LearnEthiopia(ExitExam/EntranceExam/NationalExam-G8/JobExam/GATExam)
10.3K subscribers
939 photos
5 videos
7 files
1.16K links
Ethiopian Universities Entrance Exam/Exit Exam & GAT Exam/Jobs Exam/National Exam. Largest Harmonize E-Library, Jobs and Scholarship Portal.
Download Telegram
Jigjiga University

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና የወሰዱ የተቋሙ ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ገልጿል

ዩኒቨርሲቲው ያስፈተናቸው ተማሪዎች ውጤት በተቋሙ ሬጅስትራር አማካኝነት ይፋ መደረጉንና ተማሪዎችም ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ አሳውቋል።
#HawassaUniversity #89%

የ2016 ዓ.ም ሃገርአቀፍ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተናን ለመጀመሪያ ግዜ ከወሰዱት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓም የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተመራቂ ተማሪዎች መካከል #ከ89% በላይ የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል::

ፕሬዚደንት ዶ/ር አያኖ በራሶ 👏👇

"ውድ ተመራቂ ተማሪዎቻችን:-
ሁላችሁም የሃገራቀፍ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ የዓመታት ልፋታችሁን የመጀመሪያ ምዕራፍ በድል ስላጠናቀቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!

ውድ የዩኒቨርሲቲያችን መምህራን እና አመራሮች እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞች:-
የተማሪዎቻችን ስኬትም ሆነ ውድቀት ከራሳቸው ከተማሪዎቹ ትጋትና ቁርጠኝነት በተጨማሪ በእናንተ ያላሰለሰ ጥረትና ድጋፍ ላይ የሚወሰን በመሆኑ በልጆቻችን ጥሩ ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ!

በዚህ ዙር የማለፊያ ውጤት ያላገኛችሁ ተማሪዎች ደግሞ ለሚቀጥለው ዙር ፈተና በተሻለ ዝግጅት ራሳችሁን እንድታበቁ አደራ እላለሁ!"

ዶ/ር አያኖ በራሶ
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት
                  
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና የወሰዱ የተቋሙ ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ያስፈተናቸው ተማሪዎች ውጤት በተቋሙ ሬጅስትራር አማካኝነት ከሰዓታት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
#WolloUniversity

የመውጫ ፈተና የወሰደችሁ የወሎ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ ከአሁኑ ስዓት ጀምሮ ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑን ግቢው አሳውቋል።

እንደ ኢንስቲትዩት ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ካምፓስ ከተፈተኑት ተማሪዎች 75% ተማሪዎች ማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል።

👉Software Engineering 100% pass
👉Industrial Engineering 100% pass
👉Architecture 100% pass


ምንጭ፡ የኮምቦልቻ ካምፓስ የተማሪዎች ህብረት
#WerabeUniversity

በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን  የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከወሰዱት የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የ2016 የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ከ84% በላይ  ተማሪዎች  የማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል::
#MizanTepiUniversity

የ2016 ዓ.ም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። በዚህም መሰረት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ዉስጥ 74% ማሳለፍ ተችሏል።

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት በተመራቂ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና የተገኘዉን ዉጤት አስመልክተዉ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዶ/ር ዋቆ ገዳ (ፕሬዚደንት)
#PrivateCollege #ExitExam

የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ውጤት ከትምህርት ሚኒስቴር ለተቋማቱ በመላክ ላይ መሆኑን ሰምተናል።

የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ሲደረግ እናሳውቃቹሃለን።።

የመውጫ ፈተና ውጤት ለመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች ቀድሞ የተላከ ሲሆን ተማሪዎችም ውጤታቸውን በተቋማቸው በኩል በማየት ላይ ይገኛሉል።
#WolkiteUniversity

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ካሉት 51 የቅደመ-ምረቃ ፕሮገራሞች በ50 ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ያስፈተነ ሲሆን በመደበኛ መርሀ-ግብር 85.07% በማሳለፍ በ2015 የነበረውን ከፍተኛ ውጤት በሰፊ ልዩነት ወደ ላቀ ደረጃ አሻሽሏል።

በተከታታይ ፕሮግራም የተፈተኑት ተማሪዎችን ጨምሮ የ2016 አማካይ ውጤቱ 82% ሲሆን በ10 ፕሮግራሞች ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ(100%) ማሳለፍ ችሏል።
#InjibaraUniversity

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች #83% የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል።
#BongaUniversity

4ኛው ትውልድ የሆነው ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ 87.47% ተማሪዎቹን በመውጫ ፈተና አሳለፈ!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ 869 ወንድና    400 ሴት 1269 ተማሪዎችን አስፈትኖ 773 ወንድና 337 ሴት በድምሩ 1110 (87.47%) ተማሪዎችን ማሳለፍ ችሏል፡፡
#SalaleUniversity

በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከወሰዱ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች #86% የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል።
#BongaUniversity

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከወሰዱ ዕጩ ተመራቂዎች መካከል 87.47 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ካስፈተናቸው 1,269 ተማሪዎች 1,110 (87.47 በመቶ) ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡
#WachamoUniversity

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በ2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች በተሰጠው የመውጫ ፈተና 86.13% አሰልፏል
#WollegaUniversity

የወለጋ ዩንቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ውጤት

College of Social Science and Humanities

1. Anthropology =100%
2. Civics and Ethical Studies=100%
3. Geography & Environmental Studies=100%
4. Governance & Development Studies=100%
5. History & Heritage Management = 100%
6. Political Science & International Relation=100%
7. Social Work = 100%
8. Sociology = 100%

Overall pass rate=100%


Institute of Health Sciences

1. Pharmacy program=100%
2. Nursing and midwifery=100%
3. Public Health=83.3%

Overall pass rate=95.8%

College  of Education and behavioral Sciences

1. Special needs and Inclussive Education=100%
2. Psychology=92.86%
3. Educational planning and Management=94.2%
4. Adult Education and Community Development =85.7%

Overall pass rate=93.65%

College of Engineering and Technology

1. Architecture 100%
2. Urban planning and Design 100%
3. Information Technology 100%
4. Information Science 100%
5. Hydraulics & water resources 100%
6. Mechanical Engineering 100%
7. Food Engineering 100%
8. Civil Engineering 100%
9. Electrical & Computer Eng. 100%
10. COTEM 86.89%
11. Surveying 85.71%
12. Computer Science 82.52%

Overall pass rate 92.4%
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ሰሞኑን የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በሁለት የትምህርት መስኮች ያስፈተነ ሲሆን፤ ካስፈተናቸው ዕጩ ተመራቂዎች የአነስቴዢያ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ እንዲሁም የሕክምና ተማሪዎች 90 በመቶ ማለፋቸውን ገልጿል።
የግል የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል?

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ውጤት ሰኔ 21/2016 ዓ.ም ይፋ መደረጉ ይታወቃል።

የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ውጤት እስካሁን ይፋ አልተደረገም። ይህንንም ተከትሎ የግል ተፈታኞች በርካታ ጥያቄዎችን ለቲክቫህ አድርሰዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ በትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልገሎት ዴስክን ጠይቀናል።

"ከግል ተፈታኞች ውጤት ጋር በተያያዘ ያልተጠናቀቁ ነገሮች በመኖራቸው ውጤቱ ይፋ አለመደረጉን" የዴስኩ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለቲክቫህ ተናግረዋል።

"ቀሪ መጠናቀቅ ያለባቸው ጉዳዮች እንዳለቁ የግል ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ይደረጋል" ብለዋል።

የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ በበኩላቸው፤ "ከግል ተፈታኞች አጠቃላይ መረጃ እና ክፍያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ውጤቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚለቀቅ" ለቲክቫህ ተናግረዋል።

ማኅበሩ 178 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በአባልነት ይዟል፡፡

ዘንድሮ 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ማስፈተናቸው ይታወቃል።