Seid Social
9.03K subscribers
2.19K photos
322 videos
6 files
1.39K links
አለም አቀፋዊ መረጃዎች ምልከታዎችና ታሪካዊ ክስተቶች ይቀርቡበታል
Download Telegram
በዘንድሮው የሀጂ ጉዞ የሞቱት ሁጃጅች ቁጥር 1,301 መድረሱን ዛሬ ሳኡዲ አረቢያ አሳውቃለች። ይህም በሙቀት ምክንያት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሁጃጅ የሞተበት ሆኖ ተመዝግቧል።

ሳኡዲ አረቢያ ዛሬ እንዳሳወቀቺው አብዛኛው የሞቱት ህገወጥ ሀጃጆች ናቸው ብላለች። ከሞት የተረፉ ሁጃጆች በበኩላቸው ከሳኡዲ መንግስት በቂ ድጋፍ እንዳልተደረገላቸውና በሙቀቱ ካለምንም ውሀና መጠለያ ብዙ ኪሎሜትሮችን ለመጓዝ መገደዳቸውን ገልፀዋል። ይህም በርካታ አጋሮቻቼው እንዲሞቱ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።

ሳኡዲ አረቢያ ለሀጅ ፈቃድ የሌላቸው በሚል 330,000 ሁጃጆችን በፖሊስ ማሰሯና ማባረሯ ይታወቃል። ከዚህ የፖሊስ ማባረር የተረፉት ደግሞ የመጓጓዣ አገልግሎት የውሀና የማረፊያ ቦታ እንዳያገኙ በመደረጉ ብዙዎቹ መሞታቸውን ነው Middle east eye ያስነበበው። ይህም ከ 1,300 በላይ ሁጃጆች እንዲሞቱ አድርጓል።

ሳኡዲ አረቢያ በበኩሏ ዛሬ በሰጠቺው መግለጫ ከሞቱት ውስጥ 85% የሚሆኑት "ህገወጥ" ሁጃጆች ናቸው በማለት ጉዳዩን ለማስተባበል ሞክራለች።
የሳኡዲ የሀጂና ኡምራ ሚኒስትር እንዳሳወቀው " እኛ ያዘጋጀነው መጓጓዧና ሌሎች አቅርቦቶች ለህጋዊ ሁጃጆች ብቻ ነው በነርሱ ቁጥር ልክ ቦቻ ነው ያለ ሲሆን ሌሎቹ በእርዳታ እጥረትና የነፍስ አድነሰ ስራም ባለመሰራቱ ይህ ሁሉ ሁጃጅ ሊሞት ችሏል።


ከሟቾቹ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት ግብፃውያን ናቸው። መረጃው የ Middle east eye ነው።
👉 t.me/Seidsocial
እስራኤል ዛሬ በፈፀመቺው የአየር ጥቃት 10 የኢስማኢል ሀኒያን ቤተሰቦች ገድላለች።
ወላሂ ይሄ ሰው ለካ ተፈተነ !!

ባለፈው በፈፀመቺው ጥቃት ሶስት ልጆቹና አራት የልጅ ልጆቹ የተገደሉበት የሀማሱ መሪ ኢስማኢል ሀኒያ በዛሬው እለትም 10 ቤተሰቦቹን በእስራኤል የአየር ጥቃት አጥቷል። ከተገደሉት የኢስማኢል ቤተሰቦች ውስጥ እህቱ ትገኝበታለች።

ይህንን የመርዶ ዜና እንደት እንደሚቋቋመው አላውቅም። ባለፈው ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ሸሂድ ሲሆኑበት ያሳየው ፅናት እጅግ አስገራሚ ነበር። ለአላህ ሸሂድ ልጆቼንና የልጅ ልጆቼን አስቀደምኩኝ ነበር ያለው።
ብቻ በጣም ያማል ! ኢስማኢል እጅግ ተፈተነ!
ይህ ግፍ ግፍ ይከፈላል !! መቼም ለማይሽረው ጠባሳ ፂዮናዊያኑ ዋጋ ይከፍላሉ !

👉 t.me/Seidsocial
ካናዳ በሀማስ ላይ ማእቀብ ጣለች።

የካናዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዛሬው እለት እንደገለፀው ሀማስ በእስራኤል ላይ ለፈፀመው ጥቃት ካናዳ በሀማስ ላይ ማእቀቦችን መጣሏን ገልፃለች።
ካናዳ ሀማስን በሰብአዊ መብት ጥሰት እገታ እና ሽብር በመወንጀል ነው ማእቀቡን የጣለቺው።

የካናዳ ውጭጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ በሰጠው መግለጫ
" ዛሬ ለሀማስና አጋሮቹ ግልፅ መልእክት አስተላልፈናል መልእክቱም ሽብርተኝነት በጭራሽ የምንታገሰው አለመሆኑን ነው። ከእስራኤል ህዝብ ጎን እንሰለፋለን የታገቱት ምርኮኞችም በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን " ብሏል።

ንፍቅና ከነ ሙሉ ውርደቷ ምእራባውያን ላይ ተሰብሰባለች!
ሁሉም የሚገለባበጥበት ቀን ይመጣል !

👉 t.me/Seidsocial
ፌስቡክ የእስማኢል ሀኒያ ቤተሰቦች በእስራኤል ተገደሉ ብየ ስለፖሰትኩ ብቻ አካውንቴን መፖሰት እንዳልችል አግዶኛል።
መቼስ የምእራባውያን ቆሻሻነት ልክ የለውም።
ስለዚህ ከቻልኩ በዚህች የቴሌግራም ቻናል ብቻ ለመፃፍ እሞክራለሁ ።
መረጃዎቹ ይጠቅማል ካላችሁ ተደራሽ እንዲሆን የበኩላችሁን ብታደርጉ ደስ ይለኛል። ካልሆነም ላለው ጥቂትም ሰው ቢሆን የቻልኳትን ለማስተላለፍ እሞክራለሁ ።
ሳኡዲ ባትደርስላት ልንትኮታኮት የነበረቺው አሜሪካ እንደት በሳኡዲ እርዳታ ተረፈች ?
ለመሆኑ አሜሪካን ያተረፈው ያ ስምምነት ምን ነበር ?
ሳኡዲ ምን ለማግኘት ብላ ሙስሊሙንና አረቡን አለም ከድታ የአሜሪካ ጀርባ አጥንት ሆነች ?
ታሪክን የሗሊት ተመልሰን ያን ምስጢራዊ ስምምነት እንዳስሳለን


https://youtu.be/zUPCY-zXh9g?si=80av97xSy5HzSKxF
Seid Mohammed Alhabeshiy የሚለው ዋናው አካውንቴ እግድ ላይ ስለሆነ በአድሱ የፌስቡክ አካውንቴ ጓደኛ መሆን የምትሹ በቀጣዩ ሊን Friend request ልትልኩልኝ ትችላላችሁ ።

ከዚህ በሗላ ፌስቡክ ላይ በዚህኛው አድሱ አካውንት ነው የምጠቀሙው። ስሙም ከቀድሞው ጋር ተመሳሳይ ነው ።
የአካውንቱ ሊንክ

https://www.facebook.com/profile.php?id=61551466234124
የእስራኤል ወታደሮች እኝህን ፍልስጤማዊት አዜውንት እናት በወታደራዊ ውሻቸው ሲያስነክሱ የሚያሳየው እጅግ ሰቅጣጭ ልብ ሰባሪ ምስል መውጣቱን ተከትሎ የእስራኤል ወዳጆችን ጭምር ማስቆጣቱ እስራኤልን አስደንግጧል።

እናም የእስራኤል ጦር ዛሬ በሰጠው አስቂኝ ማስተባበያ "ውሻው በሀማስ ተማርኮብን ነበር ውሻው በሀማስ እጅ ነበረ ከዚያም ሴትዮዋን ያስነከሳቸው ራሱ ሀማስ ነው ። ሀማስ ውሻውን ከማረከ በሗላ ወጥመድ ሰርቶበት ወታደሮቻችንም ውሻውንም ገድሎታል "የሚል አይን ያወጣ የቅጥፈት መግለጫ አውጥቷል። መቼስ ህፃናትን አሸባሪ ናቸው እያለ ለሚገድል አረመኔ ሀይል ይህንን ቢል አይገርም ይሆናል።

የሚደንቀው ግን ውሻውን ከሗላ ይዞት ፓውዛ አብርቶ የሚያስነክሰው የእስራኤል አረመኔያዊ ወታደር እዚያው ፎቶው ላይ እያለ ለማስተባበል መሞከራቸው ነው !

ኢንሻአላህ አንድት የምታስጠልላቸው ዛፍ እንኳ የሚያጡባት ጊዜ ትመጣለች ።

t.me/Seidsocial
Seid Social pinned «Seid Mohammed Alhabeshiy የሚለው ዋናው አካውንቴ እግድ ላይ ስለሆነ በአድሱ የፌስቡክ አካውንቴ ጓደኛ መሆን የምትሹ በቀጣዩ ሊን Friend request ልትልኩልኝ ትችላላችሁ ። ከዚህ በሗላ ፌስቡክ ላይ በዚህኛው አድሱ አካውንት ነው የምጠቀሙው። ስሙም ከቀድሞው ጋር ተመሳሳይ ነው ። የአካውንቱ ሊንክ https://www.facebook.com/profile.php?id=61551466234124»
ፍልስጤም-ጋዛን የተመለከቱ አዳድስ መረጃዎች

፨ በሀማስና በእስራኤል መካከል የሚደረገው ፍልሚያ እንደገና ተፋፍሞ በቀጠለበት በዛሬው እለት ሹጀይኢያን ጨምሮ በተለያዩ የጋዛ ከተሞች ከፍተኛ ውጊያ ሲደረግ ውሏል። በውጊያው እስራኤል ሀማስ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሻለሁ ያለች ሲሆን ከደርዘን በላይ የሀማስ ተዋጊዎችን መግደሏን አስታውቃለች። ሀማስ በበኩላቸው የእስራኤልን ወታደራዊ ስብስብ በተሳካ ሁኔታ መምታታቸውን ገልፀው ከፍተኛ ውድመትም እንዳደረሱ አስታውቀዋል።

፨ የቱርክ የደህንነት ሀላፊ ከሀማስ አመራሮች ጋር በዛሬው እለት ተገናኝቶ መክሯል። ቱርክ ጦርነቱ ከተጀመረ ጀምሮ በፖለቲካና የደህንነት አመራሮቿ በኩል ከሀማስ ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ምክክሮችን ስታደርግ ቆይታለች። ውይይቶቹና ውጤታቸው ምስጢር እንደመሆኑ በግልፅ የታወቀ ነገር የለም።

፨ በጎላን ተራራ በሰፈሰው የእስራኤል ጦር ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ከ 21 በላይ የእስራኤል ወታደሮች መጎዳታቸው ታውቋል ። ከነዚህ ውስጥ ሶስቱ በሞት አፋፍ ላይ መሆናቸውም ተገልጿል።

፨ እስራኤል እና ሂዝቡላህ የሚያደርጉት የውጊያ ልውውጥ እንደቀጠለ ሲሆን ዛሬ የእስራኤል አየር ሀይል በፈፀመው የሚሳኤል ጥቃት ሶስት የሂዝቡላህ ወታደሮች መገደላቸው ታውቋል። ሂዝቡላህ በወሰደው የአፀፋ እርምጃ ከ 21 በላይ የእስራኤል ወታደሮችን በጎላን ተራራ ያቆሰለ ሲሆን ሶስቱ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው የሞት አፋፍ ላይ መሆናቸውን እስራኤል አሳውቃለች ። ሁለቱም ሀይሎች ወደ ሙሉ ጦርነት እየተጓተቱ ይገኛሉ።

፨ ሀማስ አቅሙን እንደገና እያደራጀ መሆኑ ታውቋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ አዳድስ ሙጃሂዶችን እያፈራ የሚገኘው ሀማስ በርካታ የጦር መሳሪያዎችንም እያመረተ ይገኛል። በተለይም ደግሞ ከእስራኤል ተተኩሰው ያልፈነዱ ሚሳኤሎች ለሀማስ ከፍተኛ የመሳሪያ ማምረቻነት እያገለገሉ የሚገኙ ሲሆን ሀማስ እስራኤልን ለረጅም ጊዜ መክቶ እንዲዋጋ ያስችለዋል።

፨ የእስራኤል አውሮፕላን ባጋጠመው ችግር በቱርክ አንታሊያ ለማረፍ የተገደደ ሲሆን ቱርክ አይሮፕላኑ ምንም አይነት ነዳጅ እንዳይሞላለት አዛለች። ቱርክንም ለቆ እንዳይወጣ ትእዛዝ ሰጥታለች።
ቱርክ በእስራኤል ላይ የንግድ ማእቀብ የጣለች ሲሆን በዚህም በእስራኤል የዋጋ ንረት እንዲከሰት ማድረጓን the time of Israel ዘግቧል። ቱርክ ላይ ድንገተኛ አስተራረፍ ያረፈው የእስራኤል አይሮፕላን ከፖላንድ ዋሮሶው ተነስቶ ወደ ቴልአቪቭ እየበረረ ነበረ። ቱርክ ከእስራኤል ጋር ያላትን በረራ ማቋረጧም ይታወቃል።

ስለተከታተላችሁኝ አመሰግናለሁ !

👉 t.me/Seidsocial
ኢስላማዊት ሪፐብሊክ ኢራን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አድርጋለች ። በውጤቱም ፕሬዚዳንት መሆን የሚያስችልን ድምፅ ማግኘት የቻለ ተወዳዳሪ ባለመገኘቱ ሁለቱ ከፍተኛ ድምፅ ያገኙ ተወዳዳሪዎች ከእንደገና ከአምስት ቀን በሗላ ይወዳደራሉ።

የኢራን የፖለቲካ ጎራ ለሁለት የተከፈለ ነው ። ተራማጅና ወግአጥባቂ ተብሎ ። ማህሙድ አህመድነጃድና ሟቹ ሰይድ ኢብራሂም ረኢሲ ወግአጥባቂ ከሚባሉት ውስጥ ሲሆኑ ሀሰን ሩሀኒ እና የአሁኑ ተወዳዳሪ መስኡድ ፔዚሽኪያን ደግሞ ተራማጅ ናቸው ። ወግ አጥባቂዎቹ ኢራን ሀይማኖተኛና በኢስላም ድንጋጌዎች ብቻ እንድትመራ ምእራባውያንም ዘልአለማዊ ጠላት ስለሆኑ እነርሱን መታገል እንጅ ከነርሱ ጋር አብሮ መስራት አይቻልም ብለው የሚያምኑ ሲሆን ተራማጆቹ ደግሞ ኢራን ከአለም ተለዋዋጭ ስርአት ጋር ራሷን ማስኬድ አለባት ከምእራባውያን ጋርም ቢሆን ተነጋግራ መስራት አለባት ብለው ያምናሉ።

በአሁኑ ምርጫ ከፍተኛ ድምፅ ያገኙት ተወዳዳሪዎች ተራማጅ የሚባሉት መስኡድ ፔዜሽኪያን በአንደኛነት ሲመሩ ወግአጥባቂው ሰኢድ ጃሊሊ ደግሞ ሁለተኛ ደረጃ ስለተቀመጡ ለማጣሪያ ምርጫ ሀምሌ 5 በፈረንጆቹ አቆጣጠር ይገናኛሉ።


መስኡድ ፔዜሽኪያን ኢራን አሁን እየሄደችበት ያለውን አካሔድ መቀየር አለባት ሀይማኖታዊ ወግአጥባቂነተቀን ማላላት አለባት ፤ በሴቶች ላይ ግደታ የተደረገው ሂጃብ መልበስም መቅረት አለበት ሴቶች መልበስ ካለባቸው ፈልገው ይልበሱ እንጅ በግደታ ሂጃብ ካለበሳችሁ ተብለው መታሰር የለባቸውም ብሎ ይሞግታል። ከዚህ በተጨማሪም ከምእራባውያን ጋር መነጋገርና መደራደር አለብን በዚህ ሁሉ ማእቀብና ከበባ ውስጥ ሆነን እድገት ማምጣት አንችልም ኢራን ለአለም ክፍት መሆን አለባት ብሎም ያምናል።
ሰኢድ ጃሊሊ በኢራን ፖለቲካ ጥርሱን የነቀለ ሰው ነው ። በፕሬዚዳንት ማህሙድ አህመድነጃድ ጊዜ የኢራን ዋነኛ የኑክሌያር ተደራዳሪና ምእራባውያንን ብጥርጥር አድርጎ የሚያውቅ ጉምቱ ፖለቲከኛ ነው። እርሱ ደግሞ ኢራን ራሷን ማብቃት ላይ መስራት አለባት በዋናነት ወደ ውስጥ መመልከት አለብን ይላል። ከምእራባውያን ጋር የተፈፀሙ ስምምነቶችን እኛ አላፈረስናቸውም ያፈረሷቸው እራሳቸው ናቸው ስለዚህ ከምእራባውያን ጋር በሚደረግ ድርድር ማመን ዋጋ የለውም ይልቅ ከሌሎች አጋሮች ጋር ተባብረን የምእራባውያንን ጫና መቋቋምና መታገል አለብን ይላል።

የሆነው ሆኖ ሁለቱ ተወዳዳሪዎች ከአምስት ቀን በሗላ ይለይላቸዋል።
ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ብርቱ የምርጫ ፉክክር በማድረግ ኢራን ቱርክና እስራኤል ቀዳሚ ሲሆኑ ምእራባውያን ግን ብቸኛ የድሞክራሲ ሀገር አድርገው የሚወስዷት እስራኤልን ብቻ ነው ።
ስለተከታተላችሁኝ አመሰግናለሁ !

የቴሌግራም ቻናሌን ይቀላቀሉኝ !
👉 t.me/Seidsocial
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኔ ሴት
እንደት አድርጌ ባሞግስሽ እገልፅሻለሁ ?
ብቻ አላህ ልእልናን ያጎናፅፍሽ ። የሁለት አለም ልእልናን!
እንዳንቺ ፍትህን የሚገልፃት ለፍትህም የሚታገል ሰው አላየሁም
ዛሬ እስራኤል በፍልስጥኤማውያን ላይ የምታደርሰውን ሰቅጣጭ ግፍ ሁሉ አፄዎቹ በአባቶቻችን ላይ ፈፅመውት ነበር ምናልባትም ከዚያም በላይ !

እንደ ሀገር አብረን እንቆማለን አብረን እንኖራለን ስንል አልተበደላችሁም ሊሉን የሚዳዳቸው ብዙ ከንቱዎች አሉ። አፄዎቹማ በኛ በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ በተለይም በወሎ ሙስሊሞች ላይ ያደረሱትን ግፍና መከራ ማን ፈፀመው ?! ዛሬ መስማት የሚሰቀጥጡንን ግፎች ሁሉ ኧረ ከዚያም ብዙ እጥፍ አፄዎቹ በአባቶቻችን ላይ ፈፅመውታል።

በኪነት በሙዚቃ በኮንሰርት በድራማ በልብወለድ በተረትተረት እውነታውን ቀይረህ ሰይ-ጣ**ኖቹን መልአኮች ልታደርግ ብትጣጣር ለፍተህ ትቀራለህ እንጅ እውነታውን አትቀይረውም። የመቶ አመታት ተረት ተረታዊ ታሪክ በአንድት እውነታ ከአፈርድሜ ሲበላ አይተሀል አይተናልና!!

ያልታጠቁት አርሶአደሮቹ አባቶቻችን ቀን ቀን ተገደው ቤተክርስቲያን ሄደው ማርያምና ልጇን ኢየሱስን እያመለኩ ማታ ደግሞ ተመልሰው በጨለማ አላህን እያለቀሱ እየሰገዱ ይሄን እስልምና አሳልፈውልናል ! የታጠቁት አባቶቻችን ደግሞ እስከ ህይወት ፍፃሜያቸው ጅሀድ አድርገው የጨፍላቂዎቹን አቅም አፍረክርከው ከሱዳን መሀዲስቶች ጋር ጭምር ተሰልፈው ፍፃሜያቸውን አድርሰውላቸዋል ። መሰደድ የቻሉት ደግሞ ከአርሲ እስከ ጉራጌ ፤ ከጅማ እስከ ባሌ ኢስላምን ዘርተው የጨፍላቂዎቹን ህልም በከንቱ አስቀርተውታል።

ዛሬ እስራኤል ፍልስጤማዊያንን ሞራላቸውን ለመስበር የተለያዩ አሸማቃቂ ግፎችን ትፈፅማለች። ራቁት ማስኬድ፤ በውሻ ማስበላት ፤ ቶርች ማድረግ ወዘተ ..!! ያኔም አፄዎቹ ከዚህ የበለጠን ግፍ በአባቶቻችን ላይ ይፈፅሙ ነበር ። ሽፍታው ቴውድሮስ ከእጅና ከእግር እያፈራረቀ እየቆረጠ ህዝባችንን ለመስበር ከ 6 ጊዜ በላይ ዘምቶ ነበረ። " ምግቡንስ ፋጢማ ታበላዋለች ቂ*ጡን ማን ይጠርግለታል " እያለ ሁለት እጆቻቼውን ቆርጦ በአንገታቸው ያንጠለጠለውን የቴዎድሮስን ግፍ እኛም ታሪክም አላህም አንረሳውም !!!! የርሱን ሌጋሲ ይዞ የሚመጣ ሁሉ ዘልአለማዊ ጠላታችን ነው Our perpetual Enemy !! ግና ቴዎድሮስ አላሸነፈንም ! ከአንድት አምባ ሳይወጣ በጠላቱ ላይ አንድት ጥይት የመተኮስ አቅም ሳይኖረው የውርደት ሞቶን ሞቷል። እና ግን እስልምናችንን ተረክበናል ! ቴዎድሮስ ተቆረጠ እንጅ ኢስላማችን አልተቆረጠም !

አፄ ዮሐንስ ወይ " ተጠመቅ ወይ ሀገር ልቀቅ ብሎ " ብሎ ከቴዎድሮስ የተረከበውን ሌጋሲ ለማስቀጠል ብዙ ግፍ ብዙ መከራ በአባቶቻችን ላይ አድርሷል። ግና እንኳንስ እርሱና አስክሬኑም ኢትዮጵያ ውስጥ ለመኖር አልታደለም ነበር ። የውርደትን ፅዋ ተጎንጭቶ ዛሬ ጭንቅላቱ እንደ ከበሮ በካርቱም ሙዚየም ውስጥ ተሰቅሎለት ይኖራል። አባቶቻችንን መሻኢኾቻችንን ሀይማኖታችሁን ልቀቁ ብሎ እጅ ቆርጧል ፤ ምላስ ቆርጧል ፤ ያልሰራው ማሸማቀቅም አልበረም ግና የእርሱ መጨረሻ ራሱ መቆረጥ ሆነ ግፍ ባለቤቱን አይለቅማ !!!

ዮሐንስና ምንሊክ የቃሉ ሙስሊሞችን ሰብሮ ለማስጠመቅ በጋራ ጦራቸውን አዋጥተው ብዙ ጭፍጨፋ ፈፅመዋል ። ግና የቃሉን ሙስሊም አጠፉት ? ሀይማኖቱን ማስቀየር ተሳካላቸው ? ከላ !!! ዛሬም የቃሉ ሙስሊም ከ 99 % በላይ ሀይማኖቱን እንደያዘ አለ ። የጠፊት እነርሱ እንጅ ሊያጠፉት የሞከሩት ሙስሊም አልነበረም ።

ይህንን እውነታ የማይቀበሉ ጭራሽ አልተበደላችሁም ብለው የሚሞግቱን ብዙ ወገኖች አሉን ። እንደውም አንዳንዶቹ " ታዲያ ብትበደሉ ምን ችግር አለው እንግዳኮ ናችሁ ተቀብለናችሁኮ ነው " የሚሉም ድፍንነታቸውን በምንም ለማስረዳት የሚከብዱ መሀይሞችም አሉ ።

የሆነው ሆኖ አፄዎቹን ያዋረደ አካሔድ ማንንም አያስከብርም !
አፄዎችን ያጠፋ ትግልም ማንንም አሸናፊ አያደርግም !

👉 t.me/Seidsocial
ቱርክ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን እያደራደረች ትገኛለች።
የሁለቱ ሀገራት ተወካዮችም በአንካራ ከትመዋል።

በቱርኩ የውጭጉዳይ ሚኒስተር ሀካን ፊዳን በሚመራው በዚህ ድርድር የኢትዮጵያ የውጭጉዳይ ሚኒስትር ታየ አፅቀስላሴ እና የሶማሊያው አቻቼው አህመድ ሙአሊም ፈቂ ሀገራቸውን ወክለው እየተደራደሩ ይገኛሉ።

የቱርኩ ውጭጉዳይ ሚኒስተር ሀካን ፊዳን ጉዳዩን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለቱ ሀገራት ቁርሾ ውስብስብ መሆኑን ገልፀው ሁለቱ ሀገራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰው ችግራቸውን በውይይት እንዲቀርፉና በጋራ አብረው መስራት እንዲችሉ ቱርክ አበክራ ትሰራለች ብለዋል።
ሁለቱም ሀገራት ለፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ሙሉ ፍላጎታቸውን መግለፃቸውንና በኤርዶጋን ሙሉእምነት እንዳላቸው ማሳወቃቸውን የተናገሩት ፊዳን በድርድሩ ሂደት እየታዩ ያሉት ለውጦች እጅግ አመርቂ ናቸው ብለዋል።

ቱርክ በሁለቱ ሀገራት መቀራረብና ወዳጅነት ያላት እምነት የበለጠ እንዲበረታ ያደረገ ውይይት እየተካሄደ ነውም ብለዋል። ሁለቱ ሀገራት ለስምምነት መቃረባቸውም ታውቋል።

መረጃው የቱርኩ መንግስት የዜና ወኪል TRT world ነው ።
👉 t.me/Seidsocial
ያልቀደሰው የህንድና እስራኤል ጋብቻ በጋዛ ላይ !!
አሜሪካ ያልቻለቺውን ህንድ እስራኤልን መታደግ ይቻላታል ?
ዛሬ እስራኤል አሳማሚ ቅጣት ተከናንባለች ። እንዴት ?
የየመን አንሷሩሏህ ሁቲዎች አሜሪካ ያልታጠቀቺውን መሳሪያ ታጥቀዋል ። ምንድነው እርሱ ?
የሁቲዎችን ግስጋሴ ማን ማስቆም ይቻለው ይሆን ?

የሳኡዲና የቱርክ የጦር ትብብር እውነታ ?
ሁሉንም ከዝግጅቱ ታገኛላችሁ ። ትመለከቱልኝም ዘንዳ ጋበዝኳችሁ

https://youtu.be/90qZgXLNWig?si=lzMOkI8TtTV7lTKh
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
" ከእንቅልፌ ጧት ስነሳ ሁሌም ስለጋዛ አለቅሳለሁ ሁሌም አለቅሳለሁ እኔ 80 አመቴ ነው በዚህ ሁሉ እድሜየ እንደዚህ አይነት የዘር ማጥፋት በአይኔ ሲፈፀም አይቼ አላውቅም "
ይህ የዝነኛው አሜሪካ ሙዚቀኛና የጥበብ ከያኒ የሮጀር ወተርስ ንግግር ነው።
ሮጀር ወተርስ ከፅዮናዊው ፒርስ ሞርጋን ጋር ባደረገው ሙግት ወይንም ቃለመጠይቅ የብዚዎችን ልብ ነክቷል ። ለፍልስጤማውያን ያለው አዘኔታ እስከዚህ ተብሎ የሚገለፅ አይደለም!
የጋዜጠኛው አድሎኝነት ግን አሳፋሪ ነበር
አይ እስራኤል!
ሲለምኗት እምቢ ብላ ሲጎትቷት የሆነች ሀገር ።

በዛሬው እለት ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ለጆ ባይደን ደውሎ ከሀማስ ጋር የተኩስ አቁም ማድረግ እንፈልጋለንና ቶሎ አሸማግሉን ብሏል። የእስራኤል ፓርላማም በተኩስ አቁም ስምምነቱ ላይ ለመምከር ተሰብስቧል።

ሰሞኑን የእስራኤል የጦር ጄኔራሎች እስራኤል አስቸኳይ ተኩስ አቁም ከሀማስ ጋር የማትፈፅም ከሆነ ከፍተኛ ኪሳራ ይደርስባታል የጦር መሳሪያችንም እየተመናመነ ነው እያሉ ጠቅላይ ሚኒስተር ኔታኒያሁን እየጨቀጨቁ እንደነበር ነግሪያችሁ ነበር።

እናም ኔታኒያሁ ከጦር ጄኔራሎቹ ጋር ከመከረ በሗላ የተኩስ አቁም መደረግ እንዳለበት አምኗል። በዛሬው እለትም ለባይደን ደውሎ አደራድሩን ሲል ጠይቋል።

ከዚህ በፊት የተደረጉ የተኩስ አቁም ሙከራዎችን ሁሉ በእብሪት ውድቅ ስታደርግ የነበረቺው እስራኤል ዛሬ ላይ ይህን ማለቷ የደረሰባትን ከባድ ኪሳራ ነው የሚያሳየው።
አሜሪካም አደራዳሪዎችን አነጋግራ ለሀማስ መልእክት ልካለች ።

ሙጃሂዶቹን ግን በምን ቃል መግለፅ ይቻላል ???

👉 t.me/Seidsocial
በአብይ አህመድና በአዳነች አቤቤ መካከል ያለው የስልጣን ልዩነት ምንድን ነው ?
ሁለቱም ከከተማ ከንቲባነት የዘለለ ስልጣን የላቸውምኮ !

ሰው ወጥቶ መግባት ከበደው ! ዛሬ ላይ የልጆቻቼውን መመረቅ ለሚጠባበቁ ተማሪዎች 3 አውቶቢስ ተማሪዎች ከአድስ አበባ መቶ ሜትሮች ርቀት ላይ ታገቱላችሁ የሚል ዜና ከመስማት በላይ ምን የሚሰብር ነገር አለ ???
ከከተሞች ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብኮ ከሁሉም ነገር ውጭ ሆኗል ! ኢኮኖሚ ትምህርት ሌሎች አገልግሎቶች ይቅርና ወጥቶ መግባት ርቆበታል ህልም ሆኖበታል !
ይህንን ህመም መሸፈን ይቻል ይሆን ??

t.me/Seidsocial
የኦሮሞ ልዩ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ የጁሙአ ሶላትን ሰግዶ ሲወጣ በጥይት ተደብድቦ ተገድሏል ።
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን !!!

በጣም ልብ የሚሰብር ክስተት ነው ። አስተዳደሩን የገደለው ሰው ወዲያው የተገደለ ሲሆን ወንድማችን ግን የጁሙአ ሶላቱን ሰግዶ ሲወጣ ፍፃሜው ሆኗል።

አላህ ከሸሂዶች ያድርገው !
ገዳዮቹንም አላህ ይበቀልለት !

በዚህ አይነት ቆሻሻ አካሔድ የሚመጣ አንዳች ውጤት እንኳ አይኖርም።
ያለንበት ተጨባጭ በጣም ያሳዝናል !!!

👉 t.me/Seidsocial
ገዳዩ አሸባሪው ኦነግ ሸኔ መሆኑ ተረጋግጧል!

የኦሮሞ ልዩ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊን በዛሬው እለት ጁሙአ ሰግዶ ሲወጣ የገደለው ኦነግ ሸኔ መሆኑን የዞኑ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አሳውቋል።
ወንድም አህመድ አሊ ህዝብን ከህዝብ ለማስታረቅ ብዙ ሲለፋ የነበረ የሰላም አርበኛ እንደነበረ የገለፀው ዞኑ ይህ ያበሳጨው አሸባሪው ኦነግ ሸኔ በዛሬው እለት የበቀል እርምጃ ወስዶባታል።

ወንድማችን አህመድ ከ መስጅ ጁሙአን ሰግዶ ሲወጣ ጨካኞቹ ነፍሱን ነጥቀውታል።

አላህ በጀነቱ ይቀበለው ከሸሂዶችም ያድርገው ።
ግፈኞቹን አሸባሪዎቹን የእጃቸውን ይስጣቸው አላህ ይበቀላቸው !!

👉 t.me/Seidsocial