ቅዳሜ፡- ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ውይይት ተካሄደ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት የ9 ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ በሐዋሳ ከተማ ተካሄደ፡፡
በዚህ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ውይይት ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበራ ብሩን ጨምሮ ሌሎች የቢሮው የስራ ኃላፊዎች ፣ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተውጣጡ የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪ ቦርድ አባላት፣ የተለያዩ ኮሌጆች ዲኖች እንዲሁም የኮሌጁ ዲኖች፣ ማናጅመንት አባላትና የዲፓርትመንት ተጠሪዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ በኮሌጁ ዲን አቶ መለሰ ይግዛው እና ዶ/ር አበራ ብሩ አማካኝነት የእንኳን ደህና መጣችሁ የመግቢያ ንግግር ከተደረገ በኋላ ተቋማዊ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም ሪፓርት በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስተባባሪ አቶ ጀማል ሐሰን አማካኝነት ቀርቧል፡፡
አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራው ሂደት ምን ይመስላል የሚለውን ደግሞ በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የኮንትራክት አዲሚኒስትሬሽን ኤክስፐርት በሆኑት ኢ/ር ዘውዴ ሽፈራ አማካኝነት ገለፃ ተደርጓል።
በሌላ በኩል ተቋሙ የዉስጥ ገቢውን ለማሳደግ ይረዳ ዘንድ የተቋቋመው ኃላ/የተ/የግል ድርጅት ለቀጣይ ያሉት ተስፋዎች፣ ያመጣው ፋይዳና ያሉበት ክፍተቶችን የሚያሳይ ጥናታዊ ቀርቧል።
በመጨረሻም በቀረቡት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት እና ጥናታዊ ጽሑፍ ሰነዶች መሠረት ከተሳታፊዎች ጥያቄ ተነስቶ እና ገንቢ አሰተያየት ተሰጥቶ የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ውይይት ተካሄደ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት የ9 ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ በሐዋሳ ከተማ ተካሄደ፡፡
በዚህ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ውይይት ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበራ ብሩን ጨምሮ ሌሎች የቢሮው የስራ ኃላፊዎች ፣ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተውጣጡ የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪ ቦርድ አባላት፣ የተለያዩ ኮሌጆች ዲኖች እንዲሁም የኮሌጁ ዲኖች፣ ማናጅመንት አባላትና የዲፓርትመንት ተጠሪዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ በኮሌጁ ዲን አቶ መለሰ ይግዛው እና ዶ/ር አበራ ብሩ አማካኝነት የእንኳን ደህና መጣችሁ የመግቢያ ንግግር ከተደረገ በኋላ ተቋማዊ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም ሪፓርት በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስተባባሪ አቶ ጀማል ሐሰን አማካኝነት ቀርቧል፡፡
አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራው ሂደት ምን ይመስላል የሚለውን ደግሞ በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የኮንትራክት አዲሚኒስትሬሽን ኤክስፐርት በሆኑት ኢ/ር ዘውዴ ሽፈራ አማካኝነት ገለፃ ተደርጓል።
በሌላ በኩል ተቋሙ የዉስጥ ገቢውን ለማሳደግ ይረዳ ዘንድ የተቋቋመው ኃላ/የተ/የግል ድርጅት ለቀጣይ ያሉት ተስፋዎች፣ ያመጣው ፋይዳና ያሉበት ክፍተቶችን የሚያሳይ ጥናታዊ ቀርቧል።
በመጨረሻም በቀረቡት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት እና ጥናታዊ ጽሑፍ ሰነዶች መሠረት ከተሳታፊዎች ጥያቄ ተነስቶ እና ገንቢ አሰተያየት ተሰጥቶ የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ማክሰኞ፡- ሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም
ለኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኞች በፕሮጀክት ቤዝድ አሰጣጥ ስልጠና ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ ተሰጠ!!
ከሁሉም ኮሌጆቸ ለተወጣጡ የኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኞች በፕሮጀክት ቤዝድ ስልጠና አሰጣጥ ዙሪያ ትናንት በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒከ ኮሌጅ የጋራ ግንዛቤ ተሰጠ።
በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ 15ቱ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት ላይ ያሉ አሰልጣኞች የክህሎት ክፍተታቸውን እንዲያሻሽሉና ፕሮጀክትን መሰረት ያደረገ እውቀት እንዲያገኙ ታሳቢ በማድረግ ለተዘጋጀው ስልጠና ግንዛቤ እንዲኖራቸው በትናንትው ዕለት ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በዚህ ገለፃ ላይ ከሁሉም ኮሌጆች 583 አሰልጣኞች ተገኝተዋል።
ኮሌጁ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠናን ሲጀምር የኮነስትራክሽን ዘርፍ ማሰልጠኛ ት/ቤት የነበረ መሆኑና በቀጣይም የአካባቢን ጸጋ መሰረት ያደረገ ስልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ ኮንስትራክሽንን ቀዳሚ ምርጫ ያደረገ መሆኑ ለተዘጋጀው ስልጠና ተመራጭ አድርጎታል።
ስልጠናው ለ26 ቀናት የሚሰጠ ሲሆን መሰረታዊ ዓላማው የዘርፉ አሰልጣኞች የክህሎት ክፍተታቸውን በመሙላት የሙያ ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡና የሚሰጡትን ስልጠና ፕሮጀክትን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ለማድረግ ታቅዶ ነው ተብሏል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኞች በፕሮጀክት ቤዝድ አሰጣጥ ስልጠና ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ ተሰጠ!!
ከሁሉም ኮሌጆቸ ለተወጣጡ የኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኞች በፕሮጀክት ቤዝድ ስልጠና አሰጣጥ ዙሪያ ትናንት በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒከ ኮሌጅ የጋራ ግንዛቤ ተሰጠ።
በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ 15ቱ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት ላይ ያሉ አሰልጣኞች የክህሎት ክፍተታቸውን እንዲያሻሽሉና ፕሮጀክትን መሰረት ያደረገ እውቀት እንዲያገኙ ታሳቢ በማድረግ ለተዘጋጀው ስልጠና ግንዛቤ እንዲኖራቸው በትናንትው ዕለት ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በዚህ ገለፃ ላይ ከሁሉም ኮሌጆች 583 አሰልጣኞች ተገኝተዋል።
ኮሌጁ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠናን ሲጀምር የኮነስትራክሽን ዘርፍ ማሰልጠኛ ት/ቤት የነበረ መሆኑና በቀጣይም የአካባቢን ጸጋ መሰረት ያደረገ ስልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ ኮንስትራክሽንን ቀዳሚ ምርጫ ያደረገ መሆኑ ለተዘጋጀው ስልጠና ተመራጭ አድርጎታል።
ስልጠናው ለ26 ቀናት የሚሰጠ ሲሆን መሰረታዊ ዓላማው የዘርፉ አሰልጣኞች የክህሎት ክፍተታቸውን በመሙላት የሙያ ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡና የሚሰጡትን ስልጠና ፕሮጀክትን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ለማድረግ ታቅዶ ነው ተብሏል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ማክሰኞ፡- ሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም
#ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና ለውጪ የተቋማችን አጋር ማኅበረሰብ በሙሉ
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡
ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡
ስለዚህ ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።
#አድራሻ፡- ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
ስልክ - 0991824160
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
#ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና ለውጪ የተቋማችን አጋር ማኅበረሰብ በሙሉ
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡
ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡
ስለዚህ ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።
#አድራሻ፡- ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
ስልክ - 0991824160
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ረቡዕ:- ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም
በከተማ ደረጃ በተደረገው የአሰልጣኞች ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሸነፈ!!
የኮሌጁ አሰልጣኞች በተቋም እና በክላስተር ደረጃ የተወዳደሩበት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሰነድ በላቀ ውጤት አሸናፊ የነበረ ሲሆን በከተማ ደረጃ በተደረገውም ቀዳሚነቱን ይዞ አጠናቋል።
በውድድሩ ርዕሰ ጉዳዩ አንገብጋቢ ችግር መሆኑ፣ ከችግሩ ጋር የተሰናሰለ ዓላማ መቀረጹ፣ ችግሩን ለመፍታት የተደረገው ርቀት፣ በምርምር ሂደቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ወዘተ የሚሉ መስፈርቶች ተካተዋል።
የኮሌጁ አሰልጣኞች የሰሩት ጥናትና ምርምር ርዕስ በስልጠና መጨረሻ ዓመት ላይ በሚሰሯቸው ፕሮጀክቶች እና ድህረ ልምምዶች ላይ የሰልጣኞችን ልል ክህሎት እንዲት ማሳደግ ይቻላል? የሚል ነበር፡፡
ባለፈው ዓመትም በአሰልጣኞች የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በከተማ ደረጃ አንደኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
በሌላ በኩል በተያያዘ በሰልጣኞች መካከል ሲደረግ የነበረው የክህሎት ውድድር እንደ ከተማ በ4 ሙያዎች 1ኛ ደረጃ፣ በ2 ዘርፎች 2ኛ ደረጃን እና በ1 ሙያ ደግሞ 3ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ 7 ሜዲያሊዎችን ማግኘት ተችሏል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በከተማ ደረጃ በተደረገው የአሰልጣኞች ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሸነፈ!!
የኮሌጁ አሰልጣኞች በተቋም እና በክላስተር ደረጃ የተወዳደሩበት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሰነድ በላቀ ውጤት አሸናፊ የነበረ ሲሆን በከተማ ደረጃ በተደረገውም ቀዳሚነቱን ይዞ አጠናቋል።
በውድድሩ ርዕሰ ጉዳዩ አንገብጋቢ ችግር መሆኑ፣ ከችግሩ ጋር የተሰናሰለ ዓላማ መቀረጹ፣ ችግሩን ለመፍታት የተደረገው ርቀት፣ በምርምር ሂደቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ወዘተ የሚሉ መስፈርቶች ተካተዋል።
የኮሌጁ አሰልጣኞች የሰሩት ጥናትና ምርምር ርዕስ በስልጠና መጨረሻ ዓመት ላይ በሚሰሯቸው ፕሮጀክቶች እና ድህረ ልምምዶች ላይ የሰልጣኞችን ልል ክህሎት እንዲት ማሳደግ ይቻላል? የሚል ነበር፡፡
ባለፈው ዓመትም በአሰልጣኞች የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በከተማ ደረጃ አንደኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
በሌላ በኩል በተያያዘ በሰልጣኞች መካከል ሲደረግ የነበረው የክህሎት ውድድር እንደ ከተማ በ4 ሙያዎች 1ኛ ደረጃ፣ በ2 ዘርፎች 2ኛ ደረጃን እና በ1 ሙያ ደግሞ 3ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ 7 ሜዲያሊዎችን ማግኘት ተችሏል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ሐሙስ:- ሚያዚያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም
የትንሣኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ ኮሌጁ ለተለያዩ አካላት ስጦታ አበረከተ!!
በኮሌጁ ስጦታ ከተበረከተላቸው መካከል የቢዝነስ ዲፓርትመንት አሰልጣኝ የነበረቺውና ከ8 ወር በፊት ህይወቷ ያለፈው የአሰልጣኝ ትደነቅ ምስክር ቤተሰቦች ይገኙበታል። ለእነዚህ ቤተሰቦች ከተቋሙ ሰራተኞች 137ሺ ብር በማሰባሰብ የብርና የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። በዓይነት ተገዝተው ከተሰጡት ውስጥ የተለያዩ አስቤዛዎችን እንዲሁም የሻማ ማምረቻ እና የችብስ መጥበሻ ማሽኖች ይገኙበታል።
ሌላው መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክኒያት በማድረግ ኮሌጁ ከ260ሺ ብር /ከሩብ ሚሊዮን ብር/ በላይ ወጪ የጠየቀ የማዕድ ማጋራትን ያደረገው ደግሞ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች እና ኮሌጁ በየወሩ ድጋፍ እያደረገ ለሚያሳድጋቸው 16 ልጆች ነው።
የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ በኑሮ ውድነቱ ምክንያት ጫና ላይ ላሉ የስራ ባልደረቦች የመተሳሰብ እና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በሌላ ዜና የኮሌጁ አጋር ሆኖ 4 ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ በመስራት የተቋሙ ገፅታ እንዲቀየርና የውስጥ ገቢው እንዲያድግ ያደረገው ፉት ፒች ኃላ/የተ/የግ/ ማኅበር ለኮሌጁ የጥበቃ ሰራተኞች የበዓል መዋያ ይሁናችሁ ብሎ 50ሺ ብር ሰጥቷቸዋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የትንሣኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ ኮሌጁ ለተለያዩ አካላት ስጦታ አበረከተ!!
በኮሌጁ ስጦታ ከተበረከተላቸው መካከል የቢዝነስ ዲፓርትመንት አሰልጣኝ የነበረቺውና ከ8 ወር በፊት ህይወቷ ያለፈው የአሰልጣኝ ትደነቅ ምስክር ቤተሰቦች ይገኙበታል። ለእነዚህ ቤተሰቦች ከተቋሙ ሰራተኞች 137ሺ ብር በማሰባሰብ የብርና የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። በዓይነት ተገዝተው ከተሰጡት ውስጥ የተለያዩ አስቤዛዎችን እንዲሁም የሻማ ማምረቻ እና የችብስ መጥበሻ ማሽኖች ይገኙበታል።
ሌላው መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክኒያት በማድረግ ኮሌጁ ከ260ሺ ብር /ከሩብ ሚሊዮን ብር/ በላይ ወጪ የጠየቀ የማዕድ ማጋራትን ያደረገው ደግሞ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች እና ኮሌጁ በየወሩ ድጋፍ እያደረገ ለሚያሳድጋቸው 16 ልጆች ነው።
የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ በኑሮ ውድነቱ ምክንያት ጫና ላይ ላሉ የስራ ባልደረቦች የመተሳሰብ እና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በሌላ ዜና የኮሌጁ አጋር ሆኖ 4 ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ በመስራት የተቋሙ ገፅታ እንዲቀየርና የውስጥ ገቢው እንዲያድግ ያደረገው ፉት ፒች ኃላ/የተ/የግ/ ማኅበር ለኮሌጁ የጥበቃ ሰራተኞች የበዓል መዋያ ይሁናችሁ ብሎ 50ሺ ብር ሰጥቷቸዋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"