"Economy of words || የቃላት ኢኮኖሚ"
========
የኢትዮጵያ ፊደል እጅግ የተራቀቀ የአጻጻፍ ስልት ነው። አንድ ፊደል የሚገልጻቸውና የሚያወጣቸው ድምፆች ከሌሎቹ የተሻሉ ናቸው። በአንዳንድ ሰዎች "የግዕዝ ፊደል" በሌላ ጊዜ ደግሞ "የአማርኛ ፊደል" እየተባለ ታላቅነቱን ለመጨቆን ፈተና የገጠመው ፊደላችን "የኢትዮጵያ ፊደል"፤ ለሁሉም ቋንቋ ሊሆን የሚችል ታላቅ ችሎታ ያለው ነው። ይህ ፊደላችን ካለው ችሎታ አንዱ ፊደል ቆጣቢነቱ መሆኑን በዚህ ፎቶ ላይ በግልጽ ይታያል።
አቡነ ጴጥሮስ የሚለው የመጽሐፉ ርዕስ የፊደል ብዛት፦
** በኢትዮጵያ ፊደል= 7
** በቁቤ ፊደል= 14
** ሁለቱም መጽሐፍ ያላችሁ ሰዎች ደግሞ የመጻሕፍቱን ገጾች ብዛት ልትነግሩን ትችላላችሁ። (የፎንቱ ትልቅነት፣ በመስመር መካከል ያለው ርቀት እኩል ከሆነ) .....
========
የኢትዮጵያ ፊደል እጅግ የተራቀቀ የአጻጻፍ ስልት ነው። አንድ ፊደል የሚገልጻቸውና የሚያወጣቸው ድምፆች ከሌሎቹ የተሻሉ ናቸው። በአንዳንድ ሰዎች "የግዕዝ ፊደል" በሌላ ጊዜ ደግሞ "የአማርኛ ፊደል" እየተባለ ታላቅነቱን ለመጨቆን ፈተና የገጠመው ፊደላችን "የኢትዮጵያ ፊደል"፤ ለሁሉም ቋንቋ ሊሆን የሚችል ታላቅ ችሎታ ያለው ነው። ይህ ፊደላችን ካለው ችሎታ አንዱ ፊደል ቆጣቢነቱ መሆኑን በዚህ ፎቶ ላይ በግልጽ ይታያል።
አቡነ ጴጥሮስ የሚለው የመጽሐፉ ርዕስ የፊደል ብዛት፦
** በኢትዮጵያ ፊደል= 7
** በቁቤ ፊደል= 14
** ሁለቱም መጽሐፍ ያላችሁ ሰዎች ደግሞ የመጻሕፍቱን ገጾች ብዛት ልትነግሩን ትችላላችሁ። (የፎንቱ ትልቅነት፣ በመስመር መካከል ያለው ርቀት እኩል ከሆነ) .....
❤16
ሀገራዊ ምርጫው፦ አስፈላጊ የሆነ አላስፈላጊ ጨዋታ (Game)
==========
የዛሬ ሳምንታዊ የውይይት ጠረጴዛችን በዚህ ዓመት ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀውና በዜጎች መካከል መነጋገሪያ በሆነው ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሚያተኩር ይሆናል። ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ Abel Gashe እና Teklemichael Ab Sahlemariam እንወያያለን።
++++++
ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ፡-
** 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመዘገቡ ሲሆን 10 ሺህ 934 እጩዎችን አቅርበዋል፡፡
** 2 ሺህ 98 ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤
** 8 ሺህ 736 ደግሞ ለክልል ምክር ቤት ተወካዮች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡
https://www.youtube.com/live/gTnyj0xUGPU?si=uZ3ucvd-FhsJTY_h
==========
የዛሬ ሳምንታዊ የውይይት ጠረጴዛችን በዚህ ዓመት ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀውና በዜጎች መካከል መነጋገሪያ በሆነው ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሚያተኩር ይሆናል። ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ Abel Gashe እና Teklemichael Ab Sahlemariam እንወያያለን።
++++++
ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ፡-
** 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመዘገቡ ሲሆን 10 ሺህ 934 እጩዎችን አቅርበዋል፡፡
** 2 ሺህ 98 ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤
** 8 ሺህ 736 ደግሞ ለክልል ምክር ቤት ተወካዮች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡
https://www.youtube.com/live/gTnyj0xUGPU?si=uZ3ucvd-FhsJTY_h
YouTube
ሀገራዊ ምርጫው፦ አስፈላጊ የሆነ አላስፈላጊ ጨዋታ (Game)
ሀገራዊ ምርጫው፦ አስፈላጊ የሆነ አላስፈላጊ ጨዋታ (Game)
==========
ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ፡-
** 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመዘገቡ ሲሆን 10 ሺህ 934 እጩዎችን አቅርበዋል፡፡
** 2 ሺህ 98 ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤
** 8 ሺህ 736 ደግሞ ለክልል ምክር ቤት ተወካዮች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡
==========
ለዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ፡-
** 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመዘገቡ ሲሆን 10 ሺህ 934 እጩዎችን አቅርበዋል፡፡
** 2 ሺህ 98 ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤
** 8 ሺህ 736 ደግሞ ለክልል ምክር ቤት ተወካዮች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡
👍4❤1🤔1
ኩሽ የሚባለው ነገር የሀገራችን የፖለቲካ ዋነኛ ቃል ከሆነ ሰንብቷል። ኢትዮጵያ ውስጥ ለኩሽነት ጥብቅና የቆሙ የሚመስሉ፣ የኩሽን ትንሣኤ ለመፍጠር የሚሞከሩ፣ የኩሾችን ጥምረት እንፈጥራለን የሚሉትንም ሰምተናል። ለዚህ ጉዳይ የብርሃን ብልጭታ የሚፈጥቅ መጽሐፍ ከደረሱ የሥነ ልሳን ምሁር የተደረገውን ቃለ ምልልስ መመልከት አስተማሪ ነው::
👍13
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት ።
የቅዱስነታቸው አባታዊ መልዕክት እንደሚከተለው ይነበባል።
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ኣቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት፤
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን፡-
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፣
በቤዛዊ መሥዋዕትነቱ ከሞተ ኃጢኣት ታድጎ የትንሣኤ ሙታንን በር የከፈተልን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
‹‹ወኣነ እሜጡ ነፍስየ ቤዛ ኣባግዕየ ከመ ካዕበ ኣንሥኣ፤
ዳግመኛ ኣነሣት ዘንድ ነፍሴን የበጎቼ ቤዛ ኣድርጌ እሰጣለሁ (ዮሓ 10÷17)
ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰብኣዊ ክዋኔው ሰው ቢሆንም በመለኮታዊ ክዋኔው የኣብና የመንፈስ ቅዱስ ቃል ወይም ወልደ እግዚአብሔር ነው፤
በመሆኑም በሰብኣዊ ክዋኔው መዋች ሲሆን በመለኮታዊ ክዋኔው ተነሽና ኣንሺ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር ሥግው ቃል ሁለቱንም ተግባራት በኣንድ ኣካልና ክዋኔ የመፈጸም ሥልጣን ኣለው፤ ይህም በመሆኑ ራሴን የማኖርና የማንሣት ሥልጣን ኣለኝ በማለት እውነታውንና ምንነቱን ኣሳየ፤
ጌታችን ይህንን ኣስመልክቶ ከመሞቱና ከመነሣቱ በፊት ለቅዱሳን ሓዋርያት በተደጋጋሚ ኣስረድቶኣል፤ ስለሆነም የጌታችን ሞትና ትንሣኤ ድንገተኛና የግድ ሳይሆን ታውቆ ያደረና የውድ እንደሆነ ከዚህ እውነታ እንረዳለን፤
ጌታችን ይህንን ተግባር በውድ ፈቃዱ የፈጸመው በእግዚአብሔር ኣሰራር ከዚህ ውጭ የዓለም ድኅነት የሚከናወንበት ዕድል ስለሌለ ነው፤ በእግዚአብሔር ኣሰራር ኃጢኣትና በደል የሚሰረዘው በቤዛዊ መሥዋዕት ብቻ እንደሆነ ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ በነበረው የቤዛዊ መሥዋዕት ኣቀራረብ የታወቀ ነው፤
በመሆኑም የሰውን ምልኣተ ኃጢኣት ሙሉ በሙሉ ሰርዞ ሰውን ከሞት ቅጣት ነጻ ለማውጣት ብቃት ያለው ቤዛዊ መሥዋዕት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ነበረበት፤ ይሁን እንጂ ለዚህ ዓይነቱ ቤዛዊ መሥዋዕት ብቁ የሆነ ከፍጡራን ወገን ስላልተገኘ ‹‹ለሊሁ መሥዋዕት፣ ወለሊሁ ሠዋዒ፣ ወለሊሁ ተወካፌ መሥዋዕት ማለትም›› ራሱ መሥዋዕት፣ ራሱ መሥዋዕት ኣቅራቢ ሊቀ ካህናት፣ ራሱ ተወካፌ መሥዋዕት ኣምላክ ሆኖ የቤዛነታችንን መሥዋዕት ራሱ በራሱ ለራሱ ኣቀረበ››፤
በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕትም እኛን ከሞት ቅጣት ነጻ ኣደረገን፤ትንሣኤያችንንም በትንሣኤው ኣበሰረ፤ በክርስትና ሃይማኖት የሚገኝ ፍጹም ድኅነትና ነጻነት በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕት ላይ የተመሠረተ ነው፤
የተወዳደችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን
ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ሲያበስረን የትንሣኤ ሰዎች ሆነን በመንፈስና በሞራል በማደግ ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ እንደገና የጨለማው ኃይል መሳሪያዎች ልንሆን ኣይደለም፤ የሞቱና የትንሣኤው ምስጢር በንጹሁ ኅሊናችን ካስተዋልነው ውስጣችን እሱን ለመቀበል የሚያዳግተው ኣይደለም፤
ከዚህ ኣንጻር በትንሣኤው ኣምነን ትንሣኤያችንን እየተጠባበቅን የምንገኝ ሕዝበ ክርስቲያን በቅን ኣስተሳሰብ፣በርቱዕ ኣእምሮና በኃይለ ሃይማኖት እየታገዝን ጨለማውን ዓለም ወደብርሃን ለመለወጥ መጣርና መትጋት ይጠበቅብናል፤
የጨለማው ዓለም መንፈስ ሊያጠፋን ካልሆነ በቀር እንደማይጠቅመን በተጨባጭ የምናውቀው ነው፤ወደድንም ጠላንም ያለን ብቸኛ ኣማራጭ ብርሃንን መከተል ነው፤ እሱም እግዚአብሔር ነው፤በብርሃን የሚመላለስ እንደማይጐዳ በእግዚአብሔር የሚኖርም ተጐድቶ ኣያውቅምና ነው፤
ዓለም እንደ ኣጠቃላይ በጨለማ ተውጦ ሲተረማመስ የሚታየው ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ምርጫው ስላደረገ ነው፤ ስለሆነም የኛ ምርጫ ብርሃን የሆነውን እግዚአብሔር እንዲሆን የቤተ ክርስቲያን የዘወትር ጥሪ ነው፤
በመጨረሻም፡-
የትንሣኤ በዓላችንን ስናከብር ዓለም በክፋቱ ያጨለመባቸውን ወገኖች ጦማችው እንዳይውሉ ካለን ከፍለን የተራቡትን በማብላት፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስና የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ በማድረግ ቀኑ ለሁላችንም ፍጹም ብርሃን ሆኖ ይውል ዘንድ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ ጥሪያችንን በእግዚአብሑር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን!!
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ”
“ወስብሐት ለእግዚአብሔር”
ኣሜን!!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የቅዱስነታቸው አባታዊ መልዕክት እንደሚከተለው ይነበባል።
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ኣቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት፤
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን፡-
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፣
በቤዛዊ መሥዋዕትነቱ ከሞተ ኃጢኣት ታድጎ የትንሣኤ ሙታንን በር የከፈተልን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
‹‹ወኣነ እሜጡ ነፍስየ ቤዛ ኣባግዕየ ከመ ካዕበ ኣንሥኣ፤
ዳግመኛ ኣነሣት ዘንድ ነፍሴን የበጎቼ ቤዛ ኣድርጌ እሰጣለሁ (ዮሓ 10÷17)
ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰብኣዊ ክዋኔው ሰው ቢሆንም በመለኮታዊ ክዋኔው የኣብና የመንፈስ ቅዱስ ቃል ወይም ወልደ እግዚአብሔር ነው፤
በመሆኑም በሰብኣዊ ክዋኔው መዋች ሲሆን በመለኮታዊ ክዋኔው ተነሽና ኣንሺ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር ሥግው ቃል ሁለቱንም ተግባራት በኣንድ ኣካልና ክዋኔ የመፈጸም ሥልጣን ኣለው፤ ይህም በመሆኑ ራሴን የማኖርና የማንሣት ሥልጣን ኣለኝ በማለት እውነታውንና ምንነቱን ኣሳየ፤
ጌታችን ይህንን ኣስመልክቶ ከመሞቱና ከመነሣቱ በፊት ለቅዱሳን ሓዋርያት በተደጋጋሚ ኣስረድቶኣል፤ ስለሆነም የጌታችን ሞትና ትንሣኤ ድንገተኛና የግድ ሳይሆን ታውቆ ያደረና የውድ እንደሆነ ከዚህ እውነታ እንረዳለን፤
ጌታችን ይህንን ተግባር በውድ ፈቃዱ የፈጸመው በእግዚአብሔር ኣሰራር ከዚህ ውጭ የዓለም ድኅነት የሚከናወንበት ዕድል ስለሌለ ነው፤ በእግዚአብሔር ኣሰራር ኃጢኣትና በደል የሚሰረዘው በቤዛዊ መሥዋዕት ብቻ እንደሆነ ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ በነበረው የቤዛዊ መሥዋዕት ኣቀራረብ የታወቀ ነው፤
በመሆኑም የሰውን ምልኣተ ኃጢኣት ሙሉ በሙሉ ሰርዞ ሰውን ከሞት ቅጣት ነጻ ለማውጣት ብቃት ያለው ቤዛዊ መሥዋዕት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ነበረበት፤ ይሁን እንጂ ለዚህ ዓይነቱ ቤዛዊ መሥዋዕት ብቁ የሆነ ከፍጡራን ወገን ስላልተገኘ ‹‹ለሊሁ መሥዋዕት፣ ወለሊሁ ሠዋዒ፣ ወለሊሁ ተወካፌ መሥዋዕት ማለትም›› ራሱ መሥዋዕት፣ ራሱ መሥዋዕት ኣቅራቢ ሊቀ ካህናት፣ ራሱ ተወካፌ መሥዋዕት ኣምላክ ሆኖ የቤዛነታችንን መሥዋዕት ራሱ በራሱ ለራሱ ኣቀረበ››፤
በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕትም እኛን ከሞት ቅጣት ነጻ ኣደረገን፤ትንሣኤያችንንም በትንሣኤው ኣበሰረ፤ በክርስትና ሃይማኖት የሚገኝ ፍጹም ድኅነትና ነጻነት በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕት ላይ የተመሠረተ ነው፤
የተወዳደችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን
ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ሲያበስረን የትንሣኤ ሰዎች ሆነን በመንፈስና በሞራል በማደግ ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ እንደገና የጨለማው ኃይል መሳሪያዎች ልንሆን ኣይደለም፤ የሞቱና የትንሣኤው ምስጢር በንጹሁ ኅሊናችን ካስተዋልነው ውስጣችን እሱን ለመቀበል የሚያዳግተው ኣይደለም፤
ከዚህ ኣንጻር በትንሣኤው ኣምነን ትንሣኤያችንን እየተጠባበቅን የምንገኝ ሕዝበ ክርስቲያን በቅን ኣስተሳሰብ፣በርቱዕ ኣእምሮና በኃይለ ሃይማኖት እየታገዝን ጨለማውን ዓለም ወደብርሃን ለመለወጥ መጣርና መትጋት ይጠበቅብናል፤
የጨለማው ዓለም መንፈስ ሊያጠፋን ካልሆነ በቀር እንደማይጠቅመን በተጨባጭ የምናውቀው ነው፤ወደድንም ጠላንም ያለን ብቸኛ ኣማራጭ ብርሃንን መከተል ነው፤ እሱም እግዚአብሔር ነው፤በብርሃን የሚመላለስ እንደማይጐዳ በእግዚአብሔር የሚኖርም ተጐድቶ ኣያውቅምና ነው፤
ዓለም እንደ ኣጠቃላይ በጨለማ ተውጦ ሲተረማመስ የሚታየው ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ምርጫው ስላደረገ ነው፤ ስለሆነም የኛ ምርጫ ብርሃን የሆነውን እግዚአብሔር እንዲሆን የቤተ ክርስቲያን የዘወትር ጥሪ ነው፤
በመጨረሻም፡-
የትንሣኤ በዓላችንን ስናከብር ዓለም በክፋቱ ያጨለመባቸውን ወገኖች ጦማችው እንዳይውሉ ካለን ከፍለን የተራቡትን በማብላት፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስና የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ በማድረግ ቀኑ ለሁላችንም ፍጹም ብርሃን ሆኖ ይውል ዘንድ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ ጥሪያችንን በእግዚአብሑር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን!!
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ”
“ወስብሐት ለእግዚአብሔር”
ኣሜን!!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
❤18👏1
ወታደራዊ ግዳጅ በአሜሪካ ሊጀመር?
========
ከሚቀጥለው ኦክቶበር 2026 ጀምሮ ወታደራዊ ግዳጅ (Military conscription, or a "draft,") በሀገረ አሜሪካ ሊጀመር መሆኑ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል:: ዕድሜአቸው ከ18-26 የሆነ በአሜሪካ የሚኖሩ ወጣቶች (ወደዱም አልወደዱም) ውትድርና ይመዘገባሉ።
በሌላ በኩል ፕሬዚዳንት ትራምፕ ራሳቸውን ከጌታ ጋራ ያነጻጸሩበት የAI ሥዕልም መነጋገሪያ ሆኗል:: ይህንን እና ሌሎች አጀንዳዎችን አንሥተን ተወያይተናል። እነሆ .....
https://www.youtube.com/live/yJcN58-Y9cc?si=t7ADTb3EkErLmMF_
========
ከሚቀጥለው ኦክቶበር 2026 ጀምሮ ወታደራዊ ግዳጅ (Military conscription, or a "draft,") በሀገረ አሜሪካ ሊጀመር መሆኑ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል:: ዕድሜአቸው ከ18-26 የሆነ በአሜሪካ የሚኖሩ ወጣቶች (ወደዱም አልወደዱም) ውትድርና ይመዘገባሉ።
በሌላ በኩል ፕሬዚዳንት ትራምፕ ራሳቸውን ከጌታ ጋራ ያነጻጸሩበት የAI ሥዕልም መነጋገሪያ ሆኗል:: ይህንን እና ሌሎች አጀንዳዎችን አንሥተን ተወያይተናል። እነሆ .....
https://www.youtube.com/live/yJcN58-Y9cc?si=t7ADTb3EkErLmMF_
YouTube
የነአሕመዲን ጀበል የእምነት ግጭት የመቀስቀስ ሙከራ
ትራምፕ "ፈጣሪ ነኝ" አሉሳ || ኢራንነት እና ኢትዮጵያዊነት || የነአሕመዲን ጀበል የእምነት ግጭት የመቀስቀስ ሙከራ
👍6
"ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች":- ከዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል ጋራ ውይይት
======
ዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል በተለይ በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ 97 እና ውጤቱን ተከትሎ መንግሥት በወሰደው ርምጃ የደረሰውን ጉዳት ለመመርመርና ለመበየን የተቋቋመውን አጣሪ ኮሚሽን በመምራት ይታወቃሉ።
በወቅቱ መንግሥት ያልተመጣጠ ኃይል ተጠቅሟል በማለታቸው ምክንያት ከሀገራቸው ተሰድደው ለመኖር የተገደዱ ታላቅ የሕግ ሰው ናቸው። በቅርቡ ባሳተሙት መጽፋቸው ዙሪያ ከ Abel Gashe ጋራ ያደረጉትን ውይይት እንድትመለከቱ እንጋብዛለን።
https://www.youtube.com/live/07lP6oNT77E?si=cmZnbwaqQ6rZRJQM
======
ዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል በተለይ በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ 97 እና ውጤቱን ተከትሎ መንግሥት በወሰደው ርምጃ የደረሰውን ጉዳት ለመመርመርና ለመበየን የተቋቋመውን አጣሪ ኮሚሽን በመምራት ይታወቃሉ።
በወቅቱ መንግሥት ያልተመጣጠ ኃይል ተጠቅሟል በማለታቸው ምክንያት ከሀገራቸው ተሰድደው ለመኖር የተገደዱ ታላቅ የሕግ ሰው ናቸው። በቅርቡ ባሳተሙት መጽፋቸው ዙሪያ ከ Abel Gashe ጋራ ያደረጉትን ውይይት እንድትመለከቱ እንጋብዛለን።
https://www.youtube.com/live/07lP6oNT77E?si=cmZnbwaqQ6rZRJQM
YouTube
"ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች":- ከዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል ጋራ ውይይት
❤2👍1
የብሔረሰብ እና የእምነት ልዩነት || ኢትዮጵያውያንን የመለያያ አጀንዳ
========
ኢትዮጵያውያን ሀገራቸው ከዕለት ተዕለት እየተጎዳች የመጣችበትን ነገር ጨክነው መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ በየጊዜው ችግሩን በሌላ ችግር እያጎመሱት ነው። በተለያዩ ዘዴዎች እየተደረገ እሳት የሚጫርበት ጉዳይ አንድም የብሔረሰብ ልዩነታችንን አንድም የእምነት ልዩነታችንን የተመለከተ ነው::
==== አጀንዳዎችና ነጥቦች ======
** በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሰበብ በሌላው የሀገራችን ብሔረሰብ እና በኦሮሞ መካከል ትልቅ እሳት ለመጫር እየተሞከረ ነው።
** የአክሱም ወይም የጎንደርና ሞጣ ሙስሊሞችን ሰበብ አድርጎ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ እሳት ለመጫር እየተሞከረ ነው::
** የቴዲ አፍሮ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ነው በሚል በየመንገዱ እና አዳራሹ ቤተ ክርስቲያንን በግልጽ ማዋረድ ሕጋዊ መስሏል፣
** በአርሲ የክርስቲያኖች ፍጅት አሁንም አልቆመም፤
** ኢትዮጵያውያን ግን የዚህ ሁሉ ተንኮል በመጨረሻ ለሁላችንም ጥፋት መሆኑ
አልገባንም።
https://www.youtube.com/live/ubeeIOXSCEY?si=dg3PtOqhi8VhBQC0
========
ኢትዮጵያውያን ሀገራቸው ከዕለት ተዕለት እየተጎዳች የመጣችበትን ነገር ጨክነው መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ በየጊዜው ችግሩን በሌላ ችግር እያጎመሱት ነው። በተለያዩ ዘዴዎች እየተደረገ እሳት የሚጫርበት ጉዳይ አንድም የብሔረሰብ ልዩነታችንን አንድም የእምነት ልዩነታችንን የተመለከተ ነው::
==== አጀንዳዎችና ነጥቦች ======
** በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሰበብ በሌላው የሀገራችን ብሔረሰብ እና በኦሮሞ መካከል ትልቅ እሳት ለመጫር እየተሞከረ ነው።
** የአክሱም ወይም የጎንደርና ሞጣ ሙስሊሞችን ሰበብ አድርጎ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ እሳት ለመጫር እየተሞከረ ነው::
** የቴዲ አፍሮ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ነው በሚል በየመንገዱ እና አዳራሹ ቤተ ክርስቲያንን በግልጽ ማዋረድ ሕጋዊ መስሏል፣
** በአርሲ የክርስቲያኖች ፍጅት አሁንም አልቆመም፤
** ኢትዮጵያውያን ግን የዚህ ሁሉ ተንኮል በመጨረሻ ለሁላችንም ጥፋት መሆኑ
አልገባንም።
https://www.youtube.com/live/ubeeIOXSCEY?si=dg3PtOqhi8VhBQC0
YouTube
የብሔረሰብ እና የእምነት ልዩነት || ኢትዮጵያውያንን የመለያያ አጀንዳ
❤9
April 24 የአርመኖች ጄኖሳይድ መታሰቢያ (ወዳጅህ ሲታማ ለኔ ብለህ ስማ!!!)
======
( ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ )
** የተፈጸመበት ወቅት => የኦቶማኖች የመጨረሻ ዓመታት በሆኑት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እና ማግሥት .....
April 24 ቀን ቁጥራቸው 1.5 ሚሊዮን በላይ የሆኑ የአርመን ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመው ጄኖሳይድ መታሰቢያ ነው። ይህንን ዘግናኝ ፍጅት የፊደመው የኦቶማን ቱርክ መንግሥት ነው።
የሚደንቀው ነገር ይህንን የ1.5 ሚሊዮን ሕዝብ ፍጅት "ጄኖሳይድ" እንዳይባል ቱርክዬ ባላት አቅም ሁሉ ስትጥር ኖራለች። ዛሬም ድረስ ከጥቂት ሀገራት በስተቀር ሌላው የዓለም ሕዝብ ፍጅቱን "በጦርነት ወቅት የሚፈጸም ተራ ጉዳት" አድርጎ ብቻ እንዲመለከት በማድረግ ላይ ትገኛለች።
ኦቶማኖች በ1ኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የዘር ማጥፋት ያደረሱት በአርመናውያን ላይ ብቻ አይደለም። በትውልደ ግሪኮች አና አሦሪያውያንም ላይ ተመሳሳይ እልቂትና ፍጅት ተፈጽሟል። ከሞት የተረፉትም በስደት ሀገር ጥለው ሄደዋል። የቀሩትም ሃይማኖታቸውን እየቀየሩ እስላሞች ሆነዋል። ብዙዎችም ትውልደ ግሪክ መሆናቸው እንዳይታወቅ ስማቸውን እና ታሪካቸውን ቀይረዋል።
የሚደንቀው ታሪካቸውን እና የቤተሰባቸውን ታሪክ ከለወጡት መካከል የአሁኑ የሀገሪቱ መሪ ኤርዶጋን ይገኙበታል የሚሉ ቱርካውያን አሉ። ኤርዶጋን ከትውልደ ግሪክ ክርስቲያን ወገን የሚወለዱ ነገር ግን በአንደኛው የዓለም ጦርነት የክርስቲያኖች ጄኖሳይድ ወቅት እምነታቸውን ከቀየሩ ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው ይባላል።
በአጭሩ በዚህ የኦቶማኖች ፍጅት፦
** አርመናውያን= ከ1.5 ሚሊዮን በላይ
** ግሪኮች (በአናቶሊያ እና ፖንተስ) = ከ300 ሺህ እስከ 900 ሺህ፣
** የአሦሪያ ክርስቲያኖች (ሦሪያውያን እና ካሊዲያኖችን ጨምሮ = ከ250 ሺህ እስከ 300 ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ አልቋል።
=====
ፊልም ለምትወዱ (ስለ አርመናውያን ጄኖሳይድ) ብዙ ውዝግብ ያስነሳውን እጅግ ጠቃሚ ፊልም ተመልከቱ።
++ ርዕሱ =The Promise
++ Starring = Oscar Isaac, Christian Bale, Charlotte Le Bon
++ Director = Terry George
======
( ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ )
** የተፈጸመበት ወቅት => የኦቶማኖች የመጨረሻ ዓመታት በሆኑት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እና ማግሥት .....
April 24 ቀን ቁጥራቸው 1.5 ሚሊዮን በላይ የሆኑ የአርመን ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመው ጄኖሳይድ መታሰቢያ ነው። ይህንን ዘግናኝ ፍጅት የፊደመው የኦቶማን ቱርክ መንግሥት ነው።
የሚደንቀው ነገር ይህንን የ1.5 ሚሊዮን ሕዝብ ፍጅት "ጄኖሳይድ" እንዳይባል ቱርክዬ ባላት አቅም ሁሉ ስትጥር ኖራለች። ዛሬም ድረስ ከጥቂት ሀገራት በስተቀር ሌላው የዓለም ሕዝብ ፍጅቱን "በጦርነት ወቅት የሚፈጸም ተራ ጉዳት" አድርጎ ብቻ እንዲመለከት በማድረግ ላይ ትገኛለች።
ኦቶማኖች በ1ኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የዘር ማጥፋት ያደረሱት በአርመናውያን ላይ ብቻ አይደለም። በትውልደ ግሪኮች አና አሦሪያውያንም ላይ ተመሳሳይ እልቂትና ፍጅት ተፈጽሟል። ከሞት የተረፉትም በስደት ሀገር ጥለው ሄደዋል። የቀሩትም ሃይማኖታቸውን እየቀየሩ እስላሞች ሆነዋል። ብዙዎችም ትውልደ ግሪክ መሆናቸው እንዳይታወቅ ስማቸውን እና ታሪካቸውን ቀይረዋል።
የሚደንቀው ታሪካቸውን እና የቤተሰባቸውን ታሪክ ከለወጡት መካከል የአሁኑ የሀገሪቱ መሪ ኤርዶጋን ይገኙበታል የሚሉ ቱርካውያን አሉ። ኤርዶጋን ከትውልደ ግሪክ ክርስቲያን ወገን የሚወለዱ ነገር ግን በአንደኛው የዓለም ጦርነት የክርስቲያኖች ጄኖሳይድ ወቅት እምነታቸውን ከቀየሩ ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው ይባላል።
በአጭሩ በዚህ የኦቶማኖች ፍጅት፦
** አርመናውያን= ከ1.5 ሚሊዮን በላይ
** ግሪኮች (በአናቶሊያ እና ፖንተስ) = ከ300 ሺህ እስከ 900 ሺህ፣
** የአሦሪያ ክርስቲያኖች (ሦሪያውያን እና ካሊዲያኖችን ጨምሮ = ከ250 ሺህ እስከ 300 ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ አልቋል።
=====
ፊልም ለምትወዱ (ስለ አርመናውያን ጄኖሳይድ) ብዙ ውዝግብ ያስነሳውን እጅግ ጠቃሚ ፊልም ተመልከቱ።
++ ርዕሱ =The Promise
++ Starring = Oscar Isaac, Christian Bale, Charlotte Le Bon
++ Director = Terry George
😢9❤5😁2🤔1
የታሪክ እውነት ለቤተክርስቲያን ህልውና!
=====
(ቀሲስ ዶ/ር Mengistu Gobezie እንደጻፉት)
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የሚሰነዘረው ጥቃትና ስም የማጠልሸት ዘመቻ፣ መሠረቱን በሐሰተኛ ትርክቶች ላይ አድርጎ በስልታዊ መንገድ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በአንድ በኩል አክሱምን ማዕከል ያደረገው የወቅቱ የውሃብያ ጽንፈኞች እንቅስቃሴ የታሪክ ፈጠራን እንደ ዋና መሣሪያ ሲጠቀም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በአሩሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመው የግፍ እልቂት ለዘመናት ቤተክርስቲያንን እንደ "ጨቋኝ" አድርጎ በመሳል የተዘራው የጥላቻ ውጤት ነው። እነዚህ ወገኖች በጉልበትና በውሸት አዲስ ታሪክ ለመፍጠር ቢራወጡም፣ እውነታው ግን ከዚህ የራቀ መሆኑን እነርሱ ራሳቸው ጠንቅቀው ያውቁታል። ነጃሺ የሚባል ንጉሥ በኢትዮጵያ ምድር እንዳልነበረ ብቻ ሳይሆን፣ በስደት የመጡት አብዛኛዎቹ የመሐመድ ተከታዮች እንኳን ንጉሡን ሊያሰልሙ ራሳቸው ወደ ክርስትና መለወጣቸውን ነው ታሪክ የሚነግረን። በፈጠራ ትርክት የታሪክ ባለቤት መሆን አይቻልም!
"አበሾችን አትንኩ" የሚለው ብሂልም ቢሆን በታሪክ ምሁራን ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ የሚነሳበት ነው። ይኽ እውነት ቢሆን ኑሮ ኢትዮጵያ በታሪኳ ከውስጥም ከውጭም በተደጋጋሚ በኢስላማዊ ኃይሎች የከፍተኛ ጥቃት ሰለባ ባልሆነች ነበር። አክራሪዎቹ እንደ ጀግና የሚቆጥሩት ጨፍጫፊው አሕመድ ግራኝ እንኳ ስለ ነጃሺ ትረካ ምንም ትንፍሽ ያላለበት ምክንያት ጉዳዩ ከልብወለድ ባለፈ የታሪክ መሰረት ስለሌለውና ያኔ የማይታወቅ በመሆኑ ነው። የዚህ ሁሉ ድካም ዋነኛው ግብ ኢትዮጵያን በታሪክ "የእስላም ሀገር" አድርጎ በመሳል የአረብ ሊግ አባል የማድረግ ሕልም ሊሆን እንድሚችል ብዙዎቹ ይገምታሉ።
ይህ የታሪክ ማዛባት በእስላማዊ ትረካዎች ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም። ለምሳሌ “የደቂቀ እስጢፋኖስ” ታሪክም በፕሮቴስታንት እና በ"ተሐድሶ" ንቅናቄ አቀንቃኞች ዘንድ ተመሳሳይ መከለስ ተደርጎበታል። እስልምና በአረብ ሀገራት ከመስፋፋቱ በፊት በኢትዮጵያ ነበር ለማለት "የአል-ነጃሺን" የውሸት ትረካ እንደሚጠቀሙት ሁሉ፣ ፕሮቴስታንቶችም ማርቲን ሉተር በጀርመን ተሐድሶን ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ የፕሮቴስታንት አገር ነበረች ለማለት የደቂቀ እስጢፋኖስን ታሪክ ለፍላጎታቸው እንዲመች አድርገው ያጣምሙታል። ከፖለቲካዊ እስልምና እና ከፕሮቴስታንት አክቲቪስት ቡድኖች የሚሰነዘሩት እነዚህ ትረካዎች፣ ቤተክርስቲያኒቱን እንደ ታሪካዊ "ጨቋኝ" እና አግላይ ተቋም አድርገውም ያቀርቧታል። ይህ "የሐሰተኛ ተበዳይነት" ትረካ (Pseudo-victimhood narrative)፣ በቤተክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ፣ ታሪካዊና ተቋማዊ ቅርሶች ላይ የሚፈጽሙትን ጥሰት ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የታቀደ ስልታዊ ስሌት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።
ስለሆነም ለኦርቶዶክሳውያን ማስተላለፍ የምፈልገው መልዕክት፤ አሁን በቤተክርስቲያናችን ላይ የተጋረጠው ፈተና መሰረቱ የሀሰት ታሪክ መሆኑን ነው። ይህንን ጥፋት ለመመከት ታሪካችንን በውል ማወቅና ለቀጣዩ ትውልድ ማሳወቅ ብቸኛው አማራጭ ነው። የቻይናው ፈላስፋ ኮንፊሸስ "ጨለማን አንድ ሺህ ጊዜ ከማውገዝ አንድ ሻማ ማብራት ትልቅ መፍትሔ ነው" እንዳለው፣ የእኔ አዲስ መጽሐፍም ዋና ዓላማው ይህንኑ የታሪክ እውነት በማንጠር ቤተክርስቲያናችንንና ሕዝባችንን ከጥፋት መታደግ ነው።
ይህ ሥራ ለሕዝበ ክርስቲያኑ እንዲደርስ የሁላችሁም ትብብር ያስፈልጋል። ከ60 ሚሊዮን በላይ ከሚገመተው ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን መካከል ሁለት ሺህ የሚሆነው ሰው መጽሐፉን አስቀድሞ በማዘዝ ቢተባበር፣ ሥራው በቅርብ ጊዜ ታትሞ ለንባብ እንዲበቃ ትልቅ አቅም ይሆነናል። ታሪካችንን በማወቅ ለቤተክርስቲያችን ህልውና ዘብ እንቁም!
መጽሐፉን አስቀድሞ በማዘዝ ለሕትመት እንዲበቃ ለማገዝ ቀጥሎ ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ፦
[https://www.wegenfund.com/projects/eotchistorybook/]
=====
(ቀሲስ ዶ/ር Mengistu Gobezie እንደጻፉት)
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የሚሰነዘረው ጥቃትና ስም የማጠልሸት ዘመቻ፣ መሠረቱን በሐሰተኛ ትርክቶች ላይ አድርጎ በስልታዊ መንገድ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በአንድ በኩል አክሱምን ማዕከል ያደረገው የወቅቱ የውሃብያ ጽንፈኞች እንቅስቃሴ የታሪክ ፈጠራን እንደ ዋና መሣሪያ ሲጠቀም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በአሩሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመው የግፍ እልቂት ለዘመናት ቤተክርስቲያንን እንደ "ጨቋኝ" አድርጎ በመሳል የተዘራው የጥላቻ ውጤት ነው። እነዚህ ወገኖች በጉልበትና በውሸት አዲስ ታሪክ ለመፍጠር ቢራወጡም፣ እውነታው ግን ከዚህ የራቀ መሆኑን እነርሱ ራሳቸው ጠንቅቀው ያውቁታል። ነጃሺ የሚባል ንጉሥ በኢትዮጵያ ምድር እንዳልነበረ ብቻ ሳይሆን፣ በስደት የመጡት አብዛኛዎቹ የመሐመድ ተከታዮች እንኳን ንጉሡን ሊያሰልሙ ራሳቸው ወደ ክርስትና መለወጣቸውን ነው ታሪክ የሚነግረን። በፈጠራ ትርክት የታሪክ ባለቤት መሆን አይቻልም!
"አበሾችን አትንኩ" የሚለው ብሂልም ቢሆን በታሪክ ምሁራን ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ የሚነሳበት ነው። ይኽ እውነት ቢሆን ኑሮ ኢትዮጵያ በታሪኳ ከውስጥም ከውጭም በተደጋጋሚ በኢስላማዊ ኃይሎች የከፍተኛ ጥቃት ሰለባ ባልሆነች ነበር። አክራሪዎቹ እንደ ጀግና የሚቆጥሩት ጨፍጫፊው አሕመድ ግራኝ እንኳ ስለ ነጃሺ ትረካ ምንም ትንፍሽ ያላለበት ምክንያት ጉዳዩ ከልብወለድ ባለፈ የታሪክ መሰረት ስለሌለውና ያኔ የማይታወቅ በመሆኑ ነው። የዚህ ሁሉ ድካም ዋነኛው ግብ ኢትዮጵያን በታሪክ "የእስላም ሀገር" አድርጎ በመሳል የአረብ ሊግ አባል የማድረግ ሕልም ሊሆን እንድሚችል ብዙዎቹ ይገምታሉ።
ይህ የታሪክ ማዛባት በእስላማዊ ትረካዎች ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም። ለምሳሌ “የደቂቀ እስጢፋኖስ” ታሪክም በፕሮቴስታንት እና በ"ተሐድሶ" ንቅናቄ አቀንቃኞች ዘንድ ተመሳሳይ መከለስ ተደርጎበታል። እስልምና በአረብ ሀገራት ከመስፋፋቱ በፊት በኢትዮጵያ ነበር ለማለት "የአል-ነጃሺን" የውሸት ትረካ እንደሚጠቀሙት ሁሉ፣ ፕሮቴስታንቶችም ማርቲን ሉተር በጀርመን ተሐድሶን ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ የፕሮቴስታንት አገር ነበረች ለማለት የደቂቀ እስጢፋኖስን ታሪክ ለፍላጎታቸው እንዲመች አድርገው ያጣምሙታል። ከፖለቲካዊ እስልምና እና ከፕሮቴስታንት አክቲቪስት ቡድኖች የሚሰነዘሩት እነዚህ ትረካዎች፣ ቤተክርስቲያኒቱን እንደ ታሪካዊ "ጨቋኝ" እና አግላይ ተቋም አድርገውም ያቀርቧታል። ይህ "የሐሰተኛ ተበዳይነት" ትረካ (Pseudo-victimhood narrative)፣ በቤተክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ፣ ታሪካዊና ተቋማዊ ቅርሶች ላይ የሚፈጽሙትን ጥሰት ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የታቀደ ስልታዊ ስሌት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።
ስለሆነም ለኦርቶዶክሳውያን ማስተላለፍ የምፈልገው መልዕክት፤ አሁን በቤተክርስቲያናችን ላይ የተጋረጠው ፈተና መሰረቱ የሀሰት ታሪክ መሆኑን ነው። ይህንን ጥፋት ለመመከት ታሪካችንን በውል ማወቅና ለቀጣዩ ትውልድ ማሳወቅ ብቸኛው አማራጭ ነው። የቻይናው ፈላስፋ ኮንፊሸስ "ጨለማን አንድ ሺህ ጊዜ ከማውገዝ አንድ ሻማ ማብራት ትልቅ መፍትሔ ነው" እንዳለው፣ የእኔ አዲስ መጽሐፍም ዋና ዓላማው ይህንኑ የታሪክ እውነት በማንጠር ቤተክርስቲያናችንንና ሕዝባችንን ከጥፋት መታደግ ነው።
ይህ ሥራ ለሕዝበ ክርስቲያኑ እንዲደርስ የሁላችሁም ትብብር ያስፈልጋል። ከ60 ሚሊዮን በላይ ከሚገመተው ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን መካከል ሁለት ሺህ የሚሆነው ሰው መጽሐፉን አስቀድሞ በማዘዝ ቢተባበር፣ ሥራው በቅርብ ጊዜ ታትሞ ለንባብ እንዲበቃ ትልቅ አቅም ይሆነናል። ታሪካችንን በማወቅ ለቤተክርስቲያችን ህልውና ዘብ እንቁም!
መጽሐፉን አስቀድሞ በማዘዝ ለሕትመት እንዲበቃ ለማገዝ ቀጥሎ ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ፦
[https://www.wegenfund.com/projects/eotchistorybook/]
❤13👍5😁1
ጸረ ስደተኛ ነውጥ በደቡብ አፍሪካ || ኢትዮጵያውያን ተጎድተዋልመጪው ጊዜ የበለጠ ያስፈራል | "Operation Dudula" ምንድነው?
=====
በደቡብ አፍሪካ እየታየ ያለው ጸረ ሰደተኛ እንቅስቃሴ ዘግናኝ ነው። ብዙ ኢትዮጵያውያን እና የሌሎች አፍሪካ ሀገሮች ስደተኞች አደጋ ላይ ወድቀዋል። እየተከታተላችሁ ነው? በሀገሩም በሔደበት ሀገርም ጥቃት እየደረሰበት ያለው ወገናችን ሕይወት ልብ ይሰብራል።
https://www.youtube.com/live/5AYA3-ul9qE?si=Vfct1pehp_ipzETB
=====
በደቡብ አፍሪካ እየታየ ያለው ጸረ ሰደተኛ እንቅስቃሴ ዘግናኝ ነው። ብዙ ኢትዮጵያውያን እና የሌሎች አፍሪካ ሀገሮች ስደተኞች አደጋ ላይ ወድቀዋል። እየተከታተላችሁ ነው? በሀገሩም በሔደበት ሀገርም ጥቃት እየደረሰበት ያለው ወገናችን ሕይወት ልብ ይሰብራል።
https://www.youtube.com/live/5AYA3-ul9qE?si=Vfct1pehp_ipzETB
YouTube
ጸረ ስደተኛ ነውጥ በደቡብ አፍሪካ || ኢትዮጵያውያን ተጎድተዋል
መጪው ጊዜ የበለጠ ያስፈራል | "Operation Dudula" ምንድነው?
#Xenophobic attacks in #south #africa against African immigrants
#Xenophobic attacks in #south #africa against African immigrants
👍1
የቤተክርስቲያን ክብርና የቀኖና ጥሰት፦ በዋሽንግተን ዲሲ የታየው የሥርዓተ አልበኝነት መንፈስ!
======
(ሊቀ ካህናት Kesis Abraham Andarge )
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ባገኘችው ሰማያዊ ሥልጣንና በሐዋርያዊ ቀኖናዋ ተከብራ፣ ሥርዓቷ ተጠብቆ ለዘመናት ኖራለች። ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ መዋቅርና በብፁዓን አባቶቻችን ላይ የሚሰነዘሩት የጽርፈት ቃላት የታሪክ ጠባሳ እየሆኑ ነው። ይህ በአደባባይ የታየው የሥርዓት መፍረስና የአባቶች መናቅ፣ ዝም ተብሎ የሚታለፍ ሳይሆን ሁሉንም ካህናትና ኦርቶዶክሳውያንን ከልብ ሊያሳስብና ሊያስቆጭ የሚገባ ታላቅ የክህደት ምልክት ሆኗል።
በተለይም "እናጠምቃለን፣ እንፈውሳለን፣ አጋንንት እናስወጣለን" በሚል መንፈሳዊ ሽፋን ራሳቸውን ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት በላይ አድርገው የሾሙ ግለሰቦች፤ ከክርስቶሳዊ ትሕትና ይልቅ ትዕቢትን፣ ከሐዋርያዊ ታዛዥነት ይልቅ ዐመፅንና ስድብን የዕለት ተዕለት ተግባራቸውና የሙያቸው መታወቂያ ሲያደርጉ ማየት እጅግ ዘግናኝ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያ ተሸሽጎ፣ በአንድ ሊቀ ጳጳስ ላይ የስድብን ቃል መናገር የክህነትን ክብር ማቃለል ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ህልውና መፈታተን ነው። ለዚህ እኩይ ድርጊት ምላሽ እንዲሆንና ምዕመኑ ከእንዲህ ዓይነት "ተኩላዎች" ራሱን እንዲጠብቅ የሚከተሉትን ነጥቦች ማስተዋል ይገባል።
፩. የመንፈሳዊ ሥልጣን ልዕልና እና የሥርዓተ ክህነት ተዋረድ
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖናዊ ትምህርት መሠረት፣ የሊቀ ጳጳስን ትዕዛዝ ማክበር ለአንድ ግለሰብ መዓረግ ወይም ሰብዕና መገዛት ሳይሆን፣ በሊቀ ጳጳሱ በኩል ለሚገለጠው ለራሱ ለእግዚአብሔር ሥልጣን መታዘዝ ነው። ሊቃነ ጳጳሳት የሐዋርያት ተተኪዎች፣ የመንጋው እረኞችና የቤተክርስቲያን ዓይኖች ናቸው። በሃይማኖትና በሥርዓት ላይ የሚያስተላልፉት ትዕዛዝ ሁሉ መንፈሳዊ መሠረት አለው። ይህንን መንፈሳዊ መዋቅር መናቅና ትዕዛዝን ጥሶ በአደባባይ መቆም፣ ከበረከት ይልቅ መርገምን፣ ከብርሃን ይልቅ የነፍስ ጨለማን በራስ ላይ መጥራት ነው። የአባቶችን ቃል አክብሮ የተቀበለ በመንፈሳዊ ዕድገት ሲረካ፣ በአባቶች ላይ ያመፀ ግን እንደ ቃየን ከእግዚአብሔር ፊት ተለይቶ ለውድቀት ይዳረጋል።
በተለይም ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ በእግዚአብሔር ፈቃድና በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የተሾሙ፣ መንጋውን እንዲጠብቁ የሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን አደራ ያለባቸው አባት ናቸው። እኒህን አባት ግለሰቡ በጽሑፉ ውስጥ በሚጠቀማቸው፣ ክህነትን በማይመጥኑ "የጎዳና ቃላት" መዝለፉ፣ በምድርም በሰማይም የሚያስጠይቅ ከባድ በደል ነው። "መቅደሱን ሳይሆን ቪላውን" እያሉ መሳለቅ፣ በሊቀ ጳጳሱ መንበር ላይ በጸጋ የተቀመጠውን ክርስቶስን እንደ መሳደብና እንደ መቃወም ይቆጠራል።
፪. በፈውስ ስም የሚደረግ የንግድ ማታለልና የጋራ ኃላፊነትን የመወጣት ጥሪ
"እናጠምቃለን፣ እናስለቅቃለን፣ እንፈውሳለን" በሚል መንፈሳዊ ሽፋን ምዕመናንን የሚያስቱና የቤተክርስቲያንን መዋቅር እንደ ጠላት የሚመለከቱ ግለሰቦች፤ ዋና ተግባራቸው የነፍሳት መዳን ሳይሆን "የምዕመኑን መንፈሳዊ ተጋድሎ ለግል ጥቅም ማዋልና" የንግድ ተቋም መክፈት መሆኑን አሁን በአደባባይ በወጣው ጽሑፋቸው ለዓለም አረጋግጠዋል። እውነተኛ ፈውስና ጸጋ ባለበት ቦታ ትሕትና እንጂ ስድብና ዐመፅ ቦታ የላቸውም። አባቶችን እየዘለፉ "ፈዋሽ ነኝ" ብሎ መነሣት የሰይጣን መታወቂያና የትዕቢት መንፈስ መገለጫ ነው። እነዚህ ግለሰቦች በፈውስ ስም "ከቅድስት ቤተክርስቲያን መዋቅር ውጭ የሆነ የሥርዓተ አልበኝነት ጎዳና ለመከተልና" ምዕመኑን ከእውነተኛው የቤተክርስቲያን በረከት ለመለየት የሚጥሩ "የዘመኑ ነጋዴዎች" ናቸው። ይህ የሥልጣነ ክህነት መድፈር የአንድ ሊቀ ጳጳስ የግል ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም። ይህ ድርጊት በብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ላይ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር ላይ የተሰነዘረ ታላቅ ስድብ ነው።
ስለዚህ በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢው ያላችሁ ውሉደ ክህነት የሆናችሁ አባቶች በእናንተ መሃል ሆኖ መቅደሱንና መንበሩን የሚያረክስ "ተኩላ" ሲጮኽ ዝምታችሁ ተገቢ አይደለም! ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንዲጠበቅ ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ይህንን ጋጠ-ወጥ ድርጊት በአንድነት ልታወግዙት ይገባል። ቅዱስ ሲኖዶስም በእነዚህ ሥርዓት የለሽ ግለሰቦች ላይ አፋጣኝና የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።
"ትዕቢት ጥፋትን፣ የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች።"(ምሳሌ 16፥18) በመጨረሻም በፈውስ ስም ተሸሽገው በብፁዓን አባቶች ላይ የሚሰነዘሩ የእብሪት ቃላትና የስድብ ናዳዎች፣ በሐዋርያዊ ቅብብል የጸናውን የቤተክርስቲያን መንበር ሊያናውጡ አይችሉም። የእነዚህ ግለሰቦች እኩይነትና ሥርዓተ አልበኝነት፣ ከመንፈሳዊነት የራቁና ለሥጋዊ ጥቅም ብቻ የሚጋደሉ መሆናቸውን በአደባባይ መስክሮባቸዋል። የአባቶችን ቃል ማክበርና ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን መገዛት ለነፍስ በረከት እንጂ ለሥጋ ሸክም አይደለም። ከሥርዓት የወጡ፣ አባቶችን የዘለፉና በመቅደሱ ላይ ያመፁ እኩያን የጊዜ ጉዳይ እንጂ እንደ አርዮስና እንደ ይሁዳ መጨረሻቸው የውርደት መሆኑ አይቀሬ ነው። እኛ ግን ከእናት ቤተክርስቲያናችን፣ ከቅዱስ ሲኖዶሳችንና ከብፁዓን አባቶቻችን ጎን በሃይማኖት ጸንተን እንቆማለን።
የቤተክርስቲያን አምላክ ክብሯን ይጠብቅ!
እኩያንንና ተኩላዎችንም ከመንጋው ይለይልን!
======
(ሊቀ ካህናት Kesis Abraham Andarge )
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ባገኘችው ሰማያዊ ሥልጣንና በሐዋርያዊ ቀኖናዋ ተከብራ፣ ሥርዓቷ ተጠብቆ ለዘመናት ኖራለች። ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ መዋቅርና በብፁዓን አባቶቻችን ላይ የሚሰነዘሩት የጽርፈት ቃላት የታሪክ ጠባሳ እየሆኑ ነው። ይህ በአደባባይ የታየው የሥርዓት መፍረስና የአባቶች መናቅ፣ ዝም ተብሎ የሚታለፍ ሳይሆን ሁሉንም ካህናትና ኦርቶዶክሳውያንን ከልብ ሊያሳስብና ሊያስቆጭ የሚገባ ታላቅ የክህደት ምልክት ሆኗል።
በተለይም "እናጠምቃለን፣ እንፈውሳለን፣ አጋንንት እናስወጣለን" በሚል መንፈሳዊ ሽፋን ራሳቸውን ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት በላይ አድርገው የሾሙ ግለሰቦች፤ ከክርስቶሳዊ ትሕትና ይልቅ ትዕቢትን፣ ከሐዋርያዊ ታዛዥነት ይልቅ ዐመፅንና ስድብን የዕለት ተዕለት ተግባራቸውና የሙያቸው መታወቂያ ሲያደርጉ ማየት እጅግ ዘግናኝ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያ ተሸሽጎ፣ በአንድ ሊቀ ጳጳስ ላይ የስድብን ቃል መናገር የክህነትን ክብር ማቃለል ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ህልውና መፈታተን ነው። ለዚህ እኩይ ድርጊት ምላሽ እንዲሆንና ምዕመኑ ከእንዲህ ዓይነት "ተኩላዎች" ራሱን እንዲጠብቅ የሚከተሉትን ነጥቦች ማስተዋል ይገባል።
፩. የመንፈሳዊ ሥልጣን ልዕልና እና የሥርዓተ ክህነት ተዋረድ
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖናዊ ትምህርት መሠረት፣ የሊቀ ጳጳስን ትዕዛዝ ማክበር ለአንድ ግለሰብ መዓረግ ወይም ሰብዕና መገዛት ሳይሆን፣ በሊቀ ጳጳሱ በኩል ለሚገለጠው ለራሱ ለእግዚአብሔር ሥልጣን መታዘዝ ነው። ሊቃነ ጳጳሳት የሐዋርያት ተተኪዎች፣ የመንጋው እረኞችና የቤተክርስቲያን ዓይኖች ናቸው። በሃይማኖትና በሥርዓት ላይ የሚያስተላልፉት ትዕዛዝ ሁሉ መንፈሳዊ መሠረት አለው። ይህንን መንፈሳዊ መዋቅር መናቅና ትዕዛዝን ጥሶ በአደባባይ መቆም፣ ከበረከት ይልቅ መርገምን፣ ከብርሃን ይልቅ የነፍስ ጨለማን በራስ ላይ መጥራት ነው። የአባቶችን ቃል አክብሮ የተቀበለ በመንፈሳዊ ዕድገት ሲረካ፣ በአባቶች ላይ ያመፀ ግን እንደ ቃየን ከእግዚአብሔር ፊት ተለይቶ ለውድቀት ይዳረጋል።
በተለይም ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ በእግዚአብሔር ፈቃድና በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የተሾሙ፣ መንጋውን እንዲጠብቁ የሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን አደራ ያለባቸው አባት ናቸው። እኒህን አባት ግለሰቡ በጽሑፉ ውስጥ በሚጠቀማቸው፣ ክህነትን በማይመጥኑ "የጎዳና ቃላት" መዝለፉ፣ በምድርም በሰማይም የሚያስጠይቅ ከባድ በደል ነው። "መቅደሱን ሳይሆን ቪላውን" እያሉ መሳለቅ፣ በሊቀ ጳጳሱ መንበር ላይ በጸጋ የተቀመጠውን ክርስቶስን እንደ መሳደብና እንደ መቃወም ይቆጠራል።
፪. በፈውስ ስም የሚደረግ የንግድ ማታለልና የጋራ ኃላፊነትን የመወጣት ጥሪ
"እናጠምቃለን፣ እናስለቅቃለን፣ እንፈውሳለን" በሚል መንፈሳዊ ሽፋን ምዕመናንን የሚያስቱና የቤተክርስቲያንን መዋቅር እንደ ጠላት የሚመለከቱ ግለሰቦች፤ ዋና ተግባራቸው የነፍሳት መዳን ሳይሆን "የምዕመኑን መንፈሳዊ ተጋድሎ ለግል ጥቅም ማዋልና" የንግድ ተቋም መክፈት መሆኑን አሁን በአደባባይ በወጣው ጽሑፋቸው ለዓለም አረጋግጠዋል። እውነተኛ ፈውስና ጸጋ ባለበት ቦታ ትሕትና እንጂ ስድብና ዐመፅ ቦታ የላቸውም። አባቶችን እየዘለፉ "ፈዋሽ ነኝ" ብሎ መነሣት የሰይጣን መታወቂያና የትዕቢት መንፈስ መገለጫ ነው። እነዚህ ግለሰቦች በፈውስ ስም "ከቅድስት ቤተክርስቲያን መዋቅር ውጭ የሆነ የሥርዓተ አልበኝነት ጎዳና ለመከተልና" ምዕመኑን ከእውነተኛው የቤተክርስቲያን በረከት ለመለየት የሚጥሩ "የዘመኑ ነጋዴዎች" ናቸው። ይህ የሥልጣነ ክህነት መድፈር የአንድ ሊቀ ጳጳስ የግል ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም። ይህ ድርጊት በብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ላይ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር ላይ የተሰነዘረ ታላቅ ስድብ ነው።
ስለዚህ በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢው ያላችሁ ውሉደ ክህነት የሆናችሁ አባቶች በእናንተ መሃል ሆኖ መቅደሱንና መንበሩን የሚያረክስ "ተኩላ" ሲጮኽ ዝምታችሁ ተገቢ አይደለም! ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንዲጠበቅ ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ይህንን ጋጠ-ወጥ ድርጊት በአንድነት ልታወግዙት ይገባል። ቅዱስ ሲኖዶስም በእነዚህ ሥርዓት የለሽ ግለሰቦች ላይ አፋጣኝና የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።
"ትዕቢት ጥፋትን፣ የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች።"(ምሳሌ 16፥18) በመጨረሻም በፈውስ ስም ተሸሽገው በብፁዓን አባቶች ላይ የሚሰነዘሩ የእብሪት ቃላትና የስድብ ናዳዎች፣ በሐዋርያዊ ቅብብል የጸናውን የቤተክርስቲያን መንበር ሊያናውጡ አይችሉም። የእነዚህ ግለሰቦች እኩይነትና ሥርዓተ አልበኝነት፣ ከመንፈሳዊነት የራቁና ለሥጋዊ ጥቅም ብቻ የሚጋደሉ መሆናቸውን በአደባባይ መስክሮባቸዋል። የአባቶችን ቃል ማክበርና ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን መገዛት ለነፍስ በረከት እንጂ ለሥጋ ሸክም አይደለም። ከሥርዓት የወጡ፣ አባቶችን የዘለፉና በመቅደሱ ላይ ያመፁ እኩያን የጊዜ ጉዳይ እንጂ እንደ አርዮስና እንደ ይሁዳ መጨረሻቸው የውርደት መሆኑ አይቀሬ ነው። እኛ ግን ከእናት ቤተክርስቲያናችን፣ ከቅዱስ ሲኖዶሳችንና ከብፁዓን አባቶቻችን ጎን በሃይማኖት ጸንተን እንቆማለን።
የቤተክርስቲያን አምላክ ክብሯን ይጠብቅ!
እኩያንንና ተኩላዎችንም ከመንጋው ይለይልን!
👍14❤3
እንኳን ለልዳው ፀሐይ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!!
++++
(መ/ር ጌታቸው በቀለ እንደጻፉት)
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሰዓታት በተባለው መንፈሳዊ ድርሰቱ “ፀሐይ ዘልዳ፣ ኮከብ ዘልዳ፣ ዘልዳ ንጉሥ ነዓ ጊዮርጊስ- የልዳው ፀሐይ፤ የልዳው ኮከብ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ ና” በማለት ታላቅ ምስጋና ያቀረበለት ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘመነ ሰማዕታት ስለ እግዚአብሔር በመመስከሩ፣ በማስተማሩ፣ አምልኮተ ጣዖትን በማጥፋቱ ከንጉሡ ዱድያኖስና ሰባ ነገሥት እጅግ አሰቃቂ ዘግናኝ የሆኑ ፀዋትወ መከራዎች ተቀብሏል፡፡ ነገሥታቱ ሰማዕቱን ገደልነው ብለው ሥጋውንና አጥንቱን ፈጭተው ዐመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ ቢበትኑትም፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ዳግም አሥነሣው፡፡ ይህ የሆነው ጥር 18 ቀን ነው፡፡ ይህንንም ቀን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን “ዝርወተ ዐጽሙ” ስትል ሰማዕቱን አዘክራ ትውላለች፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡
“መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” በማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት በተናገረው ቃል መሠረት በሃይማኖት ምክንያት መከራ እየተቀበለና ስለ ክርስቶስ እየመሰከረ በግፍ የተገደለ ሰው ሰማዕት ተብሎ ይጠራል፡፡ ቃሉ ከግእዝ ወደ አማርኛ ሲተረጎም ሰማዕት ማለት ምስክር ማለት ነው፡፡ ይህ የቅድስናና የክብር ስም የሚገኘውም እንዲሁ በከንቱ ሳይሆን ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ከብዙ ተጋድሎና ፈተና በኋላ ነው፡፡ /ሐዋ ሥራ. ፩፥፰፤ ፳፪÷፳፮/፡፡ ከእነዚህ ሰማዕታት አንዱ በየዓመቱ የሰባት ዓመት ተጋድሎውና የዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በስሙ በታነጹ አብያተ ክርስቲያት ሁሉ በታላቅ ክብር የሚከበርለት የልዳው ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ግምባር ቀደም ሆኖ የሚጠቀስ ነው፡፡
“የልዳው ፀሐይ፣ የልዳው የምሥራቅ ኮከብ”
======== ቅዱስ ጊዮርጊስ ወላጅ አባቱ አንጣስዮስ (ዘሮንቶስ) የሚባል ሲሆን እናቱ ደግሞ ቴዎብስታ በመባል ትታወቃለች፡፡ የአባቱ አገር በዚያን ጊዜው አጠራር “ቀጰዶቅያ” የሚባል ሲሆን የእናቱ አገር ደግሞ ልዳ ተብሎ ይጠራል፡፡ ይህ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሰባት ዓመት ተጋድሎውን ፈጽሞ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ በተለየና ዘለዓለማዊ ዕረፍትን ባረፈ ጊዜ ሥጋው ያረፈው በዚሁ በልዳ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ጊዮርጊስ “የልዳው ፀሐይ፣ የልዳው የምሥራቅ ኮከብ” እየተባለ ይጠራል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሰዓታት በተባለው መንፈሳዊ ድርሰቱ “ፀሐይ ዘልዳ፣ ኮከብ ዘልዳ፣ ዘልዳ ንጉሥ ነዓ ጊዮርጊስ” በማለት የዘመረለትና ታላቅ ምስጋናም ያቀረበለት ይህንኑ መነሻ በማድረግ ነው፡፡ ትርጉሙም “የልዳው ፀሐይ፤ የልዳው ኮከብ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ ና” ማለት ነው፡፡
ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ የተወደለበት ዘመን ዘመነ ሰማዕታት ሲሆን ያ ዘመን ብዙ ክርስቲያኖች በመከራ የተፈተኑበትና ስለክርስትና ሃይማኖት ብዙ ዋጋ እየከፈሉ ሕይወታቸውን ለሞት የሰጡበት ዘመን ነበር፡፡ በዚያም ዘመን ያንን አገር የሚመራውና የሚያስተዳድረው “ዱድያኖስ” የሚባል ከሐዲና ጣዖት አምላኪ የሆነ ንጉሥ ነበር፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ አባት ዞሮንቶስ በዱድያኖስ ቤተ መንግሥት ታላቅ ሹመት ተሰጥቶት ሲያገለግል ከቆየ በኋላ ከዚህ ዓለም በሞት ስተለየና በዚያን ዘመንም አባት ሲሞት ልጁ በሥራው የመተካት መብት ስለነበረው የሃያ ዓመት ዕድሜ የነበረው ወጣቱ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስም በአባቱ ሹመት ተተክቶ ለመሥራት ወደ ንጉሡ በሔደ ጊዜ ንጉሥ ዱድያኖስ በቤተ መንግሥቱ ጣዖት አቁሞ ለጣዖት ሲሰግድና ሕዝቡንም ሁሉ እያስገደደ ለጣዖት እንዲሰግዱና ጣዖት እንዲያመልኩ ሲያደርግ በማግኘቱ ይህንን እኩይ ተግባር በመቃወም ገና በሃያ ዓመት ዕድሜው የሰማዕትነት ተጋድሎውን ጀመረ፡፡
የሰማዕቱ ተጋድሎ
=======
በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነትና በእግዚአብሔር ላይ ባለው የፀና እምነት መሠረትም የዚህ ዓለም ተድላና ደስታ ከንቱ መሆኑን በመገንዘብ ያለውን ሀብት ሁሉ ለድኆችና ለምስኪኖች በመስጠት ሹመቱንና ሽልማቱን በጠቅላላ የዚህን ዓለም ክብር ሁሉ በመናቅ ከንጉሡ ከዱድያኖስና ሰባ ነገሥት በመባል ከሚታወቁት ኃያላን ጋር ተጋድሎውን ቀጠለ፡፡ የዚህ ዓለም ከንቱ ነገር ሁሉ በእሱ ዘንድ ፈጽሞ የተናቀና የተጠላ ከመሆኑ የተነሣ ለሥጋዊ ሕይወቱም ሳይሳሳና ሳይፈራ በንጉሡ ፊት ቆሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን እውነተኛ ክርስቲያን መሆኑን እየገለጠና እየተናገረ ስለእውነተኛው አምላክ መመስከርና ማስተማርያ ይገኛል።
++++
(መ/ር ጌታቸው በቀለ እንደጻፉት)
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሰዓታት በተባለው መንፈሳዊ ድርሰቱ “ፀሐይ ዘልዳ፣ ኮከብ ዘልዳ፣ ዘልዳ ንጉሥ ነዓ ጊዮርጊስ- የልዳው ፀሐይ፤ የልዳው ኮከብ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ ና” በማለት ታላቅ ምስጋና ያቀረበለት ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘመነ ሰማዕታት ስለ እግዚአብሔር በመመስከሩ፣ በማስተማሩ፣ አምልኮተ ጣዖትን በማጥፋቱ ከንጉሡ ዱድያኖስና ሰባ ነገሥት እጅግ አሰቃቂ ዘግናኝ የሆኑ ፀዋትወ መከራዎች ተቀብሏል፡፡ ነገሥታቱ ሰማዕቱን ገደልነው ብለው ሥጋውንና አጥንቱን ፈጭተው ዐመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ ቢበትኑትም፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ዳግም አሥነሣው፡፡ ይህ የሆነው ጥር 18 ቀን ነው፡፡ ይህንንም ቀን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን “ዝርወተ ዐጽሙ” ስትል ሰማዕቱን አዘክራ ትውላለች፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡
“መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” በማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት በተናገረው ቃል መሠረት በሃይማኖት ምክንያት መከራ እየተቀበለና ስለ ክርስቶስ እየመሰከረ በግፍ የተገደለ ሰው ሰማዕት ተብሎ ይጠራል፡፡ ቃሉ ከግእዝ ወደ አማርኛ ሲተረጎም ሰማዕት ማለት ምስክር ማለት ነው፡፡ ይህ የቅድስናና የክብር ስም የሚገኘውም እንዲሁ በከንቱ ሳይሆን ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ከብዙ ተጋድሎና ፈተና በኋላ ነው፡፡ /ሐዋ ሥራ. ፩፥፰፤ ፳፪÷፳፮/፡፡ ከእነዚህ ሰማዕታት አንዱ በየዓመቱ የሰባት ዓመት ተጋድሎውና የዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በስሙ በታነጹ አብያተ ክርስቲያት ሁሉ በታላቅ ክብር የሚከበርለት የልዳው ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ግምባር ቀደም ሆኖ የሚጠቀስ ነው፡፡
“የልዳው ፀሐይ፣ የልዳው የምሥራቅ ኮከብ”
======== ቅዱስ ጊዮርጊስ ወላጅ አባቱ አንጣስዮስ (ዘሮንቶስ) የሚባል ሲሆን እናቱ ደግሞ ቴዎብስታ በመባል ትታወቃለች፡፡ የአባቱ አገር በዚያን ጊዜው አጠራር “ቀጰዶቅያ” የሚባል ሲሆን የእናቱ አገር ደግሞ ልዳ ተብሎ ይጠራል፡፡ ይህ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሰባት ዓመት ተጋድሎውን ፈጽሞ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ በተለየና ዘለዓለማዊ ዕረፍትን ባረፈ ጊዜ ሥጋው ያረፈው በዚሁ በልዳ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ጊዮርጊስ “የልዳው ፀሐይ፣ የልዳው የምሥራቅ ኮከብ” እየተባለ ይጠራል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሰዓታት በተባለው መንፈሳዊ ድርሰቱ “ፀሐይ ዘልዳ፣ ኮከብ ዘልዳ፣ ዘልዳ ንጉሥ ነዓ ጊዮርጊስ” በማለት የዘመረለትና ታላቅ ምስጋናም ያቀረበለት ይህንኑ መነሻ በማድረግ ነው፡፡ ትርጉሙም “የልዳው ፀሐይ፤ የልዳው ኮከብ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ ና” ማለት ነው፡፡
ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ የተወደለበት ዘመን ዘመነ ሰማዕታት ሲሆን ያ ዘመን ብዙ ክርስቲያኖች በመከራ የተፈተኑበትና ስለክርስትና ሃይማኖት ብዙ ዋጋ እየከፈሉ ሕይወታቸውን ለሞት የሰጡበት ዘመን ነበር፡፡ በዚያም ዘመን ያንን አገር የሚመራውና የሚያስተዳድረው “ዱድያኖስ” የሚባል ከሐዲና ጣዖት አምላኪ የሆነ ንጉሥ ነበር፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ አባት ዞሮንቶስ በዱድያኖስ ቤተ መንግሥት ታላቅ ሹመት ተሰጥቶት ሲያገለግል ከቆየ በኋላ ከዚህ ዓለም በሞት ስተለየና በዚያን ዘመንም አባት ሲሞት ልጁ በሥራው የመተካት መብት ስለነበረው የሃያ ዓመት ዕድሜ የነበረው ወጣቱ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስም በአባቱ ሹመት ተተክቶ ለመሥራት ወደ ንጉሡ በሔደ ጊዜ ንጉሥ ዱድያኖስ በቤተ መንግሥቱ ጣዖት አቁሞ ለጣዖት ሲሰግድና ሕዝቡንም ሁሉ እያስገደደ ለጣዖት እንዲሰግዱና ጣዖት እንዲያመልኩ ሲያደርግ በማግኘቱ ይህንን እኩይ ተግባር በመቃወም ገና በሃያ ዓመት ዕድሜው የሰማዕትነት ተጋድሎውን ጀመረ፡፡
የሰማዕቱ ተጋድሎ
=======
በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነትና በእግዚአብሔር ላይ ባለው የፀና እምነት መሠረትም የዚህ ዓለም ተድላና ደስታ ከንቱ መሆኑን በመገንዘብ ያለውን ሀብት ሁሉ ለድኆችና ለምስኪኖች በመስጠት ሹመቱንና ሽልማቱን በጠቅላላ የዚህን ዓለም ክብር ሁሉ በመናቅ ከንጉሡ ከዱድያኖስና ሰባ ነገሥት በመባል ከሚታወቁት ኃያላን ጋር ተጋድሎውን ቀጠለ፡፡ የዚህ ዓለም ከንቱ ነገር ሁሉ በእሱ ዘንድ ፈጽሞ የተናቀና የተጠላ ከመሆኑ የተነሣ ለሥጋዊ ሕይወቱም ሳይሳሳና ሳይፈራ በንጉሡ ፊት ቆሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን እውነተኛ ክርስቲያን መሆኑን እየገለጠና እየተናገረ ስለእውነተኛው አምላክ መመስከርና ማስተማርያ ይገኛል።
❤8
ንጉሡና የእሱ ተከታዮች የሚሰግዱለት ጣዖትም ምንም ምን ማድረግ የማይችል ደካማ ፍጡር መሆኑን በሚገባ ከአስረዳ በኋላ ሰማይና ምድርን፣ የሚታየውንና የማይታየውን ሁሉ የፈጠረውን እውነተኛውን አምላክ እንዲያመልኩና ለእሱም እንዲሰግዱ እያስተማረ የንጉሡን ሚስት ንግሥቲቱን ሳይቀር ሕዝቡን ሁሉ በማሳመን የሰማዕትነት ተግባሩን ቀጠለ፡፡ ከሐዲውና ጣዖት አምላኪው ዱድያኖስ በአምልኮ ጣዖት የፀና፣ እውነተኛውን አምላክ እግዚአብሔርንም የካደ ከመሆኑ የተነሣ እሱ ቃሉን ሰምቶ በእውነተኛው አምላክ ማመን ሲገባው በተቃራኒው ቅዱስ ጊዮርጊስ እሱ ለሚያመልከው ጣዖት ቢሰግድና በእሱም ጣዖት ቢያመልክ ከአባቱ የበለጠ ሹመትና ክብር እንደሚሰጠውና ከእሱም ቀጥሎ ባለው የመንግሥት ሥልጣን ላይ እንደሚያስቀምጠው ደጋግሞ ቃል በመግባት ያባብለው እንደነበር ስለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋድሎ በተጻፈው መጽሐፈ ገድል በሰፊው ተጽፎ ይገኛሉ፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን የእግዚአብሔርን እውነተኛ አምላክነት፣ ከሀላፊነቱንና ኃያልነቱን በሚገባ ያወቀ ከመሆኑም በላይ የዚህን ዓለም ከንቱነት ከልብ የተረዳ ስለሆነ የንጉሡ የዱድያኖስ ቃል አለታለለውም፣ ጊዜያዊ ሹመትና ሽልማትም አልማረከውም፡፡ እንዲያውም ሰባት ዓመት ሙሉ ተጋድሎውን በመቀጠል እጅግ አሰቃቂና ዘግናኝ የሆኑ ፀዋትወ መከራዎችን በመቀበል የኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ምስከር ሆኖአል፡፡ ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግ ብዙ አሕዛብን በኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አድርጓል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስም በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ፡፡ ቅዱሱንም እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን አሉት፡፡ በዚያን ጊዜ ጸለየ፤ እንዳሉትም አደረጋቸው፤ ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው በርካቶች በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንዱ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ፤ በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እንዲያነዱበት አደረገ፡፡ ከዚያም ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት፡፡ አቃጥለው፣ አሳርረው ሥጋውንና አጥንቱን ፈጩት፤ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረገፍ ድረስ አሰቃዩት፡፡ በዚህም ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፡፡ የሰማዕቱን ሥጋ አቃጥለው ፈጩት አመዱንም በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ላይ በተኑት “ደብረ ይድራስ” ማለት ምድረ በዳ የሆነ ቦታ ነው፡፡ ጌታችንም የሰማዕቱን ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው፡፡ ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ፡፡ በርካታ አሕዛብም ይህንን ታላቅ ተአምራት አይተው አምነዋል፡፡ በኋላም በሰማዕትነት አልፈዋል፡፡ ይህ የሆነው ጥር ፲፰ ቀን ነው ይህንንም ቀን “ዝርዎተ አጽሙ” ስትል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰማዕቱን አዘክራ ትውላለች፡፡ በስሙ በታነጹለት አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ታቦተ ሕጉ ውጥቶ በደማቅ ሥነ ሥርዐት ተከብሮ ይውላል፡፡
የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
======
ዋቤ መጻሕፍት፡-
✍️ መጽሐፍ ቅዱስ
✍️ ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
✍️ መጽሐፈ ሰዓታት
✍️ መጽሐፈ ስንክሳር
ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን የእግዚአብሔርን እውነተኛ አምላክነት፣ ከሀላፊነቱንና ኃያልነቱን በሚገባ ያወቀ ከመሆኑም በላይ የዚህን ዓለም ከንቱነት ከልብ የተረዳ ስለሆነ የንጉሡ የዱድያኖስ ቃል አለታለለውም፣ ጊዜያዊ ሹመትና ሽልማትም አልማረከውም፡፡ እንዲያውም ሰባት ዓመት ሙሉ ተጋድሎውን በመቀጠል እጅግ አሰቃቂና ዘግናኝ የሆኑ ፀዋትወ መከራዎችን በመቀበል የኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ምስከር ሆኖአል፡፡ ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግ ብዙ አሕዛብን በኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አድርጓል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስም በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ፡፡ ቅዱሱንም እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን አሉት፡፡ በዚያን ጊዜ ጸለየ፤ እንዳሉትም አደረጋቸው፤ ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው በርካቶች በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንዱ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ፤ በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እንዲያነዱበት አደረገ፡፡ ከዚያም ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት፡፡ አቃጥለው፣ አሳርረው ሥጋውንና አጥንቱን ፈጩት፤ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረገፍ ድረስ አሰቃዩት፡፡ በዚህም ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፡፡ የሰማዕቱን ሥጋ አቃጥለው ፈጩት አመዱንም በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ላይ በተኑት “ደብረ ይድራስ” ማለት ምድረ በዳ የሆነ ቦታ ነው፡፡ ጌታችንም የሰማዕቱን ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው፡፡ ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ፡፡ በርካታ አሕዛብም ይህንን ታላቅ ተአምራት አይተው አምነዋል፡፡ በኋላም በሰማዕትነት አልፈዋል፡፡ ይህ የሆነው ጥር ፲፰ ቀን ነው ይህንንም ቀን “ዝርዎተ አጽሙ” ስትል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰማዕቱን አዘክራ ትውላለች፡፡ በስሙ በታነጹለት አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ታቦተ ሕጉ ውጥቶ በደማቅ ሥነ ሥርዐት ተከብሮ ይውላል፡፡
የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
======
ዋቤ መጻሕፍት፡-
✍️ መጽሐፍ ቅዱስ
✍️ ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
✍️ መጽሐፈ ሰዓታት
✍️ መጽሐፈ ስንክሳር
❤11👍3👏3