ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
50K subscribers
12.5K photos
346 videos
31 files
7.69K links
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Download Telegram
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ አመ ፲ወ፰፦

ተዝካረ ትንሣዔሁ ለመድኀኒነ ክርስቶስ
ተዝካረ ርደተ መንፈስ ቅዱስ (ጰራቅሊጦስ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን ፦

✿ቡላ ሰማዕት (ገብሩ ለእግዚአብሔር)
✿አንስት ንጹሐት ዘኢየሩሳሌም (ዘሰበካ ትንሣዔሁ ለመድኀኒነ)
✿አውሳብዮስ ሰማዕት (ገብሩ ለቅዱስ ሱስንዮስ)
✿ጴጥሮስ ሰማዕት ኃያል (እኁሁ ለአባ ብሶይ)
✿ሰማዕታት እለ ተቀትሉ በሃገረ ተርሴስ

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn
✞✞✞ እንኩዋን ለቅዱስ "ስምዖን ዘአርማንያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+*" ቅዱስ ስምዖን ሰማዕት "*+

=>ቅዱስ ስምዖን የአርማንያ ሰው ቢሆንም ሰማዕትነትን
የተቀበለው በሃገረ ፋርስ (በአሁኗ ኢራን አካባቢ) ነው::
ፋርስ ከ1ኛው መቶ ክ/ዘ እስከ ተንባላት (መሐመዳውያን)
መነሳት (7ኛው መቶ ክ/ዘ) ድረስ ባለው ጊዜ ብዙ
ሰማዕታት ለክብር በቅተውባታል::

+ብዙዎቹ የዚያው (የፋርስ) ዜጐች ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ
የተሰዉት ከሌላ ሃገር መጥተው ነው:: ፋርሳውያን
አብዝተው ፀሐይን ያመልኩ ነበርና ክርስቲያኖቹን
የሚያሰቃዩት ይህቺውን ፍጡር እያመለኩ እንዲንበረከኩ
ነበር::

+ቅዱስ ስምዖንም ከፋርስ ግዛቶች በአንዱ ኤዺስ
ቆዾስነትን (እረኝነትን) ተሹሞ ነበርና የመከራው ተሳታፊ
ሆኗል:: በጊዜው ክርስትና እንደ ዛሬው "ሠርግና ምላሽ"
አልነበረምና ቅዱስ ስምዖን (እረኛው) እና 150 የሚያህሉ
ልጆቹ (መንጋው) ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብዙ ሆነዋል::

+በእምነታቸው ጸንተው በመገኘታቸውም እንዲገደሉ
ተወስኖባቸው 151ዱም ተሰውተዋል::

=>አምላከ ሰማዕታት በጽናታቸው አጽንቶ ከበረከታቸው
ይክፈለን::

=>ሚያዝያ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ስምዖን ሰማዕት (አርማንያዊ)
2."150" ቅዱሳን ሰማዕታት (የስምዖን ማሕበር)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
3.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
4.አቡነ ስነ ኢየሱስ
5.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም

=>+"+ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ
አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ:
ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ
አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል
የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ
ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ
መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::+"+ (ዕብ. 6:10-13)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/zikirekdusn
#Feasts of #Miyazia_19

✞✞✞On this day we commemorate the martyrdom of Saint Simeon the Armenian✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞St. Simeon the Martyr (the Armenian)✞✞✞
=>Though St. Simeon was an Armenian he received martyrdom in the land of Persia (the now Iran). Many martyrs were glorified (as pure offerings to the Lord) in Persia from the 1st century to the rise of Muslims in the 7th century.

✞Many of the martyrs were natives (citizens of Persia) but some were foreigners that came to the country and were martyred.  Persians used to worship the Sun greatly and tortured Christians to worship and bow down to this creature.

✞As St. Simeon was appointed a Bishop of one of the provinces of Persia, he partook of the afflictions as well. In those days, Christianity was not a festivity as it is today hence, St. Simeon (the shepherd) and around 150 of his spiritual children (his flock) endured much for the sake of the love of Christ.

✞And because they were found steadfast in their faith all 151 were sentenced to death and were martyred.

✞✞✞May the God of the martyrs.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 19th of Miyazia
1. St. Simeon the Martyr (Armenian)
2. The 150 Martyrs (The followers of Simeon)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Gabriel the Archangel
2. St. Isidorus (Isidore) the Martyr
3. Abune Abiye Egzi the Righteous
4. Abune Sene Iyesus
5. Abune Yoseph Brihane Alem (Light of the world)

✞✞✞ “For God is not unrighteous to forget your work and labour of love, which ye have shewed toward his name, in that ye have ministered to the saints, and do minister. And we desire that every one of you do shew the same diligence to the full assurance of hope unto the end: That ye be not slothful, but followers of them who through faith and patience inherit the promises.”✞✞✞
Heb. 6:10-13

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)

https://t.me/zikirekdusn
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠   
/(ማቴ ፫:፫/)

እንኳን አደረሰን!

🛑 ዝክረ ቅዱሳንን ላልደረሳቸው  እናድርስ እናስፋ ስለ ሀገራችን እንጸልይ ንስሐ እንግባ!!🛑

5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

👉ሃይማኖት
👉ጾም
👉ጸሎት
👉ስግደት
👉ምጽዋት
👉ፍቅር
👉ትህትና
👉ትዕግስት
👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )   ንስሐ ግቡ።

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn
እንኩዋን ለዳግሚያ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ

=>ለስም አጠራሩ ጌትነት ይድረሰውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ትንሳኤው በሁዋላ ለደቀ መዛሙርቱ በጉባኤ 3 ጊዜ ተገልጦላቸዋል:-

1.በዕለተ ትንሳኤ ምሽት በፍርሃት ሳሉ
2.ያላመነ ቶማስን ለማሳመን በተነሳ በ8ኛው ቀን (ማለትም ዛሬ)
3.ከተነሳ ከ23 ቀናት በሁዋላ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻ ላይ ነው::

+ጌታ አርባውን ቀን ለአንዱም: ለሁለቱም በግል ይገለጥላቸው ነበር:: እመቤታችንን ግን ፈጽሞ አይለያትም ነበር::

+ጌታችን ከተነሳ በሁዋላ ለሳምንት ተለይቷቸው ስለ ነበር በቤተ ክርስቲያን ውዳሴ ማርያም እንጂ መልክዐ ኢየሱስ በማሕበር አይደገምም::

+በዚሕች ዕለት ደቀ መዛሙርቱ በጽርሐ ጽዮን ሳሉ ጌታችን "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ብሏቸዋል:: ቶማስንም "ና ዳስሰኝ" ብሎታል:: ሐዋርያው እጁን ከተወጋ ጐኑ ላይ ቢያሳርፍ በመቃጠሉ "ጌታየ አምላኬም" ሲል ጮሆ ምስጢረ ተዋሕዶውን መስክሯል::

+ጌታም ቶማስን "እስመ ርኢከኒሁ አመንከኒ" (ማለትም ስላየኸኝ አመንከኝ)! "ብጹዐንሰ እለ እንዘ ኢይሬእዩኒ የአምኑኒ" (ሳያዩ የሚያምኑ ግን ብጹዐን (ማለትም ንዑዳን ክቡራን) ናቸው ብሎታል:: (ዮሐ. 20:24)

=>ከጌታችን ከትንሳኤው: ከቅዱሱም ሐዋርያ በረከት አይለየን::

=>+"+ ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ:: በመካከላቸውም ቆሞ 'ሰላም ለእናንተ ይሁን' አላቸው:: ከዚያም በሁዋላ ቶማስን 'ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ:: እጅህንም አምጣና በጐኔ አግባው:: ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን' አለው:: ቶማስም 'ጌታዬ አምላኬም' ብሎ መለሰለት:: ኢየሱስም 'ስላየኸኝ አምነሃል:: ሳያዩ የሚያምኑ ብጹዓን ናቸው' አለው:: +"+ (ዮሐ. 20:26-29)

   <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
✝️✝️✝️Resurrection Week - Pascha Week✝️✝️✝️

+*"❇️Antipascha – Dagem Tensa’e❇️ "*+

=>Glory be to the invocation of His name, the Holy Savior Jesus Christ, after His Holy Resurrection appeared to the disciples in a group setting trice.

1. During the night of the Day of Resurrection while they were frightened
2. To make doubting Thomas believe on the 8th day after His Resurrection (which is today)
3.  And at the shore of the sea of Tiberias 23 days after His Resurrection.

✝️The Lord used to appear only to one or to two of His disciples during the forty days [before His ascent]. Nevertheless, He never left our Lady.

✝️Because our Lord was not with the disciples for a week after He rose, in the Church the doxology dedicated to Jesus is not recited in a congregation but the Theotokion is prayed.

✝️On this day, while the disciples were at the Upper Room/Tsereha Tsion, our Lord said, “Peace be unto you”. He also said to Thomas “Come and touch Me”. And when the Apostle placed his hand on the Lord’s pierced side, because he was burned, Thomas cried out, “My Lord and my God” and attested the mystery of Tewahedo (the mystery of the Hypostatic Union).

✝️And the Lord said to Thomas “be not faithless, but believing!”, “blessed are they that have not seen, and yet have believed.” (John 20:24-29)

=>May our Lord not separate us from the blessings of His Resurrection and the Holy Apostle.

+"+And after eight days again his disciples were within, and Thomas with them: then came Jesus, the doors being shut, and stood in the midst, and said, Peace be unto you. Then saith he to Thomas, Reach hither thy finger, and behold my hands; and reach hither thy hand, and thrust it into my side: and be not faithless, but believing. And Thomas answered and said unto him, My Lord and my God. Jesus saith unto him, Thomas, because thou hast seen me, thou hast believed: blessed are they that have not seen, and yet have believed.+"+
(John 20:26-29)

<<<Salutations to God>>>
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ አመ ፲ወ፱፦

ተዝካረ ትንሣኤሁ ለመድኀኒነ ክርስቶስ
ተዝካረ ዳግም ትንሣኤ

✞ወበዓለ ቅዱሳን ፦

✿አበዊነ ሐዋርያት ንጹሐን
✿ቶማስ ሐዋርያ (ዘሕንደኬ)
✿ስምዖን ሰማዕት (ዘአርማንያ)
✿፻ወ፶ ሰማዕታት (ዘሃገረ ፋርስ)
✿ጽርሐ ጽዮን ቅድስት

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት=

✞ ሰማዕቱ በብኑዳ ✞

+ቅዱስ በብኑዳ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ በምድረ
ግብፅ ተባሕትዎን መርጦ የሚኖር ገዳማዊ አባት ነው::
በበርሃ
በጾምና በጸሎት ተወስኖ ለእግዚአብሔር የምስጋናን
መስዋዕት እየሠዋ አገልግሏል::

+በዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያኖች በግፍ ሲገደሉ ቅዱሱ
ሰው በበርሃ ውስጥ ነበር:: አንድ ቀን የእግዚአብሔር
መልአክ መጥቶ
ሰማዕት እንዲሆን መከረው:: እርሱም ነጭ በነጭ ለብሶ
አምሮበት ወደ ንጉሡ ሔደ:: በፊቱም ቀርቦ በክርስቶስ
ስም ታመነ::
ብዙ ጸዋትወ መከራም ተቀበለ::

+ንጉሡ (መኮንኑ) "አመጣጥህ ወደ ሞት ሳለ ምነው
እንዲህ እንደ ሠርገኛ ማጌጥህ?" ቢለው "እኛ
ክርስቲያኖች ትልቁ
ሠርጋችን ሞታችን ነው:: ልንሔድ ከክርስቶስም ጋር
ልንኖር እንናፍቃለንና" ብሎታል::

+ቅዱስ በብኑዳ ብዙ ተሰቃይቶ: ተአምራትን ሰርቶ በዚሕች
ቀን ተሰይፏል:: የጽድቅን አክሊል ከሰማዕትነት ጋር ደርቦ
አግኝቷል::

❖ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ በረከትን ያካፍለን::

❖ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ በብኑዳ (ሰማዕት ወጻድቅ)
2.ቅዱስ ቄርሎስ: ሚስቱና 12 ልጆቹ ሰማዕታት (ከቅዱስ
በብኑዳ ጋር የተገደሉ)

በ 20 የሚከበሩ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት
 

++"+ በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን
ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ
ብጹዓን ናችሁ::
ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ:: አትናወጡም:: ዳሩ ግን
ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ
ስላለ ተስፋ
ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር
የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት
ይሁን:: +"+ (1ዼጥ.3:13-16)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/zikirekdusn
#Feasts of #Miyazia_20

✞✞✞On this day we commemorate the departure of the Righteous Martyr Saint Babnuda (Paphnute)✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Babnuda (Paphnute) the Martyr✞✞✞
=>St. Babnuda was a monastic father that chose the ascetic life and lived in the 3rd century in the land of Egypt. He served in the desert devoted to fasting and prayer offering praise to God.

✞During the Era of Persecution when Christians were brutally being slaughtered the Saint was in the desert. One day an angel of the Lord came to him and advised him to become a martyr. Hence, he clothed himself in white and went to the governor. He stood before him and testified the name of Christ. And he received much affliction.  

✞And when the governor asked the martyr, “While you have come to die, why are you adorned in such a way like a Groom?” the Saint replied, “For us Christians our death is our ultimate nuptials because we desire to depart and live with Christ.”

✞St. Babnuda was slain on this day after enduring many afflictions and performing several miracles. He has received the crowns of righteousness and martyrdom together.

✞✞✞May the Good God grant us from the Martyr’s blessings.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 20th of Miyazia
1. St. Babnuda (Paphnute) the Martyr
2. St. Cyril, his wife and his twelve children martyrs (Slain with St. Babnuda)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. Honorable Saint Mar Theodore the Martyr
2. St. John Colobos (the Short)
3. St. Kloag (Bagoug)/ Aklog/Eclogius, the Priest
4. The Emperor St. Kaleb the Righteous (Emperor of Ethiopia)/St. Elesbaan
5. Abba Ammonius of Tounah/ Tona
6. St. Sades the Meek

✞✞✞ “And who is he that will harm you, if ye be followers of that which is good? But and if ye suffer for righteousness' sake, happy are ye: and be not afraid of their terror, neither be troubled; But sanctify the Lord God in your hearts: and be ready always to give an answer to every man that asketh you a reason of the hope that is in you with meekness and fear:”✞✞✞
1Pet. 3:13-15

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)

https://t.me/zikirekdusn