الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
22.2K subscribers
386 photos
18 videos
8 files
919 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
❥:::::::::::ፍቅር ማለት:::::::::::::❥

ፍቅር ማለት የአመታት ብዛት
አይደለም። አንዳንዴ አንድ ሠዉ እንደጋጣሚ ህይወትህ ዉስጥ ይገባል.

☞በዉስን ጊዜዎች ዉስጥ ልብህን ይገዘዋል የልብህ ንጉስ ይሆናል።

☞ከሱ በላይ መኖር አልችልም እስክትል ድርስ ለህይወትህ አላስፈላጊ ሁኖ ታገኘዉአለህ

#ፍቅር_ማለት_የልብ_መገናኘት_እንጂ
#የእድሜ ብዛት አይደለም..👌

❥ሀያት ቢንት ከድር ❥

💍:::::::::::::ቴሌግራማችን::::::::::::::💍

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8pkvHISwAMj2w
“ማንኛውም ሰው በህይወታችሁ ገብቶ ምን ያህል እንደሚያፈቅራችሁ ሊነግራችሁ ይችላል፤ነገር ግን አንድ ልዩ ሰው ብቻ ነው አብሮ እየኖረ ፍቅርን የሚያሳያችሁ።”

#ፍቅር_ያለ_ኒካ_የለውም_በረካ


የቴሌግራም ቻናላችን #ሼር ያድርጉ

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8pkvHISwAMj2w
👌ኢማን ያላት ሴት

ለፍቅር እንጂ ለብር አትገዛም👌

#ፍቅር_በሀላል እንጂ የለም 🚫

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8pkvHISwAMj2w


የ You Tube 👇 አድራሻችን #Subscribe ያድርጉ👇👇

https://youtu.be/FWKerxTPxnQ
🚫::::::::::ፍቅረኛ::::::::::🚫

#ፍቅረኛ በሚል የሸይጣን እስር ቤት የገባ ሰው በዚና ይፈተናል።

☞ረሱል ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም
አይን ዝሙት ይሰራል የማለታቸው ሚስጥር በአይን የሀራም እይታ ሸይጣን ለዚና ስለሚያነሳሳ የአይን ሀራም ላይ ያረፈች እይታ እንደ ዚና ተቆጥራለች

አላህ ሀላል ያላደረገልንን እንስት ምን ያክል ነው በሀራም ያወራናት ምን ያክል ነው ስቅርቅር ድምፇን በስልካችን ያዳመጥነው ሌላም ሌላም

#ፍቅር የአላህን ትእዛዝ እየፈፀም በመኖር አላህ በሁለት ተጣማሪዎች መካከል የሚያኖረው የተአምሩ ውጤት ነው

በሀራም የቀረብካት ሴት አላህ ላንተ የመረጠልክ ሴት ስላልሆነች ተዋት አላህን አታሳምፃት

ነገ #የቂያም ቀን አላህ ፊት ቀርበክ ያልፈቀድኩልክን ሴት ለምን በድብቅ በፍቅር ስም ያዝክ ሲልክ መልስክ ምንድነው

💍:::::::::::ቴሌግራማችን::::::::::::💍

https://t.me/Tidar_Be_Islam
https://t.me/Tidar_Be_Islam
❥:::::::::በትዳር ዉስጥ::::::::❥

አንዲት ሴት ባል አግብታ ከባልዋ እናት ጋር ትኖር ነበር. በአጭር ግዜውስጥ የባልየው እናት እና ሚስትዮው በሆነው ባልሆነው መጣላት ጀመሩ.
በሀገሪቱ ህግ መሰረት ደግሞ ማነኛዋም ሚስት ለ ባልዋ እናት የመታዘዝ እና የመገዛት ግዴታ አለባት. የባልየው እናትየባህል አጋጣሚ ተጠቅመው ያስቃይዋት ጀመሩ. በዚ ምክንያትም ባልየው ስላም አጣ እቤታቸውም ሰላም ያጣ ሆነ. ይሄንን መቃቃም ያቃታት ሚስትም የባህል መድሃኒት የሚሸጥ የአባትዋ ጋደኛ ጋር እርዳታ ፍለጋ ሄደች.

የለችበትን ከባድ ሁኔታ አስረድታም መርዝ እንዲስጣት እናስትሞት ካለችበት ስቃይ እንዲገላግላት እያለቀሰች ለመነቺው.
ሰውየውም ካዳመጣት ቦሃላ ስላሳዘነቺው ሊረዳት ፍቃደኛ ሆነ. ´እንዲህም አላት´ የባልሽ እናት ሰው እንዳይጠረጥር መድሃኒቱ ከረጂም ግዜ ቦሃላ ነው ሚገላት. ´በነዚ ወራቶች ውስጥ አንቺ ጥሩ ጥሩ ምግብ እያበስልሽ እዛ ውስጥ እየጨመርሽ ስጫት, የፈለገችውን እርጊላት ታዘዥያት እንደ እናትሽ ተንከባክብያት. ቁታሽንምእናትዋ ተቆጣጣሪ ብሎ እስጠንቅቆ መክራት, ሳምንታት አለፉ ሚስትየውም ጥሩ ምግብ ማብሰል እና እንደ መንከባከብ ጀመረች, ባለ መድኃኒቱ ሰውየ ያላትን እያስታወስች ንዴትዋን መቆጣጠር ቻለች, በሆነው ባልሆነው መቆጣትም አቆመች .የባልየው እናትም።

ለሚስትየው ያላቸው አመለካከት ተቀይሮ እንደልጃቸው ማየት ጀመሩ. ለጋደኘቻቸውን እና ለዘመዶቻቸው ጥሩ ምራት እንደ አገኙ መናገር ጀመሩ ለ 7 ወራትም እቤታቸው በፍጹም ደስታ ተሞልቶ አለፈ. አንድ ቀን ሚስትዮ ባለ መድኃኒት ሰውየው ጋር ሂዳ እንደ መጀመሪያ ግዜው እያለቀሰች መርዙን ማክሸፍያ መድኃኒት እንዲሰጣት ለመነቺው እንዲህም አለቺው"

የባሌ እናት እኔ እንዳሰብካት ሴት አልነበረችም ልክ እንደልጅዋ ነው ምታየኝ አሁን በጣም ተቀይራለች እንድትሞትብኝ አልፈልግም ታስፈልገኛለች" መድኃኒት ቀማሚው እንዲህ አላት" ምንም የማያሳስብሽ ነገር የለም የሰጠሁሽ መርዝ ሳይሆን ጤናዋን የሚያሻሽል ቢታሚን ነው, መርዙ ያለው አእምሮሽ ውስጥ ነበር እሱም በስጠሻት ፍቅር ከሽፍዋል አላት.
ጥላቻን #ፍቅር ነው ሚያሸንፈው, ለፍቅር ደግሞ መስዋዕት መክፈል እድለኝነት ነው አላት።..👌

ከፁሁፉ መልካም ነገር እንደተረዳቹ ተስፍ አለኝ ። በዚዉ አጋጣሚ እህቶቼ ለባሏቻቹ እናት መልካም ሰዉ እና መልካም ፍቅር እድኖራቹ መልክቴን መስተላለፍ እወደለዉ። بارك الله فيكم

#ሼር በማድረግ አስተላልፉ


💍:::::::ቴሌግራማችን:::::::💍

╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam🌸🍃
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam🌸🍃
🌊  በባህር የሰጠመችዋ  #ጀግና ሴት ልጅ

     አስገራሚ
#ታሪክ_ነው_ሼር_አድርጉ 👇

ጥብቅ ጨዋ የሆነችው ሙስሊሟ ሴት ገላዋን በአደባባይ አታሳይም ስብእናዋን አታቆሸሽም ክብሯን አታሰደፍርም ለምን የህይወት መስዋእትነት ጭምር አያስከፍላትም በክብር አትደራደርም

#አል_ኸጣብ ዑዳለት አስሰማእ በተሰኘው መጽሐፋቸው ውስጥ እንዳሰፈሩት ከአርባ አመት በፊት በባግዳድ እንሰሳት እያረደ ሥጋ በመሸጥ የሚተዳደር አንድ ሰው ነበር ገና ሳይነጋ በፊት ወደ ሱቅ ይሄድና የሚሸጠውን በግ አርዶ በማዘጋጀት ወደ ቤቱ ይመለሳል ፀሐይ ከወጣች በኋላ ደግሞ ተመልሶ በመውጣት ሱቁን ይከፍታል ያዘጋጀውን ሥጋ ለመሸጥ  #ከዕለታት አንድ ቀን ሌሊት ላይ ሥጋውን አርዶ ሲመለስ በድቅድቅ ጨለማ በመመለስ ላይ እያለ በመንገዱ ላይ ከጨለማ ውስጥ የጨኸት ድምጽ ሰማ ባረደው የበግ ደም ልብሱ ተበላሽቶ ነበር ፈጠን ብሎ ድምፁን ወደ ሰማበት አቅጣጫ አመራ ወዲያውኑ በተደጋጋሚ በጩቤ የተወጋ አንድ ሰው ላይ ወደቀ ሰውዬው ደሙ በከፍተኛ ሁኔታ ይፈሰው ነበር ጩቤውም ሰውነቱ ላይ እንደተተከለ ነው ጩቤውን ነቅሎለት በእጁ ይዞ ሰውዬውን ለመርዳት ብሎ ሊሸከመው ተንደረደረ የስውዬው ደም ልብሱን አጠበው በዚሁ ሁኔታ ላይ እያለ ጨኸት የሰሙ ሰዎች ከያቅጣጫው ተሰባሰቡ ጩቤውን በእጁ ሲያዩና ልብሱ በደም የተጨማለቀ መሆኑን ሲመለከቱ እንዲሁም ሰውዬውም የደነገጠ መሆኑን በደም የተጨማለቀ መሆኑን ሲመለከቱ እንዲሁም ሰውዬውም የደነገጠ መሆኑን ሲያስተውሉ ሰውዬውን የገደለው እሱሰለመሆኑ እርግጠኛ ሆኑ ከዚያም እንዲገደል ወሰኑበት ግዲያው ወደሚፈፀምበት ቦታም ወሰዱት እንደሚገደል እርግጠኛ መሆኑን ባወቀ ጊዜ ድምፁንሸ ከፍ አድርጎ ጮኸ #ሰዎች_ሆይ ‼️ወላሂ ይህንን ሰውዬ እኔ አልገደልኩም ነገር ግን ከሀያ አመት በፊት ሰው ገድዬ ነበር በዚህ ወንጀል ምክንያት ዛሬ ቅጣት እየተፈፀመበኝ እንደሆነ ይገባኛል አላቸውና #ታሪኩን ማውጋት ጀመረ

ከሀያ ዓመት በፊት በባህር ላይ ጀልባ ሰዎችን የማመላልስ ወጣት ነበርኩኝ ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት ሀብታም ወጣት ከእናቷ ጋር ሆነው ወደ ባህር ማዶ ለመሻገር መጡ እኔም አሻገርኳቸው በሁለተኛው ቀንም መጡና ጀልባዬ ላይ ተሳፈሩ አሻገርኳቸው ቀናት አለፉ ልቤ በዚህች ወጣት ላይ ተንጠለጠለ ወደድኳት እሷም ወደደችኝ እንዲድሩልኝ ብዬ ለአባቷ ሽማግሌ ብልክም በድህነቴ ምክንያት ጥያቄዬን ውድቅ አደረጉት ከዚህ እሷም ምን እንደገጠማት አላውቅም ብቻ ቀረች ተጠፋፋን እሷንም ሆነ እናቷን ለረጅም ጊዜ ማግኘት አልቻልኩም ልቤ ግን እንዳፈቀራት ኖረ
#ከሁለት_ወይም_ከሶስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ነበር አንድ ቀን ጀልባዬን ይዥ ተሳፋሪዎችን በመጠበቅ ላይ እያለሁ አንዲት ሴት ትንሽ ልጅ ይዛ መጣችና ወደ ዚያኛው ማዶ እንዳሻግራት ጠየቀችኝ ተሳፍራ መሃል ባህር ላይ በደረሰች ጊዜ ተመለከትኳት ያቺ አባቷ የለያየን ሴት መሆኗንም አወቅኩኝ ሰለገኘኋት ደስ አለኝ ያለፈውን ጊዜ አስታወስኳት #ፍቅር መቼስ የማይሸር እዳ ነው እሷ ግን ሰርዓት ባለው መልኩ አናገረችኝ እንዳገባችና የያዘችውም #ህፃን  መሆኑን አስረዳችኝ ቀስ በቀስ ሸይጣን በኔ ውስጥ ሥራውን ይሰራ ጀመር መጥፎ ነገርም አሳሰበኝ ተጠጋኋት ጮኸችብኝ #አላህን እንድፈራ አስታወሰችኝ ሆኖም ግን ማስጠንቀቂያዋ ምንም ግድ አልነበረኝም  እሷ የቻለችውን ያህል ትከላከል ትገፋኝ ጀመር ህፃን ልጇ ያለቅሳል ይህንን ባስተዋልኩ ጊዜ ይበልጥ እልህ ያዘኝ ልጇን ወሰድኩና ወደ ውሃው አስጠጋሁት ፈቃደኝነቷን ካልገለፀችልኝ አሰመጥዋለሁ ብዬ አስፈራራኋት አለቀሰች ለመነችኝ ተማፀነችኝ አልሰማኋትም የልጁን ጭንቅላት ይዥ ውሃ ውስጥ እየነከርኩ እየመለስኩ አስፈራራታለሁ እሷ ታለቅሳለች ትማፀናለች አልራራሁላት ልጁን አጥብቄ ውሃው ውስጥ ነከርኩት ትንሽምአቆየሁት እሷ ታያለች ክስተቱን ላለማየት #ዐይኗን ትሸፍናለች ልጁ ተንፈራፈረ ተልፈሰፈሰ ከውሃ ውስጥ ሳወጣው በድን ሆኗል #ሞቷል በድኑን ውሀሰ ውስጥ ወረወርኩት ከዚያም ተነሳሁና ወደሷ ሄድኩኝ በቻለችው ሁሉ ተከላከለችኝ ጮሃ አለቀሰች ፀጉሯን ይዠ በመጎተት ወደ ውሃ አሰጠጋኋት አየነከርኩ አስወጣታለሁ ደጋግሜ ባደርግም በእንቢተኝነቷ ፀናች በፍፁም አላደርገውም አለች እጄን ሲደክመኝ ነክሬ አቆየኋት እሷም እንደ ልጇ ሁሉ ተንፈራፈረች ከዚያም ፀጥ አለች ሞተች ውሃው ውስጥ ወረወርኳትና ተመለስኩኝ ይህንን ወንጀሌን አንድም ሰው ሳያውቅ ለዓመታት ኖርኩኝ ቢያቆይ እንጂ የማይረሳ የሆነው ጌታ ዛሬ ያለ ወንጀሌ ያዘኝ አላቸው ሰዎች ታሪኩን ሲሰሙ አለቀሱ አንገቱ ተቆርጦ እንዲገደልም አዘዙ #አላህ በዳዮች የሚፈጽሙትን ወንጀል የሚረሳ አይደለም እስቲ የዚህችን ወጣት #እናስተውል ዐይኗ እያየ ልጇ ለፊቷ ተገደለ እሷም ሞተች ይህ ሁሉ ለምን ሆነ #ክብሯን  ከማስደፈርና በዝሙት ከመዋረድ በሞት መገላገልን መረጠች ይህ ከጨዋ ሴቶች ታሪክ መጠነኛ ማሳያ ነው ብዙ ትምህርትም  እናገኝበታለን ።

#አደራ_እህት_ወንድሞቼ
እሄንን ድንቅ አስገራሚ የፀናት ታሪክ ሼር አደርጉ
     ለሙስሊም እህት ወንድሞች እናድርስ

💍:::::::ቴሌግራማችን:::::::💍

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam🌸🍃
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam🌸🍃
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞:::::ትዳር በኢስላም:::::☜   #ክፍል_ሰባት_⑦ት       #ከአንድ_በላይ_ሚስት_በኢስላም    ባለፈው እንዳሳለፍነው በጃሂሊያ ዘመን (ኢስላም ከመታደሱ በፊት) በአለም ላይ ያሉ ሀገራት ለሴት ልጅ ያላቸው ክብር እና ግምት በእጅጉ የወረደ በመሆኑ ያለምንም የቁጥር ገደብ ብዙ ሴቶች በአንድ ባል ስር እንዲተዳደሩ ይገደዳሉ።በዚህ ድርጊት ምክንያት በሴቶች ላይ የሚደርስባቸው ግፍና በደል ወንዶችን…
☞::::::ትዳር በኢስላም:::::☜

  .
#ክፍል_ስምንት/⑧ት
     
#ከአንድ በላይ ሚስት በኢስላም

#እስከ_አራት_የተፈቀደ_ለመሆኑ_ማስረጃ

               
#ቁርአናዊ_ማስረጃ
   አላህ ሱብሀነ ወተአላ እንዲህ ብሏል፣

وَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تُقْسِطُوا فِي الْيَتَامَىٰ فَانكِحُوا مَا طَابَ لَكُم مِّنَ النِّسَاءِ مَثْنَىٰ وَثُلَاثَ وَرُبَاعَ ۖ فَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تَعْدِلُوا فَوَاحِدَةً أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُكُمْ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَلَّا تَعُولُوا

በየቲሞችም (ማግባት) አለማስተካከላችሁን ብትፈሩ (ዝሙትንና ከተወሰነላችሁ በላይ ማግባትንም ፍሩ)፡፡ ከሴቶች ለእናንተ የተዋበላችሁን ሁለት ሁለት ሦስት ሦስትም አራት አራትም አግቡ፡፡ አለማስተካከልንም ብትፈሩ አንዲትን ብቻ ወይም እጆቻችሁ ንብረት ያደረጉትን ያዙ፡፡ ይህ ወደ አለመበደል በጣም የቀረበ ነው፡፡ (ሱረቱ አል-ኒሳእ - 3)

#ከአንቀፁ_የምንማራቸው_ቁም_ነገሮች

_አንቀፁ አንድ ወንድ ማግባት የሚችለው ከፍተኛው ቁጥር አራት መሆን እንዳለበት ይደነግጋል።ከአራት ሚስት በላይ ከነብዩ ሰአወ  ውጭ ማንኛውም ሰው መጨመር እንደማይፈቀድለት ኢማም አሻፊኢይ ኢጅማእ (የሙስሊም ሊቃውንት የጋራ አቋም)) አለው ይላሉ።ነብዩ ሰአወ ለምን ከአራት በላይ እንደተፈቀደላቸው እና ከአንድ በላይ የማግባታቸው ጥበብ ሌላው ተራው ሰው ከአንድ በላይ ከሚያገባበት ምክንያት የተለየ ነው።ይህን በተመለከተ እራሱን የቻለ ምዕራፍ ስላለው ከማውጫው ላይ በመፈለግ በዝርዝር ማንበብ ጠቃሚ ነው።

_አንቀፁ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት የፈለገ ሰው
#ፍትሃዊነት ቅድመ መስፈርት መሆን እንዳለበት ያስተምራል።በፍትህ ማስተዳደር የማይችል ወይም ፍትሃዊነት ሊጎለኝ ይችላል
ብሎ የሚያስብ ወንድ ከሆነ ከአንድ በላይ ማግባት እንደማይፈቀድለት አንቀፁ ከሚሰጠን ግንዛቤ የተወሰኑት ናቸው።

    ☞ ፍትሃዊነት ሲባል አንድ ሰው ማድረግ በሚችለው
#እንደቀለብ_ልብስ_መኖሪያቤት_እና_አብሮማደርን የሚያካትት ነው።ነገር ግን ከእርሱ ቁጥጥር ውጭ ሆኖ በማይችለው እና ከአቅሙ በላይ በሆነው እንደ #ፍቅር_መስጠት ያሉ ነገሮች ሁሉንም ሚስቶቹን እኩል ላድርግ ቢል ማድረግ አይችልም።ምክንያቱም አላህ በልቡ ላይ #ትወደድ_ያላት_ሴት_እሱ_ዘንድ_የበለጠ_ትወደዳለች።ለዚህ ሲባል አላህ እንዲህ ይላል፣

وَلَن تَسْتَطِيعُوا أَن تَعْدِلُوا بَيْنَ النِّسَاءِ وَلَوْ حَرَصْتُمْ ۖ فَلَا تَمِيلُوا كُلَّ الْمَيْلِ فَتَذَرُوهَا كَالْمُعَلَّقَةِ ۚ وَإِن تُصْلِحُوا وَتَتَّقُوا فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا
በሴቶችም መካከል ምንም እንኳ ብትጓጉ (በፍቅር) ለማስተካከል አትችሉም፡፡ እንደ ተንጠለጠለችም አድርጋችሁ ትተዋት ዘንድ (ወደምትወዷት) መዘንበልን ሁሉ አትዘንበሉ፡፡ ብታበጁም ብትጠነቀቁም አላህ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡[ ሱረቱ አል-ኒሳእ - 129 ]

☞ ከቁርአን አንቀፁ የምንማረው ቁምነገር፣ አንድ ሰው በሚስቶቹ መካከል በልብ ላይ ባለው ነገር(
ፍቅር) ማስተካከል የማይችል መሆኑን ነው። ነገር ግን የሰው ልጅ የሚችለውን ማስተካከል ጠብቆ መያዝ እንዳለበት ካለፈው የቁርአን አንቀፅ ለማየት ሞክረናል። እንደውም በሚስቶች መካከል ፍትሃዊ መሆን የመጀመሪያ መስፈርት ከሚባሉት ውስጥ ነው።

#ማሳሰቢያ፣ አንዳንድ አዕምሯቸው እንዳያገናዝብ የተዘጋባቸው ሰዎች ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት አይቻልም ብለው የሚከራከሩ በኢስላምም ውስጥ ብቅ ብለዋል።ማስረጃ ብለው ያቀረቡት ከላይ ያሳለፍነውን የቁርአን አንቀፅ ነበር።እንደነሱ አባባል የቁርአኑ አንቀፅ "በሴቶች መካከል ምንም እንኳን ብትጓጉ ለማስተካከል አትችሉም" ብለው በመተርጎም * በሴቶች መካከል ማስተካከል ደግሞ ቅድመ መስፈርት ስለሆነ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት አይቻልም* የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሱ። #ትርጉሙን_ለስሜታቸው_እንዲመቻቸው_አድርገው_በመተርጎም_እነሱ_ይህን_ይበሉ_እንጂ_ትክክለኛ_የአንቀፆቹ_መልእክት_እንዳሳለፍነው_ነው

    📚 የመጀመሪያው የቁርአን አንቀፅ የሚለው በየቲሞች መካከል ፍትህን እናጓድላለን ብላችሁ ከፈራችሁ ሌሎች ሴቶችን እስከ አራት ማግባት ትችላላችሁ የሚል ሲሆን የሁለተኛው የቁርአን አንቀፅ የሚያስረዳው ደግሞ በሴቶች መካከል ፍቅርን እኩል ማካፈል አትችሉም።ነገር ግን በምትችሉት ነገር ሴቶቻችሁን ችላ ብላችሁ እንዳትተዋቸው የሚል መልክ አዝሏል።
#ትክክለኛውም_የቁርአኑ_መልእክት_ይህ_ነው
  ☞ በሚችለው ነገር በሚስቶቹ መካከል ፍትሃዊ ያልሆነ ወንድ አላህ ዘንድ ትልቅ ቅጣት እንደሚጠብቀው ነብዩ ሰአወ ተናግረዋል።

    ☞አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ ሰአወ እንዲህ አሉ፣ "ሁለት ሚስቶች እሱ ዘንድ ያሉት እና በመካከላቸው ፍትሃዊ ያልሆነ ወንድ የቂያማ ቀን አንድ ጎኑ የተዘነበለ ሆኖ ይመጣል"  (ቲርሚዝይ ዘግበውታል

      ❗️ሙስሊም ሲባል ከዚህም ባለፈ በሁሉም ነገር ላይ በሚችለው አቅሙ በፈቀደው ፍትሃዊ መሆን መለያ ባህሪይው ሲሆን በተለይ ደግሞ በውስጡ ባሉት የኑሮ አጋር ከሆኑት ሚስቶቹ ጋር ሲሆን በእጅጉ ትኩረት የሚሰጠው ነው.።

  
#ይቀጥላል

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
☀️"በመፋቂያሽ ቀናሁ ከንፈርሽን አልፎ ጥርስሽን ሲነካዉ"

አሊይ (ረዲየላሁ አንሁ) ለሚስቱ ፋጢማ...
እውነተኛ
#ፍቅር እንዲህ ነው