Zoble Post
655 subscribers
10 photos
120 links
Dedicated to political affairs!
Download Telegram
አጫጫር ዜናዎች!

1ኛ✓
ሦስት ከፍተኛ የህወሓት ወታደራዊ አመራሮች ከትግራይ አዲስ አበባ ገብተዋል። አመራሮቹ ከዚህ ቀደም የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩና በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል በተደረገው ጦርነት የህወሓት ታጣቂዎችን ሲመሩ እና ሲያዋጉ የነበሩ ናቸው።

በትናንትናው ዕለት አዲስ አበባ የገቡት የህወሓት ወታደራዊ አመራሮቹ ብርጋዲየር ጄኔራል ጉዕሸ ገብረ፣ ብርጋዴየር ጄኔራል ከበደ ፍቃዱ፣ እና ኮሎኔል ንጉሥ ወልደ ገብርኤል ናቸው። ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮቹ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ የገቡበት ምክንያት በግልፅ ባይነገርም "ከህወሓት አፈንግጠው ወጥተው" ሊሆን ይችላል ተብሏል።

2ኛ✓
የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባ መቀመጡ ተነግሯል። ማዕከላዊ ኮሚቴው አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከርና ውሳኔ ለማሳለፍ መሆኑ የተሰማ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት እንደዚሁም በፌዴራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል ያለው መካረር ዋነኛ የውይይት አጀንዳ ናቸው ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ፣ ለሦስት ዓመታት ያህል በእስር ላይ በሚገኙ የአማራ ተወላጅ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ እንደዚሁም የሕዝብ እንደራሴዎች ጉዳይ ላይ ለመወያየት አጀንዳ መያዙ ተነግሯል። በፖለቲካ እስረኞቹ ጉዳይ ውይይት ይደረጋል ቢባልም አጀንዳው እስረኞቹን ስለመፍታት ይሁን አይሁን የታወቀ ነገር የለም።

3ኛ✓
የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በርካታ የመካከለኛው ምሥራቅ የሚዲያ አውታሮች ዘግበዋል። ፕሬዚዳንቱ በአዲስ አበባ ለአንድ ቀን የሚቆይ የስራ ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን፣ በቆይታቸው የሶማሌንድን እውቅና፣ እንደዚሁም እስራኤል "ቀጠናዊ ተገዳዳሪዎቼ" የምትላቸው ተርኪየ ጠቅላይ ሚንስትር ረሲብ ጣይብ ኤርዶጋን እና የሳዑዲ አረቢያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፈርሃን አል-ሳዑድ በቀናት ልዩነት በኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

4ኛ✓
አንድ የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ወደ ትግራይ ክልል እንዳይበር መከልከሉ ተነግሯል። "መቀመጫው በአዲስ አበባ የሆነና ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ዘጋቢዬ ወደ ትግራይ ክልል ሽሬ ለመብረር ሲሞክር ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፈቃድ የለህም በሚል ከቦሌ አየር ማረፊያ እንዲመለስ ተደርጓል" ሲል የዜና አገልግሎቱ አስታውቋል። የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ቡድን (RSF) በበኩሉ "መረጃ የማግኘት መብት ጥሰት ነው” ሲል በጋዜጠኛው ላይ የተደረገውን ክልከላ ተቃውሟል።
👍71👏1
አጫጭር ዜናዎች

1ኛ✓
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ በትግራይ እና በአማራ ክልላዊ መንግሥታት መካከል "አከራካሪ" በተባሉት የሑመራ፣ የአዲረመፅ፣ የኮረም አፍላ፣ የጠለምትና፣ የራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውጪ ሆነው ለብቻቸው በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲደረግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በቁጥር ፌደም/አፈ/5/13138 ለቦርዱ በጻፈው ደብዳቤ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳውቋል።

ወሳኔውን ተከትሎ፣ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ስምረት ፓርቲ "የሀገሪቱን ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት መሠረት የሚንድ፣ ተቋማዊ ነፃነትን የሚደፈጥጥ፣ ሥርዓት አልበኝነትን የሚያውጅ ነው" እንደዚሁም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር "የትግራይ ሕዝብ በከፈለው መስዋዕትነት የተገነባውን ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በመጣስ፣ አደገኛ መዘዝ የሚያስከትል ውሳኔ ተላልፏል" ሲሉ ተመሳሳይ የተቃውሞ ድምጾችን አሰምተዋል። 

2ኛ✓
የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ታጣቂዎች ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘልቀው በመግባት ቡለን እና ወንበራ ተብለው የሚጠሩ አካባቢዎችን መቆጣጠራቸው ተሰምቷል። ቡድኑ ሠራዊቱ ወደ ክልሉ እንዲገባ ከማድረጉ በፊት የፌደራል መንግሥቱ መከላከያ ሠራዊቱን ከአካባቢው ለቅቆ እንዲወጣ ማድረጉ ተሰምቷል።

3ኛ✓
የሳዑዲ አረቢያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ድኤታ ኢንጂነር ወሊድ አብደልከሪም አል-ኸሪጂን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ጋር በወቅታዊ የአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ውጥረት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል። ከአሥር ቀናት በፊት የሳዑዲው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፈርሃን አል-ሳዑድ  ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በነገው ዕለት ደግሞ የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።     

4ኛ✓
የሶማሊላንድ መንግስት በእስራኤል ዋና ከተማ ቴል-አቪቭ የኤምባሲ ህንፃ ግንባታ እና የሰው ኃይል ማደራጀት ስራ ማጠናቀቁ ተሰምቷል። ባሳለፍነው የፈረንጆቹ 2025 ዓመት መገባደጃ ላይ እስራኤል ሶማሊላንድን እንደ ነጻ እና ሉዓላዊት ሀገር በይፋ እውቅና መስጠቷ ተከትሎ ነው ኤምባሲ የመክፈት ስራ የተጀመረው። የእስራኤሉ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ሰዓር ባለፈው ወር ሶማሌላንድን በጎበኙበት ወቅት ሀገራቸው በተመሳሳይ በሐርጌሳ ኤምባሲዋን እንደምትከፍት መናገራቸው ይታወሳል።
3👍1
አጫጭር ዜናዎች!

1ኛ)✓
አቶ ጌታቸው ረዳ የምርጫ ቦርድ ውሳኔን ተቃውመው ለፍርድ ቤት ያስገቡትን ክስ በዛሬው ዕለት በፍቃዳቸው ማንሳታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሳውቀዋል። ይሄንን ተከትሎ በ7ኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ከትግራይ ክልል ውጭ ሆኖ በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድበት የፌደሬሽን ምክር ያሳለፈውን ውሳኔ የምርጫ ቦርድ ተፈፃሚ ያደርጋል ተብሏል።

2ኛ)✓
ህወሓት ግዳጃቸውን ፈፅመው በክብር የተሸኙ፣ በተለያዩ ምክንያቶች ከሠራዊት አባልነት አቋርጠው የተመለሱ፤ የአርሚ ማሰልጠኛ ቦታዎችን በተመለከተ መረጃ ሳይኖራቸው ቀርተው ወደ ቡድኑ ለመቀላቀል ያልቻሉ፣ እንደዚሁም የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩ እና በእስር ላይ የቆዩ የትግራይ ተወላጆች የህወሓትን ሰራዊት እንዲቀላቀሉ በትግራይ የተለያዩ ወረዳዎች በማስታወቂያ ጥሪ እያደረገ ነው ተብሏል።

3ኛ)✓
የመከላከያ የውጪ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሜጄር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ "የአሰብ አፈጣጠር ለአባት ሀገሩ ኢትዮጵያ እንጅ ለኤርትራ አይደለም'' ሲሉ መናገራቸው ተሰምቷል። ጄኔራሉ ከዚህ ቀደም "የኢትዮጵያ ወጣት የአሰብ ወደብን ለማስመለስ ተዘጋጅ!" ሲሉ መናገራቸው አይዘነጋም።

4ኛ)✓
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን በትናንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በጋጮ ባባ ወረዳ ማዞ ዶይሳ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ እስካሁን የ52 ሰዎች ሕይወት ማለፉንና 50 የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ የደረሱበት እንዳልታወቀ የጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።

5ኛ)✓
የመከላከያ ሠራዊቱ ከወለጋ አካባቢዎች መውጣቱን ተከትሎ "አካባቢያችሁን ከኦነግ ሸኔ መጠበቅ አለባችሁ" በሚል በምስራቅ ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞኖች የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ለወጣቶች እና አርሶ አደሮች "አስገዳጅ" ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተሰምቷል።
👍2