Bilaluna Edris (Xuqal.X.Qafarey)
480 subscribers
3.13K photos
208 videos
46 files
2.15K links
♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)(ﷺ)

« ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ» ﷻ
                 ቁርኣን[ 3:104 ]


መወያያ ግሩፓችን ☞ https://t.me/+1qmNqy265XoyNGY0
Download Telegram
“ውዱዑ አድርጎ ውዱዑን ያሳመረው ሰው፤ ኃጢአቶቹ ከጥፍሮቹ ስር እንኳ ሳይቀር ከአካላቱ ይወጣሉ።”
ረሱል ﷺ
“በምድር ላይ ካሉት ውሃዎች ምርጡ የዘምዘም ውሃ ነው። በምግብነት ለተጠቀመው ምግብ ለበሽታ ለተጠቀመው ደግሞ መድኃኒት ነው።”
ረሱል ﷺ
አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ወርቃማ ቀናቶች

ጌታችን አላህ በራሱ ካላቃቸው እና ካከበራቸው አራት ወራቶች መካከል የዙልሒጃ ወር አንዱ ነው:: ከቀናቶች ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስር ቀናቶችም ያሉት በዚሁ በተከበረው የዙልሒጃ ወር ውስጥ ነው::

እነዚህ አስር ውድ ቀናቶችም ጌታችን አላህ(ሱወ) ምሎባቸዋል::

የአላህ መልዕክተኛ (الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል፤

ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው » አልበዛር እና አልሐይሰሚይ ዘግበዉታል አልባኒም ሰሂህ ብለዉታል (ሰሂሁል ጃሚዕ 1133)

በነዚህ ውድ ቀናቶች የሚሰሩ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ እና በላጭ ናቸው::

ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸም መልካም ስራዎች በበለጠ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።» ቡኻሪ ዘግበውታል

በመሆኑም እነዚህን ውድ ቀናቶች በተገቢው መልኩ ልንጠቀምባቸው ይገባል:: በነዚህ ውድ ቀናቶች ከሚወደዱ ኢባዳዎች መካከል:-


1. ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም)

2. ዚክሮችን ማብዛት ቁርዓን መቅራት ፤ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣ ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል።

ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩه እንዲህ ብለዋል፤«ከእነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ስራ እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ስለዚህ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል

3. ሐጅ ማድረግ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት አቅሙ ለቻለ ሰው የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ የአላህ መልዕክተኛه ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤

ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛه እንዲህ ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል

4. ኡድሂያ- በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው።
ኡድሂያን ለማረድ ያቀደ ሰው የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን መቁረጥ የለበትም::

5. የፈርድ ሰላቶችንን ጠብቆ በጀምዓ መስገድ፣ የሱና እና የለሊት ሰላቶችን ማብዛት

6. ለወላጆች መልካም መዋል

7. ለተቸገሩ ወገኖች ሰደቃ ማብዛት

8. የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣

9. ዝምድናን መቀጠል፣

10. ለራሳችንም ለሀገራችንም ለኡማውም በብዛት ዱዓን ማብዛት ያስፈልጋል።

11. ተውበት ማድረግ

በነዚህ ውድ ቀናቶች ከተጠቀሱት ውጪ ያሉትንም መልካም ስራዎች በሙሉ መስራት ምንዳው ላቅ ያለ ነው::

እነዚህን ወርቃማ ቀናቶች በኢባዳ ከሚያሳልፉት አላህ ያድርገን 🤲

የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
@ https://t.me/Xuqal
ቁርኣንን ለልባቸው ቀለብ ያደረጉ፤ ምንኛ ታደሉ?
ሚና!
"ደስታ ማለት አላህን ለመታዘዝ መወፈቅ ነው አንድ ሰው አላህን ለመታዘዝ ተወፍቆ ካየሀው ደስተኛ መሆኑን እወቅ"
ያኔ ላቦራቶሪ ባልነበረበት፤ ደምህ ከፍ ብሏል፣ ሙቀትህ ጨምሯል፣ ስኳርህ ተባብሷል ... የሚል ወሬ በማንሰማበት ዘመን እኮ በጣም ተረጋግተን ነበር የምንኖረው።
ዛሬ ላይ የሚያሸብረን ነገር በዝቷል። ደሜ ከፍብሎ፣ ስኳሬ ጨምሮ፣ ሪሕ ተገኝቶብን .. እያልን በራሣችን ላይ ሽብር !!

አንዳንድ ጊዜ በሽታን በመሸሽ ብቻ በሽታ ላይ እንወድቃለን ።
ሞትን በመፍራትም በተደጋጋሚ እንሞታለን ።
በጣም ተጠንቅቀን ከምንኖረው ይልቅ ዝምብለን የምንኖረው ኑሮ እንዴት ደስ ይላል መሠላችሁ ።

የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
@ https://t.me/Xuqal
ኢናሊላሂ ወኢና ኤለይሂ ራጂኡን

ለኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፈርድ ወንድም፣የወንድማችን አብዱሰላም ድንገተኛ ሞት ለሁላችንም አይቀርምና አላህ የወሰነው ውሳኔ በፀጋ መቀበል ብቻ ነው ምርጫችን። አላህ ይዘንልህ። ለመላው ቤተሰቡ ፣ የሥራ አጋሮችህ በሙሉ መፅናናትን እመኛለሁ። አላህ በጀነት ይሞሽርህ
በዚህ አመት ሐጅ ላልተሳካለት
~
ኢብኑ ረጀብ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ:–

★ በዐረፋ መቆም ላልቻለ ከአላህ ወሰኖች ዘንድ ይቁም።

★ በሙዝደሊፋ ማደር ላልቻለ ወደ አላህ ያቃርበው ዘንድ ለትእዛዙ ይደር።

★ ሀድዩን (እርዱን) ሚና ላይ ማረድ ያልቻለ ከምኞቱ ይደርስ ዘንድ ስሜቱን ይረድ።

★እሩቅ በመሆኑ ቤቱ (በይተል ሐራም) መድረስ ያልቻለ የቤቱን ባለቤት ያስብ። ወደ እርሱ ከደም ጋኑ የቀረበ ነውና።"

የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
@ https://t.me/Xuqal
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
@ https://t.me/Xuqal