Seid Social
9.03K subscribers
2.19K photos
322 videos
6 files
1.39K links
አለም አቀፋዊ መረጃዎች ምልከታዎችና ታሪካዊ ክስተቶች ይቀርቡበታል
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሂዝቡላህ በትላንትናው እለት የእስራኤልን የአየር መከላከያ የሆነውን Irone Domeን ማውደሙ በአለምአቀፍ ደረጃ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል። ሂዝቡላህ የእስራኤል የአየር መከላከያ Irone dome ያወደመበትን ቪዲዮ ጭምር በመልቀቁ እስራኤል ተደናግጣለች ።

እስራኤል ዛሬ በሰጠቺው መግለጫ ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃ አልሰጥም ከአየር መከላከያው ጋር የነበረ ወታደርም ተገድሎብናል ለእኛ ትልቅ ኪሳራ ነው ሲል የእስራኤል ጦር ቃልአቀባይ ኮሎኔል ፒተር ለርነር ተናግሯል።

ሂዝቡላህ የእስራኤልን አየር መከላከያዎች እንደት ማለፍ ሲቻልም እንደት ማውደም እንደሚቻል ተደጋጋሚ ሙከራዎችን እያደረገ የከረመ ሲሆን አሁን ላይ እየተሳካለት ይመስላል።
በመሆኑም እስራኤል ከየትኛውም የአየር ጥቃት ትከላከልበት ዘንዳ ከአሜሪካ የተሰጣትን የ Irone dome ቴክኖሎጂ ሂዝቡሏህ በስኬት ማውደም ችሏል። ሂዝቡላህ ከዚህ በተጨማሪ የእስራኤል የስለላ ፋሲሊቲውችን እያወደመ ይገኛል ።

👉 t.me/Seidsocial
ቭላዲሚር ፑቲን ምእራባውያንን ማጥቃት ለሚፈልጉ ሀይሎች አህጉር አቋራጭ ሚሳኤሎቻችንን እናስታጥቃቸዋለን አሉ ።

ፕሬዚዳንት ፑቲን ዛሬ በሰጡት መግለጫ ምእራባውያን ድንበራቸውን እያለፉ ነው በመሆኑም የአውሮፓ እና የአሜሪካ ከተሞችን መምታት የሚችል ረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎቻችንን ለምእራባዊያን ጠላቶች እናስታጥቃቸዋለን ብለዋል ።

ምእራባውያን ዩክሬይንን ማስታጠቃቸውን ከቀጠሉ እኛ የነርሱን ጠላቶች የማናስታጥቅበት ምን ምክንያት አለን ? ሲሉም ተደምጠዋል።

ይህ የፑቲን መግለጫ ድንጋጤ የፈጠረባት አሜሪካም ለዩክሬይን ሩሲያን ዘልቃ በአሜሪካ መሳሪያዎች እንዳታጠቃ ትእዛዝ አስተላልፋለች ።
በሁለቱ ሀያላን ጎራዎች መካከል ያለው ፍጥጫ ተፋፍሞ ቀጥሏል።

👉 t.me/Seidsocial
ይህ የአስክሬን ክምር እስራኤል የጨፈጨፈቻቼው የጋዛዊያን አስክሬን አይደለም !
ይህ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በራሱ ዜጎች ላይ ያደረሰው እጅግ ሰቅጣጭ ጭፍጨፋ ነው።
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በአንድ ቀን ብቻ 140 ሱዳናዊያንን በመግደል ጠበሳ ታሪክ ፅፏል።
ሱዳኖች እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ናቸው።

የሙስሊም ሀገራት ጦር በተለይም የአረብ ሀገራት ጦር ጀግንነቱ እንደዚህ ምንም ያልታጠቁ ዜጎቻቼውን ለመግደል ነው። እንጅ በጠላት ላይማ እንኳንስ የጥይት የቃል ጥቃት እንኳ ለመፈፀም ብርክ ይይዛቸዋል።

አላህ በግፍ የተገደሉትን በጀነት ይካሳቸው። ገዲዮቹንም የእጃቸውን ይስጣቸው!

👉👉 t.me/Seidsocial
ይህ የምታዩት ልኡክ የሳኡዲ አረቢያው የኡለሞች ሊግ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሙሀመድ ቢን አብዱልከሪም አልኢሳ በጀርመን ጭፍጨፋ የተፈፀመባቸውን የአይሁዶች መታሰቢያን የሳኡዲ ኡለሞችን እየመራ የጎበኘበት ክስተት ነው ።
ሸይኽ ሙሀመድ አልኢሳ ሳኡዲ አረቢያ ለአይሁዶች ያላትን አጋርነት ለማሳየት ነው ልኡካኑን እየመራ አይሁዶች የተጨፈጨፉበትን ቦታ የጎበኘው ። ሸይኹ ቀድሞ የሳኡዲ የፍትህ ሚኒስትር ሲሆን አሁን ላይ የሳኡዲ የአለም ሙስሊሞች ሊግ ፕሬዚዳንት ተደርጎ ኡለሞችን እንዲመራ ተመርጧል ። ያው በሳኡዲ ላይ በጣም ከሚደመጡ የነገስታት አሊምች አንዱ ነው።

ሳኡዲ አረቢያ በአሁኑ ሰአት አይሁድነትንና እስራኤልን የሚያጥላሉ አስተምህሮዎችን ኡለሞቿ እንዳያስተምሩ አድርጋለች። እንኳን ኡለሞቿ ማንኛውም ሳኡዲያዊ ታዋቂ ግለሰብ በአሁኑ ሰአት እስራኤልን የሚያወግዝ ስለፍልስጤም ድምፅ የሚያስተጋባ ነገር ማስተላለፍ አይፈቀድለትም ። በግብፅም ያለው ሁኔታ ተመሳሳይ ነው ።

ሳኡዲ አረቢያ ከትምህርት ካሪኩለሟ ላይ እስራኤልን የሚያጥላሉ ፅሁፎችን ከትምህርት ገበታዋ ማውጣቷ ይታወቃል። የፍልስጤምንም ካርታ ከአለም ካርታዋ ላይ ፍቃ ግልፅ ማንነቷን አሰያሳየች ነው።

ይህንን አስመልክቶ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች ሀላፊ ኒምሮድ ጎሬን ለ THE TIMES OF ISRAEL በሰጡት መግለጫ የሳኡዱ አረቢያ ጅምር ጥሩ ቢሆንም በጣም አነስተኛ ነው ገና ብዙ መስራት ይጠበቅባታል ብለዋል።
ዋና ላፊው " ይህ ሳኡዲ እስራኤል የተሳለችበትን ስእል ለመቀየር ያደረገቺው ገና ትንሽ እርምጃ ነው ከዚህም በላይ ብዙ መስራት ይጠበቅባታል እስራኤልን ማክበር እና ለእስራኤልም ክፍት መሆን ላይ ገና ብዙ ነገር ማድረግ ይጠበቅባታል " በማለት የእስራኤሉ የውጭጉዳይ ፖሊሲዎች ሀላፊ ኒምሮድ ጎሬን አሳስበዋል።

ዋና ሀላፊው አክለውም " ሳኡዲ አረቢያ የእስራኤል የልብ ወዳጅ መሆን ከፈለገች ዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ የተከተለችውን መንገድ መከተል አለባት ልክ እንደ ኢማራት ስለ ሀይማኖት መቻቻል አይሁድም እስላምም የአብረሀም ሀይማኖቶች መሆናቸውን ኡለሞቿ እንዲያስተምሩ በማድረግ የተሻለ መቀራረብ እንዲፈጠር ማድረግ አለባት " በማለት ጎሬን ተናግረዋል። የሳኡዲ እና የእስራኤል የወዳጅነት ጅምርም ዛሬ የተጀመረ አለመሆኑን በመጠቆም ከበርካታ አስርት አመታት በፊት የተጀመረ ቀስበቀስ እያዘገመ የመጣ ወዳጅነት ነው ብለዋል።

በተለይም ሳኡዲ አረቢያ አይሁዶችን የሚያጥላላውን የቁርአን አስተምህሮ እንድታጤነው የእስራኤል ሀላፊ አሳስበዋል ።
ሳኡዲ በትምህርት ካሪኩለሟ ላይ ከቁርአን ላይ የተጠቀሰውን " አይሁዶችን በወንጀላቸው ወደ ዝንጀሮና ከርከሮ ቀየርናቸው " የሚለውን አስወግዳለች።
የእስራኤሉ የውጭጉዳዮች ሀላፊ ኒምሮድ ጎሬን ሳኡዲ የፍልስጤም ካርታን ከአለም ካርታ ላይ ማንሳቷን በማሞገስ ግና ፍልስጤምን ካነሳች በሗላ የእስራኤልን ካርታ በቦታው ላይ ማስገባት ነበረባትም ብለዋል።

ይህ እየሆነ ያለው እውነታ ነው። ብዙዎች ይህ ውሸት ወይንም ጥላቻ ይመስላቸዋል ። ላ !!! ወላሂ ውሸት አይደለም። ማንም እውነት ፈላጊ ማረጋገጥ ይችላል!!
እኔ ሳኡዲ በሙስሊሙ አለም ላይ ይህን ሁሉ ሸፍጥ ባትሰራ ኖሮ ለምን አገዛዟን አጥላላለሁ ! በግሌ ያደረሰችብኝ በደል የለ !!

ለማንኛውም ሙስሊሙ ማን ጠላቱ ማን ወዳጁ እንደሆነ ያውቅ ዘንድ የበኩሌን ማሳወቄን እቀጥላለሁ።
ሸኹ የአይሁዶችን መታሰቢያ የሚጎበኝበትን ምስል ግሩፑ ላይ አስቀምጥላችሗለሁ !

t.me/Seidsocial
ሶማሊያ የፀጥታው ጥበቃ ምክርቤት አባል በመሆን በታሪክ ትልቁን የፖለቲካ ድል ተቀዳጀች።

ምስራቅ አፍሪካዊቷና በእርስበርስ ጦርነትና ረሀብ የምትታወቀው ሀገር ሶማሊያ የአለም ፖለቲካ በሚዘውረው የፀጥታው ጥበቃ ምክርቤት አባል ሆናለች። በዚህም መሰረት ከ 15ቱ የአለም የፖለቲካ ውሳኔ ሰጭ ሀገራት አንዷ ለመሆን ችላለች። ይህ ሶማሊያ በአለምአቀፍ ፖለቲካ ያላትን ድርሻ የሚያጎላው ሲሆን ፖለቲካዊ ጥቅሞቿን በአለምቀፍ መድረክ እንድታስጠብቅ እድሉን ያጎናፅፋታል።

የፀጥታው ጥበቃ ምክርቤት 15 አባል ሀገራት ያቀፈና የተመድ ከፍተኛው የውሳና ሰጭ አካል ሲሆን ከ 15ቱ አምስቱ ሀገራት ማለትም አሜሪካ ሩሲያ ቻይና እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ቋሚና ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ያላቸው ሀገሮች ናቸው። አስሩ ደግሞ ተለዋጭ አባል ሀገራት ናቸው።

ከኢትዮጵያ ጋር ከፍተኛ ፖለቲካዊ ውዝግብ የገባቺው ሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር ከሀገሯ ሙሉ ለሙሉ ለቆ እንዲወጣ ቀነገደብ አስቀምጣለች።

👉 t.me/Seidsocial
እስራኤል በዛሬው እለት በጋዛ በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ላይ በፈፀመቺው ጭፍጨፋ 210 ለፍልስጤማውያን በአንድ ጀንበር ተገድለው ውለዋል።

እስራኤል በማእከላዊ ጋዛ በኑሰይራት የስደተኞች መጠለያ ላይ ከሰማይ ከምድር ባወረደቺው የቦንብ ውርጅብኝ ከመጠጠለያው ካሉ ተፈናቃዮች ውስጥ 210 የሚሆኑትን ጨፍጭፋለች። አለምም ይህንን ጭፍጨፋ በዝምታ ማለፍን መርጧል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታኒያሁ ጭፍጨፋውን " ታሪክ ሁሌም ሲያስታውሰው የሚኖረው የእስራኤል ገድል " ሲል አሞካሽቶታል።

ዛሬ እስራኤል ይህን ሁሉ ጭፍጨፋ የፈፀመቺው ከአሜሪካ ጋር በቀጥታ በመተባበር ነበር። አሜሪካ እና እስራኤል ምርኮኞቹን ለማስለቀቅ በመሩት ዘመቻ ነው የኑይሰራትን መጠለያ ያወደሙት።

በዛሬው እለት አሜሪካና እስራኤል ባደረጉት ዘመቻም አራት ምርኮኞችን ማስለቀቅ የቻሉ ሲሆን ሌሎች የእስራኤል ምርኮኞች ግን ከእስራኤል በተተኮሰ መሳሪያ ተገድለዋል።

ሀማስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሜሪካ በጦርነቱ ቀጥታ መግባቷን በማውገዝ ዛሬ አራት ምርኮኞችን ማስለቀቅ ቢችሉም ገና በመቶዎች የሚቆጠሩ ምርኮኞች በእጃችን ናቸው ብሏል። እንደዚህ አይነት ዘመቻ የሚቀጥሉ ከሆነ ግን ምርኮኞቻቼውን በህይወት ማግኘት ይከብዳቸዋል ብሏል።
እስራኤል አንድም ምርኮኛዋን ያለማስለቀቅ ውርደቷን ለማካካስ ዛሬ ከአሜሪካ ጋር በመተባበር የፈፀመቺው የጦር ወንጀል እጅግ ዘግናኝ ነበር ።

t.me/Seidsocial
ከቀናት በፊት የግሪኩ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪርያኮስ ሚትሶታኪስ ቱርክን ጎብኝተው ነበር።
ታዲያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚትሶታኪስ ከኤርዶጋን ጋር የጋራ መግለጫ እየሰጡ በነበረበት ወቅት ሀማስን ለመውቀስ እየዳዳቸው ነበርና ኤርዶጋን ንግግራቸውን ያዝ አድርጎ መናገር ጀመረ

" ሀማስ ለእኛ የነፃነት ታጋይ ነው ሀማስ ስለህዝቡ ህልውና ስለፍልስጤምም ህልውና ሁሉን ሰውቶ እየተፋለመ የሚገኝ የነፃነት ፈርቀዳጅ ነው ። ሀማስ ለእኛ የቱርክን ህልውና ለማትረፍ እንደተዋደቁት እንደነዚያ የቱርክ አርበኞች ነው። እናም ሀማስን በክፉ የሚያነሳብን ሰው እኛን ያስቀይመናል ! ሀማስን በሽብርተኝነት መፈረጅም አሳፋሪ ነው እናንተ ምእራባውያን እኛም ለነፃነታችን በምንታገል ወቅት አሸባሪ እንደምትሉን አንጠራጠርም ። እናም ሀማስን በክፉ እንዳያነሱ " በማለት ለግሪኩ መሪ ይናገራል ።

የግሪኩ ጠቅላይ ሚኒስትርም የኤርዶጋንን ንግግር ከሰማ በሗላ " መልካም ከፊታችሁ ሀማስን አናወግዝም ግና በዚህ ጉዳይ ላይ ባለመስማማት እንስማማ " በማለት ጉዳዩን ቋጭቷል።

በመግለጫው ወቅት ኤርዶጋን " ቱርክ 1,000 የሀማስ ቁስለኞችን በሀገሯ እያከመች ነው " በማለት መናገሩ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር ።
በዛሬው እለትም የቱርክ የደህንነት መሪ ከሀማስ አመራሮች ጋር በኳታር ዶሀ በምስጢርእየመከሩ ይገኛሉ። የሚደርሱበትን ነገር ወደፊት የሚታይ ይሆናል።
ቱርክ በእስራኤል ላይ የንግድ ማእቀብም መጣሏ የሚታወቅ ነው ። በዚህም በእስራኤል ላይ ማእቀብ የጣለች ብቸኛዋ ሀገር ያደርጋታል። የቱርክ ማእቀብ የእስራኤልን ኢንዱስትሪ በከፍተኛ ሁኔታ እየፈተነው መሆኑም ተረጋግጧል። እስራኤል ቱርክ የጣለቺውን ማእቀብ እንዲታነሳ ብትወተውትም ቱርክ ግን እስራኤል ጭፍጨፋዋን እስከቀጠለች ድረስ ማእቀቡ እንደሚፀና ተናግራለች ።

ቱርክ ለፍልስጤም እያደረገች ያለቺው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ ከፍተኛ ቢሆንም ግና የምትችለውንና ማድረግ የሚገባትን ያክል እያደረገች እንዳልሆነ በኩሌ አምናለሁ። ቱርክ ለፍልስጤም ከዚህ በላይ መስራት ይገባታል !

👉 t.me/Seidsocial
የእስራኤሉ የትላንት ዘመቻ ምርኮኞችን ማስመለስ አልነበረም በፍፁም !
ከዚያ ይልቅ የወደቀባትን የውርደት ማቅ በትንሹም ገፈፍ የማድረግ ህልም ነበረው። ይህንን ለማድረግ ነው አሜሪካ በቀጥታ የተሳተፈችበትን ኦፕሬሽን ትላንት የከፈተቺው። ኦፕሬሽኑንም " operation Arnon " በማለት ነበር የሰየመቺው።

የትላንቱ ዘመቻ በአሜሪካ የስለላ ተቋም CIA ይመራ ነበር ። እናም ምርኮኞቹ ያሉበትን ቦታ አሜሪካ ከጠቆመች በሗላ አሜሪካ ሰራሽ ጄቶች ከሰማይ የቦንብ ዝናብ ያዘንቡ ነበር። ከስር ያማም የተሰኘው የእስራኤል ልዩ ኮማንዶ ተልእኮውን ሊወጣ በእስራኤል አየር ወለድ እየታጀበ አካባቢውን አፈራረሱት።

በዚህ ኦፕሬሽን የሞተው ምርኮኛ ሞቶ ትንሽም ቢሆን ነፃ መውጣት እንዳለባቸው ኔታኒያሁ ቀጭን ትእዛዝ አስተላልፏል። ምክንያቱም አለምአቀፍ ማህበረሰብና የእስራኤል ህዝብም የእስራኤልን ጦር " የጋዛ ንፁሀንን ከመጨፍጨፍ የዘለለ ያሳካችሁት ነገር የት ነው ?" ሲባሉ መልስ ስለጠፋ !

እናም ትላንት እስራኤል በገዛ ምርኮኞቿ ላይ ጨከነች ። በርካታ ምርኮኞችን ገድላም አራት ምርኮኞችን ብቻ አስጣለች። ኔታኒያሁም የመንተፍረቱን " ታሪካዊ ድል " በማለት ተቦተረፈ።
ግና አለም የእስራኤልን ገድል ከማሞገስ ይልቅ የበለጠ ቁጣውን ገለፀ። አራት ምርኮኞችን ለመግደል እንደት 274 ንፁሀን ይሰዋሉ ? እንደትስ በሌሎች የራሷ ምርኮኛ ዜጎች ላይ ትጨክናለች ? የሚል ውግዘት።
ቢጠቅምም ባይጠቅምም ከክስተቱ በሗላ አውሮፓ ህብረት የእስራኤልን ድርጊት "ጭፍጨፋ" በማለት ሲያወግዝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ እስራኤል "ለህፃናት አደገኛዋ ሀገር " በማለት በጥቁር መዝገብ ላይ ስሟን አስፍሯታል። ባይጠቅምም ለታሪክ መፋረጃ ይሆናል።

በሀማስ እጅ ከ 100 በላይ የወራሪዋ ምርኮኞች ይገኛሉ

👉 t.me/Seidsocial
በነገራችን ላይ ትላንትና ምርኮኞችን ለማስለቀቅ የእስራኤል ልዩ ኮማንዶ የመራው የጦር መሪው አርኖን ዛሞራ በሀማስ ተደምስሷል።
ትላንት በነበረው እልህ አስጨራሽ ትግል ከፍተኛ ምት አርፎበት የነበረው የጦር መሪው ብዙም ሳይቆይ ይህችን አለም ተሰናብቷል።

እስራኤልም ለርሱ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ኦፕሬሽኑን " ኦፕሬሽን አርኖን" ስትል ሰይማዋለች።

ለጨረሳቸው ህፃናትና ንፁሀን አላህ ፊት ይተሳሰባታል !

👉 t.me/Seidsocial
የአማራ ክልል ሁኔታ በዚሁ ከቀጠለ አማራ ክልል በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ተክለቁመና ውስጥ አዳድስ ከተመሰረቱት ክልሎችም በታች እንዲንኮታኮት ያደርገዋል።

መርህና አላማ አልባ ታጋዮች ከሴረኛና ደንታ ቢስ መንግስት ጋር በሚያደርጉት ትግል የክልሉ ህዝብ እየደቀቀ ይቀጥላል።
ፅንፈኛ ሀይማኖት ቀመስ ተጋዳዮች ክልሉን የሀይማኖት ተኮር ግድያና ማፈናቀል ማእከል ያደርጉትና አማራ ክልል በኢትዮጵያ ሗላቀሩ ክልል እንዲሆን ይሆናል።

ክልሉ ሽፍታዎች የሚተረማመሱበት እገታዎች የሚፋፋሙበት እንኳንስ ለኢንቨስትመንት ለመኖርም የማይመች የህቦቹ የስቃይ ምድር ይሆናል ። እየሆነ ያለውም ይሄው ነው!

የክልሉ ህዝብ ምርር ብሎታል። የገጠሩ ማህበረሰብ በሁለት ጉልበተኞች ግብር እንዲከፍል እየተገደደ ነው። በሬ የሸጠ ገበሬ መረጃው ተጣርቶ የሸጠበት ገንዘብ እየተወሰደበት ነው።
ፋኖ ውጭ ሀገር ልጆች ያላቸውን ቤተሰቦች እያጣረ ብር እያስላከ መቀበል ጀምሯል። በየገጠሩ ከተሞች ገበያዎች ላይ ግብር መገበር ግደታ ተደርጎ ህዝቡ እየተዘረፈ ነው። ቀለብ አውጣ ፣ የትጥቅ አምጣ እየተባለ ህዝቡ መድረሻ አጥቷል።
በዚህ ሁሉ መሀል በነዘመነ ካሴ የሚመራው ፋኖ አልደራደርም በማለት በህዝብ ላይ ፈርዷል!

ትግሉ ከሀዲዱ ስቶ ጥቂቶች የሚከብሩበት ብዙ የአማራ ህዝብ የሚያለቅስበት ክስተት ተፈጥሯል።

የአማራን ህዝብ ከዚህ የቁልቁለት ጉዞ ለማዳን ከተፈለገ የአማራ ኢሊቶች ቆም ብሎ ማሰቢያቸው አሁን ነው። የአለምንና የሀገሪቱን ተጨባጭ የማያውቅ ሁሉ ገና ነፍጥ ስለጨበጠ ብቻ የህዝብን ጥያቄ ሊያስመልስ አይችልም!!

👉 t.me/Seidsocial
የሳኡዲ አረቢያው ንጉስ ሰልማን ቢን አብዱልአዚዝ ለ 1,000 ጋዛዊያን በነፃ ሀጅ እንዲያደርጉ ፈቅጃለሁኝ ብሏል።

ይሄ አጁዛ የምእራባውያን ገረድ ጋዛዊያን እንኳንስ ወደ ሀጅ መሄጃ ቀርቶ እዚያው ጋዛ ውስጥ እንኳ መንቀሳቀስ በማይችሉበት ፤ ረሀቡ ድካሙ መጠለያ አልባነቱ አዳክሟቸው በህይወት ለመቆየት በሚታገሉበት ሁኔታ ውስጥ እርሱ ገና ለገና መካና መድናን በእንግሊዝ እገዛ ተቆጣጥሪያለሁ ብሎ በሀጅ ሊቆምር ይፈልጋል።

ዛሬ የጋዛ ነዋሪዎችን ማትረፍ ከሙጃሂዶቹ ጎን መሰለፍ ሀጅ ከማድረግም በላይ ነበር። በምግብ የምትጫወተው ረብጣ ዶላሮችን በአሜሪካ ካዝና ውስጥ አጭቃ የምትንደላቀቀው ሳኡዲ በጋዛዊያን ላይ በፍልስጤማውያን ላይ መሳለቋን ቀጥላለች።

ካርታቸውን ከአለም ካርታዋ ፍቃ ፤ ለፍልስጤማውያን መርዳትን በሽብርተኝነት የሚያስወነጅል ሀጢአት አድርጋ ሳለ ግና ፃድቅ ፃድቅ ሊያጫውታት ከሞት አምልጣችሁ መምጣት የምትችሉ ከሆነ 1,000 ሆናችሁ ኑና ሀጂ አድርጉ ብላለች ማፈሪያዋ ሀገር !

ከሀጅና ኡምራ በየአመቱ ከ 15 ቢሊዮን ዶላር በላይ የምትሰበስበው ሳኡዲ የምታገኘውን ገንዘብ ለሙስሊሞች መምቻ መጠቀሟ የሚያሳዝን ነው ።

👉 t.me/Seidsocial
አሁን ነው መፍራት ማለታቸው የሚቀር አይመስልም ሳኡዳዊያን!

የእስራኤሉ ትልቁ ሚዲያ Jerusalem post በዛሬ እትሙ ሙሴ ከእግዚአብሔር አስርቱ ትእዛዛትን የተቀበለው በግብፅ ሲናይ ሳይሆን በሳኡዲ አረቢያ ነው በመሆኑም ሳኡዲ አረቢያ የእስራኤል ህዝቦች አጥመርስት ናት የሚልን ሀተታ ይዞ ቀርቧል።
እስራኤል በሳኡዲ አረቢያ ላይ ያላትን ይገባኛል እያጠነከረች ትመስላለች።

የእስራኤል ትልቁ ፖለቲከኛና ፀሀፊ ዴኒስ አቪ ሊፕኪን " Return to Mecca " በተሰኘው እጅግ አወዛጋቢ መፅሀፉ " ህዝቦቼ ወደዚያች ወደ መካ ይሂዱ እዚያ ከበረሀው እኔን ይከቡኝ ያጅቡኛል " የሚል ትንቢት ያዘለን መፅሀፍ በመፃፍ መካ የአይሁዶች አጥመ እርስት መሆኗን ያሰምራል።

እናም አሁን ጄሩሳሌም ፖስት ሲጀመር ሙሴ አስርቱ ትእዛዛትን የተቀበለው በግብፅ ሳይሆን በሳኡዲ አረቢያ ነው የሚል ከፍተኛ መነጋገሪያ ህትመት ይዞ ብቅ ብሏል።

እስራኤላውያን የፍልስጤምን ምድር ከመቀማታቸው በፊት ይሄዱት የነበረው አካሔድ ልክ እንደዚሁ ነበር። ሰለሞን ኖሮባታል ዳዊት ቀድሶባታል እያሉ ታሪክ እየመዘዙ ነው ፍልስጤምን በእንግሊዝ እርዳታ የተረከቡት።

አሁን ጣታቸውን ወደ ሳኡዲ እየቀሰሩ ይመስላል። በፍረሀት ቆፈን ተሸብባ የምትኖረው ሳኡዲ ፍረሀቷ የሚያድናት አይመስልም።

በነገራችን ላይ እስራኤል ሳኡዲን ልውረር ብትል ምእራባውያን እንደሚያግዟት አያጠያይቅም። እስራኤል ግን በዜጎቿ ላይ የሳኡዲ ምድር ባለቤትነትን እየቀረፀች እያሰረፀች ነው።

👉 t.me/Seidsocial
የአለም አብያተክርስቲያናት ህብረት WCC የፍልስጤማውያን በጅምላ መጨፍጨፍ እንዲያበቃ ተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠየቀ ። ህብረቱ በጋዛ በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግና ሁሉም ወገኖች ከውጊያ እንዲቆሙም ጠይቋል።

በስሩ የ 110 አብያተክርስቲያናትን ያቀፈው ህብረቱ እስራኤል በጋዛ የምትፈፅመው ጅምላ ጭፍጨፋ አለምአቀፉን የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች የተጣሰ ጨካኝነት ነው በማለት አውግዟል።
ዘገባው የአልጀዚራ ነው።

እዚህ አንድ መራር ጥያቄ ልጠይቅ!

የትኛው የመስጅድ ህብረት ወይንም የኡለማኦች ህብረት ወይንም የሙስሊሞች ካውንስል ክለ ጋዛ ድምፁን አሰማ ? የትኛው እስራኤልን አወገዘ ? የትኛው በጋዛ የሚፈፀመው በቃላት የማይገለፅ ጭካኔ እንዲቆም ለአለምአቀፉ ማህበረሰብና ለሙስሊሙ አለም ጥያቄ አቀረበ ?
አያችሁ ውድቀታችን እስከዚህ ድረስ ነው!!

አንድ ነገር እርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ ። ለጋዛዊያን ከሙስሊሙ አለም ይልቅ ሙስሊም ያልሆነው ፍትህ ወዳድ ህዝብ ያዝንላቸዋል !! እኛማ ማፈሪያ ነንኮ !

👉 t.me/Seidsocial
የቱርክ ቀይ ጨረቃ ማህበር ወደ ጋዛ ገብቶ በረሀብ የተጎዱ ፍልስጤማዊያንን እየመገበ ይገኛል።
በዚህም መሰረት የምገባ ዘመቻውን በማስፋት በአሁኑ ሰአት የቱርክ የቀይ ጨረቃ ማህበር በየቀኑ 15,000 ጋዛዊያንን እየመገበ ይገኛል ።

ማህበሩ የተደራሽነት አቅሙን ለማስፋፋት እየተንቀሳቀሰ ሲሆን ቱርክ ወደ ጋዛ የምታጓጉዘዘውን እርዳታ አጠናክራ ቀጥላለች።

ከ 13 በላይ እርዳታ የያዙ መርከቦችንና በርካታ የአይሮፕላን በረራዎችን ለጋዛ ነዋሪዎች ያጓጓዘቺው ቱርክ በረሀብ ለሚሰቃየው የጋዛ ህዝብ ማስታገሻ ሆናለች።

በርካታ ህፃናት በረሀብ ለመሞት እያጣጣሩ ባሉባት ጋዛ የምግብ እርዳታ በእጅጉ አስፈላጊ ነው። የቱርክ ቀይ ጨረቃ ማህበር ዛሬ በሰጠው መግለጫም " ከፍልስጤማውያን ወንድሞቻችን ጎን እስከመጨረሻው እንቆማለን " ብሏል። መረጃው የ Daily Sabah ነው።

👉 t.me/Seidsocial
የእስራኤል ጦር ከአራት የአረብ ሀገራት ጦር ጋር ሲያደርግ የነበረውን ትልቅ የውይይት ስብሰባ ማጠናቀቁን አስታወቀ።

ከእስራኤል ጋር ሆነው በቀጣይ አብረው በሚሰሩባቸው ሁኔታዎች ላይ የመከሩት አራት ሀገራት ሳኡዲ አረቢያ ፣ ግብፅ ፣ ዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ እና ጆርዳን መሆናቸውን የእስራኤል ጦር አሳውቋል። በባህሬይኗ ዋና ከተማ ማናማ በተደረገው በዚህ ትልቅ ምክክር ላይ እስራኤል እና አራቱ የአረብ ሀገራት በወታደራዊ ዘርፍ አብረው የጋራ ጠላቶቻቼውን መመከት የሚያስችላቸውን ውይይት ማድረጋቸውን ነው እስራኤል ያስታወቀቺው።

እስራኤልና የአረብ ሀገራት ወዳጅነታቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።
መረጃው የ Gaza Now ነው

👉 t.me/Seidsocial
እናትነት ግን እንደት ይገለፃል ?
እንደዚህ አይነት ልጅነትስ ?
ድህነት ግን 😢