Focus On Christ
124 subscribers
274 photos
82 videos
20 files
80 links
ቆላስይስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ ሰውን ሁሉ እየገሠጽን ሰውንም ሁሉ በጥበብ ሁሉ እያስተማርን የምንሰብከው እርሱ ነው፤
²⁹ ለዚህም ነገር ደግሞ፥ በእኔ በኃይል እንደሚሠራ እንደ አሠራሩ እየተጋደልሁ፥ እደክማለሁ።
@Focusonch
@Focusonc
Download Telegram
ወደ መንፈስ ቅዱስ ሙላት በጣም ካልተጠጋን፣ የእግዚአብሔርን ቃል በእግዚአብሔር መንፈስ ውስጥ ሆነን ካላነበብን፣ የተረጋጋ መንፈሳዊ ህብረት ከእግዚአብሔር ጋር ከሌለን፣ ድምፁን ካልሰማን እና በውስጣችን የሚፈሰውን የመንፈስ ቅዱስ እርካታ ካላጣጣምን እና ካልተሰማን፣ በቅድስና ህይወት ለመኖር ስጋችንን ካልገደብን
ሁልጊዜ ደጅ፣ሁልጊዜ social media፣ ሁልጊዜ ከጓደኛ ጋር ጨዋታ፣ ሁልጊዜ የራስ ነገር፣ሁልጊዜ ትምህርት፣ሁልጊዜ ስራ ከሆነ ህይወታችን
የእግዚአብሔርን ፈቃድ አናውቅም።እውነተኛውን የእግዚአብሔርን ፍቅር እና የመንፈስ ቅዱስን ህልውና አናስተውልም።ምን ማድረግ እንዳለብን እንኳን ግራ ይገባናል።ጊዜው ይረዝምብናል።ምናደርገው ሁሉ ይሰለቸናል።እረፍት እናጣለን።
ከዚህ የከፋው የአግዚአብሔርን ነገር(መንፈሳዊውን ነገር) በስጋዊ አዕምሮአችን እንተረጉማለን።የእግዚአብሔርን መንግስት ጉዳይ ሌላው እንደሚለው እንላለን።
ከሌሎች የምንለይበት መለያ መስመሩ ይደበዝዛል።ከሌላው ጋር ተመሳሳይ የህይወት ምልልስ ይኖረናል።
ጊዜ መስጠት ላለብን ጊዜ እንስጥ! ማስቀደም ያለብንን እናስቀድም!
#ዛሬ #እስቲ #ይህን #ቃል #ይዛችሁ #በእግዚአብሔር #ፊት #በእንባ #ቅረቡ!!👇
ያዕቆብ 4:÷7_10
@Focusonch