Addis Ababa Education Bureau
126K subscribers
14.4K photos
107 videos
2.31K files
4.52K links
ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡
Download Telegram
ቀን 23/07/2012 ዓ/ም

ታክሲዎች እና ባጃጆች ትርፍ መጫናቸውን ካላቆሙ ለዜጎች ደህንነት ሲባል ከሥራ ውጪ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስጠነቀቀ::

በታክሲዎች እና በባጃጆች በኩል የሚታየው ትርፍ የመጫን ሁኔታ በፍጥነት ካልቆመ ለዜጎች ደህንነት ሲባል ተሽከርካሪዎቹን ከሥራ ውጪ ለማድረግ የሚገደድ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስጠንቅቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የነዋሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ያወጣቸው መመሪያዎች ይከበሩ ዘንድ ነዋሪዎችም የራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡ አስተዳደሩ አሳስቧል፡፡

በአዲስ አበባ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በከተማዋ የትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ተሸከርካሪዎች ትርፍ እንዳይጭኑ የተከለከለ መሆኑ ይታወሳል፡፡

ይህን ለማስቆም ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን የጠቀሰው የከተማ አስተዳደሩ በተለይ ታክሲዎች እና ባጃጆች እስካሁንም ትርፍ እየጫኑ ስለመሆኑ መረጃዎች እየደረሱኝ ነው ብሏል፡፡

ምንጭ፡- የከንቲባ ጽ/ቤት

ትኩስ ትምህርታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ እና የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/channel/UCMoKzm9xgyid8CYTbh4-Ckw/
https://youtu.be/wRoB3KmIGdM
ቀን 23/07/2012 ዓ/ም


YouTube
የትምህርት ሚንስቴር በመገናኛ ብዙሃን ትምህርት እያስተላለፈ መሆኑን ገለፀ፡፡
የትምህርት ሚንስቴር በመገናኛ ብዙሃን ትምህርት እያስተላለፈ መሆኑን ገለፀ፡፡ #ebc #etv #EthiopianBroadcastingCorporation
ቀን 23/07/2012 ዓ/ም

ትኩስ ትምህርታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ እና የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/channel/UCMoKzm9xgyid8CYTbh4-Ckw/
Telegram፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቀን 23/07/2012 ዓ/ም

የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ እና የእጅ ጓንት መጠቀም የቫይረሱን ስርጭት ሊያስፋፋ እንደሚችል የጤና ባለሙያዎች ገለፁ፡፡
ትኩስ ትምህርታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ እና የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/channel/UCMoKzm9xgyid8CYTbh4-Ckw/
Telegram፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቀን 23/07/2012 ዓ/ም

ኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና ህዳሴ ግድብን ለማጠናቀቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ አንድ ሆኖ እንዲነሳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጥሪ አቀረቡ፡፡
ትኩስ ትምህርታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ እና የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/channel/UCMoKzm9xgyid8CYTbh4-Ckw/
Telegram፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
ቀን 23/07/2012 ዓ/ም

አትክልት ተራ ወደ ጃንሜዳ እንዲዛወር ተወሰነ፡፡

ኢ/ር ታከለ ኡማ ከከተማው የፀጥታ አካላት ጋር አትክልት ተራ አካባቢ እየታየ ባለው መጨናነቅ ዙሪያ ተወያይተዋል።
ቦታው የከተማዋ ከፍተኛ የአትክልት ምርት ማከፋፈያ ሲሆን ከፍተኛ የሰው ጭንቅንቅ በየእለቱ የሚታይበትና ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘም ለቁጥጥር አስቸጋሪ መሆኑ ተገምግሟል።

ስለሆነም ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የአትክልት ግብይቱ በጊዜያዊነት ወደ ጃንሜዳ እንዲዘዋወር ተወስኗል።
አትክልት ተራ ለጊዜው ለነጋዴዎቹ እንደ እቃ ማስቀመጫ(ስቶር) ብቻ እንዲያገለግል ተወስኗል።

ጃንሜዳ ቦታው ሜዳማ እንደመሆኑ ለእንቅስቃሴ ምቹ መሆኑና ለቁጥጥር አመቺ መሆኑ ግምት ውስጥ በማስገባት ነው የአትክልት ግብይቱ ወደ ጃንሜዳ እንዲዘዋወር የተደረገው።
ትኩስ ትምህርታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ እና የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You Tube: https://www.youtube.com/channel/UCMoKzm9xgyid8CYTbh4-Ckw/
Telegram፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau