ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
50.1K subscribers
12.6K photos
346 videos
31 files
7.73K links
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Download Telegram
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ አመ ፳ወ፰፦

ተዝካረ በዓሉ ለአማኑኤል (አምላክነ ዘበአማን)
ወተዝካረ ቅዱሳን (አርዕስተ አበው)

✞ወበዓለ ቅዱሳን፦

✿ሜልዮስ ጻድቅ ወሰማዕት (ጽሙድ ወመስተጋድል)
✿ብስጣውሮስ ሰማዕት (ዘሃገረ መቅሱር)
✿ዋሲሊኮስ ሰማዕት
✿ወብዙኃን ማኅበራኒሁ (ሰማዕታት)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

❖ ሚያዝያ ፳፱  ❖

✞✞ እንኩዋን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርሐዊ በዓለ ልደትና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ ✞✞

+"+ ተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን ቅዱስ አርስጦስ ሐዋርያ ወአባ አካክዮስ ጻድቅ +"+

=>ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዕለት ከምታስባቸው ቅዱሳን ሐዋርያው ቅዱስ አርስጦስና አባ አካክዮስ ቅድሚያውን ይይዛሉ::

+"+ አርስጦስ ሐዋርያ +"+

=>ቅዱስ አርስጦስ ከ72ቱ አርድእት አንዱ ሲሆን ከጌታችን እግር ለ3 ዓመታት ቁጭ ብሎ የተማረ: ፈጣሪው ከዋለበት ውሎ: ካደረበት አድሮ: የእጁን ተአምራት ያየ: የቃሉንም ትምሕርት ያደመጠ ሐዋርያ ነው::

+ከጌታችን ዕርገት በሁዋላም በጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ወጥቷል:: መጀመሪያ ከዋኖቹ ሐዋርያት ጋር በረዳትነት አገልግሏል:: ከቆይታ በሁዋላ ግን ሃገረ ስብከት ተሰጥቶት ብዙ ነፍሳትን ማርኩዋል:: አሕዛብንም ካለማመን ወደ ማመን አምጥቷል::

+በነዚህ ጊዜያት ጭንቅ ጭንቅ መከራዎች ደርሰውበታል:: ቅዱስ አርስጦስ ሐዋርያ በተሰጠው መክሊት አትርፎ ፈጣሪውንም ደስ አሰኝቶ በዚሕች ቀን አርፏል::

+"+ አባ አካክዮስ +"+

=>ዳግመኛ በዚህ ቀን አባ አካክዮስ አርፏል:: ቅዱሱ ከሕጻንነቱ ጀምሮ ንጽሕናን ያዘወተረ: በገዳማዊ የቅድስና ሕይወቱ የተመሠከረለት ነው:: ምሑርነቱንና ቅድስናውን የተመለከቱ ሰዎች በኢየሩሳሌም ላይ ዽዽስናን ሹመውታል::

+በመንበረ ዽዽስናውም ላይ እያለ ዕረፍት አልነበረውም:: ኢ-አማንያን ይገርፉት: ያስሩት: ያረሰቃዩትም ነበር:: ቤተ ክርስቲያን ስለ ተጋድሎው ጻድቅ: የዋሕና ንጹሕ ብላ ትጠራዋለች::

=>እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ረድኤት: ጸጋና በረከት ይክፈለን::

=>ሚያዝያ 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አርስጦስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
2.አባ አካክዮስ ዘኢየሩሳሌም (ጻድቅና ንጹሕ)
3.አባ ገምሶ ሰማዕት

=>ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
5.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
6.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)

=>+"+ ሰብዓውም በደስታ ተመልሰው ጌታ ሆይ! አጋንንት
ስንኩዋ በስምህ ተገዝተውልናል አሉት:: እንዲህም
አላቸው:- 'ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ
አየሁ:: እነሆ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም
ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችሁአለሁ::
የሚጐዳችሁም ምንም የለም:: ነገር ግን መናፍስት ስለ
ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ:: ስማችሁ ግን
በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ:: +"+
(ሉቃ.10:17-20)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/zikirekdusn
#Feasts of #Miyazia_29

✞✞✞On this day we commemorate the monthly feast of the Nativity of our Lord and Savior Jesus Christ, and the departures of the Saints Erastus the Apostle and Abba Acacius the Righteous✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Erastus the Apostle✞✞✞
=> was an Apostle who was one of the 72 Disciples that had learned under our Lord for 3 years by spending where He did and dwelling where our Lord dwelt, and who saw His miracles and had heard His teachings.

✞After the Ascension of our Lord, St. Erastus, once he received the Holy Spirit (the gifts of the Holy Spirit) at the Upper Room, went forth to preach the Gospel. He first served as an aid to the main Apostles.  Then, after he was allotted a diocese, he captured many souls. And he converted gentiles from nonbelief to faith.

✞And in those days, he received cruel afflictions. St. Erastus the Apostle, after bringing forth profit from the talents he was given and delighting his Creator, departed on this day.

✞✞✞ Abba Acacius✞✞✞
=>Also on this day, Abba Acacius departed. The Saint frequented a pure life from his childhood, and his ascetic life together with his holiness were attested to as well. Thence, people that saw his scholarship and sanctity ordained him as the Bishop of Jerusalem.

✞And upon his See, he had no rest. Unbelievers used to lash, imprison, and torture him. And the Church for his struggle calls him righteous, meek and pure.

✞✞✞May God grant us from the aid, grace and blessings of the Saints.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 29th of Miyazia
1. St. Erastus the Apostle (One of the 72 Disciples)
2. Abba Acacius of Jerusalem (Righteous and Pure)
3. Abba Gemso the Martyr

✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Birth of our Lord and God Jesus Christ
2. St. Arsema/Arbsima/Repsima/Hripsime the Virgin
3. St. Peter the Seal of the Martyrs
4. St. Mark of Tormak
5. St. Fikerte Kirstos the Ethiopian
6. St. Zera Kirstos (Righteous and Martyr)

✞✞✞“And the seventy returned again with joy, saying, Lord, even the devils are subject unto us through thy name. And he said unto them, I beheld Satan as lightning fall from heaven. Behold, I give unto you power to tread on serpents and scorpions, and over all the power of the enemy: and nothing shall by any means hurt you. Notwithstanding in this rejoice not, that the spirits are subject unto you; but rather rejoice, because your names are written in heaven.”✞✞✞
Luke 10:17-20

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
https://t.me/zikirekdusn
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠   
/(ማቴ ፫:፫/)

እንኳን አደረሰን!

🛑 ዝክረ ቅዱሳንን ላልደረሳቸው  እናድርስ እናስፋ ስለ ሀገራችን እንጸልይ ንስሐ እንግባ!!🛑

5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

👉ሃይማኖት
👉ጾም
👉ጸሎት
👉ስግደት
👉ምጽዋት
👉ፍቅር
👉ትህትና
👉ትዕግስት
👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )   ንስሐ ግቡ።

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn

👉
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ አመ ፳ወ፱፦

ተዝካረ ልደቱ ለአማኑኤል አምላክነ ዘበአማን
ወተዝካረ በዓላ ለድንግል ማርያም (እግዝእትነ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿አርስጦስ ሐዋርያ ክቡር (እም፸ወ፪ቱ እርድእት)
✿አካክዮስ ዘኢየሩሳሌም (ጻድቅ፥ ወየዋህ፥ ወንጹሕ)
✿አባ ገምሶ ሰማዕት
✿ወብዙኃን ማኅበራኒሁ (ሰማዕታት)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሚያዝያ ፴ ❖

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

=>እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ
ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት::
እግዚአብሔር
ግን ደግ ነውና ይሔው ሚያዝያን አስፈጸመን::

+ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ:-
*ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::
*ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል
(ሙተዋል)::

+እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪዋን ዘመን ደግሞ ለንስሃና
ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::

+"+ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ +"+

+በዚሕች ዕለት ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነ: ወንጌላዊ:
ሐዋርያ: ሰማዕት: ዘአንበሳና ርዕሰ ሊቃነ ዻዻሳት የተባለ
ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ግብፅ ውስጥ ዐርፏል::

+ቅዱስ ማርቆስ እናቱ ማርያም: አባቱ አርስጥቦሎስ
ይባላሉ:: በልጅነቱ ኦሪትንና የዘመኑን ጥበብ ሥጋዊ
በሚገባ ተምሮ
ክርስቶስን ከቤተሰቦቹ ጋር ተከትሏል::

+የመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ ሲሆን ከ120ው ቤተሰብ
በእድሜ በጣም ትንሹ (20 ዓመት) እርሱ ነበር:: ለ3
ዓመታት ከጌታ
እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን
ተቀብሎ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ ደክሟል::

+በተለይ የግብፅና የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን አባት ነው::
ክህነትን ያገኘን ከርሱ ነውና:: ቅዱስ ማርቆስ 16 ምዕራፍ
ያለውን ወንጌሉን ሲጽፍ ኪሩብ ገጸ አንበሳ በቀኙ: ሊቀ
ሐዋርያት በግራው ሆነው ይራዱት ነበር::

+ቅዱሱ ክቅዱስ ዻውሎስ: ከበርናባስና ዼጥሮስ ጋር
ተጉዟል:: ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ሰሜን አፍሪካ
አካባቢ በዚህ ቀን [በ60 ዓ/ም አካባቢ]
አረማውያን ገድለውታል::

=>ዳግመኛ በዚህ ቀን የቅዱስ ማርቆስን ወላጆችን
እናስባቸው ዘንድ ይገባል::

❖ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ) የጌታ ቅን አገልጋይ
የነበረ፡፡

❖ቅድስት ማርያም (እናቱ)
*ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ:
*ጌታችንን ያገለገለች:
*ቤቷን ለሐዋርያትና ለጌታ በስጦታ ያበረከተች ቅድስት
ናት::

+ቤቷም (ጽርሐ ጽዮን) የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን
ስትሆን ይህች ቤት መንፈስ ቅዱስ ወርዶባታል::
የእመቤታችን ግንዘትም
ተከናውኖባታል::

❖እግዚአብሔር ከሐዋርያዊው ቅዱስ ቤተሰብ በረከትን
ያድለን::

=>ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ)
3.ቅድስት ማርያም (እናቱ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት

=>+"+ . . . እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ
ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ
ማርያም ቤት መጣ:: ዼጥሮስም የደጁን መዝጊያ
ባንኩዋኩዋ ጊዜ ሮዴ የሚሏት አንዲት አገልጋይ ትሰማ
ዘንድ ቀረበች:: የዼጥሮስ ድምጽ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ
ከደስታዋ የተነሳ ደጁን አልከፈተችም:: ነገር ግን ወደ
ውስጥ ሮጣ ዼጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች::
+"+ (ሐዋ. 12:12-15)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
#Feasts of #Miyazia_30

✞✞✞On this day we commemorate the Martyrdom of Saint Mark the Evangelist and it is the last day of the Month of Miyazia✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞In this day and age where the cup of our sins has filled and is overflowing, even an hour is a precious time for repentance. Nonetheless, as God is merciful, He enabled us to complete the Month of Miyazia.

=>Though we do not notice it, in this month
*Millions have become bedridden due to illnesses
*And millions have slept (died) without attaining repentance.

=>May our God bless and give us the rest of the year for repentance and to do good.
✞✞✞Saint Mark the Lion✞✞✞
=>On this day is commemorated the departure of Saint Mark the Lion, the Evangelist, the Apostle, the Martyr and Patriarch, who was one of the 72 Disciples, as a martyr.

✞St. Mark’s mother was called Mary while his father was named Aristobulus. And after learning well in his childhood the Old Testament and the wisdom of the time, the Saint followed Christ with his family.

✞The Saint’s first name was John and was the youngest (20 years old) of the 120 followers of Christ. And after learning under the Lord for 3 years and after receiving the gifts of the Holy Spirit on Pentecost, he did labor much for the apostolic mission (evangelization).

✞He is in particular a father to the Churches of Egypt and Ethiopia. And that is because we have received priesthood - our apostolic succession (the priestly line) from him. When St. Mark wrote his Gospel, which has 16 chapters, a cherub – of a lion figure on his right and the Arch-apostle on his left used to aid him.

✞The Saint did also travel with Sts. Paul, Barnabas and Peter. Later, Arameans (nonbelievers), on this day, killed him in Northern Africa after many trials and torments.

=>Also on this day, it is meet and right for us to commemorate the parents of St. Mark.

✞St. Aristobulus (the Saint’s father) was the Lord’s servant.

✞And St. Mary (the Saint’s mother) was a righteous lady,
*who was one of the 36 Holy Women
*who served the Lord
*and who gave her home to the Apostles and the Lord as a gift.

✞And her house (The Upper Room) was the first church and there, the Holy Spirit did descend. And in that house, the shrouding of our Lady took place as well.

✞✞✞May God grant us from the blessings of the Apostle and the Apostle’s holy family.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 30th of Miyazia
1. St. Mark the Apostle
2. St. Aristobulus (the Saint’s father)
3. St. Mary (the Saint’s mother)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. John the Baptist
2. Abba Shalusi the Honorable Righteous
3. St. Gregory the Theologian
4. St. Sophia Martyr

✞✞✞“. . . he came to the house of Mary the mother of John, whose surname was Mark; where many were gathered together praying. And as Peter knocked at the door of the gate, a damsel came to hearken, named Rhoda. And when she knew Peter's voice, she opened not the gate for gladness, but ran in, and told how Peter stood before the gate.”✞✞✞
Acts 12:12-14

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠   
/(ማቴ ፫:፫/)

እንኳን አደረሰን!

🛑 ዝክረ ቅዱሳንን ላልደረሳቸው  እናድርስ እናስፋ ስለ ሀገራችን እንጸልይ ንስሐ እንግባ!!🛑

5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

👉ሃይማኖት
👉ጾም
👉ጸሎት
👉ስግደት
👉ምጽዋት
👉ፍቅር
👉ትህትና
👉ትዕግስት
👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )   ንስሐ ግቡ።

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn
Audio
"" ነገሥታትን ያጠፋቸዋል! "" (መዝ. ፻፱:፭)

"ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዳዊ"

"ወዝክረ ቅዲስ ዳዊት - ዘወርኀ ሚያዝያ"

(ሚያዝያ 23 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn
እንኳን አደረሰነ!

☞ተፈጸመ ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር፤ አሜን።
ወአመ ፴፦

✞በዓለ ቅዱሳን፦

✿ማርቆስ ዘአንበሳ (ወንጌላዊ፥ ሰማዕት ወሐዋርያ)
✿ማርያም ቅድስት (እሙ)
✿አርስጦቦሎስ ክቡር (አቡሁ)
✿ጽርሐ ጽዮን ቅድስት (ማኅደሩ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn