ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
49.8K subscribers
12.3K photos
341 videos
31 files
7.61K links
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Download Telegram
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ አመ ፰፦

ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ ስቡሕ)
ጥንተ ጾመ ድኅነት (ጾመ ረቡዕ)
ሰሙነ ሕማማት ቅድስት

✞ወበዓለ ቅዱሳን፦

✿አጋሊስ፥ ወኢራኒ ወሱስንያ (ዘተሰሎንቄ)
✿ጢሞቴዎስ አብ (ሊቀ ጳጳሳት)
✿፻ወ፶ ሰማዕታት (ዘብሔረ ፋርስ)
✿ማርያም እንተ ዕፍረት (እኅተ ጥጦስ ዘየማን)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn
††† እንኳን ለብጹዐን ጻድቃን: ቅዱስ ዞሲማስ እና አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ብጹዐን ጻድቃን †††

††† በዚህ ቀን ብሔረ ብጹዐን ውስጥ የሚኖሩ ጻድቃን ይታሠባሉ::
በሃይማኖት ትምሕርት 5 ዓለማተ መሬት አሉ:: እነሱም አቀማመጣቸው ቢለያይም ከላይ ወደ ታች:-
1.ገነት (በምሥራቅ)
2.ብሔረ ሕያዋን (በሰሜን)
3.ብሔረ ብጹዐን (ብሔረ - አዛፍ - እረፍት) {በደቡብ}
4.የእኛዋ ምድር (ከመሐል) እና
5.ሲዖል (በምዕራብ) ናቸው::

††† ከእነዚሕ ዓለማት ባንዱ የሚኖሩ የብሔረ ብጹዐን ጻድቃን:-
*ኃጢአትን የማይሠሩ::
*ለ1,000 ዓመታት የሚኖሩ::
*ሐዘን የሌለባቸው::
*በዘመናቸው 3 ልጆችን ወልደው (2 ወንድና አንድ ሴት) ሁለቱ ለጋብቻ: አንዱን ለቤተ እግዚአብሔር አገልግሎት የሚያውሉ ሰዎች ናቸው::

††† ቅዱሳኑ ወደዚሕ ቦታ የገቡት በነቢዩ ኤርምያስ እና በቅዱስ እዝራ ዘመን ሲሆን አንዴ የተወሰኑት በዘመነ ሰማዕታት ወጥተው በዚሕ ቀን ተሰይፈዋል::

††† በመጨረሻ ግን በሐሳዌ መሲሕ ዘመን ወጥተው ሰማዕትነትን ይቀበላሉ::

††† የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሕረቱና ይቅርታው ለምናምን ሁሉ ይደረግልን:: ከደግነታቸውም በረከትን አይንሳን::

+*" አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ "*+
=>አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ :
እናታቸው ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ
ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለት
ተነስተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ "ስብሐት ለአብ
: ስብሐት ለወልድ : ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው
አመስግነዋል፡፡
+የስማቸው ትርጓሜ "የአብ : የወልድ : የመንፈስ ቅዱስ
እስትንፋስ" : አንድም "የክርስቶስ እስትንፋስ" ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ
እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን
ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጽሐፍት
ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን፣ ድርሳናትንም ጠንቅቀው
ዐውቀዋል፡፡
+በተወለዱ በ14 ዓመታቸው ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ
ደብረ ሐይቅ ገዳም ሄደው ከባሕር ዳር ቆመው የሙሴን
ጸሎት ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ የታዘዘ መልአክ
መጥቶ ባህሩን አሻግሯቸው ወደ ቤተክርስቲያን
ገብተዋል፡፡ ለ3 ዓመትም በኃይቅ ገዳም ለመነኮሳት
እንጨት በመልቀምና ውሃን በመቅዳት : ለአባቶች
መነኮሳት ምግብ ሊሆናቸው ከባህር ውስጥ አሳን
በማውጣት አገልግለዋል፡፡
+አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ 40 መዓልትና 40 ሌሊት
ከጾሙ በኋላ ምንም እህል ሳይቀምሱ ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ አስቀድሞ ለሙሴ በደብረ ሲና እንደሰጠው
ለአባታችንም ወደ እርሳቸው መጥቶ ዓሥሩን ቃላተ ኦሪትና
ስድስቱን ቃላተ ወንጌል በውስጣቸው የተጻፈባቸው ሁለት
ጽላቶችን ሰጥቷቸዋል፡፡
+አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከሠሩ በኋላ
ዕለቱን ስንዴ ዘርተው፣ ወይን ተክለው፣ ጽድን ወይራንና
ግራርን ተክለው በአንዲት ቀን ለቤተ ክርስቲያን
አገልግሎት ዕለቱን አድርሰዋል፡፡ ስንዴውን ለመስዋዕት
ወይኑን ለቁርባን በታምራት አድርሰዋል፡፡
+አባታችን በጸሎት ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል
ተልኮ መጥቶ አባታችንን በደመና ጭኖ ወስዶ ከጌታችን
ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አቆማቸው፡፡
ጌታንም በቅዱሳኖቹ ሁሉ እንዲባረኩ ካደረጋቸው በኋላ
መልአኩን ‹‹ወደ ተወለድኩባትና ወደ ኖርኩባት ቦታ ወደ
ኢየሩሳሌም አድርሰው›› ብሎት ኢየሩሳሌምን አሳልሞ
ሀገራችን መልሶ አምጥቷቸዋል፡፡ ሁሉንም የኢትዮጵያን
ቅዱሳት ገዳማትንም ተዘዋውሮ ሲጎበኙ በሕይወተ ሥጋ
የሌሉት የየገዳማቱ ቅዱሳን ሁሉ በአካል ይገለጡላቸው
ነበር፡፡
+ጎጃም ውስጥ እያስተማሩ፣ እያጠመቁ፣ የታመሙትን
እየፈወሱ፣ የዕውራንን ዐይን እያበሩና ሙታንን እያስነሱ
ብዙ ካገለገሉ በኋላ ለዘጠኝ ዓመታት በባሕር ውስጥ
ገብተው ቁልቁል ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ጸልየው
የምሕረት ቃልኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ
ጌታችን መጥቶ ‹‹ከመነኮሳት ሁሉ ብልጫ ያለህ ወዳጄ
እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን
ምሬልሃለሁ ከዚህች ባሕር ውጣ›› በማለት በሞት
የሚያርፉበትን ቦታ ነግሯቸዋል፡፡
+ጻድቁ ወደ ደብረ አስጋጅ በሚሄዱበት ጊዜ ጸሐይ
ልትገባ ስትል ‹‹በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
አውግዤሻለሁ፡፡ ለመስፍን ኢያሱ በገባኦን እንደቆምሽ
አሁን ቀጥ ብለሽ ቁሚ›› ብለው ገዝተው ፀሐይን
አቁመዋል፡፡
+አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስም ደብረ አስጋጅ ሲደርሱ
ፀሐይ አፍ አውጥታ ‹‹አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ እገባ
ዘንድ ፍታኝ›› ስትላቸው ‹‹እግዚአብሔር ይፍታሽ›› ባሏት
ጊዜ ጠልቃለች፡፡ ጻድቁ ሌላው በእጅጉ የሚታወቁበት
አንድ ትልቅ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡
+በአምላክ ፣ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ፣
በቅዱስ ሚካኤልና በቅዱስ ገብርኤል ልቡና የሚገኝ እንደ
መልክአ ኢየሱስ ያለች እጅግ አስገራሚ ጸሎት አለቻቸው፤
እርሷን ጸሎት በጸለዩ ጊዜ እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል
ያወጣሉ፡፡ ጸሎቷም የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች
በሙሉ እየጠቀሰች እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሎቹ
የተቀበሉትን ጸዋትዎ መከራዎች ሁሉ ታዘክራለች፡፡
በእያንዳንዱ ክፍልም የጸሎት ማሳረጊያ አቡነ ዘበሰማያት
ይደግማሉ፡፡
+ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ
እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን
ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ
ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡ እያንዳንዱን የመድኃኔ ዓለምን
የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች መከራዎቹን
የምታዘክረውን ይህቺን በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም
የሆነች ጸሎት "ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም" ብሎ
የሚጠራጠር ቢኖር ግን መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡
+ጻድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ታህሳስ 9 ቀን ተወልው
ሚያዝያ 9 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ (ገድለ አቡነ
እስትንፋሰ ክርስቶስ)
=>አምላከ ቅዱሳን በጻድቁ አማላጅነት ሃገራችንን
ይጠብቅልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† ሚያዝያ 9 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን የብሔረ ብጹዐን ጻድቃን
2.አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ጻድቅ (ኢትዮዽያዊ)
3.ቅዱስ ዞሲማስ ገዳማዊ (ብሔረ ብጹዐንን ያየ እና ዜናቸውን የጻፈ አባት)
4.ቅዱስ ኤስድሮስ ሕጻን ሰማዕት (ገና በ10 ወር ዕድሜው ሰማዕት የሆነ)
5.አባ ሱንቱዩ ሊቀ ዻዻሳት

††† ወርሐዊ በዓላት
1.አባ በርሱማ ሶርያዊ (ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት)
2."318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት (ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ)
3.አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ (ኢትዮዽያዊ)

††† "ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና በመጠን ኑራችሁ: ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ:: እንደሚታዘዙ ልጆች ባለ ማወቃችሁ አስቀድሞ የኖራችሁበትን ምኞት አትከተሉ:: ዳሩ ግን 'እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ' ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሯችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ::" †††
(1ዼጥ. 1:13-15)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Miyazia_9

✞✞✞On this day we commemorate the Blessed Saints, Abba Zosimas and the departure of Abune Estenfase Kirstos ✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Blessed Saints✞✞✞
=>On this day are commemorate the Saints that live in the Realm of the Blessed.

✞According to the teachings of the faith, there are 5 worlds/realms. Though their arrangement differs, they can be listed from top to bottom as follows.
1. Paradise (in the East)
2. Realm/World of the Living (in the North)
3. Realm of the Blessed (The Realm of Rest) (in the South)
4. Our world (Earth) (in the Middle) and
5. Sheol/Hell (in the West)
 
✞The Saints of the Realm of the Blessed
-do not sin,
-live for a 1,000 years,
-feel no grief,
-and are people that bear three children (2 sons and a daughter) from which two are to be wedded and one is for the service of the House of God.

✞The Saints entered this place/realm during the times of the Prophet Jeremiah and St. Ezra. Some of them came out and were martyred, on this day, in the Era of Persecution.

✞They will also come out in the time of the Antichrist and receive martyrdom.

✞✞✞May the mercy and forgiveness of our Lord Jesus Christ be with us all that believe. And may He not deprive us from their blessings.

✞✞✞Abune Estenfase Kirstos the Ethiopian✞✞✞
=>Our father Abune Estenfase Kirstos was born from his father Meleake Mikru and his mother Welete Mariam in Wollo at a place called Dawent. On the day he was born, he stood with his feet and praised thrice saying, “Glory be to the Father, glory be to the Son and glory be to the Holy Spirit.”

✞His name has the meaning “Breath of the Father, the Son and the Holy Spirit” and “Breath of Christ”. He grew up being protected and guided in all his ways by St. Michael.

✞Because the Holy Spirit made his mind bright, he knew the words of Scripture, the Old and New Testaments, and other homilies at the age of 5.

✞When he was 14 years old, he went to Abune Iyesus Moa, to the Monastery of Debre Hayik and standing at the shore of the lake while he prayed the prayers of Moses unto God an angel that was sent from God came to him, with his aid crossed, and entered the Church. He served in the Monastery of Hayik by gathering firewood for the monks, fetching water and fishing for the consumption of the fathers for 3 years.

✞After our father, Estenfase Kirstos, fasted for 40 days and 40 nights without consuming anything, our Lord Jesus Christ gave to our father as He did to Moses at Mt. Sinai two tablets that were engraved with the Ten Commandments and  the Six Instructions of the Gospel.

✞And later, after Abune Estenfase Kirstos built a church, in the same day, he sowed wheat, planted grapes, cedar and acacia and prepared them for that day’s service of the church. He prepared the wheat for the host and the wine for the chalice miraculously.

✞And while our father was praying, the Archangel St. Michael came and brought him before our Lord and Savior Jesus Christ upon a cloud. And after our Lord made him receive the blessings of all the saints told the angel, “Take him to where I was born and lived, to Jerusalem” and he did and returned him to our country. And when he visited the holy monasteries of Ethiopia, the Saints of the Monasteries that had departed in the flesh used to reveal themselves to him.

✞Thereafter, he preached in Gojjam, baptized the people, healed the sick, made the blind see and raised the dead, then entered into a lake and prayed while upside down for Ethiopia for nine years and received a covenant. After nine years, our Lord came to him and said, “O My beloved Estenfase Kirstos, greater than all the monks, I have forgiven Ethiopia and her people for your sake thence, come out of the lake” and told him the place where he would depart.✞While the Saint went to and reached Debre Asgaje the sun in the tongue of men said, “Absolve me Abune Estenfase Kirstos so that I may set” and as the Saint replied, “May God absolve you” it set.
The Saint is known for one great covenant he has. And the covenant is as follows.

✞He had a wondrous prayer, which indwells in the heart of God, the Virgin St. Mary our Lady, St. Michael and St. Gabriel, which was like the Effigy of Jesus (Melkea Iyesus - Hymn to Jesus). And when he prayed it ten thousand souls used to come out of hell. The prayer commemorates each part of the Savior and the passion It received. And at the end of each part he used to pray “Our Father”.

✞Even if a sinful man that had repented prays this prayer our Lord in His unchanging word has given to our father Abune Estenfase Kirstos a covenant to take out a thousand souls from hell. However, if there is a person that doubts this prayer, which invokes and commemorates the passions of each part of the Holy Savior’s body, does not take out souls from hell, he/she will not see the Heavenly Kingdom.
 
✞The Righteous Abune Estenfase Kirstos was born on Tahisas 9 (December 18) and departed in great glory today on Miyazia 9 (April 17). (The Hagiography of Abune Estenfase Kirstos)

✞✞✞May the God of the Saints preserve our country by the intercession of the righteous man. And may He grant us from his blessings.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 9th of Miyazia
1. Saints of the Realm of the Blessed
2. Abune Estenfase Kirstos the Righteous (Ethiopian)
3. St. Zosimas/Zosimus/Zocima the Monastic (The one who saw the Realm of the Blessed and wrote their accounts.)
4. St. Isidore the Child Martyr (Martyred at the age of 10 months old)
5. Abba Sinuthius (Shenouda l) the 55th Archbishop of Alexandria

✞✞✞ Monthly Feasts
1. Abba Barsauma the Syrian (Father to all Syrian Monks)
2. The “318” Holy Scholars (Fathers assembled at the Council of Nicaea)
3. Abba Melchizedek of Mida (Ethiopian)

✞✞✞ “Wherefore gird up the loins of your mind, be sober, and hope to the end for the grace that is to be brought unto you at the revelation of Jesus Christ; As obedient children, not fashioning yourselves according to the former lusts in your ignorance: But as he which hath called you is holy, so be ye holy in all manner of conversation; Because it is written, Be ye holy; for I am holy.”✞✞✞
1 Pet.1:13-15

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠   
/(ማቴ ፫:፫/)

እንኳን አደረሰን!!

🛑 ዝክረ ቅዱሳንን ላልደረሳቸው  እናድርስ እናስፋ ስለ ሀገራችን እንጸልይ ንስሐ እንግባ!!🛑

5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

👉ሃይማኖት
👉ጾም
👉ጸሎት
👉ስግደት
👉ምጽዋት
👉ፍቅር
👉ትህትና
👉ትዕግስት
👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )   ንስሐ ግቡ።

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn

👉 ግእዝ መማር የምትሹ https://t.me/lisanegeez5
ዐቢይ ጻድቅ፤ በዓለ ኪዳን፤ አበ ብዙኃን ዘደብረ አስቄ ቀርሜሎስ፤ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት!!
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
✞✞✞ እንኩዋን ለበዓለ ምሴተ ሐሙስ በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+*"+ ምሴተ ሐሙስ +"*+

=>ስም አጠራሩ ከፍ ከፍ ይበልና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ከ1978 ዓመታት በፊት "ምሴተ ሐሙስ"
በምትባለው በዚሕች ዕለት:-

1.በወዳጁ በዓልዓዛር ቤት የዓለማት ፈጣሪ ሲሆን
በትሕትና ዝቅ ብሎ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጥቧል::

2.ለእኛ ድኅነት ይሆነን ዘንድ ቅዱስ ሥጋውን : ክቡር
ደሙን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰጥቷል::

3.በጌቴሴማኒ ላበቱ እንደ ደም እየተንጠፈጠፈ ጸልዮ
"ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ" ሲል አስተምሯል::

4.ምሽት 3 ሰዓት አካባቢ ይሁዳ ሊቃነ ካህናቱን አስከትሎ
መጥቶ ለ30 ብር አሳልፎ ሰጥቶታል::
(ማቴ. 26:26 / ዮሐ. 13:1)

=>ይሕ ሁሉ ለእኛ ድኅነት ተፈጽሟልና ምስጋናና ክብር
ለፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን::

=>+"+ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘለዓለም
ሕይወት አለው:: እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለሁ::
ሥጋዬ እውነተኛ መብል: ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና::
ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል:: እኔም
በርሱ እኖራለሁ:: +"+ (ዮሐ. 6:53-56)

=>+"+ እግራቸውን አጥቦ: ልብሱንም አንስቶ ዳግመኛ
ተቀመጠ:: እንዲሕም አላቸው:- 'ያደረግሁላችሁን
ታስተውላላችሁን? እናንተ መምሕርና ጌታ ትሉኛላችሁ::
እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ:: እንግዲህ እኔ ጌታና
መምሕር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ እናንተ ደግሞ እርስ
በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባል::' +"+
(ዮሐ. 13:12-14)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/zikirekdusn
#ምሴተ_ሐሙስ

☞የተቀደሰውን ስዕል ልብ ብላችሁ ተመልከቱት! (ቅዱስ #ጴጥሮስ የጌታን እግር እያጠበ ነው)

በቤተክርስቲያን ትውፊት ጌታ ደቀመዛሙርቱን በትህትና ካጠባቸው በኋላ፦

፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጌታ ታጥቋት የነበረችውን "መክፌ" ተቀብሎ ታጥቋታል፤ በዚህ ከንጽሐ ጠባይእ ማዕረግ ደርሷል።

፪. አስቀድሞ "አልታጠብም" በሚል ተከራክሮ የነበረ ቅዱስ ጴጥሮስ (ፈጣሪነቱን ቢያስብ፥ ትህትናው ቢበዛበት) እሺ ብሎ ታጥቧል። ኋላም "ካልቀረስ እኔም ልጠብህ" ብሎ ጌታን ለምኖታል፡፡ ጌታም "እሺ" ብሎ ታጥቦለታል፡፡ ይህም ለቅዱስ ጴጥሮስ የክብር ክብር ሆኖለታል፡፡ (ለመኑ ተውህበ!)

በዚህ አብነትም በአድባራቱ ፥ በገዳማቱ ትልልቆቹ (ሊቃነ ጳጳሳት፡ ጳጳሳት፡ ኤጲስ ቆጶሳት፥ ቆሞሳት፡ አበምኔቶች፡ ገበዛዝቱ) አስቀድመው ያጥባሉ!
ኋላ በፈንታው ካህናት ያጥቧቸዋል!

#አብነት

የተቀደሰው ስዕል ደብረ መድኃኒት ዓቢየ እግዚእ (ጎንደር ውስጥ) ይገኛል፡፡

እንኳን አደረሳችሁ!

ሐዋርያቱን በትህትና ያጠበ ቸሩ መድኃኔዓለም ፥ እኛንም ከከፋው ነገር ሁሉ ልቡናችንን ይጠብልን!
አሜን!
https://t.me/zikirekdusn