Yop Poem ️
6.53K subscribers
114 photos
9 videos
25 files
61 links
፨Yop Poem
አዳዲስ እና የቆዩ ግጥሞችና ወጎችን በቀላሉ ያገኙበታል። 🤲
እርስዎም የግጥም ተሰጥዖ ካልዎት መልቀቅ ይችላሉ።👐
Our main channale :- @Utophiainfo

ቻናላችንን #share ያድርጉ👍

for promo & cross 👉 @Yared642
Download Telegram
Forwarded from ❤Ⓢⓔⓛⓘⓝⓐ🥰
Forwarded from ❤Ⓢⓔⓛⓘⓝⓐ🥰
ሊዘጉብኝ ሲታገሉ ለማመንመን የኔን
                  መክሊት
በቀን ፀሀይ ያበረቱኝ በሩን ገፉ ያው
                   በለሊት
  ፍሙን እሳት አመድ ሊያሹ ወዳጅ
        መስለው ሲጠጋጉኝ
በድን አርገው ለመጣሉን የዋሁ እኔ
               መች አወኩኝ !

ግን ባነንኩኝ
ሊሰብሩኝ ሲል ደነደንኩኝ
ማን አለው ብለው በድቅድቅ ሲርቁኝ
            ጋኑን ከርችመው
ከፍቶታል የልቤን መስኮት እምነትን ከስሬ
                  አክርመው !

@Yoppoem
#code01

1500
Only 1000 birrr
Cargo suri & T-shirt

Inbox
@Yared642
አምላክን አመስግን
       

በምግብ እጦት ቢገረጣ ፊትህ
ልክ እንደአውሬ ሰው ሁሉ ቢሸሽህ
ቤተሰቤ ያልከው እንደባዳ ቢያይ
የልብ ጓደኛ ቢሆንም ገዳይ

የለበስከው ልብስህ ከብርድ ባያድንም
የምቆጥረው ገንዘብ ከኪስህ ባይኖርም
ምትመኘው ነገር ሆኖቢቀር ቅዠት
ያፈቀርካት ላንተ ክብር ባይኖራት

ሞላውትም ያልከው ሁሌም ቢጎልብ
በጎ ያልከው ነገር ክፋ ቢመዝብ
እጅ ስትዘረጋ ሰጪ ባታገኝም
የሰጠከው ሁሉ ምላሽ ባይሰጥህም

ጊዜ ያንተ ጠላት ሆኖ ቢዋጋህ
አምላክ ነው ብለህ አትዘን በድልህ
ይቺን እንድታነብ እድል የሰጠህን
ጎንበስ በልና አምላክን አመስግን

              ተ መ ስ ገ
n

@Yoppoem
ግጥም ልፃፍልሽ🤗


ሹመት ቀባብቼ
ከነገስታት እኩል ዙፋን ባልሰጥሽም
ከአየር ጋር ተንፍሼሽ
ሁሉምጋ ማገኝሽ ነፍስ ባላረግሽም

ኮከብ ባልሰርቅልሽ
ጨረቃ ባላገኝ ምታስሪው ከአንገትሽ
ከአራዊት ታግዬ
የዱር ፍሬ ባለቅም ጠብ የሚል ከአንጀትሽ

እሳት ባልጨብጥም ባህር ባልከፍልልሽ
ፍቀጅልኝና
መውደዴን የሚገልፅ ግጥም ልፃፍልሽ!

እንደሰው ወደድኩሽ እንደህፃን ሳሳሁ
ሳቅሽን ስስቀው በልክሽ ተሰፋሁ🙈

እንደልቤ አፈቀርኩ እንደጅል አሳቅሽኝ
አንድ ጊዜ ባሰብኩሽ ደጋግመሽ ናፈቅሽኝ🥹

ቤቴን አደማምቂ ነይ ግጥም ሁኝልኝ
ነፍሴን አሳምሪ ነይ ዜማ ሙይልኝ
በቆንጆ ንግስት ስር ዘመኔን ምሪልኝ😍

ከቀለም አ'ብሬ ይሄንን መልክሽን
       ከንፁህ ሸራ ላይ ችየ እንኳን ባልስልሽ
እስኪ ምንአለበት
ስለእዚህ ውብ ሳቅሽ ግጥሞ ብፅፍልሽ

ለሰጠሽኝ ደስታ ወጥቼ ባልፎክር
አሁን ምናለበት
በጠያይም ቃላት ስንኝ ብደረድር

ለዘመኔ ድምቀት
ለሰበብነትሽ ሻማ ባላበራ
ልክ አይደለሁም ወይ
ለምስክርነት ቃላትን ብዘራ

ይመስክሩ ሁሉም
ኮከብ ከላይ ሆኖ አበባ ከመሬት
አላየንም ብለው
ያንቺ አይነት ፍቅር ሴት

የጧት ፀሀይ እዪ ታምራለች እንዳንቺ
ለመልካም ምኞቴ እቺን ግጥም እንቺ😘

          (እንኳንም ወለዱሽ😍)
@Yoppoem
ምጨነቅ ይመስልሻል?

አንድ አሮጌ የአፍሪካ መሪ ሞተ ቢሉ ሞቱን ?
ህዝብ ግልብጥ ቢል ትቶ ያደረገውን ?
ከንፈሬን መጥጬ  ይመስልሻል ማዝን?

አንድ የአፍሪካ መሪ ከወንበር ተቀምጦ ስላመሼና
አገሩም ስርአቱም አስረጅቶ አረፈደና
ቂጡ  ስለተላ ሱፉ እንደላላ ከዛው እንደሸና

(ማስብ ይመስልሻል)..አቦ ጉዳዬ😏....

ደሞስ መሪው ሁሉ
የእንግሊዝ ቶክሲዶን መነፀር ሰክቶ
አበባ ቢታቀፍ ከአስክሬኑ ታይቶ
ስለተነሳ...የሚዲያ ፎቶ

(..ምደነቅ.. ይመስልሻል😏 )

ፓርላማ ላይ ቢሰበሰቡ...
ዝግ ምክክር በአዋጅ ቢቃለቡ ፣
እዛው ተኝተው ሲጨበጨብ ነቅተው ስላጨበጨቡ ።
ዜና ላይ ወጠው ሀይለ ቃል ስላረበረቡ ፣
ይመስልሻል የኔ ልብ ማሰቡ ?

አይደለም እናቴ
የኔ ጭንቀት ሀዘን ነው የኔ ዕንባ አንታርቲካ
በውስጥ ሀዘን ሞልቶ በበርሃ የተለካ

የኔ ጭንቀት...
አንዲት እናት  አርግዛ  ሳትገደል
በሰላም ማዬት ነው የአራስ ጨቅላን ገድል

የኔ መደነቅ የኔ ይላቅ...
ሰው መንገስ አቁሞ መለኮታዊ ቢላክ
በምዕናብ መዳከር በህልም ሰላም ነበር የኔ  ስላቅ ¡?

ወከባ ስለበዛ ሱፍ የለበሰ አዋቂ ቢመስልም
ባታውቂኝ እንኳ ስለብልጭልጭ ሀገር ምጨነቅ አልመስልም
'
'
አቦ ጉዳያቸው

@Yoppoem
'ለምን አልፈጠርክም.. ?'

(ኤፍሬም ስዩም)

ሳይደምን ሳይዘንብ ሳይጨልም ሳይነጋ ፤
ምድርና አርያምን ቀድሞ ሳትዘረጋ ፤
ፊተኛው ኋለኛው አልፋና ኦሜጋ ፤
እንዴት ነበር ኑሮህ ስፍራህስ ምኑጋ ?
ምንት ሳይኖር በፊት ኢምንት እያለ ፤
ያሁኑ ዙፋንህ ኪሩቤል ከሌለ ፤
ያኔ ያንተ ሀገር ከየት ነበር ያለ ?
ሀገርህ እንዳልል ያኔ ሀገር የለም ፤
ምንም ሳይኖር በፊት ስትኖር በምንም ፤
በእግዚአብሔርነትህ እግዜር ከሌለብህ ፤
ሁሉንም አዋቂ አንተ ብቻ ከሆንህ ፤
ስንት ዘመን ሆነህ ሆነህ ከተገኘህ ?
ፍጥረትስ ነበረ ከመፍጠርህ በፊት ?
ቀድመው የተሰሩ ከሰው ከመላዕክት ?
ካልነበረም ፍጥረት ፤
የዘመናት አምላክ የዘመናት ንጉስ ጥያቄዬን መልስ ፤
ለምን አልፈጠርክም እስክትፈጥር ድረስ ?
.



@Yoppoem
ፍቃዱ ግርማ

    አያድርስ ከቶ

እማታገኝውን ሺህ ግዜ መናፈቅ
ለማይሆነው ነገር ሺህ ግዜ መጨነቅ
እራስክን ከማጣት ምንም አታተርፍም
ዝብርቅርቅ ባለበት በዚህ ከንቱ አለም
አይጣልብህ እንጂ አያድርስ ከቶ
በዚች አለም ኑሮ ማንስ ያቃል ረክቶ ። ?
  
        ማንም

@Yoppoem
Messages in this channel will no longer be automatically deleted
Asmarino
Dawit Tsige
❤️❤️❤️
@Yoppoem
ማያልፍ የመሰለኝ ዳምኖ ህይዎቴ
ባዘነብኩት እንባ ታጥቦ ማንነቴ
ግርዶሹ በርትቶ ነገየን ጋርዶብኝ
ፍፁም አንዳልጓጓ ህመም በርትቶብኝ
ዛሬ ነገ እያልኩኝ ሞቴን ሲጠባበቅ
ህመሜን ሳዳምጥ ስሜቶቼን ሳረቅ
.
.
.
         መኖር ማለት ስቃይ
         መኖር ምለት ህመም
         መኖር ማለት ጭንቀት
         መኖር ማለት ድካም....

ወደ ተስፋ መንደር እልፍ ጊዜ ባመራ
የ እድሌን ልሻማ ከ እኩዮቼ ጋራ
ብፈልግ... ብጠብቅ ድርሻ የለኝ ሁኖ
ጠብታ እንኳን ሳይቀር ከ እኔነቴ ተኖ
ፀሐይ የለኝ ሁና ሕይዎቴ ዳምኖ
.
.
.
       ትላንት በመኖሬ ተስፋ እንኳን ሳይኖረኝ
       ምንም ያህል ባዝን የሚያልፍ ባይመስለኝ
       ቀን እየቆጠረ ቀን እየጨመረ
       የደመናው ጥቁረት መጠኑ ቀንሶ
       የስቃይ ዉርጅብኝ ከነበረው አንሶ
       ከ ሕይወቴ ጠፋ ቀስ በቀስ ጨርሶ...
.
.
.
የ ፀሐይ ዉበቷ
የፀሐይ ድምቀቷ
የዉበት ፍካቷ
ዛሬ ላይ ብሸፈን
ደመናው ሲገፈፍ ወደጎን ሲበተን....
.
.
.
       ህመም ብርድ ሁኖ ያገረጣው ትናንት
       ተንፏቆ እየዳሀ ዛሬን በመጠጋት
       አንድ ቀን ልጨምር ብዬ በመኖሬ
       ተስፋ ፀሐይ ሁኖ ከች አለልኝ ዛሬ!!
           
           @Yoppoem
አባቶች እናቶች
በፍቅር ተጋግዘው ፣ ያቆሙልን እውነት
በዘመን ጠልሽቶ...
ለእኛ ለልጆች ፣ ይመስለናል ተረት፡፡
።።።።።።
የኛ ትልቅ ችግር ፣ የኛ ትልቅ ህመም
"ተረት ተረት"ሲባል
መሰረት ሳንይዝ
"የመሰረት" ብሎ ፣" እሺ" እያሉ ማዝገም፡፡
።።።።።።፣
ተረት ተረት
"የመሰረት"
አንድ ሀገር ነበረች
"እሺ"
እምነትን ከፍቅር ፣ ገምዳ ያስተማረች፡፡
"እሺ"
አናም በዚች ሀገር...
ሙስሊሞች በእምነት ፣ መስጅድ ሲገነቡ
ክርስቲያኖች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ምሶሶ ሲያቀርቡ፡፡
"እሺ"
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም በዚች ሀገር...
ክርስቲያኖች በምነት ፣ ቤተስኪያን ሲያንፁ
ሙስሊሞች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ጉልላት ሲቀርፁ፡፡
"እሺ"
እናም በዚ መልኩ ፣ ሲኖሩ ሰኖሩ
እንደተዋደዱ እንደተፋቀሩ
እንደተጋገዙ እንደተባበሩ
መሰረት እንድናይ...
አንዋር ከራጉኤል ፣ ተጎራብተው ቀሩ
"እሺ"
"እሺ" ማለት ጥሩ
መሰረት ሳይዙ ...
የመሰረት ብሎ ፣ መኖር ነው ችግሩ!!!
።።።።።

By Belay Bekele Weya

@Yoppoem