እና ለ 8 ቀናት

ያህል ንፋሱ ዘለቀ። በነዚያ የቅጣት ቀናት ሰውም እንስሳትም ምንም አይነት ፍጥረት አልቀረም ነበር።በሁድ ዐ ሰ ያመኑት ምዕመናን ሲቀሩ ሁሉም የመቅሰፍቱ ሰለባ ሆኑ.....

አሏህ ሱበሃነሁ ወተዓላ ነቢዩሏህ ሁድን ዐ ሰ እና ከሱጋ ያመኑት አዳነቸው፡፡

•••✿ ❒ ተ_ፈ_ፀ_መ ❒✿•••

በቀጣይ #ነብዩሏህ ሉጥ(ዐ.ሰ) ታሪክ እንጀምራለን 🥰
#share
@alahu_akber1
«ያ ረቢ!
ይህ ሁሉ እያመፅኩህ አልቀጣኸኝም!» አለ።
እንዲህ ተባለ: ‐

«ይህን ሁሉ እየቀጣሁህ እስከሁን አላወቅክም!?…
ከኔ ጋር የማንሾካሾክን ጣዕም አልከለከልኩህም?!»

[ኢማም ኢብኑል‐ጀውዚይ፥ ሶይዱል‐ኻጢር]
:
@alahu_akber1
አንተ እየጠነከርክ ሂድ እንጅ::
ሕይወት እየቀለለች ትመጣለች ብለህ እንዳትጠብቅ!!

@alahu_akber1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
'
ያረብ ይሄን የላጤ ሂወት በቃ በለን 😭

@alahu_akber1
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
'
ሷሊህ ሴት እና ሷሊህ ወንድ...
በዱአ ብዛት እንጂ በጅንጀና ዉጤት አይገናኙም 😎

@alahu_akber1
لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّة إِلَّا بِاللَّه

لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّة إِلَّا بِاللَّه

لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّة إِلَّا بِاللَّه

በተጨማሪ  እናንተም ጨምሩበት መልካም አዳር
'
•••✿❒ ነብዩሏህ ሉጥ ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••

#ክፍል 1

★ የሉጥ ሕዝቦች ነብያቸውን በምድር ላይም ብልሹነትን አነገሱ፥ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦

وَلُوطًا إِذْ قَالَلِقَوْمِهِۦٓ أَتَأْتُونَ ٱلْفَـٰحِشَةَ وَأَنتُمْ تُبْصِرُونَ ﴿٥٤﴾ أَئِنَّكُمْ لَتَأْتُونَ ٱلرِّجَالَ شَهْوَةًۭ مِّن دُونِ ٱلنِّسَآءِ ۚ بَلْأَنتُمْ قَوْمٌۭ تَجْهَلُونَ ﴿٥٥﴾
“ሉጥንም ለሕዞቦቹ ባለ ጊዜ (አስተውስ) እናንተ የምታዩ ስትኾኑ ጸያፍን ነገር ትሠራላችሁን።

እናንተ ከሴቶች አልፋችሁ ወንዶችን ለመከጀደል ትመጣላችሁን በውነቱ እናንተ የምትሳሳቱ ሕዝቦች ናችሁ። (አን-ነምል፥ 54-55)

እነዚህ ሕዝቦች በምሥራቃዊ ዮርዳኖስ ይኖሩ ነበር።

ይህ ቦታ በሙት ባህር አቅራቢያ ይገኛል። በአካባቢው አምስት መንደሮች ነበሩ። እነሱም;- “ሰዱም፣ ዑመራ” “አደመህ” “ሱወይም” “ባሊ’ዕ” ናቸው።ሉጥ (ዐ.ሰ) በዋናው መንደር ሰዱም ይኖሩ ነበር። መጥፎና ርካሽ ተግባራትን ትፈፅም የነበረችውም መንደር እሷ ነች።

የሰዱም ነዋሪዎች እርኩሶችና መጥፎ ከመሥራት የማይፈሩ ነበሩ። አስፀያፊ ተግባራቸውን በግልጽ የሚፈጽሙበት መሰብሰቢያ ቦታ ነበራቸው። መንገደኛን ይዘርፋሉ። ከሌላ አካባቢ ነጋዴዎች ከመጡ ተሰብስበው ዕቃቸውን ይቀማሉ።

የሉጥ ሕዝቦች ነፍሳቸውንም በእጅጉ የሚበድሉ እጅግ ቆሻሾች ነበር።ካቆሻሻነታቸው የተነሳ በፆታ ግንኙነት ከሴት ይልቅ ወንድ ከወንድ ጋር መገናኘት ይመርጡ ነበር።

እነዚህ ሰዎች መጥፎ ተግባራቸው ወሰን ያለፈ ስለሆነ ይህ አስፀያፊ ተግባር ወደ ሌሎችም አካባቢዎች እንዳይዛመት እነሱን በማስተካከል ወይም በማጥፋት ይህን መጥፎ ተግባራቸውን ማስወገድ የግድ ነበር። ምክንያቱም ሲባል ነው።

#የሉጥ_ጥሪ

★ ሉጥ (ዐ.ሰ) ሕዝቦቻቸው የሚሠሩትን አስፀያፊ ነገር ሲያዩ የወገኖቻቸው በዚህ ሁኔታ መገኘት አሳሰባቸው።

ሥነ-ምግባራቸው እንዲስተካከል በማሰብም ምክር መለገስ ጀመሩ። የሉጥ ጥሪ ሥነ-ምግባራቸው በጅጉ ለተበላሹና ቀልባቸው ለደረቀ ሰዎች የሚደረግ በመልካም ተግባር ማዘዝና ከመጥፎ መከልከል ነበር።

እነዚህ ሰዎች ምንም ሐያእ /ሐፍረት/ የሌላቸውና አስጸያፊ ወንጀልን በጠራራ ፀሐይ የሚፈፅሙ ነበሩ።

ከዚህም በላይ ሴት በማግባት አላህ የፈቀደላቸውን ግንኙነት መፈጸም ትተው ከወንዶች ጋር በመገናኘት ማንም አድርጎት የማያውቀውን አስጸያፊ ተግባር ይፈፅሙ ነበር።

ስለዚህም አላህ (ሱ.ወ) ሉጥ (ዐ.ሰ) ወደ እነዚህ ሕዝቦች ሄደው ከቆሻሻ ተግባራቸው እንዲፀዱ ጥሪ እንዲያደርጉላቸው ላካቸው።

ሉጥ (ዐ.ሰ) የነበዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) የወንድም ልጅ ሲሆኑ በኢራቅ ባቢል ነበር የተወለዱት።

ነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) ወደ ተውሂድ ጥሪ ሲያደርጉ አምነው ከሳቸው ጋር ወደ ሻም አካባቢ ስደት በመሄድ በምሥራቅ ዮርዳኖስ በሚገኘው ሱዲም ሸለቆ አካባቢ ሰፈሩ።በአካባቢው ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የምትፈጽስም ሰዱም የምትባል መንደር ነበረች።

አላህ (ሱ.ወ) ነቢዩላህ ሉጥን ወደ ሰዶምና አካባቢዋ ሕዝቦች፣ አላህን ብቻ እንዲያመልኩና ከመጥፎ ተግባራቸው እንዲርቁ ለማስተማር ና

ወንድ ለወንድ ግንኙነት መፈጸማቸውን ትተው አላህ የፈቀደላቸውን ሴቶቻቸውን በማግባት ግንኙነት እንዲፈፅሙ እንዲያዟቸው አላህ ሉጥን ላካቸው።ይህ ዓይነቱ ወንጀል ከሰዶም ሕዝቦች በፊት ማንም ያልሠራው አስጸያፊ ወንጀል ነበር

إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْلُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ ﴿١٦١﴾ إِنِّى لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌۭ ﴿١٦٢﴾ فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ﴿١٦٣﴾

“አትጠነቀቁምን? እኔ ለናንተ ታማኝ መልዕክተኛ ነኝ። አላህንም ፍሩ። ታዘዙኝም” (አሽ-ሹዐራእ፥ 161-163)

አሏቸው። እንዲሁም ሉጥ እያዘኑላቸው ለዘብ ባለ ቃል!

وَمَآ أَسْـَٔلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِىَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلْعَـٰلَمِينَ﴿١٦٤﴾

“በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም። ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ አይደለም።” (አሽ-ሹዐራእ፥ 164) በማለት አስገነዘቧቸው።
በዚህ ቃላቸው ውስጥ ሉጥ (ዐ.ሰ) ከነሱ ዓለማዊ ጥቅም እንደማይሹና ብቸኛው ፍላጐታቸው የነሱ መስተካከልና አላህን ብቻ ማምለካቸው እንደሆነ አስረዷቸው።

በመቀጠልም ሉጥ (ዐ.ሰ) ወደነዚህ ሰዎች አስፀያፊ ተግባር በመዞር የሚከተለውን ተናገሯቸው።

وَلُوطًا إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِۦٓ أَتَأْتُونَ ٱلْفَـٰحِشَةَوَأَنتُمْ تُبْصِرُونَ ﴿٥٤﴾ أَئِنَّكُمْ لَتَأْتُونَ ٱلرِّجَالَ شَهْوَةًۭ مِّن دُونِ ٱلنِّسَآءِ ۚ بَلْأَنتُمْ قَوْمٌۭ تَجْهَلُونَ ﴿٥٥﴾ ۞

“ሉጥንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስተውስ) እናንተ የሚታዩ ስትኾኑ ጸያፍን ነገር ትሠራላችሁን። እናንተ ከሴቶች ወንዶችን ለመከጀል ትመጣላችሁን በውነት እናንተ የምትሳሳቱ ሕዝቦች ናችሁ። (አን-ነምል፥ 54-55)

የሰዶም ሰዎች አስፀያፊ ተግባራቸውን በግልጽና በስብሰባ ቦታዎች ሁሉ ሳይቀር መፈጸማቸው ሉጥን በጣም አሳዘነ።
ሉጥ (ዐ.ሰ) ከዚህ አስፀያፊ ተግባር ቢከለክሏቸውም «አንተ ሴቶችን አስተናግድ ወንዶችን ተውልን።»በማለት አስፀያፊ መልስ ሰጧቸው።

ይህ ሁሉ ቢሆንም ነቢዩላህ ሉጥ (ዐ.ሰ) ተስፋ ባለመቁረጥ የተለያዩ ማስረጃዎችን በመጥቀስ ጥሪያቸ እውነት መሆኑን ሊያሳምኗቸው ሞከሩ።

ነገር ግን ድካማቸው በከንቱ ነበር። ቀናት ወራትን ወራት ዓመታትን እየተኩ ዘመኑ ሄደ። ሉጥም ዳዕዋቸውን ቀጠሉ። ነገር ግን ከቤተሰባቸው ውጭ አንድም ሰው አላመነላቸውም ነበር። ከቤተሰባቸውም ውስጥ ሚስታቸው አላመነችም ነበር።

ከከሓዲያን ጐን ተሰለፈች። ይህም ሁኔታ ሉጥ (ዐ.ሰ) ከቤታቸው ውጭ ከሓዲያንን፣ በቤት ውስጥ ደግሞ ከሓዲት ሚስታቸውን መታገል አስገደዷቸው።ስለሆነም በጣም ድካም ይሰማቸው ነበር። ቢሆኑም ግን ትዕግስት እያደረጉ ያለ መሰላቸት ወደ አላህ ጥሪ ማድረጋቸውን ቀጠሉ።

ሕዝባቸው ግን ማመናቸው ቀርቶ በዳዕዋቸው በማላገጥ “ከእውነተኞቹ እንደ ሆንክ የአላህን ቅጣት አምጣብን።
” (አል-ዐንከቡት፥ 29)

ሉጥ (ዐ.ሰ) ሕዝባቸው ቢቀልዱባቸውም ታግሰውና ችለው አሁንም ማስተማራቸውን ቀጠሉ። ከሓዲያኑ የሰዶም ሕዝቦች ሉጥ ላይ ማፌዛቸውንና ማስቸገራቸውን አጠናክረው ቀጠሉ።

ሉጥ (ዐ.ሰ) በአላህ (ሱ.ወ) እንደሚጠበቁ በመዘንጋት የሰዶም ሕዝቦች ሊያጠቋቸው ሞከሩ። ሉጥንና ቤተሰባቸውን በመናቅም።

وَمَا كَانَ جَوَابَ قَوْمِهِۦٓ إِلَّآ أَن قَالُوٓا۟ أَخْرِجُوهُممِّن قَرْيَتِكُمْ ۖ إِنَّهُمْ أُنَاسٌۭ يَتَطَهَّرُونَ ﴿٨٢﴾
“ሉጥንና ተከታዮቹን ከከተማችሁ አውጧቸው። አሉ። እነሱ፡ የሚጥራሩ ሰዎች ናቸውና።” (አል-አዕራፍ፥ 82)

አሉ።የሰዶም ሕዝቦች ቆሻሾች ስለነበሩ ነቢያቸው ሉጥ «ከመጥፎ ነገር ተመለሱ። በተመሳሳይ ፆታ መካከል ግብረ ሥጋ ግንኙነት አትፈጽሙ።»

ብለው ሲመክሯቸው በሉጥና ተከታዮቻቸው ንፁህነት በመቀለድ “እነሱ ንፁሃን ናቸው” ሲሉ አሾፉባቸው።

★ ሉጥ (ዐ.ሰ) ሕዝባቸው ቢቀልዱባቸውም ታግሰውና ችለው አሁንም ማስተማራቸውን ቀጠሉ።


ክፍል 2 ይቀጥላል....

#share
@alahu_akber1
ምናልባት የአንድ ቀን ስህተት
ትክክለኛውን መንገድ ያሳይሃል!

@alahu_akber1
#ኢስቲغፋር❔

ግርም ይለኛል የኛ ነገር ምላሳችን አስተጝፊሩላህ ይላል ልባችን፣ አካላችን ግን ወንጀሉ ላይ ነው ያለው! 

ኢስቲጝፋር ማለት፦ ባደረጉት ወንጀል መፀፀት፣ ሁለተኛ ወደዛ ወንጀል ላለመመለስ ቃል መግባትና ቀሪ ህይወትን ለማስተካከል መወሰን ማለት ነው!

እንደዚሁም የሆነ ወንጀል ትዝ ሲለን ብቻ መሆን የለበትም በተገቢው መልኩ ላልተወጣነው ግዴታችን፣ ለፈጠር ነው ጉድለትም ኢስቲግፋር ማደረግ አለብን።  

  ችግር ላይ ጭንቀት ላይ ካለን ተውበት እናድርግና ወደ አላህ እንመለስ። ማንኛውም ችግር የሚመጣብን በወንጀላችን እንደሆነ አላህ ነግሮናል á‹¨áŠ¸á‹­áˆŠáŠ• በር በወንጀላችን ዘግተን ለምን እያልን ማማረራችን በራስ ላይ ማሾፍ ነው።
ስለዚህ👉      فَفِرُّوا إِلَى اللَّهِ 
                       «ወደ አላህም ሽሚ

🫧 Share

   ወንጀል ልብን ይገላል!

@alahu_akber1
'
•••✿❒ ነብዩሏህ ሉጥ ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••

#ክፍል 2

ከሓዲያኑ የሰዶም ሕዝቦች ሉጥ ላይ ማፌዛቸውንና ማስቸገራቸውን አጠናክረው ቀጠሉ።

#ውዶቼ በባለፈው ትምህርታችን ላይ ታስታውሱ እንደሆነ መላእክት ነቢዩላህ ኢብራሂም ቤት ሄደው ዘይሯዋቸው ከዚያም መላእክት ራሳቸውን ለኢብራሂም አስተዋወቁ።

“እኛ አዋቂ ልጅ እንደምታገኝ ልናበስርህ ከጌታህ ዘንድ የተላክን መልዕከተኞች ነን።” አሏቸው። «አሁን ከአንተ ቤት ወጥተን ወደ ሉጥ ሕዝቦች በመሄድ ሉጥን እንረዳዋለን።
የሕዝቦቹ መጥፊያ በዚህች ሌሊት ነው። ቀጠሯቸው ጐህ ሲቀድ ነው። በማለት መላእክቱ የመጡበትን ዓለማ ለኢብራሂም (ዐ.ሰ) አስረዱ።
ኢብራሂም በሁኔታው ተደናግጠው ነገሩ እንዲዘገይ ለማድረግ ሞከሩ። መላእክቱ ግን የአላህ ትእዛዝ ስለሆነ ሳይዘገይ የሚፈጸም መሆኑን አስረዷቸው።
መላእክቱ ከነብዩ ኢብራሂም ቤት ወጥተው ወደ ሰዶም መንደር አመሩ። አስር ሶላት ወቅት ሲሆን ሰዶም መንደር ዳርቻ ደረሱ።
እዚያ ቦታ ላይ በደን ውስጥ የሚፈስ ወንዝ ነበር። ከወንዙ ዳርቻ አንዲት ልጅ ውሃ ለመቅዳት ቆማ አገኟት። ይህች ልጅ የሉጥ (ዐ.ሰ) ልጅ ነበረች።

4ቱን ወጣቶች ስታይ ለየት ያለ ውበት ስለነበራቸው ተደናገጠች። ከ4ተኛው አንደኛው የሉጥ ቤት የት እንደሆነና እንግዳም ይቀበሉ እንደሆነ ጠየቃት።
ልጅቷም የሰዶም ሰዎችን አስፀያፊ ተግባር ስለምታውቅ «ለአባቴ ነግሬ መልሱን እስከምነግራችሁ ድረስ እዚሁ ቆዩ። ወደ ሰዶም እንዳትገቡ» ብላ አስጠነቅቃቸው የውሃ እቃዋን ወንዙ ዳር ተወችና ፈጥና ወደ አባቷ ሉጥ (ዐ.ሰ) ዘንድ በመሄድ ሦስት ወጣቶች እሳቸውን ፈልገው እንደመጡ ነገረቻቸው።

ሉጥ ይህን መልዕክት ሲሰሙ ተደሰቱ ወይስ አዘኑ? ስለሁኔታው አላህ (ሱ.ወ) በሁድ ምዕራፍ ውስጥ እንዲህ ይላል፦

وَلَمَّا جَآءَتْ رُسُلُنَا لُوطًۭا سِىٓءَ بِهِمْوَضَاقَبِهِمْ ذَرْعًۭا وَقَالَ هَـٰذَا يَوْمٌ عَصِيبٌۭ ﴿٧٧﴾
“መልዕክተኞቻችን ሉጥን በመጡት ጊዜ በነሱ (ምክንያት) አዘነ። ልቡም በነሱ ተጨነቀ። ይህ ብርቱ ቀን ነውም አለ።“ (ሁድ፥ 77)

ሉጥ (ዐ.ሰ) «ዛሬ አስቸጋሪ ቀን ነው። አሉና ፈጥነው ወደ እንግዶቹ ሄዱ። እንግዶቹን ሲያዩ ለሰዶም ሰዎች መጥፎ ተግባር እንዳይጋለጡ በመፍራት ይበልጥ አዘኑ።

ሉጥ እንግዶቹን ከየት እንደመጡ ጠየቋቸው። መልስ ሰጧቸው። ወደ የት እንደሚሄዱ ሲጠይቋቸው ግን መልስ አልሰጧቸውም ነበር። ይልቁንም በእንግድነት እንዲቀበሏቸው ጠየቋቸው። ሉጥ (ዐ.ሰ) እንግዶቹን ለማስተናገድ ስስት አልነበረባቸውም።

ነገር ግን መላእክት መሆናቸውን ስላላወቁ የመንደሩ ሰዎች አስፀያፊ ተግባራቸውን እንዳይፈጽሙባቸው ፈርተው ነበር ያዘኑት።
ከዚያም ፊት ለፊት እየመሩ እንግዶቻቸውን አስከትለው ወደ ሰዶም መንደር ገቡ።
በመንገድ ላይ እያሉ ሉጥ (ዐ.ሰ) ቆም አሉና «ከዚህ አገር ሰዎች አስጠንቅቃችኋለሁ። በመሬት ላይ እንደነዚህ ሰዎች ቆሻሻ ሰው የለም» አሏቸው። መላእክቱ ሉጥ በሰጧቸው ማስጠንቀቂያ ላይ ምንም አስተያየት ሳይሰጡ ዝም ብለው መንገዳቸውን ቀጠሉ።

ሉጥ (ዐ.ሰ) ለእንግዶቹ ይህን ያሏቸው ከሰዶማዊያን ዓይን እንዲርቁ ፈልገው ነበር። እንግዶቹ ግን ምንም ሳይናገሩ ፀጥ ብለው ቆዩ።
በዚህን ጊዜ ሉጥ (ዐ.ሰ) ወደ ሰዶም መንደር በሌሊት ተደብቀው እንዲገቡ ጠየቋቸው።

እንግዶቹ ይህን ተቀብለው ማንም ሳያያቸው ከሉጥ ጋር በመሆን በሌሊት ወደ ከተማዋ ገቡ።

ሉጥ (ዐ.ሰ) እንግዶቹ ሌሊት ገብተው ጠዋት ጐህ ሲቀድ ማንም ሳያያቸው ይወጣሉ በሚል አስበው ነበር።
ሉጥ (ዐ.ሰ) አሁን ካሁን መጥፎዎቹ ሰዎች እነዚህን እንግዶች እንዳያይዋቸው እየተጨነቁ ከ4ቱ እንግዶቻቸው ጋር

እንደምንም ወደ ቤታቸው ገቡ።ከመንደሩ ሰዎች ማንም አላያቸውም ነበር።
ነገር ግን በቤት ውስጥ የነበረችው ከሓዲዋ ሚስታቸው እንግዶቹን እንዳየች ተደብቃና ድምጽዋን አጥፍታ ከቤት ወጣች።

★ የሉጥ (ዐ.ሰ) ሚስት በፍጥነት ወደ ሰዶማዊያኑ በመሄድ በሉጥ ቤት ከሰዶም ያልሆኑ እንግዶች እንዳሉ ነገረቻቸው።

ብልሹዎቹ ሰዎች ይህን ሲሰሙ ተደስተው እየተጠራሩ ወጡ። ከዚያም በአንድ ላይ ተሰብስበው ወደ ሉጥ ቤት አመሩ።
ሉጥ (ዐ.ሰ) ማን እንደነገራቸው ሲያስቡ፡ ሚስታቸው ቤት ውስጥ አለመኖሯን አወቁ። ሐዘናቸው በጣም ጠና።
ከየአቅጣጫው የተሰበሰቡት ሰዶማዊያን የሉጥን ቤት ከበቡ። ቀጥሎም በሩን መቆርቆር ጀመሩ። ሉጥ (ዐ.ሰ) ምን እንደምፈልጉ ጠየቋቸው።
በፊታቸው ላይ መጥፎ ነገር ይነበብ ነበር። ሉጥ (ዐ.ሰ) ተንኮለኞችን ለመመለስ ቢሞክሩም አልቻሉም። ከዚያም፦

وَجَآءَهُۥ قَوْمُهُۥ يُهْرَعُونَ إِلَيْهِ وَمِن قَبْلُ كَانُوا۟يَعْمَلُونَ ٱلسَّيِّـَٔاتِ ۚ قَالَ يَـٰقَوْمِ هَـٰٓؤُلَآءِ بَنَاتِى هُنَّ أَطْهَرُ لَكُمْ ۖ فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَلَا تُخْزُونِ فِى ضَيْفِىٓ ۖأَلَيْسَ مِنكُمْ رَجُلٌۭ رَّشِيدٌۭ ﴿٧٨﴾
“ሕዝቦቼ ሆይ! እኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው። እነሱ ለእናንተ ይልቅ በጣም የጸዱ ናቸው። (አግቧቸው)።

አላህንም ፍሩ። በእንግዶቼም አታሳፍሩኝ። ከናንተ ውስጥ ቅን ሰው የለምን?” (ሁድ፥ 78)በማለት አናገሯቸው።
ሉጥ (ዐ.ሰ) ሰዎቹ ሐራምን ትተው ወደ ሐላል እንዲዞሩ መንገድ ቢያሳዩዋቸውም አሻፈረኝ በማለት መጥፎ የመሥራት ፍላጎታቸውን ለማሳካት መሞከራቸውን ቀጠሉ።
በዚህን ጊዜ ሉጥ (ዐ.ሰ) በራቸውን ዘጉ። ሰዎቹም በሩን በኃይል ነቀነቁት። ሉጥ (ዐ.ሰ) በሁኔታው ተስፋ ቆረጡ።

قَالَ لَوْ أَنَّ لِى بِكُمْ قُوَّةً أَوْ ءَاوِىٓ إِلَىٰ رُكْنٍۢ شَدِيدٍۢ ﴿٨٠﴾
“ በናንተ ላይ ለኔ ኃይል በኖረኝ ወይም ወደ ብርቱ ወገን ቢጠጋ ኖሮ (የሚሠራውን በሠራሁ ነበር)።” (ሁድ፥ 80)

አሏቸው። ሉጥ (ዐ.ሰ) የተንኮለኞቹን ክፋት ለመከላከል በቂ ኃይል በነበረኝ ብለው ተመኙ ።
በዚህን ጊዜ መልአኩ ጅብሪል ቆመና፦ይህን የሉጥን ሁኔታ እና እንግልት የተመለከቱት በወጣቶች የተመሰሉት መላዕክት ሉጥን ጠሩት'ና ሁሉንም ነገር ግልፅ አደረጉለት። መላዕክት መሆናቸውንም አክለው ነገሩት።
1፦ጂብሪል
2፦ሚካኢል
3፦ኢስራፊል
4መለከል ሞት....ነበሩ።
በመጨረሻም ይህችን ከተማ ሊያጠፏት እንደሆነ እና ሉጥ ቤተሰቦቹን እና ተከታዮቹን ሁሉ ሰብስቦ ሱብሂ ሰዐት ከተማይቱን ለቅቆ እንዲወጣ አዘዙት።በዚህ ሁኔታ ሉጥ እንግዶቹን እያወራ ሳለ ህዝቡ በሩን ሊገነጥል ተቃረበ ያን ግዜ ጂብሪልም አላህን አስፈቀደ'ና አንድ ግዜ በሩን ከፍቶ በመውጣት በክንፉ ፊት ፊታቸውን ክፉኛ መታቸው አይኖቻቸውም እዛው መፍሰስ ጀመሩ።

ጠዋት ሲነጋ ሉጥን እንደሚገድሉት እየዛቱ ሁሉም ከበሩ እየተተራመሱ ሄዱ።ከዚያም ሉጥ መላዕክቱን፦መቼ ነው እነዚህን ህዝቦች ምታጠፉት አላቸው።
እነሱም፦"ሱብሂ ላይ ነው" አሉት።

ሉጥም፦"አሁኑኑ ብታጠፏቸውስ" ሲላቸው...

መላዕክቱም፦"እንዴ ሱብሂ ቅርብ አይደል ወይ!!!" አሉት።

በነጋታው ሉጥ ተከታዮቹን፣ቤተሰቦቹን እና አመፀኛዋን ሚስቱን ይዞ ከመቅሰፍቱ ሽሽት ከከተማይቱ መውጣት ጀመረ። ሲወጣም ለተከታዮቹ በከተማይቱ የሚወርደውን መቅሰፍት ማንም ዞሮ ማየት እንደሌለበት አስጠንቅቆ ተናገረ።

አሁም ጉዞ ጀምረዋል...መላዕክቱ እዛው ከተማ ውስጥ ናቸው...ሉጥ እና ተከታዮቹ ከተማይቱን ልክ ለቀው እንደወጡ ከወደ ከተማይቱ በኩል ከፍተኛ ድምፅ ሰሙ።
ማንም ወደ ከተማዋ እንዳይዞር ማስጠንቀቂያ ስለተሰጠ ማንም አልዞረም ነበር።የሉጥ ሚስት ግን ወደኋላ በመዞር፦"ወይኔ ወገኔ,,,,!!!" በማለት ጮኸች።
ትልቅ የድንጋይ ፍንጣሪ መጣና እራሷን ለሁለት ከፈለላትና የመቅሰፍቱ ሰለባ ሆነች።

አላህም ይህን ዘግናኝ ክስተት ሲተርክ እንዲህ ይላል፦
"ትዕዛዛችንም በመጣ ግዜ (የከተማይቱን) ላይዋን ከታች አደረግን(ገለባበጥናት) ተከታታይም የሆነ የሸክላ ድንጋይ በርሷ ላይ አዘነብን" (ሱረቱል ሁድ)

እንዴት አድርጎ እንደገለባበጣቻው ታውቃላችሁ...!!!
መጀመሪያ ጂብሪል ክንፉን በከተማይቱ መሬት ውስጥ ዘቅዝቆ አስገባው።
ከዚያም ከተማይቱን ከነ ህንፃዎቿ ነቅሎ ወደ ሰማይ ከፍ ካደረገ በኋላ ገለበጠው'ና መልሶ ወደ ምድር ተከለው።

ሉጥ ከነ ተከታዮቹ ብዙ ርቀት ከተጓዘ በኋላ ሱዒር የተባለ አከባቢ በመስፈር ይህ ነው ተብሎ በታሪክ መዛግብት እድሜው ባይሰፍርም እዛው ሱዒር ላይ ህይወቱ አልፏል። (ዐለይሂ ሰላቱ ወሰላም)

•••✿ ❒ ተ_ፈ_ፀ_መ ❒✿•••

በቀጣይ #ነብዩሏህ ሷሊህ(ዐ.ሰ) ታሪክ እንጀምራለን 🥰
#share
@alahu_akber1
'
ውበትሽ ቤቴ ሊያስገባሽ ይችላል...
ነገር ግን ፀባይሽ አባትሽ ጋር ሊመልስሽ ይችላል እና ተጠንቀቂ 😁

@alahu_akber1
'
•••✿ ❒ ነብዩሏህ_ሷሊህ_ዐለይሂ_ሰላም_ታሪክ ❒✿•••



የሰሙድ ህዝቦች ከሁድ ህዝቦች በኋላ የመጡ ሲሆኑ በጣም ትዕቢተኛ እና ኩራተኛ ናቸው።
በሳውዲ ዐረቢያ ምድር በሂጃዝ እና በተቡክ መሀከል የሚገኝውን ግዙፍ ተራራ በመፈልፈል ከዘመኑ ጋር የማይመጣጠን ውብ ውብ... ህንፃዎችን ሰርተው ነበር የሚኖሩት።በጣም ትላልቅ ናቸው አሁን ያለው ትውልድ በጉልበትም ሆነ በግዝፈት ከነሱ አይስተካከልም።
ምንም እንኳን ድንጋያማ አካባቢ የሚኖሩ ህዝቦች ቢሆኑም አላህ ምድራቸውን ለቡቃያ ምቹ አድርጓት የምንጮቹንም ብዛት ለጉድ አድርጎታል።
ግዜው ከአባቶቻቸው የወረሱርትን የጣኦት አምልኮ አጧጡፈው የያዙበት ዘመን ነበር።

በዱንያ ሰክረው...አላህን ረስተው...በወንጀል ተጨማልቀው ሳለ አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ ሳሊህ ኢብን ዑበይድ ኢብን ሂሻም ኢብን.....ዓድ ኢብን ኣርም ኢብን ሳም ኢብን ኑህ (ዐ ሰ) የተባለን መልካም ነቢይ ከመሀከላቸው ላከላቸው።
ሳሊህ ዐ ሰ በነቢይነት ከመመረጣቸው በፊት ህዝቡ ዘንድ በምልካም ስነ ምግባራቸው የሚታወቁ፣ከከበርቴ ቤተሰብ የተወለዱ፣ከዚያም አልፎ ሰዎች ለፍርድ ሚያስቸግር ክርክር ሲገጥማቸው እሳቸው ጋር የሚሄዱ ምርጥ የአላህ ባርያ ናቸው።

ወደፊት ሀገሪቷን በንግስና ያስተዳድሯታል ተብሎም ይገመት ነበር።
በንዲህ አይነት ሁኔታ ላይ ሳለ ሳሊህ ዐ ሰ የጌታቸውን ተልዕኮ እንደተቀበሉ በትኩስነቱ፦" ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለእናንተ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ ከዓድም በኋላ ምትኮች ባደረጋችሁና በምድሪቱም ላይ ባስቀመጣችሁ ጊዜ አስታውሱ፡፡ ከሜዳዎቿ (ሸክላ) ሕንጻዎችን ትገነባላችሁ፡፡ ከተራራዎችም ቤቶችን ትጠርባላችሁ፡፡ ስለዚህ የአላህን ጸጋዎች አስታውሱ፡፡ በምድርም ውስጥ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ" በማለት ጥሪውን አስተጋባ።
ይህን በሰሙ ግዜ ትዕቢታቸው አናታቸው ላይ ወጣ...ኩራታቸው ገነፈለ...የከተማይቱ መሳፍንትም፦"አንተ ሳሊህ! ቆይ አንተ ከኛ በምን ተሽለህ ነው አላህ መልዕክተኛ አድርጎ ሊመርጥህ የቻለው? ይልቁኑ አማልክቶቻችን በመጥፎ አይን ሳያዩህ አልቀሩም'ና አብደሀል" አሉት።

ከዚያም እንደተለመደው ሳሊህ(ዐ ሰ) የድሆች እና ምስኪኖች ተከታይ ይበራከቱለት ጀመር።ይሁን እንጂ በለፀጋዎች እና ጉልበተኞቹ ዝም ማለትን አልመረጡም'ና ምእመናኑ ዘንድ በመሄድ፦"እናንተ ባመናችሁት ነገር እኛ ክደናል" በማለት ይሳለቁባቸው ነበር።

ከዛላችሁ እነዚህ አመፀኛ ህዝቦች አንደ ቀን የሳሊህን ዐ ሰ ጥሪ ለማስቆም እና ተከታዮቹን ከሱ ለማራቅ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሊመካከሩ አንድ ቦታ ተሰበሰቡ።ብዙ ከመከሩ በኋላ በመጨረሻም ሳሊህን (ዐ ሰ) ያለ ተከታይ ብቻውን ለማስቀረት አንድ መፍትሄ አገኙ።
እሱም፦"ሳሊህን የሚከተል ከአማልክቱ በኩል የማይድንን በሽታ ይይዘዋል።ከሳሊህም የሚርቅ ከነዚህ ነገሮች የተጠበቀ ይሆናል" በማለት ከተማይቷን ቀወጧት።

ነገር ግን ትክክለኛይቱ የዳዕዋ ጥሪ መንገዷን ይዛ ቀጥላለች።በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ አንድ ቀን ሳሊህ ዐ ሰ ጥሪያቸውን በህዝብ ፊት ሲያደርሱ ህዝቡም፦"አንተ ሳሊህ እውን አንተ ነቢይ ከሆንክ ማረጋገጫ ይሆነን ዘንድ እስቲ ተዐምር አምጣልን" አሉት።

የከተማይቱ ሹማምንት እና የተከበሩ ሰዎች በቦታው ነበሩ።የማይችለውን ነገር በመጠየቅ እንዳደናገሩት በማሰብ የማላገጥን ሳቅ ይስቁበትም ጀመር።(ወላሂ ነቢያቶች አላህ ምንዳቸውን ከፍ ያድርግላቸው።በገዛ ሀገራቸው ይሳቀቃሉ)

ከመሳፍንቱ መሀክል አንዱ ቆመ'ና፦"አንተ ሳሊህ ተዐምር ማሳየት እችላለሁ የምትል ከሆነ የተዐምሩን አይነት እኛ ነን ምንመርጠው ያንተ ስራ እኛ የመረጥነውን ተዐምር መተግበር ብቻ ነው" አሉት

እኛ እያየን ከዚህ ተራራ ውስጥ በግዝፈቷ አቻ የሌላት የአስር ወር እርጉዝ የሆነች፣መልኳም ቀይ የሆነ፣ከግዝፈቷ የተነሳ የከተማይቱ ይዝብ እና እንስሳት የሚጠጡትን ውሀ በአንዴው መጠጣት የምትችል ትልቅ ግመል አውጣልን"አሉት።

ነቢዩላህ ሳሊህም (ዐ ሰ) ህዝቡ ሁሉ ተዐምሩን አይተው በማመን ከጀሀነም ይድኑ ዘንድ የከተማይቱ ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ አዘዙ'ና ሁሉም ተሰበሰቡ።

ከዚያም ሳሊህ (ዐ ሰ) ለጌታቸው ሱጁድ በመውረድ ጌታቸውን ይማፀኑ ጀመር።አላህም የሱን መልዕክተኞች በህዝባቸው ፊት አያሳፍራቸውም'ና ተራራው በጣም መንቀጥቀጥ ጀመረ።

ህዝቡ ሁሉ አይኑን ተራራው ላይ ተክሏል።ካሁን አሁን ምን ሊከሰት ነው በማለት እርስ በርስ ይተያያሉ።

በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ተራራው ከፍተኛ ጩኸት ካስተጋባ በኋላ በጣም በመሰንጠቅ ከመሀከሉ ህዝቡ በጠየቀው መልኩ ትልቅ እና እርጉዝ ቀይ ግመል ወጣች።

ይህን ባዩ ግዜ አይኖቻቸው ፈጠጠ፣ አንደበታቸው ደረቀ፣ምላሶቻቸው ተሳሰሩ።ሳሊህም ዐ ሰ፦"ህዝቦቼ ሆይ! ይህች ግመል የአላህ ተዐምር ናት።

ታይዋታላችሁ፤ ትዳስሷታላችሁም እናንተ ዘንድም ትኖራለች።

ባስቀመጣችሁት መስፈርት መሰረት ትልቅ እና እርጉዝ ሴት ግመል እንደመሆኗ መጠን ካሁን በኋላ ውሀችሁንም ለጋራ ነው ምትጠጡት።
አንድ ቀን ግመሊቱ ስትጠጣ ቀጣይ ቀን እናንተ ትጠጣላችሁ። ምክንያቱም መጀመርያ ያስቀመጣችሁት መስፈርት ይህ ነው'ና።

ነገር ግን ይህችን ግመል አንዳችሁ በመጥፎ ከተተናኮላችኋት የአላህ ፈጣኑ ቅጣት ይወርድባችኋል" በማለት አስረዳቸው።
ከዚያም ህዝቡ ለሳሊህ ዐ ሰ ያለው አመለካከት 100% ተቀየረ።ሁሉም ከማንም በላይ ሳሊህን ያከብር ጀመረ።ብዙ ሺህ ሰውም የሳሊህ ተከታይ ሆነ።
ይህ ያሳሰባቸው የከተማይቱ ሹማምንት አንድ ቀን ተሰብስበው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሲወያዩ ውለው በመጨረሻም ግመሊቱን በመግደል ተስማሙ።
ይህ የተወሰነውም በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ ሆነው ነበር።አጋጣሚ እዛው መጠጥ ቤት ሳሉ የመጠጥ ጥማቸው ሳይቋረጥም ከመጠጡ ቤት ጓዳ "መጠጥ አልቋል" የሚል መርዶ ደረሳቸው።
ሹመንቱም፦"ለምንድነው በርከት አድርጋችሁ ማትሰሩት" ብለው ሲጮሁባቸው
የመጠጥ ቤቱ ባለቤት፦
"ዛሬ ውሀ የግመሊቱ ተራ ስለሆነ ውሀ የለም'ና ብዙ መስራት አልቻንም" ብላ መለሰችላቸው።

ከመሀከላቸውም አንድ ቀዳር ኢብን ሳሊፍ ኢብን ጁንደዕ የተባለ አመፀኛ ከመሰል ጓደኛው ጋር ተነሳ'ና ግመሏን ሊገድል ጉዞ ጀመረ።
በጉዞ ላይ ሳሉም ሌላ ሰባት ሰዎችን መንገድ ላይ በመቀላቀል ዘጠኝ ሁነው ግመሏ ውሀ የምትጠጣበት ስፍራ ደረሱ።

ውሀው ዘንድም ደረሱ'ና በያዙት ሰይፍ ገደሏት።ከአጠገቧ ግልገሏ ነበር'ና ግልገሏንም አሳድደው በትልቅ ተራራ ላይ ይዘውት ገደሉት።ከሙጅሪምነታቸው የተነሳ የግመሊቱን ስጋ ቀኑኑ ተከፋፈሉት።

ሳሊህም ዐ ሰ ይህን በተመለከተ ግዜ፦"አሁን የጌታችሁን ቅጣት ተጠባበቁ።
የጌታችሁ ቅጣት ከመውረዱም በፊት ስጋውን ተሎ ተሎ በልታችሁ ጨርሱ" አላቸው።

ህዝቡም፦"አንተ ምን ዝም ብለህ ቅጣት ቅጣት እያልክ ትዝትብናለህ! እስቲ አምጣ ቅጣት ምትለውን" ሲሉት
ሳሊህም፦"በዚህ 3 ቀን ውስጥ የጌታችሁ ቅጣት እናንተ ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።ለዚህም ማረጋገጫ ዛሬ ፊታችሁ ብጫ ይሆናል።
ነገ ደሞ ቀይ ይሆናል።ከነገ ወዲያ ደግሞ ጥቁር ይሆንና ትጠፋላችሁ ይህም ሀሰት የሌለው ዛቻ ነው" አላቸው።
እነዚህ የሀፅያትን ፅዋ ጠጥተው የማይጠግቡ ህዝቦችም ሳሊህን ዐ ሰ ለመግደል ወስነው ዝግጅታቸውን አጠናቀው ሳለ፣

በመጀመርያ ግመሏን በገደሉት ዘጠኙ ሰዎች ላይ እቤት ተደረመሰባቸው፣
አሁን የአመፀኞቹ ህዝቦች ፊታቸው መቀያየር ጀምሯል።ሀሉም የፊቱ ብጫ መሆን አስፈርቶት እርስ በርስ ይተያያል።