Adebabay Media
4.46K subscribers
1.5K photos
58 videos
37 files
1.49K links
በወገንተኝነት፣ በጊዜአዊ ጥቅም እና አጋርነት ብቻ የሚደረግ ወደ አንድ ወገን ያጋደለ ጋዜጠኝነት ጥቅም እንደሌለው በመረዳት ዕውቀትና መረጃ ላይ የተመረኮዘ፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ፣ ሀገርንና ወገንን በመጥቀም ላይ የተመሠረተ ሁሉን አቀፍ ባለ ብዙ ቋንቋዎች ሚዲያ፤ ቤተሰባችን ስለሆኑ እናመሰግናለን። በFacebook/YouTube (@adebabaymedia) ይመልከቱን። www.adebabay.com
Download Telegram
ዓለም አቀፍ ጉባኤ
============
Time: Mar 29, 2025
** 12:00 PM Eastern Time (US and Canada)
** 17:00 CET (16:00 UK time).
------------
Join Zoom Meeting

https://us02web.zoom.us/j/87410937873?pwd=L7iJj7Bh36ZJvxJPSWM4deVTckLxBp.1

Meeting ID: 874 1093 7873
Passcode: 580214
መንፈሳዊ ጥሪ
==========
በዝርወት የርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን!
=======
** ቀን፡- እሑድ April 6, 2025 1PM ላይ

** አድራሻ:
11931 Tech Rd, Silver Spring, MD 20904
ኢየኀድግ ርእሶ ዘእንበለ ሰማዕት (የሐዋ. ሥራ 14፥17)
======
"He did not leave Himself without witness." (Acts 14:17)
ራሱን ያለ ምስክር አልተወም። (የሐዋ. ሥራ 14፥17)
=====
(ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)
እግዚአብሔር አምላካችን በየዘመናቱ ለራሱ ምስክሮች (ሰማዕታት) የሚሆኑ ምልክቶችን ይሰጠናል። የHarvard ዩኒቨርሲቲ ተማሪው ዲ/ን ምሕረት መልአኩ ከአንድ የፕ*ሮ*ቴ*ስ*ታ*ንት ሰባኪ ጋራ ያደረገው ክርክር፣ ያቀረበው ኦርቶዶክሳዊ መከራከሪያ፣ የቃላት አመራረጡ፣ ክህነታዊ እርጋታው (ስክነቱ) ኹሉ አስደማሚ ነው:: ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከሐዋርያነ አበው፣ ከትውፊት እየጠቀሰ በዓለም አስተሳሰብ የተሸቃቀጠውን ኢመጽሐፍ ቅዱሳዊ ስብከት ተገዳድሮታል።

ዲ/ን ምሕረትን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቅኹት የዛሬ 7 ዓመት ገደማ ስብከቱን በፌስቡክ አይቼ ነው። ከዚያም በዚያ የልጅነት ዕድሜው ያሳተማትን መጽሐፍ አግኝቼ አነበብኹ። ትልቅ ደስታ ተሰማኝ። "ኢየኀድግ ርእሶ ዘእንበለ ሰማዕት" ማለት ይህ ነው:: ዛሬ ትልቅ ወጣት፣ ያውም የተዋቂው MIT ተማሪ ነው። ከነዲ/ን Gorgorios Dejene ጋራ ያደረጉትንም የዩቲዩብ ውይይታቸውን በደስታ ተከታትያለሁ።

ስለነዚህ ልጆቻችን እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን። በዚህ በባዕድ ምድር ለቤተ ክርስቲያን ምሥክሮች ያደረጋቸው አምላክ የተመሠገነ ይኹን። ራሱን ያለ ምስክር አልተወምና። (የሐዋ. ሥራ 14፥17)

ክህነት ይባርክ!!!!
የቤተ ክርስቲያን ፌስቡክ ገጾች ኃላፊዎች ጥንቃቄ ጉድለትና መዘዙ
======
(ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ/Media of Addis Ababa Diocese ሰሞኑን የሚያጋራቸው ተገቢነት የሌላቸው ፎቶግራፎች ጉዳይ በሌሎች ብዙ የግለሰብ እና የድርጅት ገጾች ላይ የሚታይ ትልቅ ችግር ነው:: የማኅበራዊ ሚዲያ ጥንቃቄአችን የተጠና አለመሆኑን ያሳያል።

"ሃክ ተደርገናል" የሚል ምላሽ በቂ አይደለም።አድሚኖቹ መንካት የሌለባቸውን ሊንክ መንካት የለባቸውም። እንዲህ ያሉ official የቤተ ክርስቲያን ገጾችን manage የሚያደርጉ ባለሙያዎች ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል። አሁንም አንዳንድ የመፍትሔ ርምጃዎችን ቢወስዱ መልካም ነው። ያየራቸውን አንዳንድ አስቀያሚ ሊንኮች አይቼ ለማን ልንገር እያልኩ ነበር። ለጊዜው Search አድርጌ ያገኘኹት መፍትሔ የሚከተለው ነው።
=======
If your Facebook page is displaying inappropriate or unwanted images, there are several steps you can take to address the issue and regain control over the content. Here’s a straightforward guide to help you resolve this:

1. Report the Images: If the images are posted by others or appearing in your feed, report them to Facebook. On mobile, tap the three dots (...) in the top right corner of the post, select "Report," and follow the prompts to flag it as inappropriate (e.g., nudity, violence, or spam). Facebook will review it and remove it if it violates their Community Standards.

2. Hide Unwanted Posts: If you can’t immediately remove the images (e.g., they’re in your feed or tagged posts), hide them. Tap the three dots (...) and choose "Hide Post" to remove it from your view. This won’t delete it but will reduce its visibility to you.

3. Adjust Your Feed Preferences: To prevent similar content from appearing, tweak your news feed settings. On mobile, tap the three horizontal lines (menu), go to "Settings & Privacy" > "Settings" > "News Feed Preferences," and select "Manage Your Feed." Here, you can prioritize content you want to see and reduce unwanted categories like "Sensitive Content" by selecting "Reduce."

4. Review Tagged Posts: If the bad images are tagged posts on your page, enable tag review. Go to "Settings & Privacy" > "Settings" > "Profile and Tagging," and turn on "Review posts you’re tagged in before they appear on your profile." This lets you approve or reject tagged content before it’s public.

5. Block Problematic Accounts: If specific users or pages are posting the images, block them. Go to their profile, tap the three dots (...), and select "Block." This stops them from interacting with your page or tagging you.

6. Check for Hacked or Compromised Account: If the images are being posted without your consent, your account might be compromised. Go to "Settings & Privacy" > "Settings" > "Security and Login" and check "Where You’re Logged In." Log out of unfamiliar devices and change your password immediately.

7. Manage Ad Preferences: If the images are from ads, adjust your ad settings. Go to "Settings & Privacy" > "Settings" > "Ad Preferences," and review "Ad Topics." Remove topics related to inappropriate content and report any offending ads by clicking the three dots (...) on the ad and selecting "Report Ad."

8. Clean Up Your Page: If the images are on your own page (e.g., posted by mistake or by a hacked account), delete them manually. Go to the post, tap the three dots (...), and select "Delete." For multiple posts, do this for each one.

9. Contact Facebook Support: If the problem persists (e.g., you can’t remove the content or it keeps reappearing), reach out to Facebook. Go to the "Help Center" via the menu, search for your issue, and use the "Report a Problem" feature to explain the situation.

10. Secure Your Account: Prevent future issues by enabling two-factor authentication. Go to "Settings & Privacy" > "Settings" > "Security and Login" > "Two-Factor Authentication" and set it up. This adds an extra layer of protection.

By taking these steps, you should be able to remove the bad images and reduce the chances of them showing up again. If it’s an ongoing issue tied to specific users or spam, stay proactive by monitoring your page and reporting violations as they occur. Let me know if you need help with any of these steps!
"America First" VS "ብሔረሰቤ FIRST" እና ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች
======
ዛሬ ምሽት (8 PM በዲሲ ሰዓት) ጥሩ ውይይት ይኖረናል። የውይይት ጠረጴዛችን ተሳታፊ ጠበቃ Teklemichael አበበ ነው:: የዓለም ፖለቲካ ከሉላዊነት ወደ ድንበርተኝነት (ሀገራዊ አርበኝነት) እየተለወጠ ባለበት በዚህ ዘመን የሀገራችን ሁኔታ ደግሞ ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል:: በዚህ ወቅት ኮስተር ያለውን አጀንዳ ማንሣቱ ግድ ነው፡፡

https://www.youtube.com/live/I_NcZ2i8tDk?si=J6AvobO9gWAEWvOn
ከበሮ፣ ጸናጽል፣ መቋሚያ በቤተ ክርስቲያን ባለቤትነት በሕግ ተመዝገቡ
========
{አደባባይ ሚዲያ):- የቅድስት ቤተ ክርስቲያ የዜማ ንዋያተ ቅዱሳት እና ከ10 በላይ ቅዱሳት መጻሕፍት አእምሯዊ ንብረት ሆነው መመዝገባቸው ን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግኑኝነት መምሪያ ዘገባ ያስረዳል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዜማ ንዋያተ ቅዱሳት የሆኑት ከበሮ፣ ጸናጽል፣ መቋሚያና እንዲሁም ከ10 በላይ ቅዱሳት መጻሕፍት በኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በቅጂና ተዛማች መብቶች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡

ሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም የዜማ ንዋያተ ቅዱሳቱ እና ቅዱሳት መጻሕፍቱ ተመዝግበው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አእምሯዊ ንብረት መሆናቸው ከባለሥጣኑ በወጣው ደብዳቤ ተረጋግጧል።

የመምሪያው ኃላፊ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ በአእምሯዊ ንብረት ዐቢይ ኮሚቴ አማካኝነት በርካታ ንብረቶች ተመዝግበው ዕውቅና አግኝተዋል።
ፕሮቴስታንቶች ለምን ከበሮ፣ ጽናጽልና መቋሚያን ለመዝሙሮቻቸው ማጀቢያነት መጠቀም አይችሉም ?
==============
(ክፍል አንድ Melaku Berhanu )
ጋዜጠኛ መላኩ ብርሃኑ እንደጻፈው
+++++
የከበሮ፣ ጽናጽል እና መቋሚያ የዐዕምሮ ንብረት ምዝገባ ጉዳይ በአንዳንድ የፕሮቴስታንት እምነት ገጾች በብዙ አወዛጋቢ ሃሳቦች እየተንሸራሸሩበት፣ አንዳንድም እልህ መሰል ደስ የማይሉ አስተያየቶች እየተሰነዘሩበት መሆኑን እያስተዋልኩ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በቂና አጥጋቢ ማብራሪያ እስኪሰጡበት ድረስ እኔ በግሌ በጥቂት ከማውቀው፣ በብዙ ደግሞ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ገጾችን አስሼ ካገኘሁት መረጃ ላይ ተመርኩዤ በጉዳዩ ላይ ሰፋ አድርጌ ልጽፍበት ወድጃለሁ፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሄርን የምታመሰግንበትና የምታወድስበት የዜማ ዕቃዎቿ ሁሉ በተምሳሌትነት የተሰሩና ንድፋቸውም ከመጽሃፍ ቅዱስ ታሪኮች ጋር የተዛመደ ትርጉም የያዙ መሆናቸውን ስንማር አድገናል፡፡ ዜማው፣ አቋቋሙ፣ ወረቡ፣ ሽብሸባው ሁሉ በዘፈቀደ የተሰራና እንደዘፈን ኬርዮግራፊ የሚለዋወጥ አይደለም፡፡ ቋሚ ነው፡፡ ለዜማና አቋቋም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ማህሌታይ ምስጋና ይሁንና እያንዳንዱ ኦርቶዶክሳዊ የምስጋናና ውዳሴ ዜማና ከዜማው ጋር ያለ አቋቋም ሁሉ ለቤተክርስቲያናችን ተሰርተው የተሰጡ ንብረቶች ናቸው፡፡ ቤተክርስቲያን በያሬዳዊ ዜማዋ የዜማ ሊቆች፣ በአቋቋምም የአቋቋም ሊቆች ያሏት ፣ በዘርፉም ለአገልጋዮቿ ትምህርት የምትሰጥ ጥንታዊ የዕምነት ተቋም ናት፡፡

እነዚህ ሃብቶች እንደሃገር የሃገር ቅርሶች፣ እንደራሷ ደግሞ በዓለምአቀፍ መድረክ ልዩ፣ ብርቅ እና ክቡር ሆና እንድትቃጥል ያደረጓት ሃብቶቿ መሆናቸው እንዳይዘነጋ፡፡ እነዚህ ዜማዎች ሲዜሙ፣ ወረብ ሲወረብ መዝሙር ሲዘመር፣ ያሬዳዊ ቅርጹን ሳይለቅ በዜማ ዕቃዎች ታጅቦ ይቀርባል፡፡አሁን ጥያቄ እየተነሳ ያለው በዜማ እቃዎቹ ላይ ነው፡፡ ቤተክርስቲያኒቱ ደግሞ የኔ ነው ብላለች፡፡ በንብረትነት አስመዝግባለች፡፡

ቤተክርስቲያን በገናንም ይሁን ጽናጽልን፣ ከበሮንም ይሁን መቋሚያን ለመዝሙራቷና ለወረቧ እንዲሁም ለዜማዋ ማጀቢያነት ስትጠቀምባቸው መጽሃፍ ቅዱሳዊ አድርጋ ነው፡፡ ለዚህም በመጽሀፍ ቅዱስ የተጠቀሱትን በገና፣ ጽናጽልም ይሁን ከበሮ በራሷ አስተምህሮ ልክ ሰፍታ ፣ ንድፍ አውጥታና አምርታ ስትጠቀም ትናንትን ሳይሆን ሺህ ዘመናትን ተሻግራለች፡፡

አሁን በአንዳንድ ፕሮቴስታንቶች ዘንድ የተነሳው አቧራ “ቤተክርስቲያኒቱ በዐዕምሮ ንብረትነት አስመዘገብኩት የምትላቸው ጸናጽልና ከበሮ መጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ስማቸው ተጠቅሷል፡፡ስለዚህ እኛም መጽሃፍ ቅዱሳዊ ስለሆነ የመጠቀም መብት አለን” የሚል ካለማወቅ ወይም እያወቁ ከማጥፋት የመነሸ ነው የሚል ምልከታ አለኝ፡፡

በርግጥ ከዚህ ቀደም የተዋህዶን የዜማ ዕቃዎች “የጣዖት ማምለኪያ” ብለው የሚያጣጥሉ ፕሮቴስታንቶች ዛሬ ድንገት ተነስተው “የዜማ እቃዎቹ መጽሃፍ ቅዱሳዊ ናቸው” ወደሚል ልብ መግዛት መሸጋገራቸው እጅግ በጣም ደስ ይላል፡፡ ጊዜ የማያሳየን የለም፡፡ በነካ እጃቸው ደግሞ ጣዖት እያሉ የሚሳለቁበትን ታቦተ ህጉም መጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ መኖሩን መስክረው አክብረውት አሳይተውን ልብ እንዲገዙ እንጠብቃለን፡፡
ለማንኛውም ጉዳዩን በነጥብ በነጥብ እንየው፡፡

አንደኛ !
======
የኢትዮጵያ ዐዕምሮ ንብረት ባለስልጣን አሰራሩን ካልቀየረ በቀር እኔ እስከማውቀው አንድን የዐዕምሮ ንብረት የሆነ ቁስ ንድፍ (ዲዛይን) የቅጂና ተዛማጅ የዐዕምሮ መብቶች መዝገብ ላይ ከመመዝገቡ በፊት በአሰራሩ መሰረት ጠያቂው አካል ንድፉን እንዲያቀርብ ያዝና ያንን ንድፍ ‘ጠያቂው አካል ይህ ንድፍ የኔ ብቸኛ ዐዕምሮአዊ ንብረት ነው ስላለ ተቃዋሚ ካለ ይቅረብ’ ብሎ በጋዜጣ ላይ ያትመዋል፡፡ ተቃዋሚ እስኪመጣ ድረስ ለሶስት ወራት ይጠብቃል፡፡ከዚያ በኋላ ነው በዐዕምሮ ንብረትነት የሚመዘግበውና የምስክር ወረቀት የሚሰጠው፡፡ በዚህ 90 ቀን ጊዜ ውስጥ “አንድም የእምነት ተቋም እንዴት የኔ ነው ብሎ እንዴት ተቃውሞ አላስገባም?” ብዬ ብጠይቅ መልስ ያለው ሰው የለም፡፡ ምዝገባው እንግዲህ ያለምንም ‘ንድፉ የኔ ነው’ ባይ ተቃውሞ የተካሄደ ነው፡፡

ሁለተኛ !
======
እንደዜማ እቃነት በገና፣ ከበሮ፡ ጽናጽል፣ እምቢልታ በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሰዋል፡፡ በነዚህም “እግዚአብሄርን ዘምሩለት አመስግኑትም” ተብሎ ተጽፏል ፡፡ ይህ ልክ ነው፡፡ ነገር ግን የትኛው አይነት ከበሮ? የትኛው አይነት ጽናጽል ወዘተ የሚል ማብራሪያ ወይም የዲዛይኑ ምስል መግለጫ ግን እስከማውቀው ድረስ በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ያለ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ የመጽሃፉን ስያሜ ወስዶ፣ የተሰየመውን በምናብ ፈጥሮ፣ በራስ መንገድ አምርቶ መጠቀም ሊያስፈልግ ነው ማለት ነው፡፡

ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እነዚህን የዜማ ዕቃዎች ከቃሉ ፈቀቅ በማትልበት ቅዱስ መጽሃፍ ላይ ተመርኩዛ ‘በዚህ አመስግኑ’ ተብላ በታዘዘችው መሰረት ንድፉን ሰርታና በንድፉ መሰረት ዕቃውን አምርታ “ከበሮ፣ ጽናጽል፣ በገና” ብላ ሰይማለች፡፡ ይህንን የዜማ ዕቃ ስትጠቀም በክፍል ሁለት ጽሁፌ እንደምናየው ስሙን ብቻ ሳይሆን ንድፉን ሁሉ በትርጉም አንጻ፣ ለእያንዳንዱ የንድፉ ገጽ ጥልቅ ትንታኔ ሰጥታ ጭምር ነው፡፡ ይኼ እንግዲህ የሺህ አመታት እድሜ ያለው፣ በስርዓቱ በቤተክርስቲያኒቱ እንደአንድ ዕውቀት የተመዘገበ፣ የማይቀየር፣ ቋሚ ነገር ነው ማለት ነው፡፡ በዚህ አግባብ ስንረዳው ቤተክርስቲያኒቱ የተጠቀሱትን የዜማ ዕቃዎች ስም ብቻ ነው የወሰደችው፡፡ ሌላውን በራሷ ትርጉም ሰጥታ ፣ የራሷን የዜማ ዕቃ ነው የሰራችው ማለት ነው፡፡እንዲህ ከሆነ ንድፉ የግል ንብረቷ መሆኑን ያጠነክርልናል፡፡

“ከበሮና ጽናጽል መጽሃፍ ቅዱሳዊ ስለሆነ የኛም ጭምር ነው” የሚሉ ፕሮቴስታንቶች አነድ መበት አላቸው፡፡ ተዋህዶ ከምትጠቀምበት ከበሮና ጽናጽል እንዲሁም በገና የተለየ ንድፍ ያለውን ከቻሉም የራሳቸውን አይነት ንድፍ ሰርተው አምርተው የመጠቀም መብታቸውን የሚከለክል የለም፡፡ በመሰረቱ ከበሮ እኮ አዝማሪም የሚደበድበው፣ታምቡር መሳይም፣ አታሞ መሳይም፣ ጠፍጣፋና ሰፊም በየዓይነቱ ተሰርቶ ለዘፈን የሚውል ከበሮ አለ፡፡ቤተክርስቲያን የኔ ነው ያለችው ይህንን አይደለም፡፡ ጽናጽልም ቢሆን የርሱ ዘር የሆነ ቻክቻክ፣ ሼከር ፣ ማራካስ ወዘተ የሚባል የዘፈን ማጀቢያ ጽናጽል አለ፡፡ በገናም ቢሆን ቦሎን፣ ፔዳል፣ ቼልቲክ፣ ቻንግ ወዘተ የሚባል የበገና (ሃርፕ) ዘር በየሃገሩ አለ፡፡

ከላይ የጠቀስኳቸው በሙሉ ዘፈን የሚታጀብባቸው መሳሪያዎች ናቸው፡፡ ማንም ቢሆን ልክ እንደኪቦርድ፣ ጃስ እና ድራም እነዚህን ከወደደዳቸው ሊጠቀምባቸው መብቱ ነው፡፡ መብቱ ያልሆነው ግን ቤተክርስቲያኒቱ የራሷ የሆነውንና ራሷ የሰራችውን የዜማ ዕቃዋን ነው፡፡ይህ የዜማ ዕቃዎች ደግሞ ከዕቃነታቸውም በላይ ለቤተክርስቲያኒቱ ንዋየ ቅዱሳን ጭምር ናቸው፡፡ እንኳን ተመዝግቦና ባይመዘገብም የገባው ዐዕምሮ ይህንን ልንጠቅ፣ መዋል ከሚገባቸው ቦታና ሁኔታ በተለየ አለአግባብ እያዋለ ልጠቀምበት ቢል የጤና አይደለም፡፡ እየተደረገ ያለው ነገር ይሄ ስለሆነ ነው እኮ ህጋዊ ለማድረግ ወደማስመዝገቡ የተሄደው፡፡ አሁን እንግዲህ በህግ ቋንቋ ካወራን የሌላን ንብረት የኔ ነው ብሎ መናደድ ይቻል ይሆናል እንጂ መጠቀም ግን አይቻልም ማለት ነው፡፡ አራት ነጥብ!!
ይህ ከሆነ ዘንዳ የማያውቁ ያውቁ ዘንድ ፣ትርጉሙንም አውቀውም ይጠነቀቁ ዘንድ፣ አውቀውም ያከብሩት ዘንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምትጠቀምባቸው የዜማ ዕቃዎች (ለዚህ ጽሁፍ ከበሮው፣ጽናጽሉና የዜማ ዕቃ ባይሆንም በራሱ ከዜማ ጋር ተሰናስሎ አቋቋምን የሚያጅብ ዕቃ በመሆኑ መቋሚያውም ጭምር ) ….የተሰሩበት ንድፍና ቅርጽ ትርጉም ምን እንደሆነ እንይ፡፡

(እንዳይረዝምባችሁ በክፍል ሁለት ፖስት እንገናኝ? )
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሰሙነ ሕማማት ስግደት፤ Prostrations at @Holyweek #GoodFriday
"ጕልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል" (ትንቢተ ኢሳይያስ 45፥23)
** "That to Me every knee shall bow" (Isaiah 45:23)
=====
© Ethiopian Orthodox Tewahido Church Holy Week video