የዓለማችን ፈጣኑ ሱፐር ኮምፒውተር "Summit" የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለማቆም የሚያግዝ አዲስ መላ አግኝቷል
************************
ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ የምርምር ተቋማትን በእጅጉ ያሳሳበ ጉዳይ ነው፡፡ አብዛኞቹ በእነዚህ የምርምር ተቋማት የሚሰሩ ሳይንቲስቶች በኮሮናቫይረስ ዙሪያ የሚያደርጉት የምርምር ስራ ቅልጥፍና የታከለበት ቢሆንም ከእነሱ ፍጥነት በላይ ቫይረሱ የሚሰራጭበት ሁኔታ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ብዙዎችን ያሳሳበ ነው፡፡
ይሁንና "Summit" ለተሰኘው ፈጣን ሱፐር ኮምፒውተር ክብር ይግባውና ምናልባት ከዚህ በኋላ ብዙ ወራቶችን ሊወሰድ የነበረው የተሳካ የምርምር ውጤት በዚሁ ኮምፒውተር የተነሳ ሊያጥር ችሏል፡፡ ሱፐር ኮምፒውተሩ በተገጠሙለት የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ ግብዓቶች አማካኝነት በሺዎች የሚቆጠሩ ማስመሰያዎችን (simulations) በማንቀሳቀስ ቫይረሱ የሚያርፍባቸውን ተጠቂ ህዋሳት በመመርመር የትኞቹ የመድኃኒት ውህዶች (drug compounds) ቫይረሱን ማቆም እንደሚችሉ ፍንጭ የሰጠ ነው፡፡ ሱፐር ኮምፒውተሩ ይህን ሰፊ ትንተና ሲያደርግ በጥቅሉ 77 የሚሆኑ ኬሚካሎችን ወይም የመድሃኒት ውህዶችን መለየት የቻለ ሲሆን በጥቅሉም ውጤታማ የሆነ የክትባት መድሃኒት ለመስራት በሚደረገው ጥረት ላይ መልካም ጅምር እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
ኦክ ሪጅ የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም በአጋርነት የሰራው ይህ ጥናት በፈረንጆቹ ጥር ወር ላይ በተሰራው የኮሮናቫይረስ spike protein መለያ ጥናት ላይ ተመርኩዞ የተከናወነ ሲሆን፤ ይኸውም ቫይረሱ ሰዎችን በሚያጠቃበት ጊዜ በሚያርፍባቸው ህዋሳት ላይ የሚፈጠረውን የመባዛት እና የመሰረጨት መጠን የሚጠቁም ነበር፡፡ ታዲያ ተመራማሪዎቹ ሱፐር ኮምፒውተሩን በመጠቀም እንደተረዱት የተጠቀሟቸው ብዛት ያለቸው ማስመሰያ ውህዶች በቫይረሱ spike protein ላይ በመጣበቅ ቫይረሱ በማረፊያ ህዋሳት ላይ የሚኖረውን ስርጭት መግታት እንደሚቻልና፤ ከዚህ ውስጥም ከ1 እስከ 77 የሚደርሱት የኬሚካል ውህዶች አስገራሚ ውጤት እንደነበራቸው ለመረዳት የቻሉበት ነው፡፡
በዚህ ፍሬያማ ጥናት ላይ ምርምሩን በበላይነት የመሩት የኦክ ሪጅ ብሄራዊ ላብራቶሪ ዳይሬክተር ጄርሚ ስሚዝ ግኝቱ ኮሮናቫይረስን ማከም የሚችል መድሃኒተ አገኘን ማለት ባይቻልም ክትባቱን ለመስረት በምናደርገው ጥረት ላይ የተሻለ እርምጃ የተራመድንበት ነው ብለዋል፡፡
የምርምር ስራውን ሲያቀላጥፍ የነበረው "Summit" ሱፐር ኮምፒውተር በ2019 በአሜሪካ የኢነርጂ ዲፓርትመንት እና በIBM አማካኘነት የተሰራ የዓለማችን ፈጣኑ ሱፐር ኮምፒውተር ሲሆን፤ በሰኮንድ 200 ኳድሪሊዮን (15 ዜሮዎችን የሚስከትል) ስሌቶችን ኮምፒውት በማድረግ መሰል ጥናቸን የሚያቀላጥፍ ወደር የማይገኝለት ቴከኖሎጂ ነው፡፡ ኮምፒውተሩ 200 petaflops አጠቃላይ አቅም ያለው በመሆኑ ፈጣን ከሚባሉት ላፕሎቶፖች አንድ ሚሊዮን እጠፍ ስራውን ማከናወን እንደሚችል ይነገራል፡፡
ለበለጠ https://edition.cnn.com/2020/03/19/us/fastest-supercomputer-coronavirus-scn-trnd/index.html
************************
ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ የምርምር ተቋማትን በእጅጉ ያሳሳበ ጉዳይ ነው፡፡ አብዛኞቹ በእነዚህ የምርምር ተቋማት የሚሰሩ ሳይንቲስቶች በኮሮናቫይረስ ዙሪያ የሚያደርጉት የምርምር ስራ ቅልጥፍና የታከለበት ቢሆንም ከእነሱ ፍጥነት በላይ ቫይረሱ የሚሰራጭበት ሁኔታ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ብዙዎችን ያሳሳበ ነው፡፡
ይሁንና "Summit" ለተሰኘው ፈጣን ሱፐር ኮምፒውተር ክብር ይግባውና ምናልባት ከዚህ በኋላ ብዙ ወራቶችን ሊወሰድ የነበረው የተሳካ የምርምር ውጤት በዚሁ ኮምፒውተር የተነሳ ሊያጥር ችሏል፡፡ ሱፐር ኮምፒውተሩ በተገጠሙለት የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ ግብዓቶች አማካኝነት በሺዎች የሚቆጠሩ ማስመሰያዎችን (simulations) በማንቀሳቀስ ቫይረሱ የሚያርፍባቸውን ተጠቂ ህዋሳት በመመርመር የትኞቹ የመድኃኒት ውህዶች (drug compounds) ቫይረሱን ማቆም እንደሚችሉ ፍንጭ የሰጠ ነው፡፡ ሱፐር ኮምፒውተሩ ይህን ሰፊ ትንተና ሲያደርግ በጥቅሉ 77 የሚሆኑ ኬሚካሎችን ወይም የመድሃኒት ውህዶችን መለየት የቻለ ሲሆን በጥቅሉም ውጤታማ የሆነ የክትባት መድሃኒት ለመስራት በሚደረገው ጥረት ላይ መልካም ጅምር እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
ኦክ ሪጅ የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም በአጋርነት የሰራው ይህ ጥናት በፈረንጆቹ ጥር ወር ላይ በተሰራው የኮሮናቫይረስ spike protein መለያ ጥናት ላይ ተመርኩዞ የተከናወነ ሲሆን፤ ይኸውም ቫይረሱ ሰዎችን በሚያጠቃበት ጊዜ በሚያርፍባቸው ህዋሳት ላይ የሚፈጠረውን የመባዛት እና የመሰረጨት መጠን የሚጠቁም ነበር፡፡ ታዲያ ተመራማሪዎቹ ሱፐር ኮምፒውተሩን በመጠቀም እንደተረዱት የተጠቀሟቸው ብዛት ያለቸው ማስመሰያ ውህዶች በቫይረሱ spike protein ላይ በመጣበቅ ቫይረሱ በማረፊያ ህዋሳት ላይ የሚኖረውን ስርጭት መግታት እንደሚቻልና፤ ከዚህ ውስጥም ከ1 እስከ 77 የሚደርሱት የኬሚካል ውህዶች አስገራሚ ውጤት እንደነበራቸው ለመረዳት የቻሉበት ነው፡፡
በዚህ ፍሬያማ ጥናት ላይ ምርምሩን በበላይነት የመሩት የኦክ ሪጅ ብሄራዊ ላብራቶሪ ዳይሬክተር ጄርሚ ስሚዝ ግኝቱ ኮሮናቫይረስን ማከም የሚችል መድሃኒተ አገኘን ማለት ባይቻልም ክትባቱን ለመስረት በምናደርገው ጥረት ላይ የተሻለ እርምጃ የተራመድንበት ነው ብለዋል፡፡
የምርምር ስራውን ሲያቀላጥፍ የነበረው "Summit" ሱፐር ኮምፒውተር በ2019 በአሜሪካ የኢነርጂ ዲፓርትመንት እና በIBM አማካኘነት የተሰራ የዓለማችን ፈጣኑ ሱፐር ኮምፒውተር ሲሆን፤ በሰኮንድ 200 ኳድሪሊዮን (15 ዜሮዎችን የሚስከትል) ስሌቶችን ኮምፒውት በማድረግ መሰል ጥናቸን የሚያቀላጥፍ ወደር የማይገኝለት ቴከኖሎጂ ነው፡፡ ኮምፒውተሩ 200 petaflops አጠቃላይ አቅም ያለው በመሆኑ ፈጣን ከሚባሉት ላፕሎቶፖች አንድ ሚሊዮን እጠፍ ስራውን ማከናወን እንደሚችል ይነገራል፡፡
ለበለጠ https://edition.cnn.com/2020/03/19/us/fastest-supercomputer-coronavirus-scn-trnd/index.html
CNN
The world’s fastest supercomputer identified chemicals that could stop coronavirus from spreading, a crucial step toward a treatment…
IBM’s Summit supercomputer identified 77 drug compounds that could stop the coronavirus spike from infecting host cells. This could help scientists create the most effective vaccine.
የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መቆጣጠሪያ ሥርዓት በይፋ ስራ ጀመረ
========================
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭት ያለበትን ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ አዳዲስ መረጃዎች በየጊዜው ይፋ የሚያደርግ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት በማበልጸግ ለኢፌዲሪ የጤና ሚኒስቴር በትናንትናው ዕለት አስረክቧል፡፡
ኤጀንሲው ያዘጋጀው “የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መቆጣጠሪያ ሥርዓት” የበሽታው ምልክት የታዩባቸው ወይም ስጋት ያደረባቸው ዜጎች ጥቆማ የሚሰጡበት ነው፡፡ ከዚህም ባለፈ የኮሮኖ ቫይረስ በሽታን ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን አሳሳቢ ችግር በተቀናጀ መልኩ ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጪዎችን በቀጥታ እንዲመዘገቡ የሚያስችል መሆኑን የኢመደኤ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው በርክክቡ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ እንዳሉት የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ ህብረተሰቡ በኮቪድ-19 በሽታ ላይ ያለውን ግንዛቤ የሚያሳድጉና ወቅታዊ መረጃዎችን የሚሰጥ ከመሆኑም ባሻገር የበሽታው ምንነት፣ የበሽታው ምልክቶች፣ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዘዴዎቹ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን የሚያቀርብ ነው ብለዋል፡፡
ፕላትፎርሙ ከችግሩ አንገብጋቢነት አንጻር ኤጀንሲው እንደ ተቋም ምን ማድረግ አለብኝ በሚል በአጭር ጊዜ ውስጥ የበለጸገ መሆኑን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ ፕላትፎርሙ በአማረኛ እና በእንግሊዘኛ የቀረበ ሲሆን በቀጣይ ሌሎች ተጨማሪ ቋንቋዎች በሲስተሙ እንደሚካተትበት ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ተናግራዋል፡፡
የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው በመንግስት እየተወሰደ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት የመከላከል ሥራን ለማገዝ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አዘጋጅቶ ባቀረበው “የኢትዮጵያ የተቀናጀ የኮቪድ-19 መቆጣጠሪያ ሥርዓት” ሊመሰገን ይገባል ብለዋል፡፡ ሥርዓቱ ለህብረተሰቡ በበሽታው ዙሪያ ወቅታዊ መረጃ እና አገልግሎት ለመስጠት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእጅጉ የሚያግዝ እንደሆነም ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ቫይረሱን ለመከላከል በሚደረገው ርብርብ የበኩሉን አስተዋጽ ማድረጉን የገለጹት ሚኒስትሯ ቫይረሱን ለመግታት ቴክኖሎጂው ጠቃሚ መሆኑ ባያጠያይቅም ውጤታማ መሆን የሚቻለው ቴክኖሎጂውን በአግባቡ መጠቀም ሲቻል መሆኑን አንስተዋል፡፡
የበሽታው ምልክት የታዩባቸውም ሆነ ማንኛውንም ጥንቃቄ የሚጠይቁ ምክሮችን የሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች በፕላትፎርሙ የተቀመጠውን የነጻ የስልክ መስመር በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከዚህ ባለፈ ዜጎች በአቅራቢያቸው ስለሚገኙ ሆስፒታል፣ ፋርማሲ ወይም የፖሊስ ጣቢያ መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርአት መሆኑ ተገልጿል፡፡
ወደ ፕላትፎርሙ ለመግባት ይህን ሊንክ መጫን ይችላሉ
http://www.etwisdom.gov.et/covid-19
ምንጭ፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ
========================
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭት ያለበትን ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ አዳዲስ መረጃዎች በየጊዜው ይፋ የሚያደርግ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት በማበልጸግ ለኢፌዲሪ የጤና ሚኒስቴር በትናንትናው ዕለት አስረክቧል፡፡
ኤጀንሲው ያዘጋጀው “የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መቆጣጠሪያ ሥርዓት” የበሽታው ምልክት የታዩባቸው ወይም ስጋት ያደረባቸው ዜጎች ጥቆማ የሚሰጡበት ነው፡፡ ከዚህም ባለፈ የኮሮኖ ቫይረስ በሽታን ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን አሳሳቢ ችግር በተቀናጀ መልኩ ለመከላከል ይረዳ ዘንድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጪዎችን በቀጥታ እንዲመዘገቡ የሚያስችል መሆኑን የኢመደኤ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው በርክክቡ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ እንዳሉት የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ ህብረተሰቡ በኮቪድ-19 በሽታ ላይ ያለውን ግንዛቤ የሚያሳድጉና ወቅታዊ መረጃዎችን የሚሰጥ ከመሆኑም ባሻገር የበሽታው ምንነት፣ የበሽታው ምልክቶች፣ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዘዴዎቹ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን የሚያቀርብ ነው ብለዋል፡፡
ፕላትፎርሙ ከችግሩ አንገብጋቢነት አንጻር ኤጀንሲው እንደ ተቋም ምን ማድረግ አለብኝ በሚል በአጭር ጊዜ ውስጥ የበለጸገ መሆኑን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ ፕላትፎርሙ በአማረኛ እና በእንግሊዘኛ የቀረበ ሲሆን በቀጣይ ሌሎች ተጨማሪ ቋንቋዎች በሲስተሙ እንደሚካተትበት ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ተናግራዋል፡፡
የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው በመንግስት እየተወሰደ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት የመከላከል ሥራን ለማገዝ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አዘጋጅቶ ባቀረበው “የኢትዮጵያ የተቀናጀ የኮቪድ-19 መቆጣጠሪያ ሥርዓት” ሊመሰገን ይገባል ብለዋል፡፡ ሥርዓቱ ለህብረተሰቡ በበሽታው ዙሪያ ወቅታዊ መረጃ እና አገልግሎት ለመስጠት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእጅጉ የሚያግዝ እንደሆነም ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ቫይረሱን ለመከላከል በሚደረገው ርብርብ የበኩሉን አስተዋጽ ማድረጉን የገለጹት ሚኒስትሯ ቫይረሱን ለመግታት ቴክኖሎጂው ጠቃሚ መሆኑ ባያጠያይቅም ውጤታማ መሆን የሚቻለው ቴክኖሎጂውን በአግባቡ መጠቀም ሲቻል መሆኑን አንስተዋል፡፡
የበሽታው ምልክት የታዩባቸውም ሆነ ማንኛውንም ጥንቃቄ የሚጠይቁ ምክሮችን የሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች በፕላትፎርሙ የተቀመጠውን የነጻ የስልክ መስመር በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከዚህ ባለፈ ዜጎች በአቅራቢያቸው ስለሚገኙ ሆስፒታል፣ ፋርማሲ ወይም የፖሊስ ጣቢያ መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችል ሥርአት መሆኑ ተገልጿል፡፡
ወደ ፕላትፎርሙ ለመግባት ይህን ሊንክ መጫን ይችላሉ
http://www.etwisdom.gov.et/covid-19
ምንጭ፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ
በኮሮና የተስተጓጎለውን ትምህርት ማገዣ መንገዶች
=======================
የኮሮና ቫይረስ በጉዳት እጆቹ ከጎበኛቸው መደበኛ የህይወት እርምጃዎቻችን መካከል ትምህርት ይገኝበታል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፤ ተማሪዎችም በቤታቸው ይገኛሉ፡፡ ታድያ በነዚህ ወቅቶች ልጆች ከትምህርታቸው እንዳይርቁ የመማሪያና አጋዥ መፅሐፍቶችን እንዲያነቡ ማድረግ ተገቢና ላለንበት የትምህርት ስርዓትም ቀዳሚው ምርጫ መሆን ያለበት ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ግን ለልጆችም ሆነ ወላጆች ጠቃሚ የሆኑ የመማሪያ ድረ-ገፆችን ልናስተዋውቃችሁ ወደድን፡፡
BBC Bitesize ( bbc.co.uk/bitesize )
ይህ ገፅ በሁሉም የዕድሜ ክልል እና ትምህርት ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የሚሆኑ ትምህርቶችን ይዟል፡፡ የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶችን አካቶ ከመያዙም በተጨማሪ በአንፃራዊነት ቀለል ብሎ ተቀምጧል፡፡
BBC Teach ( bbc.co.uk/teach/live-lessons )
እንደ ዩትዩብ ካሉ ምንጮች የሚገኙ የቪዲዮ ምስሎች ለልጆች እጅጉን ጠቃሚ ሊሆኑ ቢችሉም ቁም ነገሩን ለይቶ ማውጣት አዳጋች ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ረገድ BBC Teach ለልጆች የሚበጁ የቪዲዮ ምስሎችን አደራጅቶ የያዘ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ ገፁ ሌሎች ለተማሪዎች የሚጠቅሙ የቢቢሲ ዝግጅቶችን እንዲከታተሉ የሚያስችልና ስትከታተሏቸው የነበሩ ምስሎችንም እየተከታተለ መረጃ የሚሰጥ ነው፡፡
Khan Academy ( khanacademy.org )
በKhan Academy የሚገኙት ማንኛውም የትምህርት ግብዓቶች በነፃ ከመቅረባቸውም ባሻገር ተማሪዎች መሻሻላቸውን እንዲከታተሉ ያግዛል፡፡ ከድረ-ገፅ በተጨማሪ በስልክ መተግበሪያዎች በኩልም መከታተል ያስችላል፡፡
Duolingo ( duolingo.com )
Duolingo በተለይ ሌሎች ቋንቋዎችን መማር በሚሹ ሰዎች ዘንድ ታዋቂ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ልጆች በቋንቋ ትምህርታቸው ላይ እንዲሻሻሉ ጥሩ እገዛን የሚያደርግም ነው፡፡ ድረ-ገፁ እገዛውን የሚጀምረው ልጆች ያሉበትን የቋንቋ ደረጃ በመገምገም ሲሆን በመቀጠልም ቃላት እና ሀረጋትን በማስተዋወቅ እንዲሁም ፈተናዎችን በመስጠት ይረዳቸዋል፡፡ Duolingo የንግግር እና የፅሁፍ ችሎታን የሚያዳብሩ ትምህርቶችን ሲያቀርብ ፈጣን እና የገንዘብ ፍጆታውም እጅግ ዝቅተኛ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ እንደ Khan Academy ሁሉ ይህ ገፅም በስልክ መተግበሪያ አማካኝነት አገልግሎቱን ያቀርባል፡፡
The Artful Parent ( artfulparent.com )
ይህ ገፅ ከተለምዶው የድረ ገፅ መማር ማስተማር ሂደት በተለየ ልጆችን እያዝናኑ የፈጠራና ችሎታቸውን በሚያዳብሩና የአስተሳሰብ አድማሳቸውን በሚያሰፉ ሀሳቦች የተሞላ ነው፡፡ ስዕሎችን ከመሳል ቅርፃቅርፆችን እስከመስራት ባሉ እና ሌሎችም እንቅስቃሴዎችን ልጆችን ሳይጫን ያግዛል፡፡ በተጨማሪም ፈጠራና በራስ መተማመንን ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ምክርን የሚሰጥ ሲሆን በመደበኛ ትምህርታቸው ላይ የሚረዷቸው እና መነሳሳትንም የሚለግስ ነው፡፡
እነዚህ ሁሉ ድረ-ገፆች ጠቃሚነታቸው ባይካድም ለኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የሚሆነውን መምረጥ ግን አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም እነዚህ ትምህርቶች በሌላ ሀገር የትምህርት ስርዓት ላይ ተመስርተው የሚሰጡ ከመሆናቸው ጋራ በተያያዘ ከእኛ ሀገር የትምህርት ስርዓት የተለዩ ሊሆኑ ስለሚችሉ ለተማሪዎች የሚስማሙትን የትምህርት አይነቶች እና አሰጣጥ መንገዶች መርጦ መውሰዱ ለጥያቄ መቅረብ የለበትም፡፡
ምንጭ፡ techradar
=======================
የኮሮና ቫይረስ በጉዳት እጆቹ ከጎበኛቸው መደበኛ የህይወት እርምጃዎቻችን መካከል ትምህርት ይገኝበታል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፤ ተማሪዎችም በቤታቸው ይገኛሉ፡፡ ታድያ በነዚህ ወቅቶች ልጆች ከትምህርታቸው እንዳይርቁ የመማሪያና አጋዥ መፅሐፍቶችን እንዲያነቡ ማድረግ ተገቢና ላለንበት የትምህርት ስርዓትም ቀዳሚው ምርጫ መሆን ያለበት ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ግን ለልጆችም ሆነ ወላጆች ጠቃሚ የሆኑ የመማሪያ ድረ-ገፆችን ልናስተዋውቃችሁ ወደድን፡፡
BBC Bitesize ( bbc.co.uk/bitesize )
ይህ ገፅ በሁሉም የዕድሜ ክልል እና ትምህርት ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የሚሆኑ ትምህርቶችን ይዟል፡፡ የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶችን አካቶ ከመያዙም በተጨማሪ በአንፃራዊነት ቀለል ብሎ ተቀምጧል፡፡
BBC Teach ( bbc.co.uk/teach/live-lessons )
እንደ ዩትዩብ ካሉ ምንጮች የሚገኙ የቪዲዮ ምስሎች ለልጆች እጅጉን ጠቃሚ ሊሆኑ ቢችሉም ቁም ነገሩን ለይቶ ማውጣት አዳጋች ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ረገድ BBC Teach ለልጆች የሚበጁ የቪዲዮ ምስሎችን አደራጅቶ የያዘ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ ገፁ ሌሎች ለተማሪዎች የሚጠቅሙ የቢቢሲ ዝግጅቶችን እንዲከታተሉ የሚያስችልና ስትከታተሏቸው የነበሩ ምስሎችንም እየተከታተለ መረጃ የሚሰጥ ነው፡፡
Khan Academy ( khanacademy.org )
በKhan Academy የሚገኙት ማንኛውም የትምህርት ግብዓቶች በነፃ ከመቅረባቸውም ባሻገር ተማሪዎች መሻሻላቸውን እንዲከታተሉ ያግዛል፡፡ ከድረ-ገፅ በተጨማሪ በስልክ መተግበሪያዎች በኩልም መከታተል ያስችላል፡፡
Duolingo ( duolingo.com )
Duolingo በተለይ ሌሎች ቋንቋዎችን መማር በሚሹ ሰዎች ዘንድ ታዋቂ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ልጆች በቋንቋ ትምህርታቸው ላይ እንዲሻሻሉ ጥሩ እገዛን የሚያደርግም ነው፡፡ ድረ-ገፁ እገዛውን የሚጀምረው ልጆች ያሉበትን የቋንቋ ደረጃ በመገምገም ሲሆን በመቀጠልም ቃላት እና ሀረጋትን በማስተዋወቅ እንዲሁም ፈተናዎችን በመስጠት ይረዳቸዋል፡፡ Duolingo የንግግር እና የፅሁፍ ችሎታን የሚያዳብሩ ትምህርቶችን ሲያቀርብ ፈጣን እና የገንዘብ ፍጆታውም እጅግ ዝቅተኛ መሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ እንደ Khan Academy ሁሉ ይህ ገፅም በስልክ መተግበሪያ አማካኝነት አገልግሎቱን ያቀርባል፡፡
The Artful Parent ( artfulparent.com )
ይህ ገፅ ከተለምዶው የድረ ገፅ መማር ማስተማር ሂደት በተለየ ልጆችን እያዝናኑ የፈጠራና ችሎታቸውን በሚያዳብሩና የአስተሳሰብ አድማሳቸውን በሚያሰፉ ሀሳቦች የተሞላ ነው፡፡ ስዕሎችን ከመሳል ቅርፃቅርፆችን እስከመስራት ባሉ እና ሌሎችም እንቅስቃሴዎችን ልጆችን ሳይጫን ያግዛል፡፡ በተጨማሪም ፈጠራና በራስ መተማመንን ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ምክርን የሚሰጥ ሲሆን በመደበኛ ትምህርታቸው ላይ የሚረዷቸው እና መነሳሳትንም የሚለግስ ነው፡፡
እነዚህ ሁሉ ድረ-ገፆች ጠቃሚነታቸው ባይካድም ለኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የሚሆነውን መምረጥ ግን አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም እነዚህ ትምህርቶች በሌላ ሀገር የትምህርት ስርዓት ላይ ተመስርተው የሚሰጡ ከመሆናቸው ጋራ በተያያዘ ከእኛ ሀገር የትምህርት ስርዓት የተለዩ ሊሆኑ ስለሚችሉ ለተማሪዎች የሚስማሙትን የትምህርት አይነቶች እና አሰጣጥ መንገዶች መርጦ መውሰዱ ለጥያቄ መቅረብ የለበትም፡፡
ምንጭ፡ techradar
BBC
Home - BBC Bitesize
Use BBC Bitesize to help with your homework, revision and learning from KS1 to GCSE. Find free videos, step-by-step guides, activities and quizzes.
የኮሮና ወረርሺኝ እና የኢውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ተስፋ ሰጪ እርዳታ
=======================
የኮሮና ቫይረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ መስፋፋቱን ተከትሎ ብዙ ታላላቅ ኢንዱስትሪዎች ምርት ስጠት ማቆማቸው ይታወቃል፡፡ አሁን ታድያ እነዚህ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ እጥረት እየተከሰተባቸው ያሉ የህክምና ዕቃዎችን ለማምረት እንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡፡
ግዙፉ የመኪና አምራች ኩባንያ ፊያት ቼስለር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እጥረት የተከሰተበትን የፊት ማስክ ማምረት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ በዚህ አንድ ወር ውስጥም አንድ ሚሊዮን የፊት ማስኮችን በማምረት ሀገራት ውስጥ በሚገኙ ሆስፒታል፣ ክሊኒክ፣ ፖሊስ ጣብያ እና እሳት አደጋ መከላከል ለሚሰሩ ሰራተኞች ማሰራጨት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ ይህን የምርት ለውጥ ለማድረግ ፊያት ቼስለር ብቸኛው የመኪና አምራች አይደለም፡፡ ሌሎችም በእሲያ አውሮፓ እና አሜሪካ እሚንቀሳቀሱ የመኪና አምራቾችም በተመመሳሳይ እጥረት የተከሰረተባቸውን የህክምና ቁሳቁሶችን ለማምረት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ ባሳለፍነው ማክሰኞ ፎርድ ከጀነራል ኤሌክትሪክ እና 3ኤም ጋር በመተባበር የፊት መከለያዎችን እና የትንፋሽ መሳሪያዎችን (ventilator) ለማምረት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ፎርድ በአሁኑ ሰዓትም ቢሆን ለሆስፒታል ሰራተኞች ይሆን ዘንድ የፊት መከላከያዎችን በማምረት ላይ ሲሆን 75 ሺህ ያህሉን በዚህ ሳምንት ብቻ እንደሚያመርት ገልጿል፡፡
ዓለም አቀፍ እጥረት የተከሰተባቸው እነዚህን የህክምና ቁሳቁሶች ለማምረት እና እርዳታ ለመለገስ ከተሰናዱት ሌሎች የዘርፉ ተቋማት ውስጥ ኒሳን፣ ቴስላ፣ ማክላረን እንዲሁም የፎርምዩላ 1 መኪና ውድድር ተሳታፊ ቡድኖች ይገኙበታል፡፡ ከመኪና አምራች ኢንዱስትሪዎችም በተጨማሪ እንደ ዳይሶን፣ እና ኤርባስ ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የስራው ተካፋይ ለመሆን ከመንግስት አካላት ፍቃድ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡
ሆኖም ይህ መንገድ አልጋ በአልጋ እንደማይሆን የሚጠቁሙ ባለሙያዎች አሉ፡፡ የትንፋሽ መሳሪያዎች አምራቹ ሀሚልተን ሜዲካል ሀላፊ የሆኑት ጄምስ ሀልክ መሳሪያዎቹ ከፍ ያለ ዕውቀትን የሚጠይቁ ናቸው ይላሉ፡፡ እንደ እርሳቸው ከሆነ እነዚህ መሳሪያዎች ከቁሳዊ ይዘታቸው ባሻገር ብዙ ሶፍትዌሮችን የሚፈልጉና በውስጥ ከሚካተቱት ግብዓቶች መካከል አንዱም እንኳን በትክክል አለመስራት ሙሉ መሳርያውን ጥቅም አልባ ያደርገዋል፡፡
ሌሎች ኢንዱስትሪዎች የህክምና ቁሳቁሶችን እንዲያመርቱ ከመንግስታት እና ልዩ ልዩ ፖለቲከኞችም ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ይገኛል፡፡ እየአሜሪካን የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) በገበያው ላይ ያለውን እጥረት እንዲቀርፉ በማሰብ ቁሳቁሶቹን በማምረት ረገድ ያለውን የፍቃድ አሰጣጥ ስርዓት ማሻሻሉን አስታውቋል፡፡
ምንጭ፡ Drivetribe፣ BBC እና The Guardian
=======================
የኮሮና ቫይረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ መስፋፋቱን ተከትሎ ብዙ ታላላቅ ኢንዱስትሪዎች ምርት ስጠት ማቆማቸው ይታወቃል፡፡ አሁን ታድያ እነዚህ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ እጥረት እየተከሰተባቸው ያሉ የህክምና ዕቃዎችን ለማምረት እንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡፡
ግዙፉ የመኪና አምራች ኩባንያ ፊያት ቼስለር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እጥረት የተከሰተበትን የፊት ማስክ ማምረት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ በዚህ አንድ ወር ውስጥም አንድ ሚሊዮን የፊት ማስኮችን በማምረት ሀገራት ውስጥ በሚገኙ ሆስፒታል፣ ክሊኒክ፣ ፖሊስ ጣብያ እና እሳት አደጋ መከላከል ለሚሰሩ ሰራተኞች ማሰራጨት እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ ይህን የምርት ለውጥ ለማድረግ ፊያት ቼስለር ብቸኛው የመኪና አምራች አይደለም፡፡ ሌሎችም በእሲያ አውሮፓ እና አሜሪካ እሚንቀሳቀሱ የመኪና አምራቾችም በተመመሳሳይ እጥረት የተከሰረተባቸውን የህክምና ቁሳቁሶችን ለማምረት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ ባሳለፍነው ማክሰኞ ፎርድ ከጀነራል ኤሌክትሪክ እና 3ኤም ጋር በመተባበር የፊት መከለያዎችን እና የትንፋሽ መሳሪያዎችን (ventilator) ለማምረት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ፎርድ በአሁኑ ሰዓትም ቢሆን ለሆስፒታል ሰራተኞች ይሆን ዘንድ የፊት መከላከያዎችን በማምረት ላይ ሲሆን 75 ሺህ ያህሉን በዚህ ሳምንት ብቻ እንደሚያመርት ገልጿል፡፡
ዓለም አቀፍ እጥረት የተከሰተባቸው እነዚህን የህክምና ቁሳቁሶች ለማምረት እና እርዳታ ለመለገስ ከተሰናዱት ሌሎች የዘርፉ ተቋማት ውስጥ ኒሳን፣ ቴስላ፣ ማክላረን እንዲሁም የፎርምዩላ 1 መኪና ውድድር ተሳታፊ ቡድኖች ይገኙበታል፡፡ ከመኪና አምራች ኢንዱስትሪዎችም በተጨማሪ እንደ ዳይሶን፣ እና ኤርባስ ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የስራው ተካፋይ ለመሆን ከመንግስት አካላት ፍቃድ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡
ሆኖም ይህ መንገድ አልጋ በአልጋ እንደማይሆን የሚጠቁሙ ባለሙያዎች አሉ፡፡ የትንፋሽ መሳሪያዎች አምራቹ ሀሚልተን ሜዲካል ሀላፊ የሆኑት ጄምስ ሀልክ መሳሪያዎቹ ከፍ ያለ ዕውቀትን የሚጠይቁ ናቸው ይላሉ፡፡ እንደ እርሳቸው ከሆነ እነዚህ መሳሪያዎች ከቁሳዊ ይዘታቸው ባሻገር ብዙ ሶፍትዌሮችን የሚፈልጉና በውስጥ ከሚካተቱት ግብዓቶች መካከል አንዱም እንኳን በትክክል አለመስራት ሙሉ መሳርያውን ጥቅም አልባ ያደርገዋል፡፡
ሌሎች ኢንዱስትሪዎች የህክምና ቁሳቁሶችን እንዲያመርቱ ከመንግስታት እና ልዩ ልዩ ፖለቲከኞችም ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ይገኛል፡፡ እየአሜሪካን የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) በገበያው ላይ ያለውን እጥረት እንዲቀርፉ በማሰብ ቁሳቁሶቹን በማምረት ረገድ ያለውን የፍቃድ አሰጣጥ ስርዓት ማሻሻሉን አስታውቋል፡፡
ምንጭ፡ Drivetribe፣ BBC እና The Guardian
!ሰበር ዜና! የኮሮና ቫይረስን በሳይንሳዊ ምርምር በተደገፈ የሀገር በቀል እውቀት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ቫይረሱን ለማከም የተሰራው መድሃኒት መሰረታዊ የምርምር ሂደት በማለፍ ተደጋጋሚ የቤተ ሙከራ ሞዴሊንግ ሂደቶችን በስኬት ማለፉን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ምርምሩ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ መከሰቱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ተደጋጋሚ የምርመር ሂደት አልፎ ወደ ምርት እና ቀጣይ የእንስሳት ፍተሻ እና ክሊኒካል ፍተሻ ስራዎች እንዲሸጋገር ተደርጓል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.)፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰና ከኢትዮጵያዊያን የባህል ሃኪሞች ጋር እና የህክምና ተመራማሪዎች ጋር በመሆን የሀገር በቀል እውቀቶችን በሳይንሳዊ ሂደቶች በማሳለፍ ለዘመን አመጣሹ ኮሮና ቫይረስ( ኮቪድ -19) ወረርሽኝ ህክምና የተዘጋጀውን መድሃኒት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችላቸውን ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
መድሃኒቱ የመከላከል አቅም የሚጨምር፣ መርዛማነት የሌለው እና አዋጭነቱ የተረጋገጠ ነው፡፡
የምርምር ሂደቱ ተጠናቅቆ ወደ ምርት ለመግባት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡
ምንጭ፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
ምርምሩ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ መከሰቱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ተደጋጋሚ የምርመር ሂደት አልፎ ወደ ምርት እና ቀጣይ የእንስሳት ፍተሻ እና ክሊኒካል ፍተሻ ስራዎች እንዲሸጋገር ተደርጓል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.)፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰና ከኢትዮጵያዊያን የባህል ሃኪሞች ጋር እና የህክምና ተመራማሪዎች ጋር በመሆን የሀገር በቀል እውቀቶችን በሳይንሳዊ ሂደቶች በማሳለፍ ለዘመን አመጣሹ ኮሮና ቫይረስ( ኮቪድ -19) ወረርሽኝ ህክምና የተዘጋጀውን መድሃኒት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችላቸውን ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
መድሃኒቱ የመከላከል አቅም የሚጨምር፣ መርዛማነት የሌለው እና አዋጭነቱ የተረጋገጠ ነው፡፡
የምርምር ሂደቱ ተጠናቅቆ ወደ ምርት ለመግባት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡
ምንጭ፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
ስለኮሮና እገዛ የሚሰጥዎ የስልክ መተግበሪያ (mobile app)
====================
በአሁኑ ሰዓት ለኢትዮጵያና መላው ዓለም ትልቅ ስጋት ስለሆነው የኮሮና ቫይረስ መረጃ የሚሰጥ የስልክ መተግበሪያ (mobile app) በተቋማችን ሰራተኞች ተሰርቶ ቀርቦልዎታል፡፡ መተግበሪያው ለእርስዎ እንዲመች ተደርጎ በአማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ የሚሰራ ነው፡፡ ይህን ጠቃሚ መተግበሪያ እንድሮይድ ስልክ ያላችሁ በሙሉ አውርዳችሁ ትጠቀሙበት ዘንድ ምክራችን ነው፡፡ ለወዳጅ ዘመድዎ ማጋራቱን እንዳይረሱት፡፡
====================
በአሁኑ ሰዓት ለኢትዮጵያና መላው ዓለም ትልቅ ስጋት ስለሆነው የኮሮና ቫይረስ መረጃ የሚሰጥ የስልክ መተግበሪያ (mobile app) በተቋማችን ሰራተኞች ተሰርቶ ቀርቦልዎታል፡፡ መተግበሪያው ለእርስዎ እንዲመች ተደርጎ በአማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ የሚሰራ ነው፡፡ ይህን ጠቃሚ መተግበሪያ እንድሮይድ ስልክ ያላችሁ በሙሉ አውርዳችሁ ትጠቀሙበት ዘንድ ምክራችን ነው፡፡ ለወዳጅ ዘመድዎ ማጋራቱን እንዳይረሱት፡፡
# ከኮሮና # ቫይረስ ጋር በተያያዘ # ስራዎን # ለመስራት
# ተቸግረዋል? እነዚህን የቴክኖሎጁ አማራጮች ይሞክሩ
***************************************
ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችን ከእንቅስቃሴ ውጭ እያደረገ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ብዙዎች በሽውታውን ለመከላከል እና የስርጭት መጠኑን ለመግታት ከመንግስት በወረዱ መመሪያዎች አማካኘነት ስራዎችን ከቤት በመሆን በመከወን ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም እያንዳንዷን ግንኙነታቸውን በርቀት እየተገበሩ ይገኛል፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት እነዚህን እንቅስቃሴዎች በቀላሉ ለመፈፀም እና ደህንነታችንንም በሚገባ ለመጠበቅ የቴክኖሎጂ እገዛ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡
እነዚህ ከስር የምትመለከቷቸው መተግበሪያዎች እና ድረ ገፆች በአብዛኛው የአለም ክፍል መሰል እንቅስቃሴዎችን ከቤት ሆኖ ለመከወን እና ስራዎችን ለማቅለል የሚያገለግሉ ሲሆን፤ በእኛ ሃገር ሁኔታም በሚቻለው አቅም ቢተገበሩ የሚጠቅሙ ናቸው፡፡
መረጃዎችን በአካል መገናኘት ሳያስፈልግ መላላክ የሚቻልባቸው ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Dropbox
2. Pipebytes
3. MailBigFile
4. filedropper
5. Google drive
ስብሰባዎችን እና ውይይቶችን በርቀት ለማከናወን የሚያግዙ ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Crowdcast
2. GoToMeeting
3. Cisco Webex Teams
4. Intermedia AnyMeeting
5. https://zoom.us/download ፡ ይህ በተለይም መረጃዎችን ፊት ለፊት በገጽታ ለማዉራት የሚያስችል ታወቂ ሶፍትዌር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎችንም ተግባራት ለማከናወን ይረዳል፤ መረጃን (File) ለመላላክ፣ ጽሁፍ ለመጻጻፍ እና ከ ሁለት በላይ የሆኑ ሰዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በተለያየ ጊዜ አስቻይ በሆነ መንገድ ለማገናኘት፣ የተለያዩ ቦታ ሆኖ ህክምና ለመስጠት፣ ሪፖርት ለማድረግ፣ ኮንፈረንስ ለማካሄድ እና ሌሎችም
የርቀት ትምህርቶቸን በኢተርኔት ለማግኘት እና ለመማማር የሚያግዙ ድረገፆች
1. Adobe Connect
2. Blackboard Collaborate
3. WizIQ
4. LearnCube
5. BigBlueButton ፡ ይህ በተለይም ብዙዎች የሚመርጡት የመስመር ላይ መማሪያ ስርዓት ሲሆን፤ ሩቅ ላሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው የትምህርት እንዲያገኙ በማስቻል የተለያዩ የትምህርት አይነቶችን በቪዲዮ እና ኦውዲዮ ማጋራት የሚያስችል ነው፡፡
ከዛ ባለፈ በሃገራችን የካሽ ብር መያዝ ሳያስፈልግ ሂሳብ መክፈል የሚችሉባቸውን እነዚህን መንገዶች በሚቻለው ቦታ በመጠቀም ከበሽታው ራሳችንን መከላከል እንችላለን
1. M-birr
2. Amole
3. Helocash
4. Awash mobile
# ተቸግረዋል? እነዚህን የቴክኖሎጁ አማራጮች ይሞክሩ
***************************************
ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችን ከእንቅስቃሴ ውጭ እያደረገ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ብዙዎች በሽውታውን ለመከላከል እና የስርጭት መጠኑን ለመግታት ከመንግስት በወረዱ መመሪያዎች አማካኘነት ስራዎችን ከቤት በመሆን በመከወን ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም እያንዳንዷን ግንኙነታቸውን በርቀት እየተገበሩ ይገኛል፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት እነዚህን እንቅስቃሴዎች በቀላሉ ለመፈፀም እና ደህንነታችንንም በሚገባ ለመጠበቅ የቴክኖሎጂ እገዛ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡
እነዚህ ከስር የምትመለከቷቸው መተግበሪያዎች እና ድረ ገፆች በአብዛኛው የአለም ክፍል መሰል እንቅስቃሴዎችን ከቤት ሆኖ ለመከወን እና ስራዎችን ለማቅለል የሚያገለግሉ ሲሆን፤ በእኛ ሃገር ሁኔታም በሚቻለው አቅም ቢተገበሩ የሚጠቅሙ ናቸው፡፡
መረጃዎችን በአካል መገናኘት ሳያስፈልግ መላላክ የሚቻልባቸው ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Dropbox
2. Pipebytes
3. MailBigFile
4. filedropper
5. Google drive
ስብሰባዎችን እና ውይይቶችን በርቀት ለማከናወን የሚያግዙ ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች
1. Crowdcast
2. GoToMeeting
3. Cisco Webex Teams
4. Intermedia AnyMeeting
5. https://zoom.us/download ፡ ይህ በተለይም መረጃዎችን ፊት ለፊት በገጽታ ለማዉራት የሚያስችል ታወቂ ሶፍትዌር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎችንም ተግባራት ለማከናወን ይረዳል፤ መረጃን (File) ለመላላክ፣ ጽሁፍ ለመጻጻፍ እና ከ ሁለት በላይ የሆኑ ሰዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በተለያየ ጊዜ አስቻይ በሆነ መንገድ ለማገናኘት፣ የተለያዩ ቦታ ሆኖ ህክምና ለመስጠት፣ ሪፖርት ለማድረግ፣ ኮንፈረንስ ለማካሄድ እና ሌሎችም
የርቀት ትምህርቶቸን በኢተርኔት ለማግኘት እና ለመማማር የሚያግዙ ድረገፆች
1. Adobe Connect
2. Blackboard Collaborate
3. WizIQ
4. LearnCube
5. BigBlueButton ፡ ይህ በተለይም ብዙዎች የሚመርጡት የመስመር ላይ መማሪያ ስርዓት ሲሆን፤ ሩቅ ላሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው የትምህርት እንዲያገኙ በማስቻል የተለያዩ የትምህርት አይነቶችን በቪዲዮ እና ኦውዲዮ ማጋራት የሚያስችል ነው፡፡
ከዛ ባለፈ በሃገራችን የካሽ ብር መያዝ ሳያስፈልግ ሂሳብ መክፈል የሚችሉባቸውን እነዚህን መንገዶች በሚቻለው ቦታ በመጠቀም ከበሽታው ራሳችንን መከላከል እንችላለን
1. M-birr
2. Amole
3. Helocash
4. Awash mobile
Zoom
Download Center for Zoom Apps and Plugins | Zoom
Download Zoom apps, plugins, and add-ons for mobile devices, desktop, web browsers, and operating systems. Available for Mac, PC, Android, Chrome, and Firefox.
የስፓኒሽ ፍሉን መአት ያለፉት የ 101 ዓመት አዛውንት ለኮሮናም እጅ አልሰጡም
********************************
በሃገረ ጣልያን የኮሮናቫይረስ አደጋ እጅግ በተባባሰበት በአሁን ወቅት በተደጋጋሚ ሁኔታ እጅግ ልብ የሚሰብሩ ታሪኮችን ሲሰሙ እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡ በተለይም ሃገሪቱ ከጃፓን ቀጥሎ የብዙ አዛውንቶች መኖሪያ በመሆኗ ብዙ ሞት ለማስተናገዷም ዋና ምክንያት እንደነበረ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡ ከዚህ ሲሻገርም አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ በጊዜው ማድረግ ባለመቻሏ የአደጋው መጠን የከፋ እንዲሆን ትልቅ በር ከፍቷል፡፡ ታዲያ እነዚህ እና ሌሎች ሁነቶች ተደማምረው ወጤቱን የከፋ አደረገው፡፡
ይሁንና በእነዚህ አሳዛኝ ሁኔታዎች ወስጥ ያለፈቸው ይህች ሃገር ተስፋን የሚያለመልም መልካም ዜና ፈፅሞ አልጠፋባትም ነበር፡፡ የ 101 ዓመት አዛውንት የሆኑት Mr. P ደግሞ ለዚህ ተስፋ መለምለም ዋነኛው ምክንያት ናቸው፡፡ እኝህ የ 101 ዓመት አዛውንት በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው ብዙዎች ሞታቸውን ሲጠባበቁላቸው የቆዩ ቢሆንም በተደረገላቸው የሃኪም እገዛ እና በሰነቁት ትልቅ ተስፋ ከቫይረሱ ሙሉ ለሙሉ አገግመው የታሪክ ነጋሪ መሆናቸውን ቀጥለዋል፡፡ እኝህ አባት የስፓኒሽ ፍሉ ተብሎ በሚታወቀውና የብዙዎችን ነፍስ በቀጠፈው በዚያ ስከፊ ጊዜ እንደተወለዱ ያስታወቁት የኢንፈርሚ ሆስፒታል ዶክተሮች የዘመናችን አደጋ የሆነውን ኮሮናቫይረስን ዳግም ያሸነፉ ትልቅ አባት ሲሉ አሞግሰዋቸዋል፡፡
Mr. P በዚህ እድሜያቸው ከቫይረሱ አገግመው ወደቤታቸው የሄዱ ብቸኛው የጣልያን ዜጋ ሲሆኑ፤ ከዚህ ቀደምም በቻይና የሚኖሩ የ 103 የእድሜ ባለፀጋ ከሀኪሞች በተደረገላቸው ከፍተኛ እገዛ ከኮሮናቫይረስ ሙሉ ለሙሉ አገግመው ለብዙዎች ተስፋ እንደሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ምንጭ፡ IFLScience Store
********************************
በሃገረ ጣልያን የኮሮናቫይረስ አደጋ እጅግ በተባባሰበት በአሁን ወቅት በተደጋጋሚ ሁኔታ እጅግ ልብ የሚሰብሩ ታሪኮችን ሲሰሙ እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡ በተለይም ሃገሪቱ ከጃፓን ቀጥሎ የብዙ አዛውንቶች መኖሪያ በመሆኗ ብዙ ሞት ለማስተናገዷም ዋና ምክንያት እንደነበረ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡ ከዚህ ሲሻገርም አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ በጊዜው ማድረግ ባለመቻሏ የአደጋው መጠን የከፋ እንዲሆን ትልቅ በር ከፍቷል፡፡ ታዲያ እነዚህ እና ሌሎች ሁነቶች ተደማምረው ወጤቱን የከፋ አደረገው፡፡
ይሁንና በእነዚህ አሳዛኝ ሁኔታዎች ወስጥ ያለፈቸው ይህች ሃገር ተስፋን የሚያለመልም መልካም ዜና ፈፅሞ አልጠፋባትም ነበር፡፡ የ 101 ዓመት አዛውንት የሆኑት Mr. P ደግሞ ለዚህ ተስፋ መለምለም ዋነኛው ምክንያት ናቸው፡፡ እኝህ የ 101 ዓመት አዛውንት በኮሮናቫይረስ ተጠቅተው ብዙዎች ሞታቸውን ሲጠባበቁላቸው የቆዩ ቢሆንም በተደረገላቸው የሃኪም እገዛ እና በሰነቁት ትልቅ ተስፋ ከቫይረሱ ሙሉ ለሙሉ አገግመው የታሪክ ነጋሪ መሆናቸውን ቀጥለዋል፡፡ እኝህ አባት የስፓኒሽ ፍሉ ተብሎ በሚታወቀውና የብዙዎችን ነፍስ በቀጠፈው በዚያ ስከፊ ጊዜ እንደተወለዱ ያስታወቁት የኢንፈርሚ ሆስፒታል ዶክተሮች የዘመናችን አደጋ የሆነውን ኮሮናቫይረስን ዳግም ያሸነፉ ትልቅ አባት ሲሉ አሞግሰዋቸዋል፡፡
Mr. P በዚህ እድሜያቸው ከቫይረሱ አገግመው ወደቤታቸው የሄዱ ብቸኛው የጣልያን ዜጋ ሲሆኑ፤ ከዚህ ቀደምም በቻይና የሚኖሩ የ 103 የእድሜ ባለፀጋ ከሀኪሞች በተደረገላቸው ከፍተኛ እገዛ ከኮሮናቫይረስ ሙሉ ለሙሉ አገግመው ለብዙዎች ተስፋ እንደሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
ምንጭ፡ IFLScience Store
በቤልጂየም የ12 ዓመቷ ህፃን በኮሮናቫይረስ ህይወቷ አልፏል
ይህ ለወጣቶች ምን መልእክት ይሰጣል
************************************
በቤልጂየም በኮሮናቫይረስ የተያዘች አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ህይወቷ ማለፉን የሃገሪቱ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡ የሃገሪቱ የመንግስት ቃል አቀባይ ኢማኑዬል አንድሬ በዛሬ መግለጫቸው እንዳስረዱት ህፃኗ የትኩሳት ምልክት ከታየባት ከሶስት ቀን በኋላ በቫይረሱ መየዟን ለመረጋገጥ የተቻለ ቢሆንም በዚህ ፍጥነት ህይወቷ እንዴት ሊያልፍ እንደቻለ አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጣቶችና ህፃናት በኮሮናቫይረስ መሞታቸው እየተስተዋለ መምጣቱን ያስረዱት ቃል አቀባዩ አንድሬ ምንም አይነት መዘናጋት ሳየስፈልግ ተገቢው ጥንቃቄ በወጣቶች እንዲወሰድ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በአውሮፓ ከዚህ በፊት በእንግሊዝ የ18 ዓመት ወጣት፣ በፈረንሳይ የ16 ዓመት ሴት ልጅ፣ በፖርቹጋል የ14 ዓመት ልጅ እንዲሁም አሁን ደግሞ 12 ህፃን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መሞታቸውን ተከትሎ ወጣቶች እና ህፃናት ከአላስፈላጊ መዘናጋት ወጥተው ራሳቸውን እና ማህበረሰቡን ከበሽታው እንዲጠብቁ የጤና ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛል፡፡
በበርካታ አገራት በእድሜ የገፉ ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ በመሆናቸው እና የሚሰጡ የጤና ማሳሰቢያዎችም ከዚህ ጋር ብቻ የተያያዙ በመሆናቸው ወጣቶች እኛን አየጠቃንም ወደሚል እሳቤ እንዲሄዱና ከፍተኛ መዘናጋት ውስጥ እንዲገቡ እንዳደረጋቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለወጣቶች እንዳስጠነቀቁት የኮሮናቫረስ እድሜያቸው እንደገፋ ሰዎች ወጣቶችን በፍጥነት ባይገድልም ለሳምንታት ሆስፒታል ሊያስተኛቸው እና ከዚያም ሲያልፍ ለሞት ሊያደርሳቸው አንደሚቸል መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ወጣቶች ምንም የህመም ስሜት ባይሰማቸው እንኳ ወዴት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው እና የሚወስኗቸው እያንዳንዷ ውሳኔዎች ለሌሎች የሞትና የሕይወት ጉዳይ ሊሆን እንደሚችል በማሰብ ከመቼውም ጊዜ በማስተዋል እንዲጓዙ ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
በህጻናት በኩልም እስካሁን በይፋ እንደተረጋገጠው አብዛኞቹ በዚህ ቫይረስ የተጠቁ ህፃናት በበሽታው የመሞት መጠናቸው እጅግ ዝቅተኛ ቢሆንም በሽታውን ወደሌሎች የማስተላለፍ እድላቸው ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ግን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም በዚህ የዕድሜ ክልል ያሉ ህጻናት የሚታይባቸው የበሽታው ምልክት በጣም አናሳ በመሆኑ እና በሃላፊነት ስሜት ራሳቸውን እና አካባቢያቸውን መጠበቅ ስለማይችሉ ምናልባት የበሽታው ዋነኛ አስተላለፊዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ያም ሆነ ይህ ግን ነገሮች ይበልጥ አስከሚታወቁ ድረስ ወጣቶች እና ህፃናት በፍፁም ሃላፊነት ራሳቸውን እና በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን ከቫይረሱ መጠበቅ እንደሚገባቸው የሁሉም መልዕክት ነው፡፡
ምንጭ፡ express.co.uk/
ይህ ለወጣቶች ምን መልእክት ይሰጣል
************************************
በቤልጂየም በኮሮናቫይረስ የተያዘች አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ህይወቷ ማለፉን የሃገሪቱ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡ የሃገሪቱ የመንግስት ቃል አቀባይ ኢማኑዬል አንድሬ በዛሬ መግለጫቸው እንዳስረዱት ህፃኗ የትኩሳት ምልክት ከታየባት ከሶስት ቀን በኋላ በቫይረሱ መየዟን ለመረጋገጥ የተቻለ ቢሆንም በዚህ ፍጥነት ህይወቷ እንዴት ሊያልፍ እንደቻለ አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጣቶችና ህፃናት በኮሮናቫይረስ መሞታቸው እየተስተዋለ መምጣቱን ያስረዱት ቃል አቀባዩ አንድሬ ምንም አይነት መዘናጋት ሳየስፈልግ ተገቢው ጥንቃቄ በወጣቶች እንዲወሰድ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በአውሮፓ ከዚህ በፊት በእንግሊዝ የ18 ዓመት ወጣት፣ በፈረንሳይ የ16 ዓመት ሴት ልጅ፣ በፖርቹጋል የ14 ዓመት ልጅ እንዲሁም አሁን ደግሞ 12 ህፃን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መሞታቸውን ተከትሎ ወጣቶች እና ህፃናት ከአላስፈላጊ መዘናጋት ወጥተው ራሳቸውን እና ማህበረሰቡን ከበሽታው እንዲጠብቁ የጤና ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛል፡፡
በበርካታ አገራት በእድሜ የገፉ ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ በመሆናቸው እና የሚሰጡ የጤና ማሳሰቢያዎችም ከዚህ ጋር ብቻ የተያያዙ በመሆናቸው ወጣቶች እኛን አየጠቃንም ወደሚል እሳቤ እንዲሄዱና ከፍተኛ መዘናጋት ውስጥ እንዲገቡ እንዳደረጋቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለወጣቶች እንዳስጠነቀቁት የኮሮናቫረስ እድሜያቸው እንደገፋ ሰዎች ወጣቶችን በፍጥነት ባይገድልም ለሳምንታት ሆስፒታል ሊያስተኛቸው እና ከዚያም ሲያልፍ ለሞት ሊያደርሳቸው አንደሚቸል መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ወጣቶች ምንም የህመም ስሜት ባይሰማቸው እንኳ ወዴት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው እና የሚወስኗቸው እያንዳንዷ ውሳኔዎች ለሌሎች የሞትና የሕይወት ጉዳይ ሊሆን እንደሚችል በማሰብ ከመቼውም ጊዜ በማስተዋል እንዲጓዙ ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
በህጻናት በኩልም እስካሁን በይፋ እንደተረጋገጠው አብዛኞቹ በዚህ ቫይረስ የተጠቁ ህፃናት በበሽታው የመሞት መጠናቸው እጅግ ዝቅተኛ ቢሆንም በሽታውን ወደሌሎች የማስተላለፍ እድላቸው ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ግን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም በዚህ የዕድሜ ክልል ያሉ ህጻናት የሚታይባቸው የበሽታው ምልክት በጣም አናሳ በመሆኑ እና በሃላፊነት ስሜት ራሳቸውን እና አካባቢያቸውን መጠበቅ ስለማይችሉ ምናልባት የበሽታው ዋነኛ አስተላለፊዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ያም ሆነ ይህ ግን ነገሮች ይበልጥ አስከሚታወቁ ድረስ ወጣቶች እና ህፃናት በፍፁም ሃላፊነት ራሳቸውን እና በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን ከቫይረሱ መጠበቅ እንደሚገባቸው የሁሉም መልዕክት ነው፡፡
ምንጭ፡ express.co.uk/
Express.co.uk
Latest UK and World News, Sport and Comment | Express.co.uk
Latest news, showbiz, sport, comment, lifestyle, city, video and pictures from the Daily Express and Sunday Express newspapers and Express.co.uk