በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር የሆኑት ቤተ እስራኤላዊው አብርሃም ንጉሴ ዛሬ አፍሪካ ኅብረት የሩዋንዳውን የዘር ጭፍጨፋ ለማሰብ ካዘጋጀው ስብሰባ ተገደው እንዲወጡ ተደርገዋል። አምባሳደር ከስብሰባው እንዲወጡ የተገደዱት፣ እስራኤል በጋዛ ፍልስጤማዊያን ላይ የምትፈጽመውን መጠነ ሰፊ ጥቃት የሚቃወሙ በርካታ አባል አገራት አምባሳደሩ በተገኙበት ስብሰባ ላይ አንካፈልም ብለው ተቃውሞ በማሰማታቸውን እንደሆነ ተገልጧል። የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ አምባሳደሩ ከስብሰባው ተገደው መውጣታቸውን ተከትሎ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሃሙድ የሱፍን መውቀሱን የእስራኤል ጋዜጦች ዘግበዋል። ሚንስቴሩ፣ ድርጊቱ የዘር ጭፍጨፋ የደረሰባቸውን የሩዋንዳ ቱትሲዎች መታሰቢያ ክብር ያልሰጠ፣ ተቀባይነት የሌለውና፣ የሩዋንዳና አይሁድ ሕዝቦችን ታሪክ ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው በማለት መተቸቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። እስራኤል በድርጊቱ አሳሳቢነት ዙሪያ በዲፕሎማሲያዊ መስመሮች እንደምትገልጽ ጠቁማለች ተብሏል። አብርሃም የእስራኤል አምባሳደር ሆነው የተሾሙት፣ ባለፈው ዓመት ነሃሴ ነበር። [ዋዜማ]
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳን ከሃላፊነት ማሰናበታቸውን ዛሬ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው በትግርኛ ቋንቋ ባስላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ዐቢይ፣ ጌታቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት በመኾን ያበረከቱትን አስተዋጽዖ ፌዴራል መንግሥቱ እውቅና እንደሚሠጠው በመግለጽ ጌታቸውን አመሰግነዋል። ጌታቸው፣ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መሠረት ጊዜያዊ አስተዳደሩን እንዲመሩ በጠቅላይ ሚንስትሩ የተሾሙት ከሁለት ዓመታት በፊት ነበር። ዐቢይ፣ የቆይታ ጊዜው ለተጠናቀቀው ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ዕጩ ፕሬዝዳንቶችን የትግራይ ሕዝብ ለጽሕፈት ቤታቸው እንዲጠቁም ከቀናት በፊት ጥሪ ማድረጋቸው አይዘነጋም። ኾኖም ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ጠቅላይ ሚንስትሩ በተናጥል ፕሬዝዳንት ለመሾም እየሞከሩ ነው በማለት ጥሪውን ውድቅ አድርጎታል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ማክሰኞ፣ መጋቢት 30/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ሌተናል ጄኔራል ታደሠ ወረደ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ሹመዋቸዋል። ጄኔራል ታደሠ ሥልጣኑን ሲረከቡ፣ የክልሉ አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር የተልዕኮ አፈጻጸም የቃል ኪዳን ሰነድ ፈርመዋል። ሰነዱ፣ ከሕገ መንግሥታዊና ከሕጋዊ ሥርዓት፣ ከአገር ሉዓላዊነትና ከፕሪቶርያው የግጭት ማቆም ስምምነት ያፈነገጡ ግንኙነቶችና እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ታደሠ መስራት እንዳለባቸው ግዴታ ይዟል። የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ የተጀመሩ ሂደቶች እንዲጠናቀቁና በቀሪ አካባቢዎች በፍጥነት እንዲተገበሩ ማድረግን፤ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መሠረት ትጥቅ የመፍታትና የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም እንቅስቃሴ ባፋጣኝ ማጠናቀቅን፤ በትግራይ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን፤ ለሕዝብ ደኅንነት፣ ለሰላምና ለጸጥታ ጠንቅ የሆኑ ጉልህ ሕገወጥ እንቅስቃሴዎች ማስቆምና መደበኛ የልማት ሥራዎችን፣ መንግሥታዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን እንዲሁም የመልሶ ግንባታ ሥራዎችን ማሳለጥ፤ ክልሉ ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ዝግጁ እንዲኾን ማመቻቸት፤ በክልሉ የሲቪክና የፖለቲካ መብቶች ተግባራዊ የሆኑበትና የፖለቲካ ብዝኃነትን የሚያስተናግድ ደሞክራሲያዊ ዐውድ እንዲፈጠር ማድረግ፤ የክልሉ ሕዝብ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችና የፖለቲካ ተዋንያን በአገራዊ የምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ አስፈላጊ ሁኔታዎችን መፍጠር፤ የክልሉ መንግሥታዊ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴዎች የሀገሪቱን ሕዝቦች ትሥሥርና መልካም ግንኙነት የሚያጠናከሩ እና ሕግ እና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓትን የሚያስከብሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ የሚሉ ግዴታዎችን ጭምር አካቷል።
2፤ በባሕርዳር በመካሄድ ላይ የሚገኘው የአገራዊ ምክክር የአጀንዳዎች ማሰባሰቢያ መድረክ በዋናው አገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚሳተፉና የክልሉን አጀንዳ የሚያጠናቅሩ 270 ተወካዮችን ዛሬ መርጧል። የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተካተቱ ቡድኖች ያነሷቸውን አጀንዳዎች ባንድ ላይ የማጠናቀርና የመሰነድ ሥራም ዛሬ እንደተሠራ የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ኮሚሽኑ፣ ሚያዚያ 02 ደሞ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሁለተኛው ዙር የአጀንዳ ልየታ ይጀምራል።
3፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ በኢትዮጵያ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ከጥር እስከ መጋቢት ባለው ጊዜ ውስጥ 1 ነጥብ3 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አዲስ ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ኾኖም በምግብ ዕርዳታ እጥረት ሳቢያ፣ ቅድሚያ ድጋፍ ለመስጠት የወሰነው በከፍተኛ ደረጃ ለተጎዱና ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ተመላሾች እንደሆነ ድርጅቱ ገልጧል። ድርጅቱ በየካቲት ወር ለእያንዳንዱ ተረጂ መቅረብ ካለበት የምግብ ራሽን ውስጥ 65 በመቶውን ብቻ ማለትም ዘጠኝ ኪሎ ግራም ጥራጥሬ፣ አንድ ኪሎ ግራም የቅባት እህሎች እና አንድ ኪሎ ግራም የምግብ ዘይት ብቻ ማቅረቡን ገልጧል። ድርጅቱ፣ ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ ካልተገኘ በስተቀር፣ ዝቅተኛ የምግብ ራሽን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ይሻሻላል ተብሎ እንደማይጠበቅ ጠቅሷል።
4፤ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ለጋዜጠኞች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ለመስጠትና የጋዜጠኞች ምዝገባ ለማከናወን ሥልጣን የለውም ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ምክር ቤቱ በጋዜጠኞች ምዝገባ ለማከናወን እንቅስቃሴ ጀምሬያለሁ ማለቱን ተከትሎ፣ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኀን ተቋማት፣ ጋዜጠኞችና የሙያ ማኅበራት በጉዳዩ ሕጋዊነት ዙሪያ ማብራሪያ ለማግኘት ጥያቄ እያቀረቡ መኾኑን ባለሥልጣኑ ጠቅሷል፡፡ ባለሥልጣኑ፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጁ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጋዜጠኞችን ወይም የመገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎችን እንዲመዘግብ ወይም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ እንዲሠጥ የሠጠው ሥልጣን የለም ብሏል። በዚህ ረገድ ምክር ቤቱ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ባለሥልጣኑ እውቅና እንደማይሰጥም በመግለጫው ላይ አመልክቷል።
5፤ ንግድ ባንክ፣ መንግሥት የተበደረው ብድር 1 ትሪሊዮን ብር መድረሱን ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ላይ ገልጧል ተብሎ ሰሞኑን በተሠራጨው ዘገባ ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ ሠጥቷል። ባንኩ ባጠቃላይ ካለው 1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር የብድር ክምችት ውስጥ አንድ ትሪሊዮን ብር ያህሉ ዕዳ የመንግሥት ዕዳ መሆኑን ባንኩ እንደገለጠ ጠቅሶ ሪፖርተር ያሠራጨው ዘገባ የተሳሳተ ነው በማለት አስተባብሏል። በተያዘው በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግስት በቀጥታ አበድሮ እንደማያውቅ የገለጠው ባንኩ፣ መንግስት በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ በቀጥታ ከባንኩ የመበደር አሠራርም ሆነ ልምድ የለውም ብሏል። ባለፉት 15 ዓመታት 92 በመቶውን ብድር የሰጠው ለመንግስት ተቋማት ነው መባሉን በማስተባበልም፣ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ባንኩ በቅድሚያ ብድር የሚሠጠው ለግል ተበዳሪዎች መሆኑን ጠቅሷል። ባሁኑ ወቅት ያለው የመንግስት ተቋማት የብድር ክምችት ድርሻ ወደ 72 በመቶ ዝቅ ማለቱን፣ ይህም የመንግሥት የልማት ድርጅቶች እዳ እንደሆነና መንግስት በቀጥታ ራሱ የተበደረው አድርጎ መቁጠር እንደማይቻልም ባንኩ አብራርቷል።
6፤ ቦይንግ ኩባንያ፣ በኢትዮጵያ ከስድስት ዓመት በፊት በቦይንግ 737 ማክስ የመንገደኞች አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ ተጎጂዎች ቤተሰቦች በመሠረቷቸው ሁለት ክሶች ላይ የካሳ ስምምነት ላይ ደርሷል። ክሶቹ በድርድር መፍትሄ ያገኙት፣ ትናንት ቺካጎ ውስጥ በፍርድ ቤት ሊታዩ ዝግጅት እየተደረገ ባለበት ዋዜማ ላይ ነው። ቦይንግ፣ በሁለቱ ስምምነቶች ምን ያህል የገንዘብ ካሳ ለመክፈል እንደተስማማ አልተገለጠም። ቦይንግ፣ እስካኹን በድርድር ወይም በፍርድ ሂደት ያልፈታቸው 18 የክስ መዝገቦች ይቀሩታል። በቀጣዩ ሐምሌ ወር አንድ ቴክሳስ የሚገኝ ፍርድ ቤት የአገሪቱ ፍትሕ መስሪያ ቤት በኩባንያው ላይ የመሠረተውን ክስ ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል።
7፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም በግጭት ውስጥ የሚገኙትን ጨምሮ ለ11 አገራት አስቸኳይ የነፍስ አድን ፕሮግራሞች ለሚሠጠው እርዳታ የገንዘብ ድጋፍ ማቋረጡን ዓለማቀፍ የዜና ወኪሎች ዘግበዋል። የገንዘብ ድጋፉ መቋረጥ አስከፊ ርሃብና የምግብ እጥረት በገጠማቸው በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የተላለፈ "የሞት ፍርድ" ነው ያለው ድርጅቱ፣ በተለይ ለሕይወት አድን ፕሮግራሞች የሚውለው ድጋፍ እንዲቀጥል ከአሜሪካ ባለሥልጣናት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ገልጧል። በአሜሪካ ድጋፍ መቆም ሳቢያ ድርጅቱ የምግብና ሕክምና እርዳታዎችን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ካቋረጠባቸው አገራት መካከል፣ ሱማሊያ፣ ዚምባብዌ፣ የመን፣ ሶሪያ እና አፍጋኒስታን ይገኙበታል። ድርጅቱ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ተረጂዎች የሚሠጠው በዚህ በዚህ ውሳኔ ውስጥ ይካተት አይካተት ለጊዜው አልታወቀም። [ዋዜማ]
1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ሌተናል ጄኔራል ታደሠ ወረደ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ሹመዋቸዋል። ጄኔራል ታደሠ ሥልጣኑን ሲረከቡ፣ የክልሉ አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር የተልዕኮ አፈጻጸም የቃል ኪዳን ሰነድ ፈርመዋል። ሰነዱ፣ ከሕገ መንግሥታዊና ከሕጋዊ ሥርዓት፣ ከአገር ሉዓላዊነትና ከፕሪቶርያው የግጭት ማቆም ስምምነት ያፈነገጡ ግንኙነቶችና እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ታደሠ መስራት እንዳለባቸው ግዴታ ይዟል። የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ የተጀመሩ ሂደቶች እንዲጠናቀቁና በቀሪ አካባቢዎች በፍጥነት እንዲተገበሩ ማድረግን፤ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መሠረት ትጥቅ የመፍታትና የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም እንቅስቃሴ ባፋጣኝ ማጠናቀቅን፤ በትግራይ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን፤ ለሕዝብ ደኅንነት፣ ለሰላምና ለጸጥታ ጠንቅ የሆኑ ጉልህ ሕገወጥ እንቅስቃሴዎች ማስቆምና መደበኛ የልማት ሥራዎችን፣ መንግሥታዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን እንዲሁም የመልሶ ግንባታ ሥራዎችን ማሳለጥ፤ ክልሉ ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ዝግጁ እንዲኾን ማመቻቸት፤ በክልሉ የሲቪክና የፖለቲካ መብቶች ተግባራዊ የሆኑበትና የፖለቲካ ብዝኃነትን የሚያስተናግድ ደሞክራሲያዊ ዐውድ እንዲፈጠር ማድረግ፤ የክልሉ ሕዝብ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችና የፖለቲካ ተዋንያን በአገራዊ የምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ አስፈላጊ ሁኔታዎችን መፍጠር፤ የክልሉ መንግሥታዊ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴዎች የሀገሪቱን ሕዝቦች ትሥሥርና መልካም ግንኙነት የሚያጠናከሩ እና ሕግ እና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓትን የሚያስከብሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ የሚሉ ግዴታዎችን ጭምር አካቷል።
2፤ በባሕርዳር በመካሄድ ላይ የሚገኘው የአገራዊ ምክክር የአጀንዳዎች ማሰባሰቢያ መድረክ በዋናው አገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚሳተፉና የክልሉን አጀንዳ የሚያጠናቅሩ 270 ተወካዮችን ዛሬ መርጧል። የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተካተቱ ቡድኖች ያነሷቸውን አጀንዳዎች ባንድ ላይ የማጠናቀርና የመሰነድ ሥራም ዛሬ እንደተሠራ የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ኮሚሽኑ፣ ሚያዚያ 02 ደሞ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሁለተኛው ዙር የአጀንዳ ልየታ ይጀምራል።
3፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ በኢትዮጵያ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ከጥር እስከ መጋቢት ባለው ጊዜ ውስጥ 1 ነጥብ3 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አዲስ ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ኾኖም በምግብ ዕርዳታ እጥረት ሳቢያ፣ ቅድሚያ ድጋፍ ለመስጠት የወሰነው በከፍተኛ ደረጃ ለተጎዱና ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ተመላሾች እንደሆነ ድርጅቱ ገልጧል። ድርጅቱ በየካቲት ወር ለእያንዳንዱ ተረጂ መቅረብ ካለበት የምግብ ራሽን ውስጥ 65 በመቶውን ብቻ ማለትም ዘጠኝ ኪሎ ግራም ጥራጥሬ፣ አንድ ኪሎ ግራም የቅባት እህሎች እና አንድ ኪሎ ግራም የምግብ ዘይት ብቻ ማቅረቡን ገልጧል። ድርጅቱ፣ ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ ካልተገኘ በስተቀር፣ ዝቅተኛ የምግብ ራሽን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ይሻሻላል ተብሎ እንደማይጠበቅ ጠቅሷል።
4፤ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ለጋዜጠኞች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ለመስጠትና የጋዜጠኞች ምዝገባ ለማከናወን ሥልጣን የለውም ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ምክር ቤቱ በጋዜጠኞች ምዝገባ ለማከናወን እንቅስቃሴ ጀምሬያለሁ ማለቱን ተከትሎ፣ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኀን ተቋማት፣ ጋዜጠኞችና የሙያ ማኅበራት በጉዳዩ ሕጋዊነት ዙሪያ ማብራሪያ ለማግኘት ጥያቄ እያቀረቡ መኾኑን ባለሥልጣኑ ጠቅሷል፡፡ ባለሥልጣኑ፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጁ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጋዜጠኞችን ወይም የመገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎችን እንዲመዘግብ ወይም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ እንዲሠጥ የሠጠው ሥልጣን የለም ብሏል። በዚህ ረገድ ምክር ቤቱ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ባለሥልጣኑ እውቅና እንደማይሰጥም በመግለጫው ላይ አመልክቷል።
5፤ ንግድ ባንክ፣ መንግሥት የተበደረው ብድር 1 ትሪሊዮን ብር መድረሱን ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ላይ ገልጧል ተብሎ ሰሞኑን በተሠራጨው ዘገባ ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ ሠጥቷል። ባንኩ ባጠቃላይ ካለው 1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር የብድር ክምችት ውስጥ አንድ ትሪሊዮን ብር ያህሉ ዕዳ የመንግሥት ዕዳ መሆኑን ባንኩ እንደገለጠ ጠቅሶ ሪፖርተር ያሠራጨው ዘገባ የተሳሳተ ነው በማለት አስተባብሏል። በተያዘው በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግስት በቀጥታ አበድሮ እንደማያውቅ የገለጠው ባንኩ፣ መንግስት በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ በቀጥታ ከባንኩ የመበደር አሠራርም ሆነ ልምድ የለውም ብሏል። ባለፉት 15 ዓመታት 92 በመቶውን ብድር የሰጠው ለመንግስት ተቋማት ነው መባሉን በማስተባበልም፣ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ባንኩ በቅድሚያ ብድር የሚሠጠው ለግል ተበዳሪዎች መሆኑን ጠቅሷል። ባሁኑ ወቅት ያለው የመንግስት ተቋማት የብድር ክምችት ድርሻ ወደ 72 በመቶ ዝቅ ማለቱን፣ ይህም የመንግሥት የልማት ድርጅቶች እዳ እንደሆነና መንግስት በቀጥታ ራሱ የተበደረው አድርጎ መቁጠር እንደማይቻልም ባንኩ አብራርቷል።
6፤ ቦይንግ ኩባንያ፣ በኢትዮጵያ ከስድስት ዓመት በፊት በቦይንግ 737 ማክስ የመንገደኞች አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ ተጎጂዎች ቤተሰቦች በመሠረቷቸው ሁለት ክሶች ላይ የካሳ ስምምነት ላይ ደርሷል። ክሶቹ በድርድር መፍትሄ ያገኙት፣ ትናንት ቺካጎ ውስጥ በፍርድ ቤት ሊታዩ ዝግጅት እየተደረገ ባለበት ዋዜማ ላይ ነው። ቦይንግ፣ በሁለቱ ስምምነቶች ምን ያህል የገንዘብ ካሳ ለመክፈል እንደተስማማ አልተገለጠም። ቦይንግ፣ እስካኹን በድርድር ወይም በፍርድ ሂደት ያልፈታቸው 18 የክስ መዝገቦች ይቀሩታል። በቀጣዩ ሐምሌ ወር አንድ ቴክሳስ የሚገኝ ፍርድ ቤት የአገሪቱ ፍትሕ መስሪያ ቤት በኩባንያው ላይ የመሠረተውን ክስ ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል።
7፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም በግጭት ውስጥ የሚገኙትን ጨምሮ ለ11 አገራት አስቸኳይ የነፍስ አድን ፕሮግራሞች ለሚሠጠው እርዳታ የገንዘብ ድጋፍ ማቋረጡን ዓለማቀፍ የዜና ወኪሎች ዘግበዋል። የገንዘብ ድጋፉ መቋረጥ አስከፊ ርሃብና የምግብ እጥረት በገጠማቸው በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የተላለፈ "የሞት ፍርድ" ነው ያለው ድርጅቱ፣ በተለይ ለሕይወት አድን ፕሮግራሞች የሚውለው ድጋፍ እንዲቀጥል ከአሜሪካ ባለሥልጣናት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ገልጧል። በአሜሪካ ድጋፍ መቆም ሳቢያ ድርጅቱ የምግብና ሕክምና እርዳታዎችን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ካቋረጠባቸው አገራት መካከል፣ ሱማሊያ፣ ዚምባብዌ፣ የመን፣ ሶሪያ እና አፍጋኒስታን ይገኙበታል። ድርጅቱ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ተረጂዎች የሚሠጠው በዚህ በዚህ ውሳኔ ውስጥ ይካተት አይካተት ለጊዜው አልታወቀም። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ረቡዕ፣ ሚያዝያ 1/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፣ የፋኖ ታጣቂዎች ጥለውታል በተባለ ክልከላ የተነሳ አርሶ አደሮች ማዳበሪያ መውሰድ እንዳልቻሉ ዋዜማ በተለያዩ ወረዳዎች ካነጋገረቻቸው አርሶ አደሮች ሰምታለች። መንግሥት ላንድ ኩንታል ማዳበሪያ 8 ሺሕ ብር መተመኑን ያስረዱት አርሶ አደሮቹ፣ የፋኖ ታጣቂዎች ግን የአንድ ኩንታል ዋጋ 4 ሺሕ ብር እንደኾነ በመጥቀስና ተጨማሪው ዋጋ አርሶ አደሩን ለመበዝበዝ የወጣ ዋጋ መሆኑን በመጥቀስ፣ አርሶ አደሮቹ ማዳበሪያውን እንዳይገዙ እንዳስጠነቀቋቸው አውስተዋል። መንግሥት ባንጻሩ አርሶ አደሮች ማዳበሪያውን እንዲረከቡ በማሳሰብ ላይ እንደሆነ ታውቋል። በሰሜን ጎጃም ዞን፣ ሰሜን ሜጫ ወረዳ፣ ባችማ በተባለች የገጠር ቀበሌ፣ የማዳበሪያ ገንዘብ ሰብስቦ ሊያስገባ የነበረ አንድ የአርሶ አደሮች ተወካይ ከቀናት በፊት በታጣቂዎቹ እንደተገደለ አርሶ አደሮች ተናግረዋል።
2፤ የአማራ ክልል የአገራዊ ምክክር አጀንዳ ልየታ ወኪሎች፣ ከክልሉ በኃይል ተወስደዋል ያሏቸው ግዛቶች እንዲመለሱ የሚጠይቅ አጀንዳ አቅርበዋል። ተወካዮቹ፣ የማንነትና የወሰን አከላለልን፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያን፣ የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማና የአዲስ አበባን የባለቤትነት የሚመለከቱ አጀንዳዎችንም ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አስረክበዋል። ተወካዮቹ በኃይል ወደ ትግራይ ተወስደው ተካለዋል ያሏቸው፣ ወልቃይትን፣ ሰቲት ሁመራን፣ ጠገዴን፣ ኮረምን፣ አላማጣንና ራያን ሲሆን ሞን፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሥር ተካለዋል ያሏቸው ደሞ መተከል እና ፓዌ ናቸው። በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘው ደራ ወረዳም፣ ወደ ኦሮሚያ ክልል በኃይል ተካሏል ብለዋል። የብሄሮችና ብሄረሰቦች የመገንጠል መብት እንዲሰረዝ፣ የአገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ላይ ተቀመጠው የኮከብ ምልክት እንዲወጣ፣ የክልሎች ባንዲራ እንዲቀርና የፌደሬሽኑ አወቃቀር የሕዝቦችን መልካምድራዊ አቀማመጥ መሠረት ያደረገ እንዲሆንና የአዲስ አበባን የባለቤትነት ጥያቄ የሚመለከቱ አጀንዳዎችም ቀርበዋል።
3፤ የብሄራዊ ደኅንነት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት መብት ለማስከበር ዲፕሎማሲያዊ፣ ሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገዶችን መሠረት አድርጎ የተጀመረው ሥራ ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲጓዝና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሁለንተናዊ ቁልፍ ሚና መጫወት እንድትችል የሚያስችል አቅጣጫ ማስቀመጡን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ምክር ቤቱ፣ አገራዊ የሰላም ሁኔታዎች እየተሻሻሉ ሄደዋል በማለትም ግምገማውን አስቀምጧል። የግጭትንና የጦርነትን አስከፊነት የተረዳው ሕዝብ፣ ከግጭት ጠማቂዎች ጋር ላለመተባበር ያሳየው ውሳኔና መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሔ ያለው የጸና አቋም ለሰላም ሁኔታዎች መሻሻል ምክንያቶች እንደሆኑም ምክር ቤቱ አውስቷል። ምክር ቤቱ፣ ፍላጎታቸውን በኃይል ለማስፈጸም በዝርፊያን፣ እገታ እና ሕገ ወጥ ንግድ ተሠርተዋል ያላቸውን አካላት ላይ የሕግ ማስከበር ሥራውን እንደሚቀጥል ገልጧል። በአገር ውስጥና በውጭ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በመተባበር፣ የመንግሥት ሥራዎችን ያደናቅፋሉ እንዲሁም በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ያካሂዳሉ ባላቸው አካላት ላይ የሕግ ማስከበር ርምጃ መውሰድ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ያላቸውን አካላት ወይም ከጠላት ተልዕኮ ይቀበላሉ ያላቸውን ኃይሎች ግን ምክር ቤቱ በስም አልጠቀሰም።
4፤ ኦብነግ፣ ጅግጅጋ ውስጥ የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ነን በማለት የተሰበሰቡ አካላት መንግሥት ያደራጃቸው ናቸው ሲል አጣጥሏል። መንግሥት በምርጫ ቦርድ ታዛቢነት የተወሰኑ ግለሰቦችን አደራጅቶ በድርጅቱ ስም ስብሰባ እንዲካሄድ ማድረጉ፣ አስመራ ላይ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ይጥሳል በማለት ግንባሩ ድርጊቱን አውህዟል። በጅግጅጋው ስብሰባ የድርጅቱን ማዕከላዊ ኮሚቴ እንደሚወክሉ የገለጡ አካላት፣ የግንባሩን ሊቀመንበር አብድራህማን መሃዲን ከሥልጣን አውርደናል ማለታቸውን የመንግሥት የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
5፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የትግርኛ ቋንቋ ክፍል ጎንደር እና ሁመራን የሚያገናኘው መንገድ ጥገና እየተካሄደለት ነው በሚለው ዘገባው፣ ሁመራ በአማራ ክልል ሥር እንደሚገኝ አድርጎ የተዛባ መረጃ አሠራጭቷል በማለት ወቅሷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ዜናው "ኾን ተብሎ የትግራይ ሉዓላዊ ግዛትን ለአማራ ክልል አሳልፎ የመስጠት ያለመና የሕገ መንግሥት ጥሰት የተፈጸመበት ነው" በማለት ከሷል። የተቋሙ አዘጋገብ "ተቀባይነት የሌለው" እና "የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት በቀጥታ የሚጻረር ነው" ያለው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ዘገባው ባስቸኳይ እንዲታረምና "ስሜታዊ" እና "ተንኳሽ" ያልውን ዘገባ በሠሩ አዘጋጆች ላይ ርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። ፌደራል መንግሥቱም ሕገመንግሥታዊ ጥሰቶችን በሚፈጽሙ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ጊዜያዊ አስተዳደሩ አሳስቧል።
6፤ የአሜሪካው ዓለማቀፍ የተራድኦ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ለዓለም ምግብ ፕሮግራም አቋርጦት የነበረውን የነፍስ አድን እርዳታ በድጋሚ ለመቀጠል ወስኗል። ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ፣ የነፍስ አድን ድጋፉን እንደገና ለመቀጠል የወሰነው፣ ውሳኔው "ለርሃብና ለከባድ የምግብ እጥረት በተጋለጡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የተላለፈ የሞት ፍርድ ነው" በማለት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከትናንት ወዲያ ማስጠንቀቁን ተከትሎ ነው። ለአስቸኳይ የነፍስ አድን አሜሪካ ድርጅቱ የነፍስ አድን ፕሮግራሞቹን እንደገና ከሚቀጥልባቸው አገራት መካከል፣ ሱማሊያ እና ኒዠር ይገኙበታል። [ዋዜማ]
1፤ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፣ የፋኖ ታጣቂዎች ጥለውታል በተባለ ክልከላ የተነሳ አርሶ አደሮች ማዳበሪያ መውሰድ እንዳልቻሉ ዋዜማ በተለያዩ ወረዳዎች ካነጋገረቻቸው አርሶ አደሮች ሰምታለች። መንግሥት ላንድ ኩንታል ማዳበሪያ 8 ሺሕ ብር መተመኑን ያስረዱት አርሶ አደሮቹ፣ የፋኖ ታጣቂዎች ግን የአንድ ኩንታል ዋጋ 4 ሺሕ ብር እንደኾነ በመጥቀስና ተጨማሪው ዋጋ አርሶ አደሩን ለመበዝበዝ የወጣ ዋጋ መሆኑን በመጥቀስ፣ አርሶ አደሮቹ ማዳበሪያውን እንዳይገዙ እንዳስጠነቀቋቸው አውስተዋል። መንግሥት ባንጻሩ አርሶ አደሮች ማዳበሪያውን እንዲረከቡ በማሳሰብ ላይ እንደሆነ ታውቋል። በሰሜን ጎጃም ዞን፣ ሰሜን ሜጫ ወረዳ፣ ባችማ በተባለች የገጠር ቀበሌ፣ የማዳበሪያ ገንዘብ ሰብስቦ ሊያስገባ የነበረ አንድ የአርሶ አደሮች ተወካይ ከቀናት በፊት በታጣቂዎቹ እንደተገደለ አርሶ አደሮች ተናግረዋል።
2፤ የአማራ ክልል የአገራዊ ምክክር አጀንዳ ልየታ ወኪሎች፣ ከክልሉ በኃይል ተወስደዋል ያሏቸው ግዛቶች እንዲመለሱ የሚጠይቅ አጀንዳ አቅርበዋል። ተወካዮቹ፣ የማንነትና የወሰን አከላለልን፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያን፣ የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማና የአዲስ አበባን የባለቤትነት የሚመለከቱ አጀንዳዎችንም ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አስረክበዋል። ተወካዮቹ በኃይል ወደ ትግራይ ተወስደው ተካለዋል ያሏቸው፣ ወልቃይትን፣ ሰቲት ሁመራን፣ ጠገዴን፣ ኮረምን፣ አላማጣንና ራያን ሲሆን ሞን፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሥር ተካለዋል ያሏቸው ደሞ መተከል እና ፓዌ ናቸው። በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘው ደራ ወረዳም፣ ወደ ኦሮሚያ ክልል በኃይል ተካሏል ብለዋል። የብሄሮችና ብሄረሰቦች የመገንጠል መብት እንዲሰረዝ፣ የአገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ላይ ተቀመጠው የኮከብ ምልክት እንዲወጣ፣ የክልሎች ባንዲራ እንዲቀርና የፌደሬሽኑ አወቃቀር የሕዝቦችን መልካምድራዊ አቀማመጥ መሠረት ያደረገ እንዲሆንና የአዲስ አበባን የባለቤትነት ጥያቄ የሚመለከቱ አጀንዳዎችም ቀርበዋል።
3፤ የብሄራዊ ደኅንነት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት መብት ለማስከበር ዲፕሎማሲያዊ፣ ሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገዶችን መሠረት አድርጎ የተጀመረው ሥራ ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲጓዝና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሁለንተናዊ ቁልፍ ሚና መጫወት እንድትችል የሚያስችል አቅጣጫ ማስቀመጡን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ምክር ቤቱ፣ አገራዊ የሰላም ሁኔታዎች እየተሻሻሉ ሄደዋል በማለትም ግምገማውን አስቀምጧል። የግጭትንና የጦርነትን አስከፊነት የተረዳው ሕዝብ፣ ከግጭት ጠማቂዎች ጋር ላለመተባበር ያሳየው ውሳኔና መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሔ ያለው የጸና አቋም ለሰላም ሁኔታዎች መሻሻል ምክንያቶች እንደሆኑም ምክር ቤቱ አውስቷል። ምክር ቤቱ፣ ፍላጎታቸውን በኃይል ለማስፈጸም በዝርፊያን፣ እገታ እና ሕገ ወጥ ንግድ ተሠርተዋል ያላቸውን አካላት ላይ የሕግ ማስከበር ሥራውን እንደሚቀጥል ገልጧል። በአገር ውስጥና በውጭ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በመተባበር፣ የመንግሥት ሥራዎችን ያደናቅፋሉ እንዲሁም በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ያካሂዳሉ ባላቸው አካላት ላይ የሕግ ማስከበር ርምጃ መውሰድ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ያላቸውን አካላት ወይም ከጠላት ተልዕኮ ይቀበላሉ ያላቸውን ኃይሎች ግን ምክር ቤቱ በስም አልጠቀሰም።
4፤ ኦብነግ፣ ጅግጅጋ ውስጥ የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ነን በማለት የተሰበሰቡ አካላት መንግሥት ያደራጃቸው ናቸው ሲል አጣጥሏል። መንግሥት በምርጫ ቦርድ ታዛቢነት የተወሰኑ ግለሰቦችን አደራጅቶ በድርጅቱ ስም ስብሰባ እንዲካሄድ ማድረጉ፣ አስመራ ላይ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ይጥሳል በማለት ግንባሩ ድርጊቱን አውህዟል። በጅግጅጋው ስብሰባ የድርጅቱን ማዕከላዊ ኮሚቴ እንደሚወክሉ የገለጡ አካላት፣ የግንባሩን ሊቀመንበር አብድራህማን መሃዲን ከሥልጣን አውርደናል ማለታቸውን የመንግሥት የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
5፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የትግርኛ ቋንቋ ክፍል ጎንደር እና ሁመራን የሚያገናኘው መንገድ ጥገና እየተካሄደለት ነው በሚለው ዘገባው፣ ሁመራ በአማራ ክልል ሥር እንደሚገኝ አድርጎ የተዛባ መረጃ አሠራጭቷል በማለት ወቅሷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ዜናው "ኾን ተብሎ የትግራይ ሉዓላዊ ግዛትን ለአማራ ክልል አሳልፎ የመስጠት ያለመና የሕገ መንግሥት ጥሰት የተፈጸመበት ነው" በማለት ከሷል። የተቋሙ አዘጋገብ "ተቀባይነት የሌለው" እና "የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት በቀጥታ የሚጻረር ነው" ያለው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ዘገባው ባስቸኳይ እንዲታረምና "ስሜታዊ" እና "ተንኳሽ" ያልውን ዘገባ በሠሩ አዘጋጆች ላይ ርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። ፌደራል መንግሥቱም ሕገመንግሥታዊ ጥሰቶችን በሚፈጽሙ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ጊዜያዊ አስተዳደሩ አሳስቧል።
6፤ የአሜሪካው ዓለማቀፍ የተራድኦ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ለዓለም ምግብ ፕሮግራም አቋርጦት የነበረውን የነፍስ አድን እርዳታ በድጋሚ ለመቀጠል ወስኗል። ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ፣ የነፍስ አድን ድጋፉን እንደገና ለመቀጠል የወሰነው፣ ውሳኔው "ለርሃብና ለከባድ የምግብ እጥረት በተጋለጡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የተላለፈ የሞት ፍርድ ነው" በማለት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ከትናንት ወዲያ ማስጠንቀቁን ተከትሎ ነው። ለአስቸኳይ የነፍስ አድን አሜሪካ ድርጅቱ የነፍስ አድን ፕሮግራሞቹን እንደገና ከሚቀጥልባቸው አገራት መካከል፣ ሱማሊያ እና ኒዠር ይገኙበታል። [ዋዜማ]
Read and subscribe our latest MEMO just published at wazema.substack.com
ለቸኮለ! ሐሙስ፣ ሚያዝያ 2/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የክልሉ ጸጥታ ሃላፊና የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ ተሠጥተዋቸው የነበሩትን የሥራ ዝርዝሮች መፈጸም አልቻሉም ነበር በማለት ከቢቢሲ ፎከስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተችተዋል። የጀኔራል ታደሠ የሥራ ዝርዝር በውድቀት የተሞላ ነበር ያሉት ጌታቸው፣ እርሳቸውን በወቅቱ ከሃላፊነት ማንሳት አለመቻላቸው ውድቀታቸው እንደኾነ ገልጸዋል። ሥልጣኑን ጠቅልሎ ለመያዝ ከሚፈልገው ደብረጺዮን ከሚመሩት የሕወሓት አንጃ የሚመጣው ከቁጥጥር ውጪ የኾነ የሥልጣን ጥማት፣ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት ተግዳሮት ኾኖ ሊቀጥል እንደሚችልም ጌታቸው ጠቁመዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ሥልጣን ከሚጎመዡት የሕወሓት ሰዎች ሁሉ የተሻሉት ጀኔራል ታደሠ ናቸው በማለት ሊያሳምኗቸው እንደሞከሩና የታደሠ ሹመት የጠቅላይ ሚንስትሩ ውሳኔ እንደኾነ ጠቅሰዋል። የትግራይን ፖለቲካ ይበልጥ አስቸጋሪ ካደረጉት ጉዳዮች መካከል፣ በመንግሥት ሥር መኾን የነበረበት ሠራዊት እስካኹን ራሱን የቻለ አካል አድርጎ መቆጠሩ ተጠቃሽ እንደኾነም ጌታቸው አውስተዋል። ኤርትራን በተመለከተ፣ በእሳቸው አስተዳደር ውስጥ የተወሰኑ ሰዎች በሕገወጥ መንገድ ከኤርትራ መንግሥት ጋር ለመገናኘት ሲሞክሩ እንደነበር ጌታቸው ተናግረዋል።
2፤ ኦብነግ፣ ጅግጅጋ ላይ ሰሞኑን በመንግሥት አጋፋሪነት ተካሂዷል ያለው ስብሰባ በግንቦት ሊያደርግ ያቀደውን የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ለማሰናከልና በቀጣይም የተጭበረበረ ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ ሕልውናውን ለማጥፋት ያለመ እንደሆነ አስታውቋል። መንግሥት በፓርቲው ስም የተጭበረበረ ጠቅላላ ጉባኤ ካካሄደ የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ይከሽፋል ያለው ፓርቲው፣ ከዚያ ለሚከተለው ውጤት መንግሥት ተጠያቂ ይሆናል በማለት አስጠንቅቋል። ኦብነግ ሕገወጥ ድርጊቶች ሲፈጸሙበት በዝምታ እንደማይመለከትም አስታውቋል። ዓለማቀፉ ኅብረተሰብም፣ ለሰላም ስምምነቱ ጥሰት መንግሥትን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቋል።
3፤ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በእስር ላይ የሚገኙ፣ ለትጥቅ ትግል ጫካ የገቡ እንዲሁም በስደት የሚኖሩ ዜጎች ለአገራዊ ምክክሩ አለን የሚሉትን አጀንዳ የሚያቀርቡበትን ሁኔታ ለመዘርጋት ቁርጠኛ መሆኑን ዛሬ ባሕርዳር ላይ እየተካሄደ በሚገኘው የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ላይ አስታውቋል። ኮሚሽኑ፣ ይህንኑ ሁኔታ ለአማራ ክልል ተወላጆችም እንደሚያመቻች ኮሚሽነር መላኩ ወልደ ማርያም ለመድረኩ ተሳታፊዎች ገልጸዋል። ኾኖም ኮሚሽኑ ይህንኑ ቃል ኪዳኑን በምን ሁኔታና መቼ ተግባራዊ ለማድረግ እንዳሰበ ግን ኮሚሽነሩ አላብራሩም። ዛሬ የተጀመረው የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እስከ ቅዳሜ የሚቀጥል ሲኾን፣ በሂደቱ ከ2 ሺሕ በላይ የአምስት ባለድርሻ አካላት ወኪሎች እንደሚሳተፉ ተገልጧል።
4፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬን እና አምባሳደር ሃደራ አበራን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታዎች አድርገው እንደሾሙ ሚንስቴሩ ካሠራጨው መረጃ ተመልክተናል። ከኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን ጀምሮ በተለያዩ አገራት በአምባሳደርነት ሲያገለግሉ የቆዩት ሃደራ፣ በሚንስቴሩ የፓለቲካና ኢኮኖሚ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ እንዲኾኑ እንደተሾሙ ሚንስቴሩ ገልጧል። ላለፉት ጥቂት ዓመታት በጅቡቲ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ብርሃኑ ደሞ፣ በሚንስቴሩ የሃብት ማኔጅመንትና አገልግሎት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ተመድበዋል።
5፤ ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ቡድን (ሲፒጄ) የኢትዮጵያ መንግሥት በሰባት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞች ላይ የከፈተውን የሽብር ወንጀል ምርመራ እንዲያቋርጥ ጠይቋል። ፖሊስ ነቢዩ ጥዑመልሳን፣ ታሪኩ ኃይሌ፣ ኅሊና ታረቀኝ እና ንጥር ደረጀ፣ ግርማ ተፈራ፣ ኄኖክ አባተ እና ሐብታሙ ዓለማየሁ የተባሉትን ጋዜጠኞች ያሠረው፣ ግጭት ለመቀስቀስ፣ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማናጋትና በአማራ ክልል ከሚገኙ ጽንፈኛ ቡድኖች ጋር በመመሳጠር መንግሥትን ለመገልበጥ አሲረዋል በማለት ነው። የሲፒጄ የአፍሪካ ቢሮ ሃላፊ ሙቶኪ ሙሞ፣ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በቴሌቪዥን ጣቢያው ላይ ርምጃ በወሰደበት ሁኔታ፣ በጋዜጠኝነት ስነ ምግባር ላይ ላጋጠመ ግድፈት ጋዜጠኞችን በሽብር ወንጀል ማሰር የተመጣጠነ ርምጃ አይደለም በማለት ተችተዋል።
6፤ የስዊዘርላንድ መንግሥት፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ በትንሹ 19 ኤርትራዊያን ታዳጊዎችን ወደ አገራቸው በግዳጅ መመለሱን የስዊዘርላንድ ጋዜጦች ዘግበዋል። የአገሪቱ ባለሥልጣናት፣ 50 ኤርትራዊያን ጎልማሶችም ወደ አገራቸው እንዲባረሩ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ኾኖም የኤርትራዊያኑ ስደተኞች ጠበቆች ኤርትራዊያኑን የማባረሩን ትዕዛዝ በመቃወም ለፍርድ ቤት 70 ያህል አቤቱታዎችን አስገብተዋል ተብሏል። ያለ ወላጅ ድጋፍ ስዊዘርላንድ የገቡትን ሕጻናት ከአገር ማባረር፣ አገሪቱ ያጸደቀችውን የተመድ የሕጻናት መብቶች ድንጋጌ ይጥሳል፤ ወደ ኤርትራ በግዳጅ እንዲመለሱ የተደረጉ ስደተኞች ወደ እስር ቤት ላለመወርወራቸውና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰለባ ላለመሆናቸው ዋስትና የለም የሚሉ ትችቶች እየቀረቡ መኾኑን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።
7፤ የተመድ የዳኝነት ፍርድ ቤት፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሱዳኑ ጦርነት በዘር ማጥፋት ወንጀል ተባባሪ ናት በማለት የካርቱም መንግሥት ያቀረበውን ክስ ዛሬ መመልከት ጀምሯል። ሱዳን በፍርድ ቤቱ በመሠረተችው ክስ፣ ኢምሬቶች በምዕራብ ዳርፉር ግዛት የዓረብ ዝርያ የሌላቸውን የመሳሊት ጎሳ አባላት ከምድረገጽ ለማጥፋት፣ ከአገሪቱ ጦር ሠራዊት ጋር በመዋጋት ላይ የሚገኘውን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጦር መሳሪያ ታስታጥቃለች በማለት ወንጅላለች። ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ወንጀሎቹን የሚፈጽመው፣ ኢምሬቶች በምታደርግለት የጦር መሳሪያ፣ የሰው አልባ አውሮፕላን ሥልጠና፣ የቅጥረኛ ተዋጊዎች ቅጥር እንዲሁም የገንዘብና የፖለቲካ ድጋፍ እንደኾነ ሱዳን በአቤቱታዋ ላይ ገልጣለች። ሱዳን፣ በመሳሊት ጎሳ ላይ "ተጨማሪ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች እንዳይፈጸሙ" እና ኢምሬቶች ለቡድኑ ጦር መሳሪያ መስጠቷን እንድታቆም፣ ፍርድ ቤቱ አስቸኳይ ትዕዛዞችን እንዲሠጥ ሱዳን ጠይቃለች። ኢምሬቶች ውንጀላውን በማስተባበል ለፍርድ ቤቱ ምላሽ ሠጥታለች። [ዋዜማ]
1፤ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የክልሉ ጸጥታ ሃላፊና የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ ተሠጥተዋቸው የነበሩትን የሥራ ዝርዝሮች መፈጸም አልቻሉም ነበር በማለት ከቢቢሲ ፎከስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተችተዋል። የጀኔራል ታደሠ የሥራ ዝርዝር በውድቀት የተሞላ ነበር ያሉት ጌታቸው፣ እርሳቸውን በወቅቱ ከሃላፊነት ማንሳት አለመቻላቸው ውድቀታቸው እንደኾነ ገልጸዋል። ሥልጣኑን ጠቅልሎ ለመያዝ ከሚፈልገው ደብረጺዮን ከሚመሩት የሕወሓት አንጃ የሚመጣው ከቁጥጥር ውጪ የኾነ የሥልጣን ጥማት፣ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት ተግዳሮት ኾኖ ሊቀጥል እንደሚችልም ጌታቸው ጠቁመዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ሥልጣን ከሚጎመዡት የሕወሓት ሰዎች ሁሉ የተሻሉት ጀኔራል ታደሠ ናቸው በማለት ሊያሳምኗቸው እንደሞከሩና የታደሠ ሹመት የጠቅላይ ሚንስትሩ ውሳኔ እንደኾነ ጠቅሰዋል። የትግራይን ፖለቲካ ይበልጥ አስቸጋሪ ካደረጉት ጉዳዮች መካከል፣ በመንግሥት ሥር መኾን የነበረበት ሠራዊት እስካኹን ራሱን የቻለ አካል አድርጎ መቆጠሩ ተጠቃሽ እንደኾነም ጌታቸው አውስተዋል። ኤርትራን በተመለከተ፣ በእሳቸው አስተዳደር ውስጥ የተወሰኑ ሰዎች በሕገወጥ መንገድ ከኤርትራ መንግሥት ጋር ለመገናኘት ሲሞክሩ እንደነበር ጌታቸው ተናግረዋል።
2፤ ኦብነግ፣ ጅግጅጋ ላይ ሰሞኑን በመንግሥት አጋፋሪነት ተካሂዷል ያለው ስብሰባ በግንቦት ሊያደርግ ያቀደውን የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ለማሰናከልና በቀጣይም የተጭበረበረ ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ ሕልውናውን ለማጥፋት ያለመ እንደሆነ አስታውቋል። መንግሥት በፓርቲው ስም የተጭበረበረ ጠቅላላ ጉባኤ ካካሄደ የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ይከሽፋል ያለው ፓርቲው፣ ከዚያ ለሚከተለው ውጤት መንግሥት ተጠያቂ ይሆናል በማለት አስጠንቅቋል። ኦብነግ ሕገወጥ ድርጊቶች ሲፈጸሙበት በዝምታ እንደማይመለከትም አስታውቋል። ዓለማቀፉ ኅብረተሰብም፣ ለሰላም ስምምነቱ ጥሰት መንግሥትን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቋል።
3፤ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በእስር ላይ የሚገኙ፣ ለትጥቅ ትግል ጫካ የገቡ እንዲሁም በስደት የሚኖሩ ዜጎች ለአገራዊ ምክክሩ አለን የሚሉትን አጀንዳ የሚያቀርቡበትን ሁኔታ ለመዘርጋት ቁርጠኛ መሆኑን ዛሬ ባሕርዳር ላይ እየተካሄደ በሚገኘው የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ላይ አስታውቋል። ኮሚሽኑ፣ ይህንኑ ሁኔታ ለአማራ ክልል ተወላጆችም እንደሚያመቻች ኮሚሽነር መላኩ ወልደ ማርያም ለመድረኩ ተሳታፊዎች ገልጸዋል። ኾኖም ኮሚሽኑ ይህንኑ ቃል ኪዳኑን በምን ሁኔታና መቼ ተግባራዊ ለማድረግ እንዳሰበ ግን ኮሚሽነሩ አላብራሩም። ዛሬ የተጀመረው የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እስከ ቅዳሜ የሚቀጥል ሲኾን፣ በሂደቱ ከ2 ሺሕ በላይ የአምስት ባለድርሻ አካላት ወኪሎች እንደሚሳተፉ ተገልጧል።
4፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬን እና አምባሳደር ሃደራ አበራን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታዎች አድርገው እንደሾሙ ሚንስቴሩ ካሠራጨው መረጃ ተመልክተናል። ከኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን ጀምሮ በተለያዩ አገራት በአምባሳደርነት ሲያገለግሉ የቆዩት ሃደራ፣ በሚንስቴሩ የፓለቲካና ኢኮኖሚ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ እንዲኾኑ እንደተሾሙ ሚንስቴሩ ገልጧል። ላለፉት ጥቂት ዓመታት በጅቡቲ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ብርሃኑ ደሞ፣ በሚንስቴሩ የሃብት ማኔጅመንትና አገልግሎት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ተመድበዋል።
5፤ ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ቡድን (ሲፒጄ) የኢትዮጵያ መንግሥት በሰባት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞች ላይ የከፈተውን የሽብር ወንጀል ምርመራ እንዲያቋርጥ ጠይቋል። ፖሊስ ነቢዩ ጥዑመልሳን፣ ታሪኩ ኃይሌ፣ ኅሊና ታረቀኝ እና ንጥር ደረጀ፣ ግርማ ተፈራ፣ ኄኖክ አባተ እና ሐብታሙ ዓለማየሁ የተባሉትን ጋዜጠኞች ያሠረው፣ ግጭት ለመቀስቀስ፣ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማናጋትና በአማራ ክልል ከሚገኙ ጽንፈኛ ቡድኖች ጋር በመመሳጠር መንግሥትን ለመገልበጥ አሲረዋል በማለት ነው። የሲፒጄ የአፍሪካ ቢሮ ሃላፊ ሙቶኪ ሙሞ፣ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በቴሌቪዥን ጣቢያው ላይ ርምጃ በወሰደበት ሁኔታ፣ በጋዜጠኝነት ስነ ምግባር ላይ ላጋጠመ ግድፈት ጋዜጠኞችን በሽብር ወንጀል ማሰር የተመጣጠነ ርምጃ አይደለም በማለት ተችተዋል።
6፤ የስዊዘርላንድ መንግሥት፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ በትንሹ 19 ኤርትራዊያን ታዳጊዎችን ወደ አገራቸው በግዳጅ መመለሱን የስዊዘርላንድ ጋዜጦች ዘግበዋል። የአገሪቱ ባለሥልጣናት፣ 50 ኤርትራዊያን ጎልማሶችም ወደ አገራቸው እንዲባረሩ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ኾኖም የኤርትራዊያኑ ስደተኞች ጠበቆች ኤርትራዊያኑን የማባረሩን ትዕዛዝ በመቃወም ለፍርድ ቤት 70 ያህል አቤቱታዎችን አስገብተዋል ተብሏል። ያለ ወላጅ ድጋፍ ስዊዘርላንድ የገቡትን ሕጻናት ከአገር ማባረር፣ አገሪቱ ያጸደቀችውን የተመድ የሕጻናት መብቶች ድንጋጌ ይጥሳል፤ ወደ ኤርትራ በግዳጅ እንዲመለሱ የተደረጉ ስደተኞች ወደ እስር ቤት ላለመወርወራቸውና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰለባ ላለመሆናቸው ዋስትና የለም የሚሉ ትችቶች እየቀረቡ መኾኑን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።
7፤ የተመድ የዳኝነት ፍርድ ቤት፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሱዳኑ ጦርነት በዘር ማጥፋት ወንጀል ተባባሪ ናት በማለት የካርቱም መንግሥት ያቀረበውን ክስ ዛሬ መመልከት ጀምሯል። ሱዳን በፍርድ ቤቱ በመሠረተችው ክስ፣ ኢምሬቶች በምዕራብ ዳርፉር ግዛት የዓረብ ዝርያ የሌላቸውን የመሳሊት ጎሳ አባላት ከምድረገጽ ለማጥፋት፣ ከአገሪቱ ጦር ሠራዊት ጋር በመዋጋት ላይ የሚገኘውን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጦር መሳሪያ ታስታጥቃለች በማለት ወንጅላለች። ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ወንጀሎቹን የሚፈጽመው፣ ኢምሬቶች በምታደርግለት የጦር መሳሪያ፣ የሰው አልባ አውሮፕላን ሥልጠና፣ የቅጥረኛ ተዋጊዎች ቅጥር እንዲሁም የገንዘብና የፖለቲካ ድጋፍ እንደኾነ ሱዳን በአቤቱታዋ ላይ ገልጣለች። ሱዳን፣ በመሳሊት ጎሳ ላይ "ተጨማሪ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች እንዳይፈጸሙ" እና ኢምሬቶች ለቡድኑ ጦር መሳሪያ መስጠቷን እንድታቆም፣ ፍርድ ቤቱ አስቸኳይ ትዕዛዞችን እንዲሠጥ ሱዳን ጠይቃለች። ኢምሬቶች ውንጀላውን በማስተባበል ለፍርድ ቤቱ ምላሽ ሠጥታለች። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ዓርብ፣ ሚያዝያ 3/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ኢሰመኮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉና ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው የተመለሱ ተፈናቃዮች ለተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መጋለጣቸውን አዲስ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። ኮሚሽኑ፣ በደቡባዊ ዞን ወደ ራያ አላማጣ ወረዳና አላማጣ ከተማ የተመለሱ ተፈናቃዮች በደኅንነት ሥጋት ቤታቸው ገብተው ለመኖር አለመቻላቸውን ገልጿል። በሰሜን ምዕራብ ዞን ወደ ጸለምት፣ ላዕላይ ጸለምትና ማይጸብሪ ከተማ የተመለሱ ተፈናቃዮችም፣ ለዳግም መፈናቀል መዳረጋቸውን ኮሚሽኑ ጠቅሷል። ኮሚሽኑ በክትትሉ በሸፈናቸው አካባቢዎች፣ ከኅብረተሰቡ ጋር የተፈጠረ ቂምና ቁሩሾ በእርቅና ውይይት የሚፈታበት ሁኔታ አለመመቻቸቱ ችግሩን እንዳባባሰው አመልክቷል። ተመላሾች በጸጥታ ችግር ምክንያት በነጻነት ተንቀሳቅሰው ለመሥራት አለመቻላቸውም ተገልጧል። ኢሰመኮ፣ በተጠቀሱት አካባቢዎች በውይይትና እርቅ ሠላምን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ፣ ተመላሾች የሕግና ፍትሕ ዋስትና እንዲያገኙ የሲቪል አሥተዳደሮች እንዲዘረጉና የፍትሕ ተቋማት አገልግሎት እንዲጀምሩ ምክረ ሃሰቡን ሠጥቷል።
2፤ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ሮቢና አቡና ግንደበረት ወረዳዎች ትላንት ንጋት ላይ በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎችና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል በተደረገ ውጊያ ቁጥራቸው ያልታወቁ ንጹሃን ሕይወት ማለፉን ዋዜማ ሰምታለች። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ታጣቂዎች በተመሳሳይ ሰዓት ወደ ወረዳዎቹ መግባታቸውን ተከትሎ ለሰዓታት የዘለቀ የተኩስ ልውውጥ እንደተደረገ ምንጮች ተናግረዋል። የቡድኑ አባላት "ፉርቶ" በተባለች መንደር ወደሚገኝ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ ዘልቀው በመግባት፤ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን፣ ወታደራዊ ትጥቆችንና ቁሳቁሶችን መዝረፋቸውን ምንጮቹ ተናግረዋል። በሜታ ወልቂጤ ወረዳ "ኤላ" በተባለች ቀበሌም፣ በግጭቱ ሁለት የክልሉ ሚሊሺያ አባላት ሕይወት ማለፉ ተነግሯል።
3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ የቀድሞውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳን የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አድርገው ሹመዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ የፓርቲ ነጻነቱን እንደጠበቀ ከአዲሱ የጀኔራል ታደሠ ወረደ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ለመስራት ዝግጁ መኾኑን አረጋግጧል። ቡድኑ፣ የትግራይን ሕገመንግሥታዊነት ወደነበረበት መመለስ፣ የትግራይን የግዛት አንድነት ማስከበር፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው መመለስና በምርጫ የተመረጠ መንግሥት ማቋቋም የአዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ትኩረቶች መኾን እንዳለባቸው አሳስቧል። ጀኔራል ታደሠም፣ በቅርብ ጊዜያት በክልሉ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ በማካሄድ ችግሮችን ለመፍታት እቅድ እንደያዙና በጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራር ላይ የተወሰነ ማስተካከያ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።
4፤ አብን፣ የፌዴራል መንግሥትና የክልል መንግሥታት ከታጠቁ ኃይሎች ጋር በመነጋገር ታጣቂ ኃይሎች የአገራዊ ምክከሩ አካል እንዲኾኑ አስፈላጊውን ጥረት እንዲያደርጉ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል። ፓርቲው፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የታጠቁ ቡድኖች፣ ሲቪክ አደረጃጀቶች፣ የሙያ ማኅበራትና የኃይማኖት ተቋማት ምክክር ኮሚሽኑ ባመቻቻቸው መድረኮች እንዲሳተፉ ጠይቋል። ከዚህ በፊት በተካሄዱ የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኮች በንቃት መሳተፉንና በተለይ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የአማራን ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች ማስመዝገቡንም ፓርቲው ጠቅሷል፡፡ አብን፣ የአማራ ሕዝብ አጀንዳዎች በአማራ ክልል ብቻ የተወሰኑ አለመሆናቸውንም አውስቷል።
5፤ የሱዳን ወታደራዊ መሪ ጀኔራል አል ቡርሃን፣ ዛሬ ወደ አሥመራ አቅንተው የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተነጋግረዋል። ውይይቱ በሁለትዮሽ ግንኙነቶች፣ በሱዳኑ ጦርነትና በቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያጠነጠነ እንደነበር የሱዳን መንግሥት ገልጧል። የጀኔራል ቡርሃን ጉብኝት ዓላማ፣ በሱዳን በቅርብ ጊዜያት ውስጥ በታዩ ለውጦች ላይ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ ገለጻ ለማድረግ እንደሆነ ጠቅሷል። ፕሬዝዳንት ኢሳያስም፣ በሱዳኑ ጦርነት የውጭ ጣልቃ ገብነትን ማስወገድ ያስፈልጋል በማለት አጽንዖት ሠጥተው መናገራቸውን የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ገልጸዋል።
6፤ አሜሪካ፣ የሱማሊያው አልሸባብ ግስጋሴ ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባት መስማቱን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል። የቡድኑን መጠናከር ተከትሎ፣ አንዳንድ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባለሥልጣናት የአሜሪካ ወታደሮች ከሱማሊያ እንዲወጡና ለደኅንነት ጥንቃቄ የሞቃዲሾው የአሜሪካ ኢምባሲ እንዲዘጋ ሃሳብ እንዳቀረቡ ዘገባው ጠቅሷል። ባንጻሩ የአሜሪካ ብሄራዊ ደኅንነት ምክር ቤት አባላት፣ ኢምባሲውን መዝጋት በሱማሊያ ማዕከላዊ መንግሥት ላይ ያሉ እምነቶችን ይሸረሽራል፤ ማዕከላዊ መንግሥቱም በፍጥነት እንዲወድቅ በር ሊከፍት ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ዘገባው አመልክቷል። ባንጻሩ የብሄራዊ ደኅንነት ምክር ቤቱ አባላት፣ የቡድኑን ግስጋሴ ለመግታት አሜሪካ ዘመቻዎቿን ይበልጥ ማጠናከር አለባት የሚል አቋም ይዘዋል ተብሏል። አንዳንድ ባለሥልጣናት፣ ሱማሊያ ለአሜሪካ ብሄራዊ ጥቅም እምብዛም ፋይዳ የላትም የሚል አቋም እንዳላቸው ተገልጧል። [ዋዜማ]
1፤ ኢሰመኮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉና ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው የተመለሱ ተፈናቃዮች ለተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መጋለጣቸውን አዲስ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። ኮሚሽኑ፣ በደቡባዊ ዞን ወደ ራያ አላማጣ ወረዳና አላማጣ ከተማ የተመለሱ ተፈናቃዮች በደኅንነት ሥጋት ቤታቸው ገብተው ለመኖር አለመቻላቸውን ገልጿል። በሰሜን ምዕራብ ዞን ወደ ጸለምት፣ ላዕላይ ጸለምትና ማይጸብሪ ከተማ የተመለሱ ተፈናቃዮችም፣ ለዳግም መፈናቀል መዳረጋቸውን ኮሚሽኑ ጠቅሷል። ኮሚሽኑ በክትትሉ በሸፈናቸው አካባቢዎች፣ ከኅብረተሰቡ ጋር የተፈጠረ ቂምና ቁሩሾ በእርቅና ውይይት የሚፈታበት ሁኔታ አለመመቻቸቱ ችግሩን እንዳባባሰው አመልክቷል። ተመላሾች በጸጥታ ችግር ምክንያት በነጻነት ተንቀሳቅሰው ለመሥራት አለመቻላቸውም ተገልጧል። ኢሰመኮ፣ በተጠቀሱት አካባቢዎች በውይይትና እርቅ ሠላምን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ፣ ተመላሾች የሕግና ፍትሕ ዋስትና እንዲያገኙ የሲቪል አሥተዳደሮች እንዲዘረጉና የፍትሕ ተቋማት አገልግሎት እንዲጀምሩ ምክረ ሃሰቡን ሠጥቷል።
2፤ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ሮቢና አቡና ግንደበረት ወረዳዎች ትላንት ንጋት ላይ በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎችና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል በተደረገ ውጊያ ቁጥራቸው ያልታወቁ ንጹሃን ሕይወት ማለፉን ዋዜማ ሰምታለች። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ታጣቂዎች በተመሳሳይ ሰዓት ወደ ወረዳዎቹ መግባታቸውን ተከትሎ ለሰዓታት የዘለቀ የተኩስ ልውውጥ እንደተደረገ ምንጮች ተናግረዋል። የቡድኑ አባላት "ፉርቶ" በተባለች መንደር ወደሚገኝ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ ዘልቀው በመግባት፤ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን፣ ወታደራዊ ትጥቆችንና ቁሳቁሶችን መዝረፋቸውን ምንጮቹ ተናግረዋል። በሜታ ወልቂጤ ወረዳ "ኤላ" በተባለች ቀበሌም፣ በግጭቱ ሁለት የክልሉ ሚሊሺያ አባላት ሕይወት ማለፉ ተነግሯል።
3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ የቀድሞውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳን የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አድርገው ሹመዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ የፓርቲ ነጻነቱን እንደጠበቀ ከአዲሱ የጀኔራል ታደሠ ወረደ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ለመስራት ዝግጁ መኾኑን አረጋግጧል። ቡድኑ፣ የትግራይን ሕገመንግሥታዊነት ወደነበረበት መመለስ፣ የትግራይን የግዛት አንድነት ማስከበር፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው መመለስና በምርጫ የተመረጠ መንግሥት ማቋቋም የአዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ትኩረቶች መኾን እንዳለባቸው አሳስቧል። ጀኔራል ታደሠም፣ በቅርብ ጊዜያት በክልሉ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ በማካሄድ ችግሮችን ለመፍታት እቅድ እንደያዙና በጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራር ላይ የተወሰነ ማስተካከያ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።
4፤ አብን፣ የፌዴራል መንግሥትና የክልል መንግሥታት ከታጠቁ ኃይሎች ጋር በመነጋገር ታጣቂ ኃይሎች የአገራዊ ምክከሩ አካል እንዲኾኑ አስፈላጊውን ጥረት እንዲያደርጉ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል። ፓርቲው፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የታጠቁ ቡድኖች፣ ሲቪክ አደረጃጀቶች፣ የሙያ ማኅበራትና የኃይማኖት ተቋማት ምክክር ኮሚሽኑ ባመቻቻቸው መድረኮች እንዲሳተፉ ጠይቋል። ከዚህ በፊት በተካሄዱ የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኮች በንቃት መሳተፉንና በተለይ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የአማራን ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች ማስመዝገቡንም ፓርቲው ጠቅሷል፡፡ አብን፣ የአማራ ሕዝብ አጀንዳዎች በአማራ ክልል ብቻ የተወሰኑ አለመሆናቸውንም አውስቷል።
5፤ የሱዳን ወታደራዊ መሪ ጀኔራል አል ቡርሃን፣ ዛሬ ወደ አሥመራ አቅንተው የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተነጋግረዋል። ውይይቱ በሁለትዮሽ ግንኙነቶች፣ በሱዳኑ ጦርነትና በቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያጠነጠነ እንደነበር የሱዳን መንግሥት ገልጧል። የጀኔራል ቡርሃን ጉብኝት ዓላማ፣ በሱዳን በቅርብ ጊዜያት ውስጥ በታዩ ለውጦች ላይ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ ገለጻ ለማድረግ እንደሆነ ጠቅሷል። ፕሬዝዳንት ኢሳያስም፣ በሱዳኑ ጦርነት የውጭ ጣልቃ ገብነትን ማስወገድ ያስፈልጋል በማለት አጽንዖት ሠጥተው መናገራቸውን የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ገልጸዋል።
6፤ አሜሪካ፣ የሱማሊያው አልሸባብ ግስጋሴ ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባት መስማቱን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል። የቡድኑን መጠናከር ተከትሎ፣ አንዳንድ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባለሥልጣናት የአሜሪካ ወታደሮች ከሱማሊያ እንዲወጡና ለደኅንነት ጥንቃቄ የሞቃዲሾው የአሜሪካ ኢምባሲ እንዲዘጋ ሃሳብ እንዳቀረቡ ዘገባው ጠቅሷል። ባንጻሩ የአሜሪካ ብሄራዊ ደኅንነት ምክር ቤት አባላት፣ ኢምባሲውን መዝጋት በሱማሊያ ማዕከላዊ መንግሥት ላይ ያሉ እምነቶችን ይሸረሽራል፤ ማዕከላዊ መንግሥቱም በፍጥነት እንዲወድቅ በር ሊከፍት ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ዘገባው አመልክቷል። ባንጻሩ የብሄራዊ ደኅንነት ምክር ቤቱ አባላት፣ የቡድኑን ግስጋሴ ለመግታት አሜሪካ ዘመቻዎቿን ይበልጥ ማጠናከር አለባት የሚል አቋም ይዘዋል ተብሏል። አንዳንድ ባለሥልጣናት፣ ሱማሊያ ለአሜሪካ ብሄራዊ ጥቅም እምብዛም ፋይዳ የላትም የሚል አቋም እንዳላቸው ተገልጧል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 4/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዕለታዊ ዜናዎች
1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታ አፈጻጸም 98 ነጥብ 6 ከመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። ዐቢይ፣ የግድቡ ስድስት ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ወደ ሥራ መግባታቸውንም ገልጸዋል። ዐቢይ ይህን የተናገሩት፣ ዛሬ በተጀመረው የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ ነው። የዘንድሮው የኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እድገት 8 ነጥብ 4 በመቶ እንደሚገመትም ዐቢይ ጠቁመዋል። የአገሪቱ የውጭ ዕዳ ከአገራዊ የምርት መጠን አንጻር ያለው ምጣኔ 13 ነጥብ 7 ከመቶ ደርሷል ተብሏል።
2፤ ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ መንግስት የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት የመጣስ አካሄዱን ማቆም እንዳለበት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳስቧል። የቡድኑ ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ ሕወሓትን ከመንግሥት ጋር የሚያገናኘው ብቸኛው ገመድ የፕሪቶሪያው ስምምነት መሆኑን ጠቅሷል። ቡድኑ፣ በጀኔራል ታደሠ ወረደ የሚመራው አዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ተልዕኮውን እንዲወጣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርጉም ጥሪ አድርጓል። ቡድኑ በዚሁ መግለጫው፣ በታጠቁ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር የሚገኙ አካባቢዎችን ነጻ ለማውጣት፣ የትግራይን የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ፣ ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስና የመልሶ ግንባታ ሥራዎችን ለመስራት የተሻለ ዕድል ተፈጥሯል ብሏል። ኾኖም ሙሉ መተማመንና ሰላም ሊረጋገጥና ወደ ልማትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሸጋገር የሚቻለው፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት በትክክል ተግባራዊ ሲደረግ ብቻ እንደኾነ ቡድኑ አስምሮበታል።
3፤ የአማራ ክልል የአገራዊ ምክክር የባለድርሻ አካላት ተወካዮች 13 አጀንዳዎችን አጠናቅረው ዛሬ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። ባለድርሻዎች ለኮሚሽኑ ካስገቧቸው አጀንዳዎች መካከል፣ የሕገመንግሥት ማሻሻያ፣ የሐሰትና የጥላቻ ትርክቶች፣ ከክልሉ ውጭ የሚኖሩ የአማራ ብሄር ተወላጆች መብት፣ የማንነትና የወሰን ጥያቄዎች እንዲሁም አዲስ አበባን በክልልነት የማደራጀት አስፈላጊነት እንደሚገኙበት ተገልጧል። ላንድ ሳምንት በቆዩ የአጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረኮች፣ ስድስት ሺሕ የማኅበረሰብና የባለድርሻ አካላት ወኪሎች ተሳትፈዋል።
4፤ የአማራ ክልል የጤና ባለሙያዎች የጤና አገልግሎቶችን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ግጭት እንቅፋት እንደፈጠረባቸውየ መናገራቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። መንገድ ላይ በመድኃኒቶች ላይ የሚፈጸም ዝርፊያ፣ የበጀት እጥረትና በቂ የትራንስፖርት አገልግሎት አለመኖር ከመሰናክሎቹ መካከል ተጠቃሽ እንደኾኑም የጤና ባለሙያዎቹ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የክልሉ ጤና ባለሙያዎች ለአገልግሎታቸው ተመሳሳይ ክፍያ እንደማያገኙና የትርፍ ጊዜ ክፍያ እንደሚዘገይባቸውም ቅሬታቸውን ገልጸዋል ተብሏል። በሰዓት ዕላፊ ወቅት በተሽከርካሪዎች ላይ የተጣሉ የእንቅስቃሴ ገደቦች፣ አጣዳፊ የሕክምና እርዳታዎችን ለመስጠት ፈተና እንደፈጠረም ባለሙያዎቹ ካነሷቸው ችግሮች መካከል እንደሚገኝበት የዜና ምንጩ አመልክቷል።
5፤ የሱማሊያው ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ፣ ከሶማሌላንድ መገንጠል የሚፈልጉ የጎሳ አማጺ ኃይሎች በተቆጣጠሯት ላስ አኖድ ከተማ ጉብኝት ማድረጋቸውን ሶማሌላንድ ክፉኛ አውግዛለች። ከሱማሌያ ጋር መዋሃድ የሚፈልጉ የጎሳ ሚሊሻዎች፣ የፑንትላንድ ግዛት አጎራባች የሆነውን ሱል አውራጃ ዋና ከተማ ላስ አኖድን የተቆጣጠሩት ከአንድ ዓመት በፊት ነበር። በአማጺዎቹ ቁጥጥር ሥር የገባው አካባቢ፣ ከፍተኛ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት እንዳለው ይገመታል። የሱማሊያ ማዕከላዊ መንግሥት ከፈረሰ ከ1983 ዓ፣ም ወዲህ፣ አንድ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን በሶማሌላንድ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ የመጀመሪያቸው ነው።
6፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ፣ በዓለማቀፍ ደረጃ የሠው ኃይሉን በ20 በመቶ ሊቀንስ መኾኑን አስታውቋል። ቢሮው፣ በዘጠኝ አገራት ሥራዎችን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ መወሰኑንም ገልጧል። ቢሮው የሠራተኞቹን ብዛት ለመቀነስና በተለያዩ አገራት ሥራዎቹን ለማጠፍ የወሰነው፣ በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ የ60 ሚሊዮን ዶላር የበጀት እጥረት ስለገጠመው እንደኾነ ጠቅሷል። ቢሮው ሥራዎቹን ሙሉ በሙሉ ለማጠፍ ወይም በከፍተኛ ደረጃ ለማሸጋሸግ የወሰነባቸው አገራት፣ ኤርትራ፣ ዚምባብዌ፣ ካሚሮን፣ ሊቢያ፣ ናይጀሪያ፣ ኮሎምቢያ፣ ኢራቅ፣ ፓኪስታን እና ቱርክ ናቸው። ቢሮው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ60 አገራት 2 ሺሕ 600 ሠራተኞች ያሉት ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 500ዎቹ ይቀነሳሉ ተብሏል። [ዋዜማ]
1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታ አፈጻጸም 98 ነጥብ 6 ከመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። ዐቢይ፣ የግድቡ ስድስት ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ወደ ሥራ መግባታቸውንም ገልጸዋል። ዐቢይ ይህን የተናገሩት፣ ዛሬ በተጀመረው የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ ነው። የዘንድሮው የኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እድገት 8 ነጥብ 4 በመቶ እንደሚገመትም ዐቢይ ጠቁመዋል። የአገሪቱ የውጭ ዕዳ ከአገራዊ የምርት መጠን አንጻር ያለው ምጣኔ 13 ነጥብ 7 ከመቶ ደርሷል ተብሏል።
2፤ ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ መንግስት የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት የመጣስ አካሄዱን ማቆም እንዳለበት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳስቧል። የቡድኑ ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ ሕወሓትን ከመንግሥት ጋር የሚያገናኘው ብቸኛው ገመድ የፕሪቶሪያው ስምምነት መሆኑን ጠቅሷል። ቡድኑ፣ በጀኔራል ታደሠ ወረደ የሚመራው አዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ተልዕኮውን እንዲወጣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርጉም ጥሪ አድርጓል። ቡድኑ በዚሁ መግለጫው፣ በታጠቁ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር የሚገኙ አካባቢዎችን ነጻ ለማውጣት፣ የትግራይን የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ፣ ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስና የመልሶ ግንባታ ሥራዎችን ለመስራት የተሻለ ዕድል ተፈጥሯል ብሏል። ኾኖም ሙሉ መተማመንና ሰላም ሊረጋገጥና ወደ ልማትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሸጋገር የሚቻለው፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት በትክክል ተግባራዊ ሲደረግ ብቻ እንደኾነ ቡድኑ አስምሮበታል።
3፤ የአማራ ክልል የአገራዊ ምክክር የባለድርሻ አካላት ተወካዮች 13 አጀንዳዎችን አጠናቅረው ዛሬ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል። ባለድርሻዎች ለኮሚሽኑ ካስገቧቸው አጀንዳዎች መካከል፣ የሕገመንግሥት ማሻሻያ፣ የሐሰትና የጥላቻ ትርክቶች፣ ከክልሉ ውጭ የሚኖሩ የአማራ ብሄር ተወላጆች መብት፣ የማንነትና የወሰን ጥያቄዎች እንዲሁም አዲስ አበባን በክልልነት የማደራጀት አስፈላጊነት እንደሚገኙበት ተገልጧል። ላንድ ሳምንት በቆዩ የአጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረኮች፣ ስድስት ሺሕ የማኅበረሰብና የባለድርሻ አካላት ወኪሎች ተሳትፈዋል።
4፤ የአማራ ክልል የጤና ባለሙያዎች የጤና አገልግሎቶችን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ግጭት እንቅፋት እንደፈጠረባቸውየ መናገራቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። መንገድ ላይ በመድኃኒቶች ላይ የሚፈጸም ዝርፊያ፣ የበጀት እጥረትና በቂ የትራንስፖርት አገልግሎት አለመኖር ከመሰናክሎቹ መካከል ተጠቃሽ እንደኾኑም የጤና ባለሙያዎቹ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የክልሉ ጤና ባለሙያዎች ለአገልግሎታቸው ተመሳሳይ ክፍያ እንደማያገኙና የትርፍ ጊዜ ክፍያ እንደሚዘገይባቸውም ቅሬታቸውን ገልጸዋል ተብሏል። በሰዓት ዕላፊ ወቅት በተሽከርካሪዎች ላይ የተጣሉ የእንቅስቃሴ ገደቦች፣ አጣዳፊ የሕክምና እርዳታዎችን ለመስጠት ፈተና እንደፈጠረም ባለሙያዎቹ ካነሷቸው ችግሮች መካከል እንደሚገኝበት የዜና ምንጩ አመልክቷል።
5፤ የሱማሊያው ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ፣ ከሶማሌላንድ መገንጠል የሚፈልጉ የጎሳ አማጺ ኃይሎች በተቆጣጠሯት ላስ አኖድ ከተማ ጉብኝት ማድረጋቸውን ሶማሌላንድ ክፉኛ አውግዛለች። ከሱማሌያ ጋር መዋሃድ የሚፈልጉ የጎሳ ሚሊሻዎች፣ የፑንትላንድ ግዛት አጎራባች የሆነውን ሱል አውራጃ ዋና ከተማ ላስ አኖድን የተቆጣጠሩት ከአንድ ዓመት በፊት ነበር። በአማጺዎቹ ቁጥጥር ሥር የገባው አካባቢ፣ ከፍተኛ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት እንዳለው ይገመታል። የሱማሊያ ማዕከላዊ መንግሥት ከፈረሰ ከ1983 ዓ፣ም ወዲህ፣ አንድ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን በሶማሌላንድ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ የመጀመሪያቸው ነው።
6፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ፣ በዓለማቀፍ ደረጃ የሠው ኃይሉን በ20 በመቶ ሊቀንስ መኾኑን አስታውቋል። ቢሮው፣ በዘጠኝ አገራት ሥራዎችን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ መወሰኑንም ገልጧል። ቢሮው የሠራተኞቹን ብዛት ለመቀነስና በተለያዩ አገራት ሥራዎቹን ለማጠፍ የወሰነው፣ በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ የ60 ሚሊዮን ዶላር የበጀት እጥረት ስለገጠመው እንደኾነ ጠቅሷል። ቢሮው ሥራዎቹን ሙሉ በሙሉ ለማጠፍ ወይም በከፍተኛ ደረጃ ለማሸጋሸግ የወሰነባቸው አገራት፣ ኤርትራ፣ ዚምባብዌ፣ ካሚሮን፣ ሊቢያ፣ ናይጀሪያ፣ ኮሎምቢያ፣ ኢራቅ፣ ፓኪስታን እና ቱርክ ናቸው። ቢሮው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ60 አገራት 2 ሺሕ 600 ሠራተኞች ያሉት ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 500ዎቹ ይቀነሳሉ ተብሏል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ሰኞ፣ ሚያዝያ 6/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚያካሂደው የከተሞች የመንገድ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በሰብዓዊ መብት ላይ የሚያስከትለው ተጽዕኖ እስኪጠና፣ ነዋሪዎችን ማፈናቀሉን እንዲያቆም ጠይቋል። አምነስቲ፣ መንግሥት "ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ" በከተማ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶቹ ነዋሪዎችን እያፈናቀለ ይገኛል ሲል ከሷል። አምነስቲ፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት በኮሪደር ልማቱ ተጎጅ የኾኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በበቂ ሁኔታ እንዳላማከሩ፣ በቂ ማስጠንቀቂያ እንዳልሠጡና ካሳ እንዳልከፈሉ ጠቅሷል። ዓለማቀፍ አጋሮች ዜጎችን በግዳጅ ከመኖሪያ አካባቢያቸው ማፈናቀላቸውን እንዲያቆሙ በፍጥነት ማግባባት እንዳለባቸው አምነስቲ አሳስቧል።
2፤ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ልዩ ስም "ፍልቅልቅ" በተባለ ሥፍራ ለጂፕሰም የፋብሪካ ምርት ጥሬ ዕቃ በማውጣት ላይ የነበሩ የማሽን ሠራተኞች ጨምሮ አስር ያህል ሰዎች ትናንት በታጣቂዎች እንደታገቱ ዋዜማ ሰምታለች። አጋቾቹ ከአማራ ክልል ተሻግረው የገቡ መሆናቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። ታፍነው ከተወሰዱት ሰዎች በተጨማሪ፣ ከታጣቂዎቹ ጥቃት ለማምለጥ ሲሞክሩ የነበሩ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በተከፈተባቸው ተኩስ አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል። አጋቾቹ ሰዎቹን ወደየት እንደወሰዷቸው ምንም ፍንጭ እንዳልተገኘም ተናግረዋል።
3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በቬትናም የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ሐኖይ ገብተዋል። ዐቢይ ወደ ሐኖይ ያቀኑት፣ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር ፋም ሚን ቺን ባደረጉላቸው ግብዣ ነው። ዐቢይ በቬትናም ቆይታቸው፣ በአራተኛው ዓለማቀፍ የአረንጓዴ ልማት ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ። በኢትዮጵያ እና ቬትናም መካከል ያለው የንግድ ግንኙነት ባለፉት አራት ዓመታት ከ10 እስከ 15 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል።
4፤ የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ ከፍተኛ ቡድን በፍጥነት በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንዲወያይ መጠየቃቸውን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ደብረጺዮን ይህን የጠየቁት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ፣ አረጋጋጭና ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊ ኾነው አዲስ ከተሾሙት ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አላዴ አሶዴ ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ በተወያዩበት ወቅት ነው። ሕወሓት እና መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን የፖለቲካ ውይይት እንዳልጀመሩና የፓርቲው ሕጋዊ እውቅና እንዳልተመለሰለት ደብረጺዮን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አፍሪካ ኅብረት ጀኔራል ሳማድን የሾመው፣ የሥራ ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ጀኔራል እስጢፋኖስ ራዲናን ምትክ ነው። ሕወሓት ከኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሠራ ያረጋገጡት ደብረጺዮን፣ ኮሚቴው መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በግልጽ በመለየት ሪፖርት እንዲያቀርብ ጠይቀዋል ተብሏል።
5፤ ብሔራዊ ባንክ፣ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ቅርንጫፎችን መክፈት የሚፈልጉ ባንኮች ፍቃድ ለማግኘት እንዲያሟሉ የሚጠበቅባቸውን ልዩ ዝቅተኛ መሥፈርቶች የያዘ መመሪያ ሊያወጣ እንደሆነ ሪፖርተር ዘግቧል። በረቂቅ መመሪያው ከሚካተቱት መሥፈርቶች መካከል፣ ማናቸውም ባንክ የፍቃድ ጥያቄውን ካቀረበበት ቀን አስቀድሞ በነበረው ዓመት ውስጥ ያለው አጠቃላይ ሃብት በዚያው ዓመት ከተመዘገበው አጠቃላይ የባንክ ዘርፍ ሀብት በትንሹ ሁለት በመቶ ድርሻ ሊኖረው ይገባል የሚለው እንደሚገኝበት ዘገባው ጠቅሷል። በትንሹ 65 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ሀብት መያዝ፣ ሥጋታቸው ለሚያመዝን ብድሮች የተያዘ መጠባበቂያ ካፒታል ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው 8 በመቶ ዝቅተኛ መሥፈርት የ2 በመቶ ብልጫ ያለው እንዲሆን፣ የባንኩ የገንዘብና የገንዘብ አከል ይዞታ ምጣኔ ማመልከቻውን ካስገባበት ጊዜ በፊት ለነበሩ ሦስት ወራት በብሔራዊ ባንክ ከተቀመጠው ዝቅተኛ መሥፈርት በ3 በመቶ ብልጫ ያለው መኾን እንደሚገባውም በመስፈርትነት እንደተካተቱ ዘገባው አመልክቷል።
6፤ ሱዳን፣ ኬንያ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይልና አጋሮቹ ናይሮቢ ውስጥ በድጋሚ ስብሰባ እንዲያደርጉ ፈቅዳለች በማለት ሪፖርቶች መውጣታቸውን ጠቅሳ ኬንያን አውግዛለች። የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸውን ካምፖች ጨምሮ ዳርፉር ውስጥ በሚገኙ ጎሳዎች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመ በሚገኝበትና ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የመጀመሪያውን የቡድኑን ኮንፈረንስ ባወገዘበት ሁኔታ፣ ኬንያ የቡድኑን ሁለተኛ ዙር ኮንፈረንስ ለማስተናገድ ማሰቧ ዓለማቀፍ ሕግን አለማክበሯን የሚያሳይና በቀጠናዊ ጸጥታና በአገራት ሉዓላዊነት ላይ ስጋት የሚደቅን ነው በማለት ተችቷል። ሱዳን፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የተመድን ቻርተር ይጥሳል ያለችውን የኬንያን ድርጊት እንዲያወግዝም ጠይቃለች። የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በበኩሉ፣ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል የሱዳን መንግሥትን እንዲጥል ኬንያ ድጋፍ እያደረገች ነው የሚባለውን ክስ አስተባብለዋል። [ዋዜማ]
1፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚያካሂደው የከተሞች የመንገድ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በሰብዓዊ መብት ላይ የሚያስከትለው ተጽዕኖ እስኪጠና፣ ነዋሪዎችን ማፈናቀሉን እንዲያቆም ጠይቋል። አምነስቲ፣ መንግሥት "ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ" በከተማ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶቹ ነዋሪዎችን እያፈናቀለ ይገኛል ሲል ከሷል። አምነስቲ፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት በኮሪደር ልማቱ ተጎጅ የኾኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በበቂ ሁኔታ እንዳላማከሩ፣ በቂ ማስጠንቀቂያ እንዳልሠጡና ካሳ እንዳልከፈሉ ጠቅሷል። ዓለማቀፍ አጋሮች ዜጎችን በግዳጅ ከመኖሪያ አካባቢያቸው ማፈናቀላቸውን እንዲያቆሙ በፍጥነት ማግባባት እንዳለባቸው አምነስቲ አሳስቧል።
2፤ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ልዩ ስም "ፍልቅልቅ" በተባለ ሥፍራ ለጂፕሰም የፋብሪካ ምርት ጥሬ ዕቃ በማውጣት ላይ የነበሩ የማሽን ሠራተኞች ጨምሮ አስር ያህል ሰዎች ትናንት በታጣቂዎች እንደታገቱ ዋዜማ ሰምታለች። አጋቾቹ ከአማራ ክልል ተሻግረው የገቡ መሆናቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። ታፍነው ከተወሰዱት ሰዎች በተጨማሪ፣ ከታጣቂዎቹ ጥቃት ለማምለጥ ሲሞክሩ የነበሩ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በተከፈተባቸው ተኩስ አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል። አጋቾቹ ሰዎቹን ወደየት እንደወሰዷቸው ምንም ፍንጭ እንዳልተገኘም ተናግረዋል።
3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በቬትናም የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ሐኖይ ገብተዋል። ዐቢይ ወደ ሐኖይ ያቀኑት፣ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር ፋም ሚን ቺን ባደረጉላቸው ግብዣ ነው። ዐቢይ በቬትናም ቆይታቸው፣ በአራተኛው ዓለማቀፍ የአረንጓዴ ልማት ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ። በኢትዮጵያ እና ቬትናም መካከል ያለው የንግድ ግንኙነት ባለፉት አራት ዓመታት ከ10 እስከ 15 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል።
4፤ የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ ከፍተኛ ቡድን በፍጥነት በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንዲወያይ መጠየቃቸውን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ደብረጺዮን ይህን የጠየቁት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ፣ አረጋጋጭና ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊ ኾነው አዲስ ከተሾሙት ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አላዴ አሶዴ ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ በተወያዩበት ወቅት ነው። ሕወሓት እና መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን የፖለቲካ ውይይት እንዳልጀመሩና የፓርቲው ሕጋዊ እውቅና እንዳልተመለሰለት ደብረጺዮን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አፍሪካ ኅብረት ጀኔራል ሳማድን የሾመው፣ የሥራ ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ጀኔራል እስጢፋኖስ ራዲናን ምትክ ነው። ሕወሓት ከኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሠራ ያረጋገጡት ደብረጺዮን፣ ኮሚቴው መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በግልጽ በመለየት ሪፖርት እንዲያቀርብ ጠይቀዋል ተብሏል።
5፤ ብሔራዊ ባንክ፣ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ቅርንጫፎችን መክፈት የሚፈልጉ ባንኮች ፍቃድ ለማግኘት እንዲያሟሉ የሚጠበቅባቸውን ልዩ ዝቅተኛ መሥፈርቶች የያዘ መመሪያ ሊያወጣ እንደሆነ ሪፖርተር ዘግቧል። በረቂቅ መመሪያው ከሚካተቱት መሥፈርቶች መካከል፣ ማናቸውም ባንክ የፍቃድ ጥያቄውን ካቀረበበት ቀን አስቀድሞ በነበረው ዓመት ውስጥ ያለው አጠቃላይ ሃብት በዚያው ዓመት ከተመዘገበው አጠቃላይ የባንክ ዘርፍ ሀብት በትንሹ ሁለት በመቶ ድርሻ ሊኖረው ይገባል የሚለው እንደሚገኝበት ዘገባው ጠቅሷል። በትንሹ 65 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ሀብት መያዝ፣ ሥጋታቸው ለሚያመዝን ብድሮች የተያዘ መጠባበቂያ ካፒታል ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው 8 በመቶ ዝቅተኛ መሥፈርት የ2 በመቶ ብልጫ ያለው እንዲሆን፣ የባንኩ የገንዘብና የገንዘብ አከል ይዞታ ምጣኔ ማመልከቻውን ካስገባበት ጊዜ በፊት ለነበሩ ሦስት ወራት በብሔራዊ ባንክ ከተቀመጠው ዝቅተኛ መሥፈርት በ3 በመቶ ብልጫ ያለው መኾን እንደሚገባውም በመስፈርትነት እንደተካተቱ ዘገባው አመልክቷል።
6፤ ሱዳን፣ ኬንያ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይልና አጋሮቹ ናይሮቢ ውስጥ በድጋሚ ስብሰባ እንዲያደርጉ ፈቅዳለች በማለት ሪፖርቶች መውጣታቸውን ጠቅሳ ኬንያን አውግዛለች። የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸውን ካምፖች ጨምሮ ዳርፉር ውስጥ በሚገኙ ጎሳዎች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመ በሚገኝበትና ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የመጀመሪያውን የቡድኑን ኮንፈረንስ ባወገዘበት ሁኔታ፣ ኬንያ የቡድኑን ሁለተኛ ዙር ኮንፈረንስ ለማስተናገድ ማሰቧ ዓለማቀፍ ሕግን አለማክበሯን የሚያሳይና በቀጠናዊ ጸጥታና በአገራት ሉዓላዊነት ላይ ስጋት የሚደቅን ነው በማለት ተችቷል። ሱዳን፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የተመድን ቻርተር ይጥሳል ያለችውን የኬንያን ድርጊት እንዲያወግዝም ጠይቃለች። የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በበኩሉ፣ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል የሱዳን መንግሥትን እንዲጥል ኬንያ ድጋፍ እያደረገች ነው የሚባለውን ክስ አስተባብለዋል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 7/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ ድጎ ጽዮን ከተማ እሁድ'ለት የፋኖ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በርካታ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ዋዜማ ሰምታለች። በርካታ ታጣቂዎች በዕለቱ ጧት ላይ በአምስት አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ እንደገቡ የገለጹት ምንጮች፣ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በሚገኙባቸው ካምፖችና ምሽጎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። ከፋኖ ታጥቂዎች ሁለት መሞታቸውን እንደተሩዱና ታጣቂዎቹ የገደሏቸውን የአካባቢው ተወላጅ ሚሊሺያዎች በቤተ ክርስቲያናት እንዳይቀበሩ ጫና ሲያደርጉ እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃቱን ተከትሎ የመከላከያ ሠራዊት ለጥቃቱ አጸፋ በሚመስል መልኩ፣ መንገድ ላይ ንጹሃን ነዋሪዎች መግደላቸውን ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመለክታል። ከጥቃቱ በኋላ፣ ወደ አጎራባች ከተሞችና ወደ ባሕርዳር የሚደረግ ትራንስፖርትና የትምህርትና የንግድ እንቅስቃሴዎች መቋረጣቸውንም ምንጮች ነግረውናል።
2፤ ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን፣ በእስካሁኑ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ ተሃድሶ ሥልጠና የመስጠትና መልሶ የማዋሃድ ብሄራዊ መርሃ ግብር፣ በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያና በአፋር ክልሎች 20 ሺሕ 253 የቀድሞ ተዋጊዎችን በማረጋገጥ፣ በመመዝገብና የተሃድሶ ሥልጠና በመስጠት ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረጉን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ይህን የተናገረው፣ በ2017 ዓ፣ም የእቅድ አተገባበር ውጤቶች፣ ባጋጠሙ ችግሮችና ወደፊት ሊተገበሩ በሚገባቸው የመፍትሄ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከባለድርሻ ሚንስቴር መስሪያ ቤቶችና ከክልሎች ተወካዮች ጋር ትናንት በቢሾፍቱ ከተማ በመከረበት መድረክ ላይ ነው፡፡ በትግራይ የተቋረጠው የትጥቅ ማስፈታት፣ የተሃድሶ ሥልጠናና መልሶ የማዋሃድ መርሃ ግብር እንደገና መቼ እንደሚጀመር ግን ኮሚሽኑ አሁንም አልገለጠም። ኮሚሽኑ በየካቲት መገባደጃ ከባለድርሻ አካላት ጋር ባካሄደው ተመሳሳይ ውይይት፣ በትግራይ ባንዳንድ "ቴክኒካዊ" እና "ፖለቲካዊ" ምክንያቶች የተቋረጠው የቀድሞ ተዋጊዎችን የመበተን፣ የተሃድሶ ሥልጠና የመስጠትና ከኅብረተሰቡ ጋር መልሶ የመቀላቀል ሂደት በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት እንደገና ይጀምራል በማለት ተናግሮ ነበር።
3፤ ኢትዮጵያና ቬይትናም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባና በሃኖይ መካከል የቀጥታ በረራ እንዲጀምር የሚያመቻች የሲቪል አቪዬሽን ስምምነት ተፈራርመዋል። በቬትናም ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኘው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የመሩት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን፣ ሁለቱ አገሮች በንግድ እና በትምህርት ዘርፍ ትብብር ማድረግ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነቶችንም ከቬትናም አቻዎቹ ጋር መፈራረማቸው ተገልጧል። የዐቢይ የቬትናም ጉብኝት፣ ሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከጀመሩ ከ50 ዓመታት በኋላ በመሪ ደረጃ የተደረገ የመጀመሪያው ጉብኝት መኾኑን የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ባሠራጨው መረጃ ላይ ገልጧል።
4፤ ኢትዮጵያ፣ ለውጭ ገበያ ካቀረበችው ቡና በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በታሪክ ክብረወሰን የሰበረ ገቢ አግኝታለች። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በዘጠኝ ወራት ለውጭ ገበያ ከተላከው ቡና 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ለዋዜማ በላከው መግለጫ ገልጧል። አገሪቱ በ2016 በጀት ዓመት ባንድ ዓመት ክብረ ወሰን አድርጋ ያስመዘገበችው ገቢ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ነበር። ዘንድሮ ግን በዘጠኝ ወራት 200 መቶ 99 ሺሕ 607 ቶን ቡና ተልኮ 1 ነጥብ 508 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በመገኘቱ፣ ከበጀት ዓመቱ ዕቅድ 138 በመቶው ተሳካቷል ተብሏል። ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር፣ ዘንድሮ 672 ነጥብ 44 ሚሊዮን ዶላር ወይም 81 በመቶ ጭማሪ ተመዝግቧል። ሳዑዲ ዓረቢያ በመጠን 53 ሺሕ 844 ነጥብ 03 ቶን ቡና ወይም 18 በመቶና በገቢ ረገድ 250 ነጥብ 02 ሚሊዮን ዶላር በማስገኘት ቀዳሚዋ የቡና መዳረሻ ስትሆን፣ ጀርመንና አሜሪካ ይከተላሉ።
5፤ የትግራይ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የክልሉ መምህራን በጦርነቱ ወቅት ያልተከፈላቸው የ17 ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈላቸው ዛሬ ወስኗል። የክልሉ መምህራን ማኅበር፣ የመምህራን ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈል ክስ የመሠረተው ኅዳር ላይ ነበር። የ2014 ዓ፣ም የ12 ወራት ደመወዝን ፌደራል መንግሥቱ፣ የ2015 ዓ፣ም የ5 ወራት ደሞዝን ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንዲከፈሉ ነበር ማኅበር ክስ የመሠረተው። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ በመንግሥትና የግል ድርጅቶች ሠራተኞች ውዝፍ ደመወዝ ዙሪያ የተመሠረቱ ክሶች ታግደው እንዲቆዩ የጣለውን እግድ ታኅሳስ ላይ በድጋሚ ለ6 ወራት አራዝሞ ነበር።
6፤ በሩዋንዳ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ትናንት ከሩዋንዳው አቻቸው ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ ጋር ውይይት አድርገዋል። ለአራት ቀናት የሚቆየው የፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጉብኝት፣ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብሮችን ለማጠናከርና አዳዲስ የወታደራዊ የትብብር መስኮችን ለመለየት እንደሆነ ተገልጧል። የሩዋንዳ ጦር ኃይል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ በመጋቢት ወደ ኢትዮጵያ አቅንተው፣ ሁለቱ አገራት በወታደራዊ መስኮች በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጋር መፈራርማቸው ይታወሳል።
7፤ የሱማሊያ መንግሥት፣ የጎሳ ሚሊሻዎች ከሶማሌላንድ በኃይል ገንጥለናታል ላሏት ኤስ ኤስ ካቱሜ አውራጃ ስድስተኛዋ የፌደሬሽኑ አባል አድርጎ ተቀብሏል። ሱማሊያ ይህን ርምጃ የወሰደችው፣ ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደተገንጣይዋ አውራጃ ዋና ከተማ ላስ አኖድ ተጉዘው ጉብኝት ባደረጉ ማግስት ነው። የአዲሷ የፌደራል ግዛት አስተዳደር የፌደራል መንግሥቱና የፌደራል ግዛቶች መንግሥታት በሚያደርጉት ብሄራዊ ምክክር ላይ እንደሚሳተፍ፣ ኹለቱ ወገኖች በጸጥታ ዙሪያ ትብብር ማድረግ እንደሚጀምሩና የግዛቲቷን የጸጥታ ኃይል መልሶ የማዋቀር ሥራ እንደሚሠራ ሞቃዲሾ አስታውቃለች። ይህንኑ ተከትሎ፣ የግዛቱቷ የጎሳ አስተዳዳሪዎች ከሁለት ዓመታት በፊት ከሶማሌላንድ ኃይሎች ጋር ውጊያ ባደረጉበት የማረኳቸውን 25 የሶማሌላንድ ወታደሮች ከእስር ለቀዋል። [ዋዜማ]
1፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ ድጎ ጽዮን ከተማ እሁድ'ለት የፋኖ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በርካታ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ዋዜማ ሰምታለች። በርካታ ታጣቂዎች በዕለቱ ጧት ላይ በአምስት አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ እንደገቡ የገለጹት ምንጮች፣ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በሚገኙባቸው ካምፖችና ምሽጎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። ከፋኖ ታጥቂዎች ሁለት መሞታቸውን እንደተሩዱና ታጣቂዎቹ የገደሏቸውን የአካባቢው ተወላጅ ሚሊሺያዎች በቤተ ክርስቲያናት እንዳይቀበሩ ጫና ሲያደርጉ እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃቱን ተከትሎ የመከላከያ ሠራዊት ለጥቃቱ አጸፋ በሚመስል መልኩ፣ መንገድ ላይ ንጹሃን ነዋሪዎች መግደላቸውን ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመለክታል። ከጥቃቱ በኋላ፣ ወደ አጎራባች ከተሞችና ወደ ባሕርዳር የሚደረግ ትራንስፖርትና የትምህርትና የንግድ እንቅስቃሴዎች መቋረጣቸውንም ምንጮች ነግረውናል።
2፤ ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን፣ በእስካሁኑ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ ተሃድሶ ሥልጠና የመስጠትና መልሶ የማዋሃድ ብሄራዊ መርሃ ግብር፣ በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያና በአፋር ክልሎች 20 ሺሕ 253 የቀድሞ ተዋጊዎችን በማረጋገጥ፣ በመመዝገብና የተሃድሶ ሥልጠና በመስጠት ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረጉን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ይህን የተናገረው፣ በ2017 ዓ፣ም የእቅድ አተገባበር ውጤቶች፣ ባጋጠሙ ችግሮችና ወደፊት ሊተገበሩ በሚገባቸው የመፍትሄ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከባለድርሻ ሚንስቴር መስሪያ ቤቶችና ከክልሎች ተወካዮች ጋር ትናንት በቢሾፍቱ ከተማ በመከረበት መድረክ ላይ ነው፡፡ በትግራይ የተቋረጠው የትጥቅ ማስፈታት፣ የተሃድሶ ሥልጠናና መልሶ የማዋሃድ መርሃ ግብር እንደገና መቼ እንደሚጀመር ግን ኮሚሽኑ አሁንም አልገለጠም። ኮሚሽኑ በየካቲት መገባደጃ ከባለድርሻ አካላት ጋር ባካሄደው ተመሳሳይ ውይይት፣ በትግራይ ባንዳንድ "ቴክኒካዊ" እና "ፖለቲካዊ" ምክንያቶች የተቋረጠው የቀድሞ ተዋጊዎችን የመበተን፣ የተሃድሶ ሥልጠና የመስጠትና ከኅብረተሰቡ ጋር መልሶ የመቀላቀል ሂደት በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት እንደገና ይጀምራል በማለት ተናግሮ ነበር።
3፤ ኢትዮጵያና ቬይትናም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባና በሃኖይ መካከል የቀጥታ በረራ እንዲጀምር የሚያመቻች የሲቪል አቪዬሽን ስምምነት ተፈራርመዋል። በቬትናም ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኘው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የመሩት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን፣ ሁለቱ አገሮች በንግድ እና በትምህርት ዘርፍ ትብብር ማድረግ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነቶችንም ከቬትናም አቻዎቹ ጋር መፈራረማቸው ተገልጧል። የዐቢይ የቬትናም ጉብኝት፣ ሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከጀመሩ ከ50 ዓመታት በኋላ በመሪ ደረጃ የተደረገ የመጀመሪያው ጉብኝት መኾኑን የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ባሠራጨው መረጃ ላይ ገልጧል።
4፤ ኢትዮጵያ፣ ለውጭ ገበያ ካቀረበችው ቡና በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በታሪክ ክብረወሰን የሰበረ ገቢ አግኝታለች። የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በዘጠኝ ወራት ለውጭ ገበያ ከተላከው ቡና 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ለዋዜማ በላከው መግለጫ ገልጧል። አገሪቱ በ2016 በጀት ዓመት ባንድ ዓመት ክብረ ወሰን አድርጋ ያስመዘገበችው ገቢ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ነበር። ዘንድሮ ግን በዘጠኝ ወራት 200 መቶ 99 ሺሕ 607 ቶን ቡና ተልኮ 1 ነጥብ 508 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በመገኘቱ፣ ከበጀት ዓመቱ ዕቅድ 138 በመቶው ተሳካቷል ተብሏል። ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር፣ ዘንድሮ 672 ነጥብ 44 ሚሊዮን ዶላር ወይም 81 በመቶ ጭማሪ ተመዝግቧል። ሳዑዲ ዓረቢያ በመጠን 53 ሺሕ 844 ነጥብ 03 ቶን ቡና ወይም 18 በመቶና በገቢ ረገድ 250 ነጥብ 02 ሚሊዮን ዶላር በማስገኘት ቀዳሚዋ የቡና መዳረሻ ስትሆን፣ ጀርመንና አሜሪካ ይከተላሉ።
5፤ የትግራይ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የክልሉ መምህራን በጦርነቱ ወቅት ያልተከፈላቸው የ17 ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈላቸው ዛሬ ወስኗል። የክልሉ መምህራን ማኅበር፣ የመምህራን ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፈል ክስ የመሠረተው ኅዳር ላይ ነበር። የ2014 ዓ፣ም የ12 ወራት ደመወዝን ፌደራል መንግሥቱ፣ የ2015 ዓ፣ም የ5 ወራት ደሞዝን ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንዲከፈሉ ነበር ማኅበር ክስ የመሠረተው። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ በመንግሥትና የግል ድርጅቶች ሠራተኞች ውዝፍ ደመወዝ ዙሪያ የተመሠረቱ ክሶች ታግደው እንዲቆዩ የጣለውን እግድ ታኅሳስ ላይ በድጋሚ ለ6 ወራት አራዝሞ ነበር።
6፤ በሩዋንዳ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ትናንት ከሩዋንዳው አቻቸው ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ ጋር ውይይት አድርገዋል። ለአራት ቀናት የሚቆየው የፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጉብኝት፣ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብሮችን ለማጠናከርና አዳዲስ የወታደራዊ የትብብር መስኮችን ለመለየት እንደሆነ ተገልጧል። የሩዋንዳ ጦር ኃይል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ በመጋቢት ወደ ኢትዮጵያ አቅንተው፣ ሁለቱ አገራት በወታደራዊ መስኮች በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጋር መፈራርማቸው ይታወሳል።
7፤ የሱማሊያ መንግሥት፣ የጎሳ ሚሊሻዎች ከሶማሌላንድ በኃይል ገንጥለናታል ላሏት ኤስ ኤስ ካቱሜ አውራጃ ስድስተኛዋ የፌደሬሽኑ አባል አድርጎ ተቀብሏል። ሱማሊያ ይህን ርምጃ የወሰደችው፣ ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደተገንጣይዋ አውራጃ ዋና ከተማ ላስ አኖድ ተጉዘው ጉብኝት ባደረጉ ማግስት ነው። የአዲሷ የፌደራል ግዛት አስተዳደር የፌደራል መንግሥቱና የፌደራል ግዛቶች መንግሥታት በሚያደርጉት ብሄራዊ ምክክር ላይ እንደሚሳተፍ፣ ኹለቱ ወገኖች በጸጥታ ዙሪያ ትብብር ማድረግ እንደሚጀምሩና የግዛቲቷን የጸጥታ ኃይል መልሶ የማዋቀር ሥራ እንደሚሠራ ሞቃዲሾ አስታውቃለች። ይህንኑ ተከትሎ፣ የግዛቱቷ የጎሳ አስተዳዳሪዎች ከሁለት ዓመታት በፊት ከሶማሌላንድ ኃይሎች ጋር ውጊያ ባደረጉበት የማረኳቸውን 25 የሶማሌላንድ ወታደሮች ከእስር ለቀዋል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ረቡዕ፣ ሚያዝያ 8/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ኦብነግ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በገባበትን ውጥረት ዙሪያ የኢትዮጵያ አጋሮችና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ጣልቃ እንዲገቡ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ኦብነግ፣ በአባሎቼ ላይ ጥቃት እንዲፈጸምባቸው፣ የክልሉ ጸጥታ ኃይሎች አባሎቼን እንዲያስፈራሩና ቢሮዎቼን ዒላማ እንዲያደርጉ የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ትዕዛዝ አስተላልፏል ብሏል። በክልሉ ውስጥ ስብሰባዎችን ጭምር እንዳያደርግ የክልሉ መንግሥት እገዳ እንደጣለበት የጠቀሰው ኦብነግ፣ ትናንት በንጎብ ዞን፣ ገርባ ወረዳ ሁለቱ አባሎቼ ያላግባብ ታሠረዋል፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነርም ባንደኛው አባሌ ላይ የአካል ጥቃት ፈጽመዋል በማለት ከሷል። እነዚህ ድርጊቶች ግንባሩ በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሂደት ውስጥ እንዳይሳተፍ ለማደናቀፍ ያለሙ ናቸው ያለው ኦብነግ፣ በክልሉ ለሚፈጠር የሰላምና ጸጥታ መደፍረስ ፌደራል መንግሥቱና ገዥው ፓርቲ ተጠያቂ ይኾናሉ በማለት አስጠንቅቋል።
2፤ ብሄራዊ ባንክ፣ ነገ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚያወጣ አስታውቋል። ባንኩ ለነገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር አቀርባለሁ ብሏል። ባንኩ በየሁለት ሳምንቱ በቋሚነት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚያወጣ ከገለጠ ወዲህ፣ የነገው ጨረታ ሁለተኛው ጨረታው ይሆናል። ባንኩ ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው የ50 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ፣ ላንድ ዶላር 131 ብር 7095 ሳንቲም በኾነ አማካይ ዋጋ ማጫረቱንና በጨረታው 12 ባንኮች መሳተፋቸውን መግለጡ ይታወሳል።
3፤ የኢትዮጵያ ተቀማጭ ገንዘብ መድኅን ፈንድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከፋይናንስ ተቋማት 5 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን መሰብሰቡን አስታውቋል። ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር፣ የ11 ነጥብ 10 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን የመድኅን ፈንዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደሳለኝ አምባው ተናግረዋል። ከዓረቦኑ ውስጥ 2 ነጥብ 67 ቢሊዮን ብር ወይም 51 ነጥብ 3 በመቶው ከግል ባንኮች፣ 2 ነጥብ 47 ቢሊዮኑ ወይም 47 ነጥብ 5 በመቶው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ቀሪው ከማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት መሰብሰቡን ደሳለኝ ጠቅሰዋል። ፈንዱ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት፣ ከተቋማቱ የሰበሰበውን ዓረቦን በሙዓለ ንዋይ መልክ እያፈሰሰ መኾኑን የጠቀሱት ሃላፊው፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የፈንዱ የኢንቨስትመንት ክምችት 12 ነጥብ 11 ቢሊዮን ብር መድረሱን ተናግረዋል፡፡
4፤ የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግንባታው ለዘገየው ከኢትዮጵያ ጋር ለሚያገናኘው የመንገድ ፕሮጀክት ዲዛይን የሚያወጣ አማካሪ ድርጅት በቅርቡ ሊመርጥ መሆኑን አስታውቋል። ሁለቱ አገራት 220 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ የሚኖረውን መንገድ በጋራ ለመገንባት ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት የ738 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል። የመንገድ ፕሮጀክቱን ሙሉ ወጪ ለጊዜው የምትሸፍነው ኢትዮጵያ ስትሆን፣ ደቡብ ሱዳን ድርሻዋን ከ5 ዓመት በኋላ በነዳጅ መልክ ለኢትዮጵያ ትከፍላለች። የደቡብ ሱዳን ፓርላማም ባለፈው ዓመት ሰኔ ላይ ስምምነቱን አጽድቋል። የደቡብ ሱዳን የመንገድ ሚንስትር ሲሞን ሚጃክ፣ ፕሮጀክቱ መዘግየቱን ገልጸው፣ ኾኖም ግንባታው የማይቀር እንደሆነ መናገራቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
5፤ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይልና አጋሮቹ "የሰላምና አንድነት መንግሥት" የተሰኘ ትይዩ መንግሥት ማቋቋማቸውን አውጀዋል። የፈጥኖ ደረሹ ኃይል ዋና አዛዥ ጀኔሬል ሞሐመድ ደጋሎ፣ ቡድኑና አጋሮቹ ለአዲሲቷ ሱዳን መሠረት የሚጥል የሽግግር ሕገመንግሥት ማጽደቃቸውንም ይፋ አድርገዋል። የሽግግር ሰነዱ፣ አገሪቱን ለማስተዳደር የሁሉንም የአገሪቱ ግዛቶች ተወካዮች ያካተተ 15 አባላት ያሉት ፕሬዝዳንታዊ ካውንስል እንደሚቋቋም ይገልጣል። ጀኔራል ደጋሎ፣ በአገሪቱ የትኛውም ብሔር፣ ግዛት ወይም ኃይማኖት ከሱዳናዊ ማንነት ሊበልጥ እንደማይገባ፣ አዲሱ መንግሥት በሕግ ብቻ የሚመራ እንደሚሆን አስታውቀዋል። ኾኖም የትይዩ መንግሥት እወጃው አገሪቱን ሊበታትናት ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።
6፤ አሜሪካ፣ የአሥመራውን ጨምሮ በ30 አገራት ኢምባሲዎቿን ለመዝጋት ወይም ዲፕሎማቶቿን ለመቀነስ ማቀዳ ተሠምቷል። የሞቃዲሾው የአሜሪካ ኢምባሲም የዲፕሎማቲክ ውክልናውን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ወይም ጨርሶ ለመዝጋት እንደታሰበም ዓለማቀፍ የዜና ወኪሎች ከውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ያገኙትን ሚስጢራዊ ሰነድ ጠቅሰው ዘግበዋል። በኤርትራ፣ በደቡብ ሱዳን፣ ሌሴቶ፣ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ እና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙ ኢምባሲዎችን ጨምሮ በተለይ በአውሮፓና አፍሪካ አስር ኢምባሲዎችና 17 ቆንስላዎች ሙሉ በሙሉ ሊዘጉ ይችላሉ ተብሏል።
7፤ የሱማሊያ መንግሥት፣ የአሜሪካ የነዳጅ ኩባንያዎች ሱማሊያ ውስጥ በነዳጅ ፍለጋና ቁፋሮ እንዲሠማሩ ትናንት በይፋ ጋብዟል። የፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ መንግሥት ለአሜሪካ ኩባንያዎች ይህን ግብዣ ያቀረበው፣ ዋሽንግተን በሚገኙት አምባሳደሩ በኩል ነው። አምባሳደሩ፣ ሱማሊያ ሰሞኑን የፌደሬሽኑ አባል አድርጌያታለሁ ባለቻትና ከሶማሌላንድ በተነጠለችው "ኤስ ኤስ ካቱሜ" ግዛት፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች በነዳጅ ፍለጋና ቁፋሮ እንዲሠማሩ ነው ጥሪ ያቀረቡት።
8፤ ሕንድ፣ ካለፈው ዕሁድ ጀምሮ በሕንድ ውቅያኖስ ላይ ከአስር የአፍሪካ አገራት ጋር ለስድስት ቀናት የሚቆይ የጋራ የባሕር ኃይል ልምምድ በማድረግ ላይ ናት። በባሕር ኃይል ልምምዱ በመሳተፍ ላይ ካሉት አገራት መካከል፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ኮሞሮስ፣ ማዳጋስካር፣ ሞዛምቢክ እና ደቡብ ይገኙበታል። ልምምዱ በዋናነት የጸረ-የባሕር ላይ ውንብድና ዘመቻዎችና የመረጃ ልውውጥ ላይ ያተኮረ ነው። ሕንድ፣ ቻይና በምሥራቅ አፍሪካና በሕንድ ውቅያኖስ አካባቢ ተጽዕኖ እንዳይኖራት የማድረግ ፍላጎት አላት። [ዋዜማ]
1፤ ኦብነግ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በገባበትን ውጥረት ዙሪያ የኢትዮጵያ አጋሮችና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ጣልቃ እንዲገቡ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ኦብነግ፣ በአባሎቼ ላይ ጥቃት እንዲፈጸምባቸው፣ የክልሉ ጸጥታ ኃይሎች አባሎቼን እንዲያስፈራሩና ቢሮዎቼን ዒላማ እንዲያደርጉ የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ትዕዛዝ አስተላልፏል ብሏል። በክልሉ ውስጥ ስብሰባዎችን ጭምር እንዳያደርግ የክልሉ መንግሥት እገዳ እንደጣለበት የጠቀሰው ኦብነግ፣ ትናንት በንጎብ ዞን፣ ገርባ ወረዳ ሁለቱ አባሎቼ ያላግባብ ታሠረዋል፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነርም ባንደኛው አባሌ ላይ የአካል ጥቃት ፈጽመዋል በማለት ከሷል። እነዚህ ድርጊቶች ግንባሩ በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሂደት ውስጥ እንዳይሳተፍ ለማደናቀፍ ያለሙ ናቸው ያለው ኦብነግ፣ በክልሉ ለሚፈጠር የሰላምና ጸጥታ መደፍረስ ፌደራል መንግሥቱና ገዥው ፓርቲ ተጠያቂ ይኾናሉ በማለት አስጠንቅቋል።
2፤ ብሄራዊ ባንክ፣ ነገ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚያወጣ አስታውቋል። ባንኩ ለነገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር አቀርባለሁ ብሏል። ባንኩ በየሁለት ሳምንቱ በቋሚነት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚያወጣ ከገለጠ ወዲህ፣ የነገው ጨረታ ሁለተኛው ጨረታው ይሆናል። ባንኩ ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው የ50 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ፣ ላንድ ዶላር 131 ብር 7095 ሳንቲም በኾነ አማካይ ዋጋ ማጫረቱንና በጨረታው 12 ባንኮች መሳተፋቸውን መግለጡ ይታወሳል።
3፤ የኢትዮጵያ ተቀማጭ ገንዘብ መድኅን ፈንድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከፋይናንስ ተቋማት 5 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን መሰብሰቡን አስታውቋል። ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር፣ የ11 ነጥብ 10 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን የመድኅን ፈንዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደሳለኝ አምባው ተናግረዋል። ከዓረቦኑ ውስጥ 2 ነጥብ 67 ቢሊዮን ብር ወይም 51 ነጥብ 3 በመቶው ከግል ባንኮች፣ 2 ነጥብ 47 ቢሊዮኑ ወይም 47 ነጥብ 5 በመቶው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ቀሪው ከማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት መሰብሰቡን ደሳለኝ ጠቅሰዋል። ፈንዱ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት፣ ከተቋማቱ የሰበሰበውን ዓረቦን በሙዓለ ንዋይ መልክ እያፈሰሰ መኾኑን የጠቀሱት ሃላፊው፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የፈንዱ የኢንቨስትመንት ክምችት 12 ነጥብ 11 ቢሊዮን ብር መድረሱን ተናግረዋል፡፡
4፤ የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግንባታው ለዘገየው ከኢትዮጵያ ጋር ለሚያገናኘው የመንገድ ፕሮጀክት ዲዛይን የሚያወጣ አማካሪ ድርጅት በቅርቡ ሊመርጥ መሆኑን አስታውቋል። ሁለቱ አገራት 220 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ የሚኖረውን መንገድ በጋራ ለመገንባት ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት የ738 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል። የመንገድ ፕሮጀክቱን ሙሉ ወጪ ለጊዜው የምትሸፍነው ኢትዮጵያ ስትሆን፣ ደቡብ ሱዳን ድርሻዋን ከ5 ዓመት በኋላ በነዳጅ መልክ ለኢትዮጵያ ትከፍላለች። የደቡብ ሱዳን ፓርላማም ባለፈው ዓመት ሰኔ ላይ ስምምነቱን አጽድቋል። የደቡብ ሱዳን የመንገድ ሚንስትር ሲሞን ሚጃክ፣ ፕሮጀክቱ መዘግየቱን ገልጸው፣ ኾኖም ግንባታው የማይቀር እንደሆነ መናገራቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
5፤ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይልና አጋሮቹ "የሰላምና አንድነት መንግሥት" የተሰኘ ትይዩ መንግሥት ማቋቋማቸውን አውጀዋል። የፈጥኖ ደረሹ ኃይል ዋና አዛዥ ጀኔሬል ሞሐመድ ደጋሎ፣ ቡድኑና አጋሮቹ ለአዲሲቷ ሱዳን መሠረት የሚጥል የሽግግር ሕገመንግሥት ማጽደቃቸውንም ይፋ አድርገዋል። የሽግግር ሰነዱ፣ አገሪቱን ለማስተዳደር የሁሉንም የአገሪቱ ግዛቶች ተወካዮች ያካተተ 15 አባላት ያሉት ፕሬዝዳንታዊ ካውንስል እንደሚቋቋም ይገልጣል። ጀኔራል ደጋሎ፣ በአገሪቱ የትኛውም ብሔር፣ ግዛት ወይም ኃይማኖት ከሱዳናዊ ማንነት ሊበልጥ እንደማይገባ፣ አዲሱ መንግሥት በሕግ ብቻ የሚመራ እንደሚሆን አስታውቀዋል። ኾኖም የትይዩ መንግሥት እወጃው አገሪቱን ሊበታትናት ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።
6፤ አሜሪካ፣ የአሥመራውን ጨምሮ በ30 አገራት ኢምባሲዎቿን ለመዝጋት ወይም ዲፕሎማቶቿን ለመቀነስ ማቀዳ ተሠምቷል። የሞቃዲሾው የአሜሪካ ኢምባሲም የዲፕሎማቲክ ውክልናውን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ወይም ጨርሶ ለመዝጋት እንደታሰበም ዓለማቀፍ የዜና ወኪሎች ከውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ያገኙትን ሚስጢራዊ ሰነድ ጠቅሰው ዘግበዋል። በኤርትራ፣ በደቡብ ሱዳን፣ ሌሴቶ፣ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ እና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙ ኢምባሲዎችን ጨምሮ በተለይ በአውሮፓና አፍሪካ አስር ኢምባሲዎችና 17 ቆንስላዎች ሙሉ በሙሉ ሊዘጉ ይችላሉ ተብሏል።
7፤ የሱማሊያ መንግሥት፣ የአሜሪካ የነዳጅ ኩባንያዎች ሱማሊያ ውስጥ በነዳጅ ፍለጋና ቁፋሮ እንዲሠማሩ ትናንት በይፋ ጋብዟል። የፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ መንግሥት ለአሜሪካ ኩባንያዎች ይህን ግብዣ ያቀረበው፣ ዋሽንግተን በሚገኙት አምባሳደሩ በኩል ነው። አምባሳደሩ፣ ሱማሊያ ሰሞኑን የፌደሬሽኑ አባል አድርጌያታለሁ ባለቻትና ከሶማሌላንድ በተነጠለችው "ኤስ ኤስ ካቱሜ" ግዛት፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች በነዳጅ ፍለጋና ቁፋሮ እንዲሠማሩ ነው ጥሪ ያቀረቡት።
8፤ ሕንድ፣ ካለፈው ዕሁድ ጀምሮ በሕንድ ውቅያኖስ ላይ ከአስር የአፍሪካ አገራት ጋር ለስድስት ቀናት የሚቆይ የጋራ የባሕር ኃይል ልምምድ በማድረግ ላይ ናት። በባሕር ኃይል ልምምዱ በመሳተፍ ላይ ካሉት አገራት መካከል፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ኮሞሮስ፣ ማዳጋስካር፣ ሞዛምቢክ እና ደቡብ ይገኙበታል። ልምምዱ በዋናነት የጸረ-የባሕር ላይ ውንብድና ዘመቻዎችና የመረጃ ልውውጥ ላይ ያተኮረ ነው። ሕንድ፣ ቻይና በምሥራቅ አፍሪካና በሕንድ ውቅያኖስ አካባቢ ተጽዕኖ እንዳይኖራት የማድረግ ፍላጎት አላት። [ዋዜማ]
Liberal Optics, Illiberal Policies
In the old days, the State-Owned Enterprises (SoEs) space was dominated by corporations owned by the federal government. We are now seeing an SoE space dominated by corporations owned by regional states. In some regions, such as Oromia, regional corporations are given the monopoly to control the whole market chain. This extends from trading companies to manufacturing and onto financial institutions.
Hence, the rent collection apparatus has effectively gotten devolved. Very high corruption and excessive militarization of politics in the country mean that the running cost of the government has also gone up. The only way to sustain loyalty in such a large extractive system seems to be opening avenues for rent seeking and corruption to all sections of the state apparatus.
Read FULL - cutt.ly/yrggKtGZ
In the old days, the State-Owned Enterprises (SoEs) space was dominated by corporations owned by the federal government. We are now seeing an SoE space dominated by corporations owned by regional states. In some regions, such as Oromia, regional corporations are given the monopoly to control the whole market chain. This extends from trading companies to manufacturing and onto financial institutions.
Hence, the rent collection apparatus has effectively gotten devolved. Very high corruption and excessive militarization of politics in the country mean that the running cost of the government has also gone up. The only way to sustain loyalty in such a large extractive system seems to be opening avenues for rent seeking and corruption to all sections of the state apparatus.
Read FULL - cutt.ly/yrggKtGZ
ለቸኮለ! ሐሙስ፣ ሚያዝያ 9/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ኢሰመጉ፣ መንግሥት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ግጭቶችን በድርድር እንዲፈታ ጠይቋል። ድርጅቱ፣ የግጭቱ ተሳታፊ አካላት በግጭት አውድ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብቶችና የሰብዓዊነት ሕግጋትን ከመጣስ እንዲቆጠቡ፣ በሲቪሎች ሕይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ጥቃት ከማድረስና በሕጻናትና ወጣቶች የመማር መብት ላይ ገደብ ከመጣል እንዲቆጠቡም ጥሪ አድርጓል። መንግሥት፣ በንጹሃን ላይ የታጠቁ ቡድኖች የሚፈጽሟቸውን ግድያዎች እንዲያስቆምና የታዳጊዎችን የመማር መብት እንዲያስከብርም ኢሰመጉ ጠይቋል። ኢሰመጉ ይህን ጥሪ ያቀረበው፣ በክልሉ በታጠቁ ቡድኖች ጫና ምክንያት ተማሪዎች በነጻነት ትምህርታቸውን መከታተል ከማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸውን በመጥቀስ ነው።
2፤ በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች እስከ ምሽቱ ሦስት ሰዓት እንዲሠሩ የተገደዱ የንግዱ መደብሮች ባለቤት ነጋዴዎችና ሠራተኞች ለከፍተኛ ችግር እንደተጋለጡ ዋዜማ ሰምታለች። መርካቶ አካባቢ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን በመሸጥ የሚተዳደሩ መኖሪያቸው ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የሆኑ ነጋዴዎች፣ ደንቡ ከወጣ በኋላ ቤታቸው የሚደርሱት እኩለ ሌሊት ላይ መሆኑን ለዋዜማ ተናግረዋል። አስተዳደሩ ደንቡን በተላለፉ ነጋዴዎች ላይ 10 ሺሕ ብር ቅጣት እየጣለ መሆኑን ዋዜማ ተረድታለች። በሌሎች አካባቢዎች የሚሠሩ ነጋዴዎችና ሠራተኞች ደሞ የሥራ ቦታቸው ውስጥ ለማደር እንደተገደዱና ተጨማሪ ሠራተኛ የቀጠሩም እንዳሉ ተናግረዋል።
3፤ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ290 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። ባለስልጣኑ ርምጃ ከወሰደባቸው ውስጥ፣ አዋኪ ድርጊቶች፣ ሕገወጥ የመንገድ አጠቃቀም፣ ሕገወጥ ንግድ፣ የመሬት ወረራ፣ ሕገወጥ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ከቅጣት ብቻ ከ258 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘቱንና ከጨረታ ሽያጭ ደሞ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ዋዜማ ተረድታለች። ደንቡ ከወጣ ወዲህ፣ በከተማዋ 64 በመቶ ጥሰቶች ቀንሰዋል ተብሏል። መስሪያ ቤቱ በሕገወጥ የመንገድ አጠቃቀም ላይ ብቻ 7 ሺሕ 133 ርምጃዎችን እንደወሰደም ተገልጧል። ወደ ወንዞች ይለቀቁ የነበሩ 3 ሺሕ የሚጠጉ የፍሳሽ መስመሮችም መቆማቸውን ባለሥልጣኑ ጠቅሷል።
4፤ ብሄራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ ዶላር በ131 ብር ከ49 ሳንቲም አማካይ ዋጋ እንደሸጠ አስታውቋል። ባንኩ ለዛሬው ጨረታ ያቀረበው የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን ዶላር ነበር። በጨረታው 26 ባንኮች እንደተሳተፉና ከሁለት ሳምንት በፊት ከተካሄደው ጨረታ አንጻር የዛሬው ላንድ ዶላር የ0 ነጥብ 16 በመቶ ቅናሽ እንደነበረው ባንኩ ገልጧል።
5፤ ሱማሌላንድ፣ ከሱማሊያ ጋር ከተጀመሩ ማናቸውም የሰላም ድርድሮች መውጣቷን በይፋ አስታውቃለች። ሶማሌላንድ ይህን ርምጃ የወሰደችው፣ የሱማሊያ ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ የግጭት ማዕከል በነበረችው የሶማሌላንዷ ላስ አኖድ ከተማ ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው። የጠቅላይ ሚንስትሩ ጉብኝት "ጠባጫሪ" እና "ሕጋዊነት የሌለው" ነው በማለት ሶማሌላንድ ያወገዘችው ሱማሌላንድ፣ ሉዓላዊነቷና የግዛት አንድነቷ የማይታለፍ ቀይ መስመር መሆኑን ገልጣለች። ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ በምስራቃዊው ሱል ግዛት ሱማሊያ ለምትፈጽመው ጥሰት መፍትሄ እንዲፈልግም ሶማሌላንድ ጠይቃለች።
6፤ ዩኒሴፍ፣ የቀጣዩ አውሮፓዊያን ዓመት በጀቱን በ20 በመቶ እንደሚቀንስ ማስታወቁን ሮይተርስ ዘግቧል። ድርጅቱ በጀቱን ለመቀነስ የወሰነው፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካን እርዳታ መቀነሳቸውን ተከትሎ እንደሆነ ዘገባው ጠቅሷል። አሜሪካ ለተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች የምትሠጠውን የገንዘብ ድጋፍም እንድታቆም የዋይት ሃውስ በጀት ቢሮ ሃሳብ ማቅረቡን ዘገባው አመልክቷል። የአሜሪካ ባለሥልጣናት ይህን ሃሳብ ያቀረቡት፣ ለአብነት በማሊ እና ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ የድርጅቱ ተልዕኮዎች ውጤታቸው ውድቀት ኾኗል በማለት ነው ተብሏል። [ዋዜማ]
1፤ ኢሰመጉ፣ መንግሥት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ግጭቶችን በድርድር እንዲፈታ ጠይቋል። ድርጅቱ፣ የግጭቱ ተሳታፊ አካላት በግጭት አውድ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብቶችና የሰብዓዊነት ሕግጋትን ከመጣስ እንዲቆጠቡ፣ በሲቪሎች ሕይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ጥቃት ከማድረስና በሕጻናትና ወጣቶች የመማር መብት ላይ ገደብ ከመጣል እንዲቆጠቡም ጥሪ አድርጓል። መንግሥት፣ በንጹሃን ላይ የታጠቁ ቡድኖች የሚፈጽሟቸውን ግድያዎች እንዲያስቆምና የታዳጊዎችን የመማር መብት እንዲያስከብርም ኢሰመጉ ጠይቋል። ኢሰመጉ ይህን ጥሪ ያቀረበው፣ በክልሉ በታጠቁ ቡድኖች ጫና ምክንያት ተማሪዎች በነጻነት ትምህርታቸውን መከታተል ከማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸውን በመጥቀስ ነው።
2፤ በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች እስከ ምሽቱ ሦስት ሰዓት እንዲሠሩ የተገደዱ የንግዱ መደብሮች ባለቤት ነጋዴዎችና ሠራተኞች ለከፍተኛ ችግር እንደተጋለጡ ዋዜማ ሰምታለች። መርካቶ አካባቢ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን በመሸጥ የሚተዳደሩ መኖሪያቸው ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የሆኑ ነጋዴዎች፣ ደንቡ ከወጣ በኋላ ቤታቸው የሚደርሱት እኩለ ሌሊት ላይ መሆኑን ለዋዜማ ተናግረዋል። አስተዳደሩ ደንቡን በተላለፉ ነጋዴዎች ላይ 10 ሺሕ ብር ቅጣት እየጣለ መሆኑን ዋዜማ ተረድታለች። በሌሎች አካባቢዎች የሚሠሩ ነጋዴዎችና ሠራተኞች ደሞ የሥራ ቦታቸው ውስጥ ለማደር እንደተገደዱና ተጨማሪ ሠራተኛ የቀጠሩም እንዳሉ ተናግረዋል።
3፤ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ290 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። ባለስልጣኑ ርምጃ ከወሰደባቸው ውስጥ፣ አዋኪ ድርጊቶች፣ ሕገወጥ የመንገድ አጠቃቀም፣ ሕገወጥ ንግድ፣ የመሬት ወረራ፣ ሕገወጥ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ከቅጣት ብቻ ከ258 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘቱንና ከጨረታ ሽያጭ ደሞ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ዋዜማ ተረድታለች። ደንቡ ከወጣ ወዲህ፣ በከተማዋ 64 በመቶ ጥሰቶች ቀንሰዋል ተብሏል። መስሪያ ቤቱ በሕገወጥ የመንገድ አጠቃቀም ላይ ብቻ 7 ሺሕ 133 ርምጃዎችን እንደወሰደም ተገልጧል። ወደ ወንዞች ይለቀቁ የነበሩ 3 ሺሕ የሚጠጉ የፍሳሽ መስመሮችም መቆማቸውን ባለሥልጣኑ ጠቅሷል።
4፤ ብሄራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ ዶላር በ131 ብር ከ49 ሳንቲም አማካይ ዋጋ እንደሸጠ አስታውቋል። ባንኩ ለዛሬው ጨረታ ያቀረበው የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን ዶላር ነበር። በጨረታው 26 ባንኮች እንደተሳተፉና ከሁለት ሳምንት በፊት ከተካሄደው ጨረታ አንጻር የዛሬው ላንድ ዶላር የ0 ነጥብ 16 በመቶ ቅናሽ እንደነበረው ባንኩ ገልጧል።
5፤ ሱማሌላንድ፣ ከሱማሊያ ጋር ከተጀመሩ ማናቸውም የሰላም ድርድሮች መውጣቷን በይፋ አስታውቃለች። ሶማሌላንድ ይህን ርምጃ የወሰደችው፣ የሱማሊያ ጠቅላይ ሚንስትር ሐምዛ ባሬ የግጭት ማዕከል በነበረችው የሶማሌላንዷ ላስ አኖድ ከተማ ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው። የጠቅላይ ሚንስትሩ ጉብኝት "ጠባጫሪ" እና "ሕጋዊነት የሌለው" ነው በማለት ሶማሌላንድ ያወገዘችው ሱማሌላንድ፣ ሉዓላዊነቷና የግዛት አንድነቷ የማይታለፍ ቀይ መስመር መሆኑን ገልጣለች። ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ በምስራቃዊው ሱል ግዛት ሱማሊያ ለምትፈጽመው ጥሰት መፍትሄ እንዲፈልግም ሶማሌላንድ ጠይቃለች።
6፤ ዩኒሴፍ፣ የቀጣዩ አውሮፓዊያን ዓመት በጀቱን በ20 በመቶ እንደሚቀንስ ማስታወቁን ሮይተርስ ዘግቧል። ድርጅቱ በጀቱን ለመቀነስ የወሰነው፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካን እርዳታ መቀነሳቸውን ተከትሎ እንደሆነ ዘገባው ጠቅሷል። አሜሪካ ለተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች የምትሠጠውን የገንዘብ ድጋፍም እንድታቆም የዋይት ሃውስ በጀት ቢሮ ሃሳብ ማቅረቡን ዘገባው አመልክቷል። የአሜሪካ ባለሥልጣናት ይህን ሃሳብ ያቀረቡት፣ ለአብነት በማሊ እና ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ የድርጅቱ ተልዕኮዎች ውጤታቸው ውድቀት ኾኗል በማለት ነው ተብሏል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ዓርብ፣ ሚያዝያ 10/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት፣ ፌደራል ፖሊስ ዛሬ አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቢሮው በመግባት የድርጅቱንና የጋዜጠኞችን ንብረቶች እንደወሰደ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፖሊስ ጋዜጠኞቹን ጭምር በቁጥጥር ሥር አውሎ እንደነበር የገለጠው መጽሄቱ፣ ዘግየት ብሎ ግን የታሠሩ ባልደረቦቹ እንደተለቀቁ ጠቅሷል። ኾኖም ፖሊስ የወሰዳቸውን የቢሮና የጋዜጠኞች ላፕቶፖች፣ ሞባይል ስልኮችና ሃርድ ዲስኮች እስከ ምሽት ድረስ እንዳልመለሰ፣ ይህም በሥራው ላይ ተጽዕኖ እንደፈጠረና በጋዜጠኞቹ ደኅንነት ላይ ስጋት እንደደቀነ መጽሄቱ ገልጧል።
2፤ ብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን፣ በትግራይ ተቋርጦ የቆየውን የመጀመርያው ምዕራፍ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ የመበተንና መልሶ ከኅብረተሰቡ ጋር የመቀላቀል መርሃ ግብር ትናንት እንደገና አስጀምሯል። በክልሉ በኅዳር የተጀመረው የትጥቅ ማስፈታትና መልሶ መቀላቀል ሂደት በ"ቴክኒክ" እና "ፖለቲካዊ" ምክንያቶች ከታኅሳስ ጀምሮ ተቋርጦ ነበር። የትግራይ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀኔራል ፍስሃ ኪዳኑ፣ በትግራይ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መኾን አለበት በማለት በትናንቱ የመርሃ ግብሩ ድጋሚ ማስጀመሪያ ስነ ሥርዓት ላይ ተናግረዋል። ጀኔራል ፍስሃ፣ የግጭት ማቆም ስምምነቱና የትጥቅ ማስፈታትና መልሶ መቀላቀሉ መርሃ ግብር እንዲሳካ ፌደራል መንግስቱ በግጭት ማቆም ስምምነቱ የገባባቸውን ግዴታዎች መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል። የተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ ለመርሃ ግብሩና ለስምምነቱ ትግበራ ከፌዴራል መንግሥቱና ከአዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በትብብር እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
3፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ አየር መንገዱ አዲስ ለሚያስገነባው አውሮፕላን ማረፊያ 2 ሺሕ 500 አባወራዎች ከቀያቸው እንደሚነሱ መናገራቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ከቢሾፍቱ አካባቢ ለሚነሱት አርሶ አደር አባውራዎች አየር መንገዱ መኖሪያ ቤቶችን እንደሚያስገነባ የጠቆሙት መስፍን፣ አየር መንገዱ ቤቶቹን ገንብቶ በሚቀጥለው ዓመት ኅዳር ወር ለተነሺዎች እንደሚያስረክብ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አባውራዎቹ ቤቶቹን ከተረከቡ በኋላ፣ በዚያው ወር ግድም አየር መንገዱ የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ እንደሚያስጀምር ተናግረዋል ተብሏል።
4፤ 'ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች' የተሰኘው መንግሥታዊ ያልኾነ የመብት ተሟጋች ድርጅት፣ ፌደራል መንግሥቱ በእስር ላይ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች የኾኑ የቀድሞ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ እንዲፈታ ጠይቋል። ድርጅቱ፣ የትግራይ ተወላጆች የኾኑ 13 የቀድሞ የመከላከያ ሠራዊት አባላት አሁንም በፌደራል እስር ቤቶች ታስረው እንዳሉ እንደሚያውቅና ስም ዝርዝራቸውም በእጁ እንደሚገኝ ገልጧል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በክልሉ በተለያዩ ቡድኖች መካከል ያለውን የፖለቲካ ልዩነት ለመፍታት ቅድሚያ እንዲሠጥ ያሳሰበው ድርጅቱ፣ በትግራይ ያለው የጦርነት ደመና በጊዜ ካልተቀረፈ ከፍተኛ ወደኾነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያመራል በማለት አስጠንቅቋል። በትግራይ የሠፈነው የፖለቲካ ፍላጎቶችን በጠመንጃ አፈሙዝ የማስፈጸም አካሄድም አደገኛ ነው ሲል ድርጅቱ ስጋቱን ገልጧል።
5፤ የሱማሊያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አሕመድ ፊቂ፣ በሱማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ ተጠባባቂ ሃላፊ ሲቩየል ባም ላይ ጠንካራ ክሶችን ማሠማታቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ፊቂ፣ የኅብረቱ ልዑክ ተጠባባቂ የበላይ ሃላፊ "የአልሸባብ ደጋፊ" እና "ለሱማሊያ ደኅንነትና ልማት ስጋት የኾኑ ሰው ናቸው" በማለት ባንድ ቃለ ምልልስ ላይ መክሰሳቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ፣ ባም በሱማሊያ ዙሪያ "አሉታዊ ሪፖርቶችን ይልካሉ"፤ "የሱማሊያ ጦር ሠራዊት ከአልሸባብ ጋር በሚያደርገው ውጊያ ያስገኛቸውን ድሎች አንኳሰው ያቀርባሉ" በማለት ወቅሰዋቸዋል ተብሏል። ፊቂ ይህን ውንጀላ ያሰሙት፣ ባም አልሸባብ እያንሠራራ መኾኑን ለተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት ላይ መግለጣቸውን ተከትሎ ነው። መንግሥታቸው በባም ላይ ርምጃ መውሰዱን ፊቂ የገለጡ ሲኾን፣ የርምጃው ምንነት ግን አላብራሩም ተብሏል። [ዋዜማ]
1፤ አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት፣ ፌደራል ፖሊስ ዛሬ አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቢሮው በመግባት የድርጅቱንና የጋዜጠኞችን ንብረቶች እንደወሰደ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፖሊስ ጋዜጠኞቹን ጭምር በቁጥጥር ሥር አውሎ እንደነበር የገለጠው መጽሄቱ፣ ዘግየት ብሎ ግን የታሠሩ ባልደረቦቹ እንደተለቀቁ ጠቅሷል። ኾኖም ፖሊስ የወሰዳቸውን የቢሮና የጋዜጠኞች ላፕቶፖች፣ ሞባይል ስልኮችና ሃርድ ዲስኮች እስከ ምሽት ድረስ እንዳልመለሰ፣ ይህም በሥራው ላይ ተጽዕኖ እንደፈጠረና በጋዜጠኞቹ ደኅንነት ላይ ስጋት እንደደቀነ መጽሄቱ ገልጧል።
2፤ ብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን፣ በትግራይ ተቋርጦ የቆየውን የመጀመርያው ምዕራፍ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ የመበተንና መልሶ ከኅብረተሰቡ ጋር የመቀላቀል መርሃ ግብር ትናንት እንደገና አስጀምሯል። በክልሉ በኅዳር የተጀመረው የትጥቅ ማስፈታትና መልሶ መቀላቀል ሂደት በ"ቴክኒክ" እና "ፖለቲካዊ" ምክንያቶች ከታኅሳስ ጀምሮ ተቋርጦ ነበር። የትግራይ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀኔራል ፍስሃ ኪዳኑ፣ በትግራይ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መኾን አለበት በማለት በትናንቱ የመርሃ ግብሩ ድጋሚ ማስጀመሪያ ስነ ሥርዓት ላይ ተናግረዋል። ጀኔራል ፍስሃ፣ የግጭት ማቆም ስምምነቱና የትጥቅ ማስፈታትና መልሶ መቀላቀሉ መርሃ ግብር እንዲሳካ ፌደራል መንግስቱ በግጭት ማቆም ስምምነቱ የገባባቸውን ግዴታዎች መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል። የተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ ለመርሃ ግብሩና ለስምምነቱ ትግበራ ከፌዴራል መንግሥቱና ከአዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በትብብር እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
3፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ አየር መንገዱ አዲስ ለሚያስገነባው አውሮፕላን ማረፊያ 2 ሺሕ 500 አባወራዎች ከቀያቸው እንደሚነሱ መናገራቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ከቢሾፍቱ አካባቢ ለሚነሱት አርሶ አደር አባውራዎች አየር መንገዱ መኖሪያ ቤቶችን እንደሚያስገነባ የጠቆሙት መስፍን፣ አየር መንገዱ ቤቶቹን ገንብቶ በሚቀጥለው ዓመት ኅዳር ወር ለተነሺዎች እንደሚያስረክብ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አባውራዎቹ ቤቶቹን ከተረከቡ በኋላ፣ በዚያው ወር ግድም አየር መንገዱ የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ እንደሚያስጀምር ተናግረዋል ተብሏል።
4፤ 'ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች' የተሰኘው መንግሥታዊ ያልኾነ የመብት ተሟጋች ድርጅት፣ ፌደራል መንግሥቱ በእስር ላይ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች የኾኑ የቀድሞ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ እንዲፈታ ጠይቋል። ድርጅቱ፣ የትግራይ ተወላጆች የኾኑ 13 የቀድሞ የመከላከያ ሠራዊት አባላት አሁንም በፌደራል እስር ቤቶች ታስረው እንዳሉ እንደሚያውቅና ስም ዝርዝራቸውም በእጁ እንደሚገኝ ገልጧል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በክልሉ በተለያዩ ቡድኖች መካከል ያለውን የፖለቲካ ልዩነት ለመፍታት ቅድሚያ እንዲሠጥ ያሳሰበው ድርጅቱ፣ በትግራይ ያለው የጦርነት ደመና በጊዜ ካልተቀረፈ ከፍተኛ ወደኾነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያመራል በማለት አስጠንቅቋል። በትግራይ የሠፈነው የፖለቲካ ፍላጎቶችን በጠመንጃ አፈሙዝ የማስፈጸም አካሄድም አደገኛ ነው ሲል ድርጅቱ ስጋቱን ገልጧል።
5፤ የሱማሊያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አሕመድ ፊቂ፣ በሱማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ ተጠባባቂ ሃላፊ ሲቩየል ባም ላይ ጠንካራ ክሶችን ማሠማታቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ፊቂ፣ የኅብረቱ ልዑክ ተጠባባቂ የበላይ ሃላፊ "የአልሸባብ ደጋፊ" እና "ለሱማሊያ ደኅንነትና ልማት ስጋት የኾኑ ሰው ናቸው" በማለት ባንድ ቃለ ምልልስ ላይ መክሰሳቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ፣ ባም በሱማሊያ ዙሪያ "አሉታዊ ሪፖርቶችን ይልካሉ"፤ "የሱማሊያ ጦር ሠራዊት ከአልሸባብ ጋር በሚያደርገው ውጊያ ያስገኛቸውን ድሎች አንኳሰው ያቀርባሉ" በማለት ወቅሰዋቸዋል ተብሏል። ፊቂ ይህን ውንጀላ ያሰሙት፣ ባም አልሸባብ እያንሠራራ መኾኑን ለተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት ላይ መግለጣቸውን ተከትሎ ነው። መንግሥታቸው በባም ላይ ርምጃ መውሰዱን ፊቂ የገለጡ ሲኾን፣ የርምጃው ምንነት ግን አላብራሩም ተብሏል። [ዋዜማ]
#NewsAlert
በደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ሕወሓት፣ ፌደራል መንግሥት የትግራይ ግዛቶችን በኃይል የያዙ የታጠቁ ኃይሎችን ባስቸኳይ እንዲያስወጣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ቡድኑ፣ የትግራይን መሬት በኃይል የተቆጣጠረው አካል "የተከዜ ዘብ" የሚላቸውን አዳዲስ ታጣቂዎች እያስመረቀ በትግራይ ላይ "የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል" በማለትም ከሷል። ይህ ዓይነቱ ድርጊት የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ የሚጻረርና ዘላቂ ሰላም እንዳይመጣ እንቅፋት የሚፈጥር ነው በማለትም ቡድኑ አስጠንቅቋል። የአፍሪካ ኅብረት ፓናል ባፋጣኝ ተሰብስቦ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አጠቃላይ አፈጻጸም ላይ እንዲወያይም ቡድኑ ጠይቋል። ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ባለመኾኑ፣ የሕዝብ ሞት፣ ሥቃይና ሠቆቃ እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለትግራይ ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ አላመጣም ያለው ፓርቲው፣ የታጠቁ ኃይሎች በኃይል በያዟቸው የትግራይ ግዛቶች አኹንም ወገኖቻችን እየተገደሉ፣ እየተፈናቀሉ፣ እየታሠሩና እየተሠቃዩ ይገኛሉ ብሏል። ቡድኑ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት ተደራዳሪዎችና ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ተፈናቃዮች ወደቀያቸው እንዲመለሱ አስቸኳይ ርምጃ እንዲወስዱም ጥሪ አድርጓል። [ዋዜማ]
በደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ሕወሓት፣ ፌደራል መንግሥት የትግራይ ግዛቶችን በኃይል የያዙ የታጠቁ ኃይሎችን ባስቸኳይ እንዲያስወጣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ቡድኑ፣ የትግራይን መሬት በኃይል የተቆጣጠረው አካል "የተከዜ ዘብ" የሚላቸውን አዳዲስ ታጣቂዎች እያስመረቀ በትግራይ ላይ "የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል" በማለትም ከሷል። ይህ ዓይነቱ ድርጊት የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ የሚጻረርና ዘላቂ ሰላም እንዳይመጣ እንቅፋት የሚፈጥር ነው በማለትም ቡድኑ አስጠንቅቋል። የአፍሪካ ኅብረት ፓናል ባፋጣኝ ተሰብስቦ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አጠቃላይ አፈጻጸም ላይ እንዲወያይም ቡድኑ ጠይቋል። ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ባለመኾኑ፣ የሕዝብ ሞት፣ ሥቃይና ሠቆቃ እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለትግራይ ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ አላመጣም ያለው ፓርቲው፣ የታጠቁ ኃይሎች በኃይል በያዟቸው የትግራይ ግዛቶች አኹንም ወገኖቻችን እየተገደሉ፣ እየተፈናቀሉ፣ እየታሠሩና እየተሠቃዩ ይገኛሉ ብሏል። ቡድኑ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት ተደራዳሪዎችና ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ተፈናቃዮች ወደቀያቸው እንዲመለሱ አስቸኳይ ርምጃ እንዲወስዱም ጥሪ አድርጓል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ሰኞ፣ ሚያዝያ 13/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ በሱማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ የኢትዮጵያ ቆንስላ ውስጥ ተመድበው ይሠሩ የነበሩት ኢትዮጵያዊው ዲፕሎማት ፋራህ አይዲድ ጃማ ከሱማሌላንድ ራስ ገዝ በቅርቡ በተነጠለችው "ኤስ ኤስ ካቱሜ" ግዛት ላስ አኖድ ከተማ ውስጥ በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን የሱማሊያ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የግዛቲቷ ባለሥልጣናት፣ ግድያውን የፈጸሙት የአልሸባብ አባላት ሳይኾኑ አይቀርም የሚል ጥርጣሬ እንዳላቸው ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። በዲፕሎማቱ ሕልፈት ዙሪያ የግዛቲቱ ባለሥልጣናት ምርመራ እያደረጉ እንደኾነ ተገልጧል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በዲፕሎማቱ ሕልፈት ዙሪያ በይፋ ያለው ነገር የለም። የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት፣ ከሶማሌላንድ መገንጠል እንፈልጋለን ያሉ የጎሳ ሚሊሻዎች ከደም አፋሳሽ ውጊያ በኋላ የመሠረቷትን "ኤስ ኤስ ካቱሜ" ግዛት፣ ባለፈው ሳምንት የፌደሬሽኑ አባል ግዛት አድርጎ መቀበሉን ማወጁ ይታወሳል።
2፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የታክሲ ተራ አስከባሪ ማኅበራት ከገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግሥት እንዲሰጡ የሚያስገድድ ደንብ አጽድቋል። ደንቡ ማኅበራቱ “ዝግ እና መደበኛ የባንክ አካውንት" እንዲከፍቱና ከሁለት ዓመት በኋላ “ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ” ግዴታ ይጥላል። “የተርሚናል አገልግሎት አሠራርና ቁጥጥር” የተሰኘው ደንብ፣ ኢንተርፕራይዝ በማለት የሠየማቸው ማኅበራት የሚደራጁት በከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ መስፈርት መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች። ኢንተርፕራይዞቹ 30 በመቶ “የግዴታ ቁጠባ” መቆጠብ፣ 50 በመቶውን በተንቀሳቃሽ የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥና ያንድ ዓመት ውል መፈረም እንዳለባቸውም ይደነግጋል።
3፤ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ጀኔራል ታደሠ ወረደ እንደገና ያዋቀሩት ካቢኔ ሌሎችን ያገለለ፣ አቃፊ ያልኾነና ተቀባይነት የሌለው ነው በማለት ተቃውሟል። ካቢኔው የተዋቀረው፣ የአንድን ቡድንና የወታደራዊ አዛዦችን ፍላጎት ብቻ በመስማት ነው ያለው ቡድኑ፣ የካቢኔው አወቃቀር ባስቸኳይ እንዲስተካከል ጠይቋል። በጊዜያዊ አስተዳደሩ አወቃቀር ላይ ማስተካከያ ካልተደረገ ግን፣ የትግራይን ሕዝብ ከ"ኋላቀሩ ገዢ" ቡድን ለማላቀቅ ማናቸውንም የትግል ስልት ለመከተል እንገደዳለን በማለት አስጠንቅቋል። ጀኔሬል ታደሠ የአዲሱን ካቢኔ ዝርዝር ይፋ ባያደርጉም፣ በደብረጺዮን የሚመራው የሕወሓት ክንፍ ምክትል ሊቀመንበር አማኑዔል አሠፋን ምክትል ፕሬዝዳንት ኾነው እንደተሾሙ ተሠምቷል።
4፤ ናይጀሪያ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፍርደኛ እስረኞች ልውውጥ የመግባቢያ ስምምነትን ባስቸኳይ እንዲፈርም መጠየቁን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የናይጀሪያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ ቢያንካ ኦጁኩ፣ በአቡጃ ከኢትዮጵያ አምባሳደር ለገሠ ገረመው ጋር ሰሞኑን በተወያዩበት ወቅት፣ ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ያላቸውን ጨምሮ በአዲስ አበባ ወህኒ ቤቶች የሚገኙ ናይጀሪያዊያን የተያዙበት ሁኔታ መንግሥታቸውን እንዳሳዘነ መናገራቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን ለመፈረም ለመፈረም ዳተኝነት ማሳየቱንም ኦጁኩ ተችተዋል ተብሏል። በቅርቡ አንድ ናይጀሪያዊ እስረኛ በአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ውስጥ ሕይወቱ ማለፉንም ሚንስትር ደኤታዋ ለአምባሳደሩን ማንሳታቸውን የዜና ምንጮቹ ዘግበዋል።
5፤ ሱማሊያ ከቱርክ የጸጥታ ዋስትና መጠየቋን የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ መንግሥት ይህን ጥያቄ ያቀረበው፣ አልሸባብ በመካከለኛው ሸበሌ እና ታችኛው ሸበሌ ግዛቶች በርካታ ቦታዎችን መቆጣጠሩንና ወደ ሞቃዲሾ ሊገሰግስ ይችላል የሚል ስጋት መፈጠሩን ተከትሎ ነው። ቱርክ በሱማሊያ የባሕር ዳርቻ የተፈጥሮ ጋዝ ለመቆፈርና የሱማሊያን የባሕር ዳርቻ ለመጠበቅ፣ መርከቦቿን ቀደም ሲል በሕንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ማሠማራቷ አይዘነጋም። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሱማሊያ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ኦዱዋ የሱፍ ረጌ መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሠምቷል። [ዋዜማ]
1፤ በሱማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ የኢትዮጵያ ቆንስላ ውስጥ ተመድበው ይሠሩ የነበሩት ኢትዮጵያዊው ዲፕሎማት ፋራህ አይዲድ ጃማ ከሱማሌላንድ ራስ ገዝ በቅርቡ በተነጠለችው "ኤስ ኤስ ካቱሜ" ግዛት ላስ አኖድ ከተማ ውስጥ በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን የሱማሊያ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የግዛቲቷ ባለሥልጣናት፣ ግድያውን የፈጸሙት የአልሸባብ አባላት ሳይኾኑ አይቀርም የሚል ጥርጣሬ እንዳላቸው ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። በዲፕሎማቱ ሕልፈት ዙሪያ የግዛቲቱ ባለሥልጣናት ምርመራ እያደረጉ እንደኾነ ተገልጧል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በዲፕሎማቱ ሕልፈት ዙሪያ በይፋ ያለው ነገር የለም። የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት፣ ከሶማሌላንድ መገንጠል እንፈልጋለን ያሉ የጎሳ ሚሊሻዎች ከደም አፋሳሽ ውጊያ በኋላ የመሠረቷትን "ኤስ ኤስ ካቱሜ" ግዛት፣ ባለፈው ሳምንት የፌደሬሽኑ አባል ግዛት አድርጎ መቀበሉን ማወጁ ይታወሳል።
2፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የታክሲ ተራ አስከባሪ ማኅበራት ከገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግሥት እንዲሰጡ የሚያስገድድ ደንብ አጽድቋል። ደንቡ ማኅበራቱ “ዝግ እና መደበኛ የባንክ አካውንት" እንዲከፍቱና ከሁለት ዓመት በኋላ “ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ” ግዴታ ይጥላል። “የተርሚናል አገልግሎት አሠራርና ቁጥጥር” የተሰኘው ደንብ፣ ኢንተርፕራይዝ በማለት የሠየማቸው ማኅበራት የሚደራጁት በከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ መስፈርት መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች። ኢንተርፕራይዞቹ 30 በመቶ “የግዴታ ቁጠባ” መቆጠብ፣ 50 በመቶውን በተንቀሳቃሽ የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥና ያንድ ዓመት ውል መፈረም እንዳለባቸውም ይደነግጋል።
3፤ የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ጀኔራል ታደሠ ወረደ እንደገና ያዋቀሩት ካቢኔ ሌሎችን ያገለለ፣ አቃፊ ያልኾነና ተቀባይነት የሌለው ነው በማለት ተቃውሟል። ካቢኔው የተዋቀረው፣ የአንድን ቡድንና የወታደራዊ አዛዦችን ፍላጎት ብቻ በመስማት ነው ያለው ቡድኑ፣ የካቢኔው አወቃቀር ባስቸኳይ እንዲስተካከል ጠይቋል። በጊዜያዊ አስተዳደሩ አወቃቀር ላይ ማስተካከያ ካልተደረገ ግን፣ የትግራይን ሕዝብ ከ"ኋላቀሩ ገዢ" ቡድን ለማላቀቅ ማናቸውንም የትግል ስልት ለመከተል እንገደዳለን በማለት አስጠንቅቋል። ጀኔሬል ታደሠ የአዲሱን ካቢኔ ዝርዝር ይፋ ባያደርጉም፣ በደብረጺዮን የሚመራው የሕወሓት ክንፍ ምክትል ሊቀመንበር አማኑዔል አሠፋን ምክትል ፕሬዝዳንት ኾነው እንደተሾሙ ተሠምቷል።
4፤ ናይጀሪያ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፍርደኛ እስረኞች ልውውጥ የመግባቢያ ስምምነትን ባስቸኳይ እንዲፈርም መጠየቁን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የናይጀሪያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ ቢያንካ ኦጁኩ፣ በአቡጃ ከኢትዮጵያ አምባሳደር ለገሠ ገረመው ጋር ሰሞኑን በተወያዩበት ወቅት፣ ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ያላቸውን ጨምሮ በአዲስ አበባ ወህኒ ቤቶች የሚገኙ ናይጀሪያዊያን የተያዙበት ሁኔታ መንግሥታቸውን እንዳሳዘነ መናገራቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን ለመፈረም ለመፈረም ዳተኝነት ማሳየቱንም ኦጁኩ ተችተዋል ተብሏል። በቅርቡ አንድ ናይጀሪያዊ እስረኛ በአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ውስጥ ሕይወቱ ማለፉንም ሚንስትር ደኤታዋ ለአምባሳደሩን ማንሳታቸውን የዜና ምንጮቹ ዘግበዋል።
5፤ ሱማሊያ ከቱርክ የጸጥታ ዋስትና መጠየቋን የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ መንግሥት ይህን ጥያቄ ያቀረበው፣ አልሸባብ በመካከለኛው ሸበሌ እና ታችኛው ሸበሌ ግዛቶች በርካታ ቦታዎችን መቆጣጠሩንና ወደ ሞቃዲሾ ሊገሰግስ ይችላል የሚል ስጋት መፈጠሩን ተከትሎ ነው። ቱርክ በሱማሊያ የባሕር ዳርቻ የተፈጥሮ ጋዝ ለመቆፈርና የሱማሊያን የባሕር ዳርቻ ለመጠበቅ፣ መርከቦቿን ቀደም ሲል በሕንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ማሠማራቷ አይዘነጋም። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሱማሊያ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ኦዱዋ የሱፍ ረጌ መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሠምቷል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 14/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ በገንዘብ እጥረት የተነሳ በኢትዮጵያ ለከፍተኛ ጉዳት ከተጋለጡ 3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ስዎች በጥቂት ሳምንታት ውስጥ የተመጣጠነና መደበኛ የምግብ ድጋፍ ሊቋረጥባቸው እንደሚችል አስጠንቅቋል። ከዚህ ውስጥ፣ 650 ሺሕዎቹ በተመጣጠነ ምግብ እጥረት የተጎዱ ሴቶችና ሕጻናት እንደኾኑ ድርጅቱ ገልጧል። በአገሪቱ ውስጥ ርሃብና ከፍተኛ የምግብ እጥረት በሕጻናት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩንና 10 ሚሊዮን ስዎች ለርሃብና ለተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንደተጋለጡ ድርጅቱ ጠቅሷል። ባጠቃላይ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ነፍሰ ጡሮችና ጡት አጥቢ እናቶች የተመጣጠነ የምግብ ድጋፍ ይፈልጋሉ፤ በትግራይ፣ ሱማሌ፣ ኦሮሚያና አፋር ክልሎች የሕጻናት መቀንጨር "አጣዳፊ" ከሚባለው 15 በመቶ አልፏል ተብሏል።
2፤ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ፣ የጅቡቲ መንግሥት በአገሪቱ ያለ ሕጋዊ ሰነድ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በፍቃደኝነት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የሠጠውን የጊዜ ገደብ እንዲያራዝም የኢትዮጵያ ኢምባሲ ያቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ኢምባሲው አስታውቋል። ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸው የውጭ ዜጎች በሙሉ ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 24 ከጅቡቲ እንዲወጡና ቀነ ገደቡ ካለፈ ግን በፖሊስ ተገደው እንደሚወጡ የአገሪቱ መንግስት ቀደም ሲል የጊዜ ገደብ አስቀምጧል። ኢምባሲው፣ ከአገሪቱ የአገር ውስጥ ደኅንነት ባለሥልጣናት ጋር ባደረገው ውይይት፣ ኢትዮጵያዊያኑ ብዛት ስላላቸው በቂ የዝግጅት ጊዜ እንዲያገኙ ቀነ ገደቡ በሦስት ወር እንዲራዘምላቸው ጠይቆ እንደነበር ጠቅሷል።
3፤ ምርጫ ቦርድ፣ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ "ምንም ዓይነት ጊዜያዊም ሆነ ቋሚ ሕጋዊ እውቅና" እና "የምዝገባ ፍቃድ" እንደሌለው ገልጧል። ቦርዱ፣ ሕጋዊ እውቅና ፍቃድ የተሠጠው በማስመሰል በተለያዩ መድረኮች "አሳሳች መግለጫ" እየሠጠ ይገኛል በማለት ከሷል፡፡ ፓርቲው ሕጋዊ እውቅና ለማግኘት መስፈርቶቹን እስካሁን እንዳላሟላ የጠቀሰው ቦርዱ፣ ፓርቲው ባኹኑ ወቅት የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች "ሕዝብን የሚያሳስቱ" እና "የሚያደናግሩ" ናቸው ብሏል።
4፤ በሱዳን የሚካሄደውን ጦርነት በመሸሽ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከገቡ ስደተኞች መካከል፣ ከ40 ሺሕ የሚበልጡትን ወደ አንድ መጠለያ የማስገባት ሥራ መከናወኑን መስማቱን ሸገር ዘግቧል። ወደ ክልሉ የገቡት ስደተኞችና ኢትዮጵያዊያን ተመላሾች በመጠለያ ጣቢያና በየሰው ቤት ማረፋቸውን የክልሉ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን መግለጹን ዘገባው ጠቅሷል። በተመድ መጠለያዎች የተጠለሉት ስደተኞች ከ40 ሺሕ በላይ እንደኾኑና ለእነዚህ ስደተኞች በየወሩ ምግብ ነክ ድጋፍ እንደሚቀርብላቸውም ኮሚሽኑ ተናግሯል ተብሏል።
5፤ የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ ሊያደርጉት የነበረውን ይፋዊ ጉብኝት መሠረዛቸውን የፈረንሳዩ አፍሪካ ኢንተሌጀንስ ድረገጽ ዘግቧል። ሩቢዮ፣ በቅርቡ በጸጥታና ንግድ ዙሪያ ለመወያየት በናይሮቢ እና አዲስ አበባ ጉብኝት ለማድረግ ማቀዳቸውን የዜና ምንጩ ቀደም ሲል ዘግቦ ነበር። ሩቢዮ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ሊያደርጉት ያቀዱት ውይይት፣ ቻይና በኢትዮጵያ ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለመግታት ያለመ ጭምር እንደኾነም ዘገባው ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል።
6፤ የአሜሪካው ፔንታጎን፣ በሱማሊያ የባሕር ግዛት ውስጥ በኹለት ጀልባዎች ላይ ሚያዝያ 8 ቀን የአየር ጥቃት መፈጸሙን ዛሬ ባወጣው መረጃ ገልጧል። ፔንታጎን በጀልባዎቹ ላይ የአየር ጥቃቱን የፈጸመው፣ ጀልባዎቹ "የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን" ወደ አልሸባብ በማጓጓዝ ላይ እንደኾኑ ስለደረሰበት እንደኾነ ጠቅሷል። ፔንታጎን የጀልባዎቹን መነሻ ባይገልጽም፣ የየመን ኹቲዎች ለአልሸባብ የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን እንደሚልኩ ግን አሜሪካ ካሁን ቀደም መግለጧ አይዘነጋም። [ዋዜማ]
1፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ በገንዘብ እጥረት የተነሳ በኢትዮጵያ ለከፍተኛ ጉዳት ከተጋለጡ 3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ስዎች በጥቂት ሳምንታት ውስጥ የተመጣጠነና መደበኛ የምግብ ድጋፍ ሊቋረጥባቸው እንደሚችል አስጠንቅቋል። ከዚህ ውስጥ፣ 650 ሺሕዎቹ በተመጣጠነ ምግብ እጥረት የተጎዱ ሴቶችና ሕጻናት እንደኾኑ ድርጅቱ ገልጧል። በአገሪቱ ውስጥ ርሃብና ከፍተኛ የምግብ እጥረት በሕጻናት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩንና 10 ሚሊዮን ስዎች ለርሃብና ለተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንደተጋለጡ ድርጅቱ ጠቅሷል። ባጠቃላይ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ነፍሰ ጡሮችና ጡት አጥቢ እናቶች የተመጣጠነ የምግብ ድጋፍ ይፈልጋሉ፤ በትግራይ፣ ሱማሌ፣ ኦሮሚያና አፋር ክልሎች የሕጻናት መቀንጨር "አጣዳፊ" ከሚባለው 15 በመቶ አልፏል ተብሏል።
2፤ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ፣ የጅቡቲ መንግሥት በአገሪቱ ያለ ሕጋዊ ሰነድ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በፍቃደኝነት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የሠጠውን የጊዜ ገደብ እንዲያራዝም የኢትዮጵያ ኢምባሲ ያቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ኢምባሲው አስታውቋል። ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸው የውጭ ዜጎች በሙሉ ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 24 ከጅቡቲ እንዲወጡና ቀነ ገደቡ ካለፈ ግን በፖሊስ ተገደው እንደሚወጡ የአገሪቱ መንግስት ቀደም ሲል የጊዜ ገደብ አስቀምጧል። ኢምባሲው፣ ከአገሪቱ የአገር ውስጥ ደኅንነት ባለሥልጣናት ጋር ባደረገው ውይይት፣ ኢትዮጵያዊያኑ ብዛት ስላላቸው በቂ የዝግጅት ጊዜ እንዲያገኙ ቀነ ገደቡ በሦስት ወር እንዲራዘምላቸው ጠይቆ እንደነበር ጠቅሷል።
3፤ ምርጫ ቦርድ፣ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ "ምንም ዓይነት ጊዜያዊም ሆነ ቋሚ ሕጋዊ እውቅና" እና "የምዝገባ ፍቃድ" እንደሌለው ገልጧል። ቦርዱ፣ ሕጋዊ እውቅና ፍቃድ የተሠጠው በማስመሰል በተለያዩ መድረኮች "አሳሳች መግለጫ" እየሠጠ ይገኛል በማለት ከሷል፡፡ ፓርቲው ሕጋዊ እውቅና ለማግኘት መስፈርቶቹን እስካሁን እንዳላሟላ የጠቀሰው ቦርዱ፣ ፓርቲው ባኹኑ ወቅት የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች "ሕዝብን የሚያሳስቱ" እና "የሚያደናግሩ" ናቸው ብሏል።
4፤ በሱዳን የሚካሄደውን ጦርነት በመሸሽ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከገቡ ስደተኞች መካከል፣ ከ40 ሺሕ የሚበልጡትን ወደ አንድ መጠለያ የማስገባት ሥራ መከናወኑን መስማቱን ሸገር ዘግቧል። ወደ ክልሉ የገቡት ስደተኞችና ኢትዮጵያዊያን ተመላሾች በመጠለያ ጣቢያና በየሰው ቤት ማረፋቸውን የክልሉ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን መግለጹን ዘገባው ጠቅሷል። በተመድ መጠለያዎች የተጠለሉት ስደተኞች ከ40 ሺሕ በላይ እንደኾኑና ለእነዚህ ስደተኞች በየወሩ ምግብ ነክ ድጋፍ እንደሚቀርብላቸውም ኮሚሽኑ ተናግሯል ተብሏል።
5፤ የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በኢትዮጵያና ኬንያ ሊያደርጉት የነበረውን ይፋዊ ጉብኝት መሠረዛቸውን የፈረንሳዩ አፍሪካ ኢንተሌጀንስ ድረገጽ ዘግቧል። ሩቢዮ፣ በቅርቡ በጸጥታና ንግድ ዙሪያ ለመወያየት በናይሮቢ እና አዲስ አበባ ጉብኝት ለማድረግ ማቀዳቸውን የዜና ምንጩ ቀደም ሲል ዘግቦ ነበር። ሩቢዮ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ሊያደርጉት ያቀዱት ውይይት፣ ቻይና በኢትዮጵያ ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለመግታት ያለመ ጭምር እንደኾነም ዘገባው ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል።
6፤ የአሜሪካው ፔንታጎን፣ በሱማሊያ የባሕር ግዛት ውስጥ በኹለት ጀልባዎች ላይ ሚያዝያ 8 ቀን የአየር ጥቃት መፈጸሙን ዛሬ ባወጣው መረጃ ገልጧል። ፔንታጎን በጀልባዎቹ ላይ የአየር ጥቃቱን የፈጸመው፣ ጀልባዎቹ "የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን" ወደ አልሸባብ በማጓጓዝ ላይ እንደኾኑ ስለደረሰበት እንደኾነ ጠቅሷል። ፔንታጎን የጀልባዎቹን መነሻ ባይገልጽም፣ የየመን ኹቲዎች ለአልሸባብ የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን እንደሚልኩ ግን አሜሪካ ካሁን ቀደም መግለጧ አይዘነጋም። [ዋዜማ]
ለቸኮለ! ረቡዕ፣ ሚያዝያ 15/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት፣ በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ በግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት የቀዳሚነት ደረጃዋን በኬንያ እንደምትነጠቅ ተንብይዋል። የኢትዮጵያ ዓመታዊ ምርት 117 ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን የገለጠው ድርጅቱ፣ ባንጻሩ የኬንያ 132 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ብሏል። ባለፈው የፈረንጆች ዓመት የኢትዮጵያ አጠቃላይ ዓመታዊ ምርት 143 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን፣ የኬንያ ደሞ 121 ቢሊዮን ዶላር ደርሶ ነበር። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የምርት መጠን ወደ ሁለተኛ ደረጃ የሚወርደው፣ በገበያ-መሩ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ሳቢያ የብር ዋጋ በማሽቆልቆሉ እንደሆነ ድርጅቱ ጠቅሷል።
2፤ ጌታቸው ረዳ በአዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጀኔራል ታደሠ ወረደ ያቀረቡላቸውን የምስጋና የሽኝት መርሃ ግብር ውድቅ "ዩ ኤም ዲ" ለተባለ ጣቢያ በሠጡት ቃለ ምልልስ ላይ አስታውቀዋዋል። ጌታቸው፣ በትግራይ የተደረገው የሥልጣን ሽግግር የሕዝቡን ደኅንነትና ሕልውና አያስጠብቅም በማለት ተናግረዋል። የትግራይ ሕዝብ መልሶ ወደ ጦርነት እንዳይገባ የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉና የሕዝቡን የለውጥ ፍላጎት ወደኋላ የሚጎትት ማንኛውም እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንደማይኖረውም ጌታቸው ገልጸዋል። ጌታቸው፣ ትግራይ ውስጥ እሳቸውን ለመግደል የተሸረበ ሴራ እንደነበርም በድጋሚ ጠቅሰዋል።
3፤ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የጊዜ ቆይታ ላንድ ተጨማሪ ዓመት መራዘሙና አዲስ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት መሾማቸው፣ በክልሉ ያለውን ኹኔታ ይበልጥ አባባሰው እንጅ አላቃለለውም ብሏል። ፓርቲው፣ ዩጀኔራል ታደሠ ወረደ ካቢኔ ከአንድ የሕወሓት ክንፍ ብቻ የተውጣጣና ሌሎችን ባለድርሻዎች በሙሉ ያገለለ መሆኑን ገልጧል። አዲሱ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ገና ከመቋቋሙ፣ የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋትና ነጻ ምርጫ እንዲካሄድ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የተቋቋሙ ተቋማትን ማፍረስ ጀምሯል በማለት ፓርቲው ወቅሷል። አዲሱን ካቢኔ እንደማይቀበል የገለጠው ፓርቲው፣ ካቢኔው ይልቁንም ያንድ ፓርቲ የበላይነትንና አፈናን ያሰፍናል በማለት ስጋቱን ገልጧል።
4፤ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ለሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ያስፈልገኛል ብሏል። አስተዳደሩ፣ ሚያዚያ 20 ቀን ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ማሰናዳቱንም ገልጧል። በመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት የአጼ ፋሲል ቤተመንግስት እድሳትን ጨምሮ 1 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ወጪ መደረጉን ከንቲባው ቻላቸው ዳኛው ለዋዜማ ነግረዋታል። ከንቲባው፣ የቤተመንግሥቱን እደሳት ወጪ የሸፈነው ፌደራል መንግሥቱ እንደሆነ በመጥቀስ፣ የገንዘቡን መጠን ከመናገር ተቆጥበዋል። ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ከአጼ ቴወድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ፒያሳ አጼ ቴውድሮስ ሐውልት ድረስ ይሸፍናል ተብሏል። በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት፣ ለተነሺዎች ምትክ መኖሪያ ቤት እንደሚገነባላቸውም ከንቲባው ተናግረዋል።
5፤ ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ቡድን (ሲፒጄ)፣ ከአዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ቢሮና ከአንድ የመጽሄቱ ሠራተኛ መኖሪያ ቤት የሥራ ንብረቶችን መውሰዱና ሦስት የመጽሄቱን ሃላፊዎች ለሰዓታት ማሠሩ እንዳስደነገጠው አስታውቋል። ተቋሙ፣ ፖሊስ በወሰዳቸው የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ውስጥ የሚገኙ ከሥራ ጋር የተያያዙና የግል መረጃዎች አላግባብ ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ በማለት ስጋቱን ገልጧል። ፖሊስ የኤሌክትሮኖክስ መሳሪያዎቹን ባፋጣኝ እንዲመልስና በመጽሄቱ ላይ የጀመረውን ምርመራ እንዲያቋርጥም ሲፒጄ ጠይቋል። ስድስት የደንብ ልብስ ያልለበሱ ፖሊስ መኾናቸውን የገለጹ ግለሰቦች፣ ፖሊስ ሚያዝያ 9 ቀን የመጽሄቱን ቢሮ መበርበሩን፣ የዜናና የሰው ሃብት ሃላፊዎችን ለምርመራ ወደ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ወስዶ እንደነበር መስማቱንም ተቋሙ ጠውሷል።
6፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአፍሪካ ኅብረት የሱማሊያ ድጋፍ ሰጪና ማረጋጊያ ተልዕኮ ወታደሮችን ያዋጡ አገራት ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦችና ዲፕሎማቶች ሰሞኑን በካምፓላ ተሰብስበው ነበር። የኢትዮጵያ፣ የኬንያ፣ የጅቡቲ፣ የኡጋንዳ እና የግብጽ ተወካዮች በስብሰባው የተገኙ ሲኾን፣ የስብሰባው ዓላማም የተልዕኮውን ስኬቶችና ድክመቶች መገምገም፣ ለተልዕኮው የገንዘብ እጥረት መፍትሄ መፈለግና የተልዕኮውን የወደፊት ስትራቴጂ መንደፍ እንደሆነ ተገልጧል። ተልዕኮው፣ እስከ ቀጣዩ ሰኔ ድረስ የ90 ሚሊዮን ዶላር እጥረት እንደሚገጥመው ተነግሯል። ለተልዕኮው ወታደር ያዋጡ አገራት መሪዎች የካምፓላው ስብሰባ በሚያቀርብላቸው አጀንዳዎች ዙሪያ ለመምከርና ውሳኔ ለማሳለፍ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ይሰበሰባሉ ተብሏል።
7፤ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በመስሪያ ቤታቸው ሥር የሲቪሎችን ደኅንነት እንዲሁም የጸጥታ፣ የዲሞክራሲ፣ የሰብዓዊ መብቶችና ስደተኞች ጉዳዮችን የሚከታተሉ መምሪያዎችን እንደሚዘጉ ትናንት ይፋ አድርገዋል። ሩቢዮ፣ ቢሮዎቹ ወግ አጥባቂ የውጭ መንግሥታትን ለማጥቃት መሳሪያ ኾነው ሲያገለግል ቆይተዋል በማለት ወቅሰዋል። የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ጭምር እንደሚዘጋ ተዘግቦ የነበረ ቢሆንም፣ ሩቢዮ ትናንት ይፋ ባደረጉት እቅድ ላይ ግን ቢሮው አልተካተተም። የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር "ከልክ በላይ ተለጥጧል" ባለው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ሥር በጠቅላላው 100 ቢሮዎችን ለመዝጋት ወስኗል ተብሏል። [ዋዜማ]
1፤ ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት፣ በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ በግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት የቀዳሚነት ደረጃዋን በኬንያ እንደምትነጠቅ ተንብይዋል። የኢትዮጵያ ዓመታዊ ምርት 117 ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን የገለጠው ድርጅቱ፣ ባንጻሩ የኬንያ 132 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ብሏል። ባለፈው የፈረንጆች ዓመት የኢትዮጵያ አጠቃላይ ዓመታዊ ምርት 143 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን፣ የኬንያ ደሞ 121 ቢሊዮን ዶላር ደርሶ ነበር። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የምርት መጠን ወደ ሁለተኛ ደረጃ የሚወርደው፣ በገበያ-መሩ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ሳቢያ የብር ዋጋ በማሽቆልቆሉ እንደሆነ ድርጅቱ ጠቅሷል።
2፤ ጌታቸው ረዳ በአዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጀኔራል ታደሠ ወረደ ያቀረቡላቸውን የምስጋና የሽኝት መርሃ ግብር ውድቅ "ዩ ኤም ዲ" ለተባለ ጣቢያ በሠጡት ቃለ ምልልስ ላይ አስታውቀዋዋል። ጌታቸው፣ በትግራይ የተደረገው የሥልጣን ሽግግር የሕዝቡን ደኅንነትና ሕልውና አያስጠብቅም በማለት ተናግረዋል። የትግራይ ሕዝብ መልሶ ወደ ጦርነት እንዳይገባ የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉና የሕዝቡን የለውጥ ፍላጎት ወደኋላ የሚጎትት ማንኛውም እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንደማይኖረውም ጌታቸው ገልጸዋል። ጌታቸው፣ ትግራይ ውስጥ እሳቸውን ለመግደል የተሸረበ ሴራ እንደነበርም በድጋሚ ጠቅሰዋል።
3፤ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የጊዜ ቆይታ ላንድ ተጨማሪ ዓመት መራዘሙና አዲስ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት መሾማቸው፣ በክልሉ ያለውን ኹኔታ ይበልጥ አባባሰው እንጅ አላቃለለውም ብሏል። ፓርቲው፣ ዩጀኔራል ታደሠ ወረደ ካቢኔ ከአንድ የሕወሓት ክንፍ ብቻ የተውጣጣና ሌሎችን ባለድርሻዎች በሙሉ ያገለለ መሆኑን ገልጧል። አዲሱ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ገና ከመቋቋሙ፣ የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋትና ነጻ ምርጫ እንዲካሄድ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የተቋቋሙ ተቋማትን ማፍረስ ጀምሯል በማለት ፓርቲው ወቅሷል። አዲሱን ካቢኔ እንደማይቀበል የገለጠው ፓርቲው፣ ካቢኔው ይልቁንም ያንድ ፓርቲ የበላይነትንና አፈናን ያሰፍናል በማለት ስጋቱን ገልጧል።
4፤ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ለሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ያስፈልገኛል ብሏል። አስተዳደሩ፣ ሚያዚያ 20 ቀን ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ማሰናዳቱንም ገልጧል። በመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት የአጼ ፋሲል ቤተመንግስት እድሳትን ጨምሮ 1 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ወጪ መደረጉን ከንቲባው ቻላቸው ዳኛው ለዋዜማ ነግረዋታል። ከንቲባው፣ የቤተመንግሥቱን እደሳት ወጪ የሸፈነው ፌደራል መንግሥቱ እንደሆነ በመጥቀስ፣ የገንዘቡን መጠን ከመናገር ተቆጥበዋል። ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ከአጼ ቴወድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ፒያሳ አጼ ቴውድሮስ ሐውልት ድረስ ይሸፍናል ተብሏል። በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት፣ ለተነሺዎች ምትክ መኖሪያ ቤት እንደሚገነባላቸውም ከንቲባው ተናግረዋል።
5፤ ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ቡድን (ሲፒጄ)፣ ከአዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ቢሮና ከአንድ የመጽሄቱ ሠራተኛ መኖሪያ ቤት የሥራ ንብረቶችን መውሰዱና ሦስት የመጽሄቱን ሃላፊዎች ለሰዓታት ማሠሩ እንዳስደነገጠው አስታውቋል። ተቋሙ፣ ፖሊስ በወሰዳቸው የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ውስጥ የሚገኙ ከሥራ ጋር የተያያዙና የግል መረጃዎች አላግባብ ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ በማለት ስጋቱን ገልጧል። ፖሊስ የኤሌክትሮኖክስ መሳሪያዎቹን ባፋጣኝ እንዲመልስና በመጽሄቱ ላይ የጀመረውን ምርመራ እንዲያቋርጥም ሲፒጄ ጠይቋል። ስድስት የደንብ ልብስ ያልለበሱ ፖሊስ መኾናቸውን የገለጹ ግለሰቦች፣ ፖሊስ ሚያዝያ 9 ቀን የመጽሄቱን ቢሮ መበርበሩን፣ የዜናና የሰው ሃብት ሃላፊዎችን ለምርመራ ወደ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ወስዶ እንደነበር መስማቱንም ተቋሙ ጠውሷል።
6፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአፍሪካ ኅብረት የሱማሊያ ድጋፍ ሰጪና ማረጋጊያ ተልዕኮ ወታደሮችን ያዋጡ አገራት ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦችና ዲፕሎማቶች ሰሞኑን በካምፓላ ተሰብስበው ነበር። የኢትዮጵያ፣ የኬንያ፣ የጅቡቲ፣ የኡጋንዳ እና የግብጽ ተወካዮች በስብሰባው የተገኙ ሲኾን፣ የስብሰባው ዓላማም የተልዕኮውን ስኬቶችና ድክመቶች መገምገም፣ ለተልዕኮው የገንዘብ እጥረት መፍትሄ መፈለግና የተልዕኮውን የወደፊት ስትራቴጂ መንደፍ እንደሆነ ተገልጧል። ተልዕኮው፣ እስከ ቀጣዩ ሰኔ ድረስ የ90 ሚሊዮን ዶላር እጥረት እንደሚገጥመው ተነግሯል። ለተልዕኮው ወታደር ያዋጡ አገራት መሪዎች የካምፓላው ስብሰባ በሚያቀርብላቸው አጀንዳዎች ዙሪያ ለመምከርና ውሳኔ ለማሳለፍ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ይሰበሰባሉ ተብሏል።
7፤ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በመስሪያ ቤታቸው ሥር የሲቪሎችን ደኅንነት እንዲሁም የጸጥታ፣ የዲሞክራሲ፣ የሰብዓዊ መብቶችና ስደተኞች ጉዳዮችን የሚከታተሉ መምሪያዎችን እንደሚዘጉ ትናንት ይፋ አድርገዋል። ሩቢዮ፣ ቢሮዎቹ ወግ አጥባቂ የውጭ መንግሥታትን ለማጥቃት መሳሪያ ኾነው ሲያገለግል ቆይተዋል በማለት ወቅሰዋል። የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ጭምር እንደሚዘጋ ተዘግቦ የነበረ ቢሆንም፣ ሩቢዮ ትናንት ይፋ ባደረጉት እቅድ ላይ ግን ቢሮው አልተካተተም። የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር "ከልክ በላይ ተለጥጧል" ባለው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ሥር በጠቅላላው 100 ቢሮዎችን ለመዝጋት ወስኗል ተብሏል። [ዋዜማ]
ለቸኮለ፣ ዓርብ፣ ሚያዝያ 17/2017 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ኢትዮ ቴሌኮም፣ በሁለት ዙር በ10 ነጥብ 7 ሚሊዮን አክስዮኖች 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ አክሲዮኖችን መሸጡን ዛሬ በሠጠው መግለጫ አስታውቋል። በአክሲዮን ሽያጩ 47 ሺሕ 377 ኢትዮጵያዊያን መሳተፋቸውን ኩባንያው ገልጧል። ኢትዮ ቴሌኮም ለሽያጭ ያቀረበው፣ እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ነው። ኩባንያው ለኢትዮጵያዊን ይፋ ባደረገው የ10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ፣ ባንኮች፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊንና የተለያዩ ተቋማት ለመሳተፍ ጥያቄ ማቅረባቸውንም የኩባንያው ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ተናግረዋል።
2፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ፣ በትግራይ ድጋሚ ጦርነት የሚነሳበት ምክንያት እንደሌለ ትናንት ከአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው ስምምነት መከታተያና ማስከበሪያ ተልዕኮ ሃላፊ ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አሶዴ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ጄኔራል ታደሠ፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች ለፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተግባራዊነት ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በቅርበት እንደሚሠራ ለጀኔራል አሶዴ እንዳረጋገጡላቸው ዘገባው ጠውሷል። ባንዳንድ ወገኖች ዘንድ በትግራይ ሁለተኛ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት እንደነበር የተናገሩት ጀነራል ታደሠ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ትኩረት በማገገም፣ በመልሶ ግንባታና ተፈናቃዮችን በመመለስ ላይ ብቻ እንደሚኾን ለሃላፊው ነግረዋቸዋል ተብሏል።
3፤ በደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ክንፍ፣ የጌታቸው ረዳ ቡድን አሁንም የትግራይን ሕዝብ አንድነት ለመከፋፈል እየሠራ ይገኛል በማለት አዲስ ባወጣው መግለጫ ከሷል። የደብረጺዮን ቡድን፣ የጌታቸው ቡድን በመገናኛ ብዙኀን አማካኝነት በሕወሓት ላይ የስም ማጥፋት ድርጊቶችን የሚያሠራጨው በጫና ወደ ሥልጣን ለመመለስ በማሰብ ነው በማለት ወቅሷል። የጌታቸው ቡድን፣ "የዘር ማጥፋት ወንጀል" ፈጻሚዎችን ነጻ ለማስደረግና ባንጻሩ ሕወሓትን ተጠያቂ ለማድረግ ያለመታከት እየሠራ ይገኛል በማለት የደብረጺዮን የሕወሓት ክንፍ ክሱን አሰምቷል።
4፤ የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ አበበ ፍቅር በ10 ሺሕ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈታ የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት ዛሬ መወሰኑን ቢቢሲ ዘግቧል። ፖሊስ፣ ጋዜጠኛውን በቁጥጥር ሥር ያዋልኩት፣ "ሁከትና ረብሻ ለመፍጠር ሲንቀሳቀስ" ነው በማለት ለችሎቱ ማስረዳቱን ዘገባው ጠቅሷል። መርማሪ ፖሊስ፣ ጋዜጠኛው ፍቃድ ሳይሠጠው ወይም ጋዜጠኛ መኾኑን ሳያሳውቅ፣ በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ "ምስል ሲቀርጽ" እና "ፎቶ ሲያነሳ" በመገኘቱ ጭምር እንዳሠረው ለችሎቱ ተናግሯል ተብሏል። አበበ በክፍለ ከተማው ሥር በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ታስሮ እንደቆየ ሪፖርተር ትናንት ዘግቦ ነበር። አበበ ለዘገባ ሥራው፣ በአዲስ አበባ ከተማ የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሃላፊዎችን ለማነጋገር ረቡዕ'ለት በአስተዳደር ቅጥር ግቢ በተገኘበት ወቅት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንደዋለም ጋዜጣው መዘገቡ ይታወሳል።
5፤ የኢትዮጵያን ጨምሮ በሱማሊያ ለተሠማራው የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ ወታደሮችን ያዋጡ አገራት የመከላከያ ሚንስትሮች ዛሬም በተልዕኮው ዙሪያ ካምፓላ ውስጥ ሲመክሩ ውለዋል። ትናንት በተጀመረው በዚሁ ምክክር፣ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የኡጋንዳ፣ የኬንያ፣ የጅቡቲ፣ የግብጽ፣ የሱማሊያ መከላከያ ሚንስትሮችና የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮፓ ኅብረትና የተመድ ከፍተኛ ተወካዮች ተገኝተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ የሱፍ፣ የኅብረቱ ተልዕኮ ውድቀት እንዳይገጥመው ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ መተባበር እንዳለበት በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር ጥሪ አድርገዋል። ተልዕኮው ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ገጥሞታል ያሉት የሱፍ፣ የሱማሊያ ሰላምና መረጋጋት ለአፍሪካ ቀንድ ብቻ ሳይኾን ለዓለም ሰላም አስፈላጊ እንደኾነ ተናግረዋል። የመከላከያ ሚንስትሮች የውሳኔ ሃሳብ፣ ለተልዕኮው ተሳታፊ አገራት የመሪዎች ስብሰባ ይቀርባል።
6፤ ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሕጋዊ ሰነድ ሳይዙ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች እስከተያዘው ወር መጨረሻ በፍቃዳቸው እንዲወጡ ያዘዘችው፣ "በጸጥታ" እና "ጤና" ስጋት ሳቢያ እንደኾነ ተሠምቷል። የፕሬዝዳንት ኦማር ጌሌ አማካሪ አሌክሲስ ሞሐመድ፣ ጅቡቲ የዓለምን ድኅነት ልትሸከም አትችልም በማለት፣ የውሳኔውን ምክንያት መናገራቸው የፈረንሳይ የዜና ወኪል ዘግቧል። በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ኢትዮጵያዊያን በፍቃዳቸው ከአገሪቱ ለመውጣት ሦስት ተጨማሪ ወራት እንዲሠጣላቸው ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳላገኘ ከቀናት በፊት መግለጡ አይዘነጋም።
7፤ የሱማሊያ ፓርላማ የተፈጥሮ ሃብት ኮሚቴ፣ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከቱርክ ጋር የደረሰበትን የተፈጥሮ ጋዝ የማልማት ስምምነት ተቃውሟል። ኮሚቴው፣ ስምምነቱ ከመፈረሙ በፊት ፓርላማው እንዲያጸድቀው አልተደረገም በማለት ከሷል። ኮሚቴው ተቃውሞውን ያሠማው፣ ቱርክ ከምታለማው የሱማሊያ የተፈጥሮ ጋዝ ወጪዋን እስክትሸፍን ድረስ 90 በመቶውን እንድትወስድ መስማማቷን የሚገልጽ ሰነድ አፈትልኮ መውጣቱን ተከትሎ ነው። ስምምነቱ፣ የቱርክ ኩባንያዎች ለጋዝ ቁፋሮ ፍቃድ ለማግኘት መክፈል የሚጠበቅባቸውን ክፍያ የሚያስቀርና ቱርክ 90 በመቶ ድርሻዋን በዓለማቀፍ ዋጋ እንድትሸጥ የሚፈቅድ እንደኾነ ተገልጧል። በስምምነቱ መሠረት፣ የቱርክ መርከቦች ከቀጣዩ መስከረም ጀምሮ በሱማሊያ የባሕር ዳርቻ የጋዝ ቁፋሮ ይጀምራሉ ተብሏል። [ዋዜማ]
1፤ ኢትዮ ቴሌኮም፣ በሁለት ዙር በ10 ነጥብ 7 ሚሊዮን አክስዮኖች 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ አክሲዮኖችን መሸጡን ዛሬ በሠጠው መግለጫ አስታውቋል። በአክሲዮን ሽያጩ 47 ሺሕ 377 ኢትዮጵያዊያን መሳተፋቸውን ኩባንያው ገልጧል። ኢትዮ ቴሌኮም ለሽያጭ ያቀረበው፣ እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ነው። ኩባንያው ለኢትዮጵያዊን ይፋ ባደረገው የ10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ፣ ባንኮች፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊንና የተለያዩ ተቋማት ለመሳተፍ ጥያቄ ማቅረባቸውንም የኩባንያው ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ተናግረዋል።
2፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ፣ በትግራይ ድጋሚ ጦርነት የሚነሳበት ምክንያት እንደሌለ ትናንት ከአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው ስምምነት መከታተያና ማስከበሪያ ተልዕኮ ሃላፊ ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አሶዴ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ጄኔራል ታደሠ፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች ለፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተግባራዊነት ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በቅርበት እንደሚሠራ ለጀኔራል አሶዴ እንዳረጋገጡላቸው ዘገባው ጠውሷል። ባንዳንድ ወገኖች ዘንድ በትግራይ ሁለተኛ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት እንደነበር የተናገሩት ጀነራል ታደሠ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ትኩረት በማገገም፣ በመልሶ ግንባታና ተፈናቃዮችን በመመለስ ላይ ብቻ እንደሚኾን ለሃላፊው ነግረዋቸዋል ተብሏል።
3፤ በደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ክንፍ፣ የጌታቸው ረዳ ቡድን አሁንም የትግራይን ሕዝብ አንድነት ለመከፋፈል እየሠራ ይገኛል በማለት አዲስ ባወጣው መግለጫ ከሷል። የደብረጺዮን ቡድን፣ የጌታቸው ቡድን በመገናኛ ብዙኀን አማካኝነት በሕወሓት ላይ የስም ማጥፋት ድርጊቶችን የሚያሠራጨው በጫና ወደ ሥልጣን ለመመለስ በማሰብ ነው በማለት ወቅሷል። የጌታቸው ቡድን፣ "የዘር ማጥፋት ወንጀል" ፈጻሚዎችን ነጻ ለማስደረግና ባንጻሩ ሕወሓትን ተጠያቂ ለማድረግ ያለመታከት እየሠራ ይገኛል በማለት የደብረጺዮን የሕወሓት ክንፍ ክሱን አሰምቷል።
4፤ የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ አበበ ፍቅር በ10 ሺሕ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈታ የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት ዛሬ መወሰኑን ቢቢሲ ዘግቧል። ፖሊስ፣ ጋዜጠኛውን በቁጥጥር ሥር ያዋልኩት፣ "ሁከትና ረብሻ ለመፍጠር ሲንቀሳቀስ" ነው በማለት ለችሎቱ ማስረዳቱን ዘገባው ጠቅሷል። መርማሪ ፖሊስ፣ ጋዜጠኛው ፍቃድ ሳይሠጠው ወይም ጋዜጠኛ መኾኑን ሳያሳውቅ፣ በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ "ምስል ሲቀርጽ" እና "ፎቶ ሲያነሳ" በመገኘቱ ጭምር እንዳሠረው ለችሎቱ ተናግሯል ተብሏል። አበበ በክፍለ ከተማው ሥር በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ታስሮ እንደቆየ ሪፖርተር ትናንት ዘግቦ ነበር። አበበ ለዘገባ ሥራው፣ በአዲስ አበባ ከተማ የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሃላፊዎችን ለማነጋገር ረቡዕ'ለት በአስተዳደር ቅጥር ግቢ በተገኘበት ወቅት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንደዋለም ጋዜጣው መዘገቡ ይታወሳል።
5፤ የኢትዮጵያን ጨምሮ በሱማሊያ ለተሠማራው የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ ወታደሮችን ያዋጡ አገራት የመከላከያ ሚንስትሮች ዛሬም በተልዕኮው ዙሪያ ካምፓላ ውስጥ ሲመክሩ ውለዋል። ትናንት በተጀመረው በዚሁ ምክክር፣ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የኡጋንዳ፣ የኬንያ፣ የጅቡቲ፣ የግብጽ፣ የሱማሊያ መከላከያ ሚንስትሮችና የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮፓ ኅብረትና የተመድ ከፍተኛ ተወካዮች ተገኝተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ የሱፍ፣ የኅብረቱ ተልዕኮ ውድቀት እንዳይገጥመው ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ መተባበር እንዳለበት በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር ጥሪ አድርገዋል። ተልዕኮው ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ገጥሞታል ያሉት የሱፍ፣ የሱማሊያ ሰላምና መረጋጋት ለአፍሪካ ቀንድ ብቻ ሳይኾን ለዓለም ሰላም አስፈላጊ እንደኾነ ተናግረዋል። የመከላከያ ሚንስትሮች የውሳኔ ሃሳብ፣ ለተልዕኮው ተሳታፊ አገራት የመሪዎች ስብሰባ ይቀርባል።
6፤ ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሕጋዊ ሰነድ ሳይዙ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች እስከተያዘው ወር መጨረሻ በፍቃዳቸው እንዲወጡ ያዘዘችው፣ "በጸጥታ" እና "ጤና" ስጋት ሳቢያ እንደኾነ ተሠምቷል። የፕሬዝዳንት ኦማር ጌሌ አማካሪ አሌክሲስ ሞሐመድ፣ ጅቡቲ የዓለምን ድኅነት ልትሸከም አትችልም በማለት፣ የውሳኔውን ምክንያት መናገራቸው የፈረንሳይ የዜና ወኪል ዘግቧል። በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ኢትዮጵያዊያን በፍቃዳቸው ከአገሪቱ ለመውጣት ሦስት ተጨማሪ ወራት እንዲሠጣላቸው ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳላገኘ ከቀናት በፊት መግለጡ አይዘነጋም።
7፤ የሱማሊያ ፓርላማ የተፈጥሮ ሃብት ኮሚቴ፣ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከቱርክ ጋር የደረሰበትን የተፈጥሮ ጋዝ የማልማት ስምምነት ተቃውሟል። ኮሚቴው፣ ስምምነቱ ከመፈረሙ በፊት ፓርላማው እንዲያጸድቀው አልተደረገም በማለት ከሷል። ኮሚቴው ተቃውሞውን ያሠማው፣ ቱርክ ከምታለማው የሱማሊያ የተፈጥሮ ጋዝ ወጪዋን እስክትሸፍን ድረስ 90 በመቶውን እንድትወስድ መስማማቷን የሚገልጽ ሰነድ አፈትልኮ መውጣቱን ተከትሎ ነው። ስምምነቱ፣ የቱርክ ኩባንያዎች ለጋዝ ቁፋሮ ፍቃድ ለማግኘት መክፈል የሚጠበቅባቸውን ክፍያ የሚያስቀርና ቱርክ 90 በመቶ ድርሻዋን በዓለማቀፍ ዋጋ እንድትሸጥ የሚፈቅድ እንደኾነ ተገልጧል። በስምምነቱ መሠረት፣ የቱርክ መርከቦች ከቀጣዩ መስከረም ጀምሮ በሱማሊያ የባሕር ዳርቻ የጋዝ ቁፋሮ ይጀምራሉ ተብሏል። [ዋዜማ]