✿✟ የ҈ ዳ҈ ዊ҈ ት҈ ዜ҈ ማ҈ ✟✿
15.2K subscribers
226 photos
22 videos
51 files
445 links
╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮╭━─━─━─
ገና እንዘምራለን
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት @Zemaryan
╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯╰━─━─━─
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት ጥያቄ> creator ለማግኝት @kidanemiherat_bot
@yita21
@Binyam
https://youtu.be/Fz4JARE6-DI
Download Telegram
እንዴት አመሻችሁ
ጥያቄ ልጠይቃችሁ
የጌታችን እና የመድሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዓበይት በዐላት ስንት ናቸው እነማናቸው ?
Audio
#ቅዱስ_ሚካኤል

ቅዱስ ሚካኤል(፫)
ነፍሴ ሲጨነቅ ሲዝል ስጋዬ
ፈጥነህ ተራዳኝ ዋስ ጠበቃዬ

አንተ ስለሆንክ - - - ሚካኤል
የአምላክ ባለሟል - - - ሚካኤል
ልመናህ ፈጥኖ - - - ሚካኤል
ከአምላክ ያቀርባል - - - ሚካኤል
የዋህ መልአክ ነህ አዛኝ ለሰው(፪)
ምልጃህ ፈጣን ነው ለምናምነው (፪)
#አዝ
ደዌ የጸናበት - - - ሚካኤል
ባንተ ይድናል - - - -ሚካኤል
በአደባባይህ - - - ሚካኤል
ምስክር ሆኗል - - - ሚካኤል
ከቤትህ መጥቶ የተማፀነ(፪)
በቃል ኪዳንህ ህይወቱ ዳነ (፪)
#አዝ
ከአምላክ ተሰጥቶህ - - - ሚካኤል
ክብርህ ያበራል - - - ሚካኤል
ለጎስቋላው ሰው - - - ሚካኤል
መጠጊያ ሆኗል - - - ሚካኤል
ትንሽ ትልቁ ደሀው ሀብታሙ(፪)
ለምኖ አግኝቷል ከአምላክ በስሙ(፪)
#አዝ
በብሉይ ኪዳን - - - ሚካኤል
ከአምላክ ተልከህ - - - ሚካኤል
ሕዝበ እስራኤልን - - - ሚካኤል
ነጻ ያወጣህ - - - ሚካኤል
በአዲስ ኪዳንም ድንቅ ስራ አለህ(፪)
በተአምራትህ ትፈውሳለህ(፪)

ሊቀ መዘምራን ዲ.ን.ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
Audio
#መከራ_መካሪ_ነው

አዎ አንዳንድ ሰዎች እንደታመሙ እንጂ ለምን እንደታመሙ አያውቁም አንዳንድ ሰዎች በመከራ ውስጥ እንዳለፉ እንጁ ለምን በመከራ ውስጥ እንዳለፉ አያውቁም

╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
Audio
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝

ሼርርር
ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም በጸጥታ ኃይሎች ለጥያቄ እንፈልግሃለን ተብለው ተወስደው የነበሩት መምህር ብርሃኑ አድማስ ከስር ተለቀው ወደ ሥራ ቦታቸው መመለሳቸውን የዝግጅት ክፍላችን አረጋግጧል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸውና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት ፱ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ ውሳኔ አሳለፈ።

ምንጭ: EOTC TV

╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝

ˢᵃᵛᵉ          ˢʰᵃʳᵉ
Audio
ጊዜ አጠቃቀምና ክርስትና

◦ ክርስትና ቀልድ አይደለም
◦ ለቃለ እግዚአብሔር ጊዜ እንስጥ
◦ ለመንፈሳዊነት ጊዜ ይኑረን


ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
🔹▪️🔹▪️🔹▪️🔹▪️
ያንደበቴ ጣፋጭ ውዳሴ
========///========

ያንደበቴ ጣፋጭ ውዳሴ
ምፅናናብሽ ታዛለ ነፍሴ
ከመቅደስሽ ፍቅር ተምሬ
ማርያም ማርያም ይላል ከንፈሬ


ልመናዬን ሰምተሻል
በረድኤት ቀርበሻል
በፍቅርሽ ተሸልሜ
አረፍኩኝ ከሸክሜ{፪}


ቃሌ ነው በተሰማ
ተማፅኖዬን ሳሰማ
በዙፋኑ ቀኝ ሆነሽ
ድንግል ታስምሪናለሽ {፪}

ማግኝት ማጣት አይደለም
ልመናዬ በአለም
አድይኝ ማስተዋሉን
እንድረዳው መስቀሉን {፪}

አይመራኝም በትሬ
ድንግል ቆመሽ ከበሬ
ምርኩዜ ብዬሻለው
አንቺን እደገፋለው {፪}
በኪዳንሽ ለተማጸንን
ሞት አለፈ ሕይወት ሆነልን
የእርቃችን ሰነድ ነሽና
ልጅሽ ሠራን እንደገና።

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቃል ኪዳኗ ንግሥት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወርኃ ግንቦት መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን። የእናታችን የከበረ ቃል ኪዳኗ፣ ምልጃ ጸሎቷ አይለየን፤ ልጇ ወዳጇ ረድኤት በረከቷን ያሳድርብን። የወር ሰው ይበለን። አሜን።
አረሳውም_ያንን_እለት_አልዘነጋም_ያን_ደግነት_ሰማዕቷ_ቅድስት_አርሴማ_ደጓ_እናቴ።_አሮን_ቤቢ_6a5c
<unknown>
አልረሳውም ያንን ዕለት

አልረሳውም ያንን ዕለት
አልዘነጋው ያን ደግነት
እናቴ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት
እምዬ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት
ስላለኝ ነው ምክንያት/፪/


ለሠው ተናግሬ ያልተረዳኝ ሰው
ዕንባዬ በምሬት ከዓይኔ የሚፈሰው
የቤቴን ገመና ሁሉን ስነግርሽ
አዛኝት ነሽና እራራልኝ ልብሽ
አረሳው መቼም የአንቺን ደግነት/፪/
ውለታ አለብኝ ኪዳነ ምሕረት

አዝ

ልቤ በሐዘን ጠቁሮ ውስጤ እየደማ
መቅረዜ ሲጨልም ስጓዝ በጨለማ
በራፌን ዘግቼ ዝምብዬ አለቅሳለሁ
አይኔን አቀርቅሬ እናቴ እልሻለሁ
ዘንበል አልሽልኝ ሠምተሽ ፆሎቴን/፪/
አልተጸየፍሽም ብቸኝነቴን

አዝ


እናት የለኝ ብዬ ከቶም አልከፋ
እኔስ አይቻለሁ ስትሞይኝ በተስፋ
ምድራዋዊ እናቴ ለጊዜው ነው ፍቅሯ
ያንቺስ ግን ልዩ ነው እረ ስንቱን ላውራ
ማርያም ማርያም ብል አልሠለችሽ/፪/
በልቤ ጽላት ስለ ታተምሽ

አዝ___

ሲረበኝ መጥተሻል ሲጠመኝ ደርሰሻል
ለጎደለው ቤቴ በረከት ሆነሻል
ጭንቄም ቀለለልኝ ሐዘኔም ራቀ
ያስጨነቀኝ ጠላት ራሱ ተጨነቀ
መድሀኒት ወልደሽ ዳንኩኝ ከህመሜ/፪/
ይኸው ዘመርኩኝ በምልጃሽ ቆሜ
💖❤️💖❤️💖❤️💖❤️💖

╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝

ˢᵃᵛᵉ          ˢʰᵃʳᵉ
ስለ ዘፈን መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል??

አብዛኛውን ጊዜ ለሰው እውነቱ ሲነገረው ከመቀበል ይልቅ በአካኪ ዘራፍ አግበስብሶ ማለፉ ልማዱ ነው። ስጋዊ ህይወትና ስጋዊ አስተሳስብ ስለሚያሸንፈው ማድመጥም ሆነ መቀበልም ይቀፈዋል። #ቅዱስ #ኤፍሬም #ሶሪያዊዉ የስጋዊ ህይወት ማሸነፍ ላቃታቸው ማለትም ስጋዊህ ህይወት ላሸነፋቸው እና መግደል ላቃታቸው  መፍትሔውን ሲናገር እንዲህ ይላል፦ የስጋዊው ህይወት ማሸነፍ ምትችሉት የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት በእናንተ ውስጥ በሙላት መኖር ሲጀምር ያኔ እናንተ የስጋዊ ሕይወት ትጠየፋላችው እያለ ይናገራል። ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ በቆላ 3:16 ላይ  «የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችው» እንዳለ የእግዚአብሔር ቃል እኛ ላይ በሙላት መኖር ሲጀምርብን አብዝተን ስንጸልይ አብዝተን ስንሰግድ አብዝተን ስንፆም  የስጋዊ ህይወታችንን እንጠየፋለን ማለት ነው።

አብዛኛውን ጊዜ ዘፈን መልክ መልኩን እየቀየረ መጥቷል እያየነውም ነው። ይኼን ያነሳንበት ምክኒያት እንዳንዶቹ ስለፍቅር መዝፈን ስለሀገር መዝፈን ሀጢያት ነው ወይ የሚል ጥያቄ እያነሱ ስለምናያቸው ነው። አንድ ምሳሌ ይባላል። ምሳሌውም፦ #አዘለም_አቀፈም_ያው_ተሸከመ_ነው ይባላል። እና #ዘፈንም መልኩን ቢቀያይርና ርዕሱን ቢለዋውጥ ዘፈን ያው ዘፈን ነው። በአንድ ወቅት መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየው በriot(ርዮት) ፕሮግራም ቃለ መጠየቅ ላይ ቀርበው ስለዘፈን የሰርግ ሰፈን የሐገር ዘፈን እንዲኹም ሌሎች ሌሎችም በቤተክርስቲያን እንዴት ያዩታል ተብለው ሲጠየቁ እርሳቸውም ቤተክርስቲያንን አጥር እንዳጠረች በዚህ ጉዳይ ላይ እንደማትደራደርና ዘፈን ሀጢያት መሆኑን አስረግጠው አልፈዋል።

ዘፈን ማለት በአጭሩ የአጋንንት ግብር ነው። በአንጻሩ ስለ ሰይጣንና የግብራበሮቹ የክፋት መናፍስት ግብር ነብየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ ሲናገር፦ በዚያም የምድረ በዳ አራዊት ያርፋሉ ጕጕቶችም በቤቶቻቸው ይሞላሉ ሰጐኖችም በዚያ ይኖራሉ በዚያም አጋንንት #ይዘፍናሉ ይላል። (ኢሳ 13:21) ለሰራዊት ጌታ ለቅዱስ እግዚአብሔር የሚቀርበውን ዝማሬና ምስጋና  የሚፈፀየፉ የአጋንንትን ግብር ማድረግ ይባስ ብሎ የአጋንንት ማህበርተኛ አንድም በክፉ ስራቸው የምንተባበር መሆን ነው። «ከአጋንንትም ጋር ማህበርተኞች እንድትሆኑ አልወድም»(1ኛ ቆሮ 10:20)

#ዘፈን የስጋ ስራ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን የሐጢያት ዋና ዋናዎች አርዕስተ ሀጢያት ብሎ እንደ ዘረዘረልን እናነባለን። ከእነዚህ ከ16ቱ ድርጊቶቹ ውስጥ አንዱ ዘፈን ወይንም ደግሞ ዘፋኝነት ነው። «የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው ርሱም #ዝሙት #ርኵሰት #መዳራት #ጣዖትን_ማምለክ #ሟርት #ጥል #ክርክር #ቅንአት #ቍጣ #ዐድመኛነት #መለያየት #መናፍቅነት #ምቀኝነት #መግደል #ስካር #ዘፋኝነት ይህንም የሚመስል ነው አስቀድሜም እንዳልኹ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።»(ገላ 5፥19-21 1ኛጴጥ 4:3) ዘፋኝነት በግልጽ መንግስተ ሰማያትን አያወርስም እያለ እንዴት ነው ሰው ወደዘፋኝነት የሚገባው።

ዘፈን የዝሙት ማቀንቀኛ ነው። በየመልኩ ሊመሰገን የሚገባው ሁሉን ያስገኘ ሁሉን የፈጠረ እግዚአብሔር ነው። ነገር ግን ፈጣሪው ሳይሆን ፍጡሩን ገዢውን ሳይሆን ተገዢውን ማወደስ ማለት ትልቅ አስፀያፊ ተገባር ነው። አንዳንድ ሰው በጣም ነው ግርም የሚለው እግዚአብሔር ዘፈንን የሚፈቅድ ይመስል "ከእግዚአብሔር ጋር ዘፈን ጨርሻለሁ አሁን ይለቀቃል ከእግዚአብሔር ጋር" ሲሉ ይሰማሉ እግዚአብሔር ከሰይጣን ጋር ተባባሪ አደረጉት እኮ ይገርማል  ይህንን እንኳ ማሰብ ተስኗቸዋል እስከዚህም ድረስ ነው አስተሳሰባችን። እንደውም አለምን የፈጠረ አምላክ እንደየክብሩ ማወደስ ሲገባን በዘፈን አንድሰውን አይኑ ጥርሱ አፍንጫው እያለን ከንቱ ውዳሴ እንናገራለን። ከስልኩ እንኳ ዘፈን ለማጥፋት ያቃተው ትውልድ እኮ ነው ያለን በእውነቱ ስለዚህ ከእነዚህ አይነት ተግባር መራቅና መሸሽ ተገቢ ነው።

አንዳንድ ሰዎች ያስደንቃሉ  እኛ እኮ ለመደሰት ነው የምንዘፍነው የምንጨፍረው በማለት ሲናገሩ እናያቸዋለን። ለእነዚህ አይነት ሰዎች መጽሐፋችን እንዲህ ይለናል፦ ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር ርሱ ይጸልይ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር ርሱ ይዘምር።(ያዕ 5፥13) ስለዚህ ማናችንም ብንሆን ስንደሰት መዘመር ስናዝን ደግሞ መጸለይ እንዳለብን መጽሐፉ ነግሮናል።

ዳግም የመጋቢ ሐዲስ እሸቱን አነጋገር እንጠቀም እና እናብቃ።  መጋቢ ሐዲስ ምን አሉ ዘፈን እነ ሰርጸ እነ ማህሙድ አህመድ ሲይዙት ጽድቅ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱ ግን ሲይዘው ሀጢያት ነው በማለት አስረግጠው አስቀምጠዋል። ይኼ ነው እውነቱ ሀጢያት ነው ለሰይጣን የምናቀርበው ግብር ነው ስለዚህ እግዚአብሔር የሰጠንን አንድበት እናመስግንበት ክፉ አናውራበት መድኃኔዓለም የሰጠንን እግር ወደጭፈራ ቤት ወደ ኃጢያት አናምራበት። ቤተክርስቲያን ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድበት ኪዳኑን ሰዓታቱን ማሕሌቱን እንቁምበት በዚህ ስፍራ ያላችሁ ሁሉ ይህንን አንብባችሁ ትምህርት እንደምትወስዱበት አልጠራጠርም።

እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን

ይቆየን!!

ሼር በማድረግ በእንደዚህ አይነት ስፍራ ያሉትን ግንዛቤ እናስጨብጣቸው!!!

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ በጸጥታ አካላት ተይዘው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ውስጥ ይገኛሉ።

የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ም/ኃላፊ የሆኑት መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ ዛሬ  ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም ከቤታቸው ወደ ሥራ ብለው ከወጡ በኋላ ሥልካቸው የተዘጋ እና መገኘት ያልቻሉ ሲሆን ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ግን በጸጥታ አካላት ተይዘው ወደ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መወሰዳቸውን የዝግጅት ክፍላችን ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ችሏል።

በተመሳሳይ መ/ር ተሾመ በየነ ገላን አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
Audio
#አረገ_በስብሐት

አረገ በስብሐት አረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ
አረገ በስብሐት በእልልታ/2/
ሞትን ድል አድርጎ የሠራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ/2/

እንኳዋን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለእርገት ባዓል በሰላም አደረሳቹሁ አሜን ፫

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
ˢʰᵃʳᵉ
“ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል” (ሐዋ.፩፥፲፩)

ዕርገት
 “ዕርገት” የሚለው ቃል“ ዐርገ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም “ከታች ወደ ላይ መውጣት፣ ክፍ ከፍ ማለት፣ ማረግ” ማለት ነው፡፡ በዓለ ዕርገትም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የነበረውን የማዳኑን ሥራ ጨርሶ ወደ ላይ መውጣቱና በቀደመ ክብሩ በአብ ቀኝ መቀመጡ የሚከበርበት በዓል ነው፡፡
 
የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ዕርገት ምልክትነቱ በብዙ መልኩ የሚታይ ነው፡፡ በዋናነትም የማዳን ሥራውን የመፈጸሙ፣ የአሽናፊነቱ፣ የነፍሳችን ዕርገት ምልክት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ዳግም የመምጣቱ ምልክት ነው፡፡
 

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ
Amanuel
TIRHAS Gebreegziabher
💖 አረ እሰይ አማኑኤል 💖

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ
Ethiopia፡አላዝን አልከፋ እኔ |ዘማሪት እንቁሥላሴ ጎሳ|አዲስ ዝማሬ New Song 2020.
አላዝን አልከፋ እኔ
አላለቅስም እኔ(×2)
መጽናኛዬ አለኝታዬ
እያለ መድኅኔ(×2)

ማቀርቀሬ መተከዜ
ተስፋ መቁረጥ መቅበብበዜ
ለቅሶ ሀዘን ሁሉም አልፏል
በወደድከኝ ልቤ አርፏል

በማይጥለኝ በመዳፍህ
በሚሞቀው በእቅፍህ
አደላድለህ ይዘኸኛል
ሳታቆስል ማርከኸኛል

ያልፈረድከው በድካሜ
ፈውስ የሆንከኝ ለህመሜ
የማላጣህ ዕድሌ ነህ
ለዘለዓለም የማመልክህ

ሳትጸየፍ ተቀበልከኝ
ነጩን በፍታ አለበስከኝ
ልጄ ብለህ አቅፈኸኛል
ላትጠላኝ ወደኸኛል

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ
የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን መንበረ  ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ለመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ደብዳቤ አስገባ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳንን ቴሌቪዥን ማገዱን ተከትሎ በዛሬው ዕለት ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን መንበረ  ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዕግዱ እንዲነሳ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለባለሥልጣኑ አስገብቷል።

ብፁእ አቡነ አብርሃም የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን መንበረ  ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብዳቤው ላይ እንደጠቀሱት የማኅበሩ ቴሌቪዥን የቤተክርስቲያኒቱ አንዱ ልሣን በመሆኑ የሚያከናውናቸው ተግባራት በሙሉ በቤተክርስቲያን ሕግና ሥርዓት የሚዳኝ ይሆናል ብለዋል።

በተጨማሪም ባለሥልጣኑ ማኅበሩን ምንም ዓይነት ማብራሪያ ሳይጠይቅና ማስጠንቀቂያም ሳይሰጥ ያደረገው ዕግድ ተገቢ አለመሆኑን በመጥቀስ ዕግዱ እንዲነሳም በቤተ ክርስቲያን ስም ጠይቀዋል።

.....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ
ዕግዱ ተነሳ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ጥሎት የነበረውን #ጊዜያዊ ዕግድ ዛሬ አርብ ማንሳቱን አሳውቋል።

.....ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን 👇
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
         ʟɪɴᴋ 👆 ᴛᴀʙ . sʜᴀʀᴇ