ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
38.3K subscribers
64 photos
50 videos
19 files
1.66K links
ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ሞናርኪያውያን

ክፍል ሁለት

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥14 ከእነዚያም "እኛ ነሷራ ነን" ካሉት የጠበቀ ቃል ኪዳናቸውን ያዝን፡፡ በእርሱም ከታዘዙበት ነገር ፈንታን ተውት፡፡ وَمِنَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّا نَصَارَىٰ أَخَذْنَا مِيثَاقَهُمْ فَنَسُوا حَظًّا مِّمَّا ذُكِّرُوا بِهِ فَأَغْرَيْنَا

የኢየሱስ ቀዳማይ ተከታዮች ሐዋርያት ሙሥሊሞች ነበሩ፦
3፥52 ዒሣ ከእነርሱ ክህደት በተሰማውም ጊዜ፡- «ወደ አሏህ ረዳቶቼ እነማን ናቸው?» አለ፥ ሐዋርያትም፡- «እኛ የአሏህ ረዳቶች ነን፤ በአሏህ አምነናል፥ እኛም ትክክለኛ ታዛዦች መኾናችንን መስክር» አሉ፡፡ فَلَمَّآ أَحَسَّ عِيسَىٰ مِنْهُمُ ٱلْكُفْرَ قَالَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ قَالَ ٱلْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ ٱللَّهِ ءَامَنَّا بِٱللَّهِ وَٱشْهَدْ بِأَنَّا مُسْلِمُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚል የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُسْلِمُون ሲሆን "ሙሥሊም" مُسْلِم ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "ነሲር" نَصِير ማለት "ረዳት" ማለት ሲሆን የነሲር ብዙ ቁጥር ደግሞ "አንሷር" أَنصَار ነው። "ነስራኒይ" نَصْرَانِيّ ገላጭ ቅጽል ሲሆን "ረዳት" ማለት ነው፥ የነስራኒይ ብዙ ቁጥር "ነሷራ" نَصَارَىٰ ሲሆን "ረዳቶች" ማለት ነው፦
5፥14 ከእነዚያም "እኛ ነሷራ ነን" ካሉት የጠበቀ ቃል ኪዳናቸውን ያዝን፡፡ በእርሱም ከታዘዙበት ነገር ፈንታን ተውት፡፡ وَمِنَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّا نَصَارَىٰ أَخَذْنَا مِيثَاقَهُمْ فَنَسُوا حَظًّا مِّمَّا ذُكِّرُوا بِهِ فَأَغْرَيْنَا

አምላካችን አሏህ "እኛ የአሏህ ረዳቶች ነን" ካሉት ከሐዋርያት ጋር የያዘው የጠበቀ ቃል ኪዳን «በእኔ እና በመልእክተኛዬ እመኑ» የሚል ነው፥ እነርሱም "አመንን፥ እኛ ሙሥሊሞች መኾናችንን መስክር" አሉ፦
5፥111 ወደ ሐዋርያትም «በእኔ እና በመልእክተኛዬ እመኑ» በማለት ባዘዝኩ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ أَوْحَيْتُ إِلَى الْحَوَارِيِّينَ أَنْ آمِنُوا بِي وَبِرَسُولِي
5፥111 «አመንን፥ እኛ ሙሥሊሞች መኾናችንን መስክር» አሉ፡፡ قَالُوا آمَنَّا وَاشْهَدْ بِأَنَّنَا مُسْلِمُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሙሥሊሞች" ለሚል የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُسْلِمُون መሆኑን ልብ አድርግ! ነገር ግን ከሐዋርያት ኅልፈት በኃላ የተነሱት ሰዎች የታዘዙበትን ተውሒድ ተውት፥ በአሏህ ላይ ወሰን አልፈው አምላክን "አንድም ሦስትም ነው" በማለት አስተማሩ።
ከ 180 እስከ 313 ድኅረ ልደት በዓለም ዐቀፍ ደረጃ "ታላቂቱ ቤተክርስቲያን"Great Church" ተብላ በሮም መንግሥት መቀመጫ ያደረገች ታላቂቱ ቤተክርስቲያን በአበው ተዋቅራ ተደራጀች፥ ይህቺ ሴት በሮም መንግሥት ላይ ተቀምጣ በቅዱሳን ደም እና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ ታይታለች፦
ራእይ 17፥6 ሴቲቱም በቅዱሳን ደም እና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ አየኋት።

በታሪክ ውስጥ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የሚለውን ታላቁን እና ፊተኛውን የአምላክ ትእዛዝ የሚጠብቁትን የኢየሱስ ምስክር ያላቸው አሐዳውያንን ቤተ ክርስቲያን ደማቸውን በማፍሰስ ገላለች።
በ 200 እስከ 275 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረውን ጳውሎስ ዘሳምሳጢ"Paul of Samosata" የሳምሳጢ ኤጲስቆጶስ በግዝት እና በግዞት አሰቃይታለች። ሞናርኪያውያን "ኢየሱስ በምንነት ሰው ብቻ ነው፣ ምንነቱ ከማርያም ይጀምራል፣ ከማርያም በፊት በቃል ደረጃ እንጂ በህልውና የለም። በማንነቱ ነቢይ፣ መልእክተኛ፣ መሢሕ ነው፥ የአብ ልጅ የተባለው በግብር እንጂ በባሕርይ ስላልሆነ ልጅነቱ የማደጎ ልጅነት"Adoption" ነው" የሚል አቋም ነበራቸው፦
2ኛ ሳሙኤል 7፥12 ከወገብህ የሚወጣውን ዘርህን ከአንተ በኋላ አስነሣለሁ፥
2ኛ ሳሙኤል 7፥14 እኔም አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል።

ከወገብ የሚወጣ ዘር ፍጡር ነው፥ ከወገብ ለሚወጣ ዘር አምላክ "አባት እሆነዋለሁ" ሲል የሚወጣው ዘር ደግሞ "ልጅ ይሆነኛል" ስላለ ልጅነቱ የማደጎ ልጅነት የሚል አቋም አላቸው። እነዚህ ሞናርኪያውያን "ጠንካራ ሞናርኪያውያን"dynamic monarchian" ሲባሉ ነገር ግን በ 260 ድኅረ ልደት ሰባልስዮስ ዘሊቢያ"Sabellius of Libya" ሞናርኪያ የነበረ ሲሆን ሮም ሄዶ ከተማረ በኃላ "ኩነት"mode of existence" የተባለውን ትምህርት አስተማረ፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 5 ቁጥር 4
"ሰብልያኖስ "አብ እንደ ሰው፣ ወልድ እንደ አንደበቱ ንግግር፣ መንፈስ ቅዱስ እንደ አፉ እስትንፋስ ናቸው" አለ። ስለዚህ አንድ ገጽ ናቸው" አለ።

"አንድ ሰው አንድ ገጽ(ማንነት) ኖሮት ዋናው ልብ ሲኖረው ከልቡ ቃል እና ከአፉ እስትንፋስ እንደሚወጣ አንድ አምላክ አብ ከራሱ የሚወጣ ቃል ወልድ እስትንፋሱ መንፈስ ቅዱስ ይባላል" የሚል አቋም ያላቸው የሰባልዮስ ተከታዮች "ኩነታዊ ሞናርኪያውያን"Modalistic monarchian" ይባላሉ። ሰባልዮስ ይህንን አቋም ሊያራምድ የቻለው ሮም ውስጥ "አማልክት ከአንዱ አምላክ "ብናኝ"Aeon" እየሆኑ ይወጣሉ" የሚል የኤዎን እሳቤ አዙሮት ነው። ይህ የመኳኳን ኩነት አብን ካርዲያስ ምንጭ፣ ወልድን ሎጎስ፣ መንፈስ ቅዱስን ኑውማቶስ በማድረግ ተኳኩነት"Modalism" ነው፥ "ካርዲያስ" καρδίας ማለት "ልብ" ማለት ነው፣ "ሎጎስ" λόγος ማለት "ቃል" ማለት ነው፣ "ኑውማቶስ" ማለት "እስትንፋስ" ማለት ነው።
ሰባልዮስ በማመስጠር እና በማመናፈስ "የኢየሱስ መለኮት አብ፣ ቃሉ ወልድ፣ እስትንፋሱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ ይሁዳ 1፥4 በተሳሳተ መልኩ በመጥቀስ "ኢየሱስ ብቻ"only Jesus" በማለት ይናገር ነበር፦
ይሁዳ 1፥4 ብቻውን ያለውን ጌታ እና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ። καὶ τὸν μόνον Δεσπότην καὶ Κύριον ἡμῶν Ἰησοῦν Χριστὸν ἀρνούμενοι.

"ዴስፖቴስ" δεσπότης ማለት "ጌታ" ማለት ሲሆን በግሪክ ሰፕቱአጀንት "ያህዌህ" יְהוָ֣ה የሚለው ቴትራግራማቶን ተክቶ የመጣ ነው፥ ለዚያ ነው "ብቻውን ያለውን ጌታ" የተባለው ኢየሱስ ስላልሆነ ኮዴክስ ቤዛይ ላይ፦ "ብቻውን ያለውን ጌታ አምላክ" በማለት አብ ለማመልከት የተቀመጠው፦
ይሁዳ 1፥4 ብቻውን ያለውን ጌታ አምላክ እና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ። καὶ τὸν μόνον δεσπότην θεὸν καὶ κύριον ἡμῶν Ἰησοῦν χριστὸν ἀρνούμενοι.

"ቴዎን" θεὸν የሚለውን ቃል አትለፉት! ለዚያ ነው በ 1611 ድኅረ ልደት በታተመው ቅጂ The King James Version (KJV) ላይ "and denying the only Lord God, and our Lord Jesus Christ" ብለው ያስቀመጡት። "ዴስፖቴን ቴዎን" δεσπότην θεὸν እና "ኩርዮን ቶን ቴዎን" ማለት "ጌታ አምላክ" ማለት ሲሆን "ያህዌህ ኤሎሂም" የሚለውን ተክቶ የመጣ ነው።
ለሥላሴ ትምህርት መሠረት የጣለው የሰባልዮስ የኩነት ትምህርት ነው፥ ሥላሴ ማለት "አምላክ በአካል ሦስት ሲሆን በኑባሬ አንድ ነው" ማለት ሲሆን ይህ ትምህርት የግሪኩ ፈላስፋ የአፍላጦን"plato" ትምህርት ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 97 ቁጥር 7
"ዳግመኛም አፍአዊ አፍላጦን ስለ መለኮት የመለኮትን ምሥጢር ወደ ጢሞቴዎስ ጻፈ፦ "እግዚአብሔር በሦስት ስም በሦስት አካላት እንዳለ ይታወቃል፥ የጌትነት ሥልጣን በሦስቱ ያለ ነው፥ መጀመሪያ ጥንት ለሁሉ የሚራራ (አብ) ነው፣ ሁለተኛ ጥንት ሁሉን የፈጠረ ዕውቀት (ወልድ) ነው፣ ሦስተኛ ጥንት ለሁሉ ሕይወትን የሚያድል ነፍሳትን የሚያድን (መንፈስ ቅዱስ) ነው። ለእነዚህ (ለሦስቱ) የሚታወቁበት የአምላክነት ኃይል አላቸው"።

በቅንፍ ያስቀመጥኩት በግዕዙ ላይ ስለሌለ ነው። "አፍአዊ" ማለት "አንደበተ ርቱዕ" ማለት ሲሆን አፍላጦን የኖረው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ 427 እስከ 348 ነው፥ ለዚህ ነው "ሥላሴ ሐዋርያት እና ነቢያት ያላስተማሩት አፍላጦአዊ ፍልስፍና ነው" የምንለው። ከታዘዙት ፈንታ በመተዋቸው እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በመካከላቸው ጠብ እና ጥላቻ መኖሩ የአሏህ ቅጣት ነው፦
5፥14 ስለዚህ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በመካከላቸው ጠብን እና ጥላቻን ጣልንባቸው፡፡ አሏህም ይሠሩት የነበሩትን ሁሉ በእርግጥ ይነግራቸዋል፡፡ بَيْنَهُمُ الْعَدَاوَةَ وَالْبَغْضَاءَ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۚ وَسَوْفَ يُنَبِّئُهُمُ اللَّهُ بِمَا كَانُوا يَصْنَعُونَ

አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
እንቁጣጣሽ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

57፥3 ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ

“ጳጉሜ” የሚለው ቃል “ኤፓጎሜኖይ” ἐπαγόμενοι ከሚለው ከግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ “ተጨማሪ” ወይም “የተጨመረ” ማለት ነው፥ ጳጉሜ የወር ስም ሲሆን በነባሮች 12 ወራት ላይ የተጨመረ 13ኛ ወር ነው። ይህም ወር በነሐሴ እና በመስከረም መካከል የሚገኝ የመጨረሻው ወር ነው፥ ጳጉሜ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በዘመነ ሉቃስ ስድስት ቀናት ሲኖሩር በዘመነ ዮሐንስ፣ በዘመነ ማቴዎስ እና በዘመነ ማርቆስ አምስት ቀናት ይሆናል። ልብ በሉ! ይህ ወር ከግሪክ ሄለኒዝም የተጀመረ እና ከአሌክሳንድርያ ወደ ኢትዮጵያ የገባ እንጂ በዕብራውያን አቆጣጠር ላይ ወራት 12 ብቻ ናቸው። አምላካችን አሏህ የወሮች ቁጥር በእርሱ መጽሐፍ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር እንደሆነ ነግሮናል፦
9፥36 አላህ ዘንድ የወሮች ቁጥር በአሏህ መጽሐፍ ዉስጥ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው። إِنَّ عِدَّةَ ٱلشُّهُورِ عِندَ ٱللَّهِ ٱثْنَا عَشَرَ شَهْرًۭا فِى كِتَٰبِ ٱللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ

ይህ የሚያሳየው የኢትዮጵያው ዘመን መለወጫ በልምድ ከግሪክ የመጣ ሰርጎገብ እንጂ አገር በቀል አይደለም፥ ከዚያም ባሻገር መለኮታዊ ትእዛዝ ያለው ሳይሆን ሰው ሠራሽ ቢድዓህ ነው። ዓመተ ምሕረትን ያማከለ ዘመነ ሉቃስ፣ ዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ሰው ሠራሽ ሃይማኖታዊ አስተምህሮት ነው፥ በዛ ላይ የባዕድ አምልኮ የሚፈፀምበት ቀን ነው። በጳጉሜ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ፥ በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ ጌጦች እና የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ።

ይህ ቀን ሲያልቅ የቀኑ መጨረሻ ተጓግቶ ስለሚመጣ “እንቁ” ተባለ፥ የሚያመጣው ጣጣና መዘዝ ደግሞ “ጣጣሽ” ተባለ። በጥቅሉ “እንቁ ጣጣሽ” ተባለ፥ ጥንቆላና ድግምት ከትልቁ ሽርክ የሚመደቡ የአሏህን ሐቅ የሚነካ ትልቅ በደል ነው። እንቁጣጣሽን ማክበር አቆጣጠሩ አገራዊ ሳይሆን እምነታዊ መሠረት ያለው ሲሆን ከእርሱ ጋር የተያያዙት ባዕድ አምልኮ አስበን ከዚህ ሰው ሠራሽ በዓል እራሳችንን እንጠብቅ! እንግዲህ እንቁጣጣሽ ዓመታዊ በዓል ዓረማዊ እና ክርስትናን ቀላቅሎ የያዘ በዓል ነው፥ በዚህ ጊዜ "እንኳን አደረስን" ወይም "እንኳን አደረሳችሁ" ሲባል ይህንን በዓል ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ሙሥሊም ያሉት ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻ እና ብቻ ናቸው፥ እነርሱም ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦
ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 745
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” መዲና ሲገቡ የመዲና ሠዎች የሚደሰቱባቸው ሁለት በዓላት እንዳሏቸው ዐወቁ። እርሳቸውም፦ "እነዚህ ሁለቱ ቀናት ምንድን ናቸው? በማለት ጠየቁ፥ "ሰዎችም በጃሂሊያ ጊዜ እንጫወትባቸው የነበሩ በዓላት ናቸው አሏቸው። የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ ”አሏህ ከእነርሱ የተሻሉ ሁለት ዒዶችን ሠጥቷችኋል፥ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓን አሏቸው”። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ قَدِمَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْمَدِينَةَ وَلَهُمْ يَوْمَانِ يَلْعَبُونَ فِيهِمَا فَقَالَ ‏”‏ مَا هَذَانِ الْيَوْمَانِ ‏”‏ ‏.‏ قَالُوا كُنَّا نَلْعَبُ فِيهِمَا فِي الْجَاهِلِيَّةِ ‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ إِنَّ اللَّهَ قَدْ أَبْدَلَكُمْ بِهِمَا خَيْرًا مِنْهُمَا يَوْمَ الأَضْحَى وَيَوْمَ الْفِطْرِ ‏”‏ ‏.‏
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፥ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው”። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 91
አቡ ሰዒደል ኹድሪይ እንደተረከው፥ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” ”በሁለቱ በዓል በዒደል አደሐ እና ዒደል ፈጥር መጾም ከልክለዋል”። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، قَالَ نَهَى رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنْ صِيَامَيْنِ يَوْمِ الأَضْحَى وَيَوْمِ الْفِطْرِ ‏.

“ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። ስለዚህ ከአላህ የወረዱትን ቁርኣን እና ሐዲስ ብቻ ከተከተልን ሁለት በዓል ብቻ እና ብቻ አለን፦
7፥3 ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ

“ተከተሉ” የሚለው ቃል “ኢተቢዑ” اتَّبِعُوا ሲሆን “ኢትባዕ” إِتْبَاع‎ ማለት እራሱ የቢድዓህ ተቃራኒ "ከአሏህ ወደ ነቢያችን”ﷺ” የተወረደውን ብቻ መከተል" ማለት ነው። "ቢድዓህ" بِدْعَة የሚለው ቃል "በደዐ" بَدَعَ ማለትም "ፈጠረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ፈጠራ” ማለት ነው፥ ቁርኣን እና ሐዲስ ላይ የሌለ ነገር በዲን ላይ መጨመር "ቢድዓህ" ሲሆን ሙሥሊም ግን የተወረደውን ብቻ ሲከተል ሁለት ዒድ ብቻ እና ብቻ ያከብራል። ስለዚህ "እንቁጣጣሽ" ስንባል "እንኳን ደህና መጣሽ" ከማለት ይልቅ "ማን አመጣሽ?" ብለህ በታሪካዊ ዳራ እና ፍሰት እንሞግታለን። በዓሉን ባለማወቅ ለሚያከብሩ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
እንቁጣጣሽ
በኦሮሚኛ
https://t.me/Wahidomar1/81

በትግሪኛ
https://t.me/wahidtigriga/40

ጉራጊኛ
https://t.me/wahidcomguragiga/50

በሲዳምኛ
https://t.me/wahidcomsidamo/58

በስልጢኛ
https://t.me/wahidcomselitiy/33

ተለቋል። የቋንቋው ባለቤቶች አንብቡ አስነብቡ!
አረጋግጡ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

49፥6 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነገረኛ ወሬን ቢያመጣላችሁ በስህተት ላይ ኾናችሁ ሕዝቦችን እንዳትጎዱ እና በሠራችሁት ነገር ላይ ተጸጻቾች እንዳትኾኑ አረጋግጡ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِن جَاءَكُمْ فَاسِقٌ بِنَبَإٍ فَتَبَيَّنُوا أَن تُصِيبُوا قَوْمًا بِجَهَالَةٍ فَتُصْبِحُوا عَلَىٰ مَا فَعَلْتُمْ نَادِمِينَ

ለፍቶ አዳሪ እና ሠርቶ አዳሪ ከመሆን ይልቅ ነጥቆ አዳሪ እና አውርቶ አዳሪ የሆኑት የሚድያ ጡረተኞች ወሬን ሳያረጋግጡ ሾላ በድፍኑ ሊቦተረፉ ማየት የተለመደ ጉዳይ እየሆነ መጥቶአል፥ አበው "እፍ ብለህ ታነዳለህ እፍ ብለህ ታጠፋለህ" በሚል አገርኛ ብሒላቸው ሚድያን ለአሉታዊ ነገር የሚጠቀሙ ተንኮለኛ ሰዎች እንዳሉ ሁሉ በተቃራኒው ለአውንታዊ ነገር የሚጠቀሙ ቅን ሰዎች አሉ። የሚድያ ጡረተኞች የሚያመጡትን ወሬ ባተሎ እና ተላላ ሆኖ ከማራገብ ይልቅ ማረጋገጡ አምላካዊ ትእዛዝ ነው፦
49፥6 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነገረኛ ወሬን ቢያመጣላችሁ በስህተት ላይ ኾናችሁ ሕዝቦችን እንዳትጎዱ እና በሠራችሁት ነገር ላይ ተጸጻቾች እንዳትኾኑ አረጋግጡ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِن جَاءَكُمْ فَاسِقٌ بِنَبَإٍ فَتَبَيَّنُوا أَن تُصِيبُوا قَوْمًا بِجَهَالَةٍ فَتُصْبِحُوا عَلَىٰ مَا فَعَلْتُمْ نَادِمِينَ

"ነበእ" نَبَأ ማለት "መረጃ"information" ሲሆን የሚመጣልንን መረጃ ከማረጋገጥ ይልቅ ቸኩለን ያለ ዕውቀት እና ያለ ማስረጃ መናገር ትርፉ ሰውን መጉዳት እና የሕሊና ጸጸት ነው። እውነተኛ ሰው በማስረጃ ያረጋግጣል፦
2፥111 «እውነተኞች እንደኾናችሁ ማስረጃችሁን አምጡ» በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ

"ቡርሃን" بُرْهَان ማለት "ማስረጃ"evidence" ማለት ሲሆን አንድን መረጃ እውነት ወይም ሐሰት መሆኑን ለማረጋገጥ "ማስረጃ" ጉልህ እማኝ እና ዋቢ ነው። እውነተኛ ሰው በተጨማሪ በዕውቀት ያረጋግጣል፦
6፥143 «እውነተኞች እንደሆናችሁ በዕውቀት ንገሩኝ» በላቸው፡፡ نَبِّئُونِي بِعِلْمٍ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 229
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ ”ዕውቀት መፈለግ በሁሉም ሙሥሊም ላይ ግዴታ ነው”። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ طَلَبُ الْعِلْمِ فَرِيضَةٌ عَلَى كُلِّ مُسْلِمٍ

ያለ ዕውቀት አንድን ነገር በነሲብ፣ በጭፍን እና በደንዳናነት መከተል አይፈቀድም። ያለዚያ የፍርዱ ቀን ጭፍኑ ሰው ከጆሮ፣ ከዓይን እና ከልብ ተጠያቂ ነው፦
17፥36 ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል! መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ ተጠያቂ ነውና፡፡ وَلَا تَقْفُ مَا لَيْسَ لَكَ بِهِ عِلْمٌ ۚ إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَـٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا

ቅጥፈታዊ መረጃ እንደ ትቢያ በኖ እንደ ጢስ ተኖ የሚጠፋው እውነተኛ ሰው በማስረጃ እና በዕውቀት ሲያረጋግጥ ነው። ስለዚህ አንድ ነገር ከሚድያ ጡረተኞች ስንሰማ በመቸኮል አጀንዳ አርገን ከማራገብ ይልቅ ተረጋግተን በማስረጃ እና በዕውቀት መፈተሽ አለብን! መረጋጋት ከአሏህ ነው፥ ችኮላ ከሸይጧን ነው፦
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27 ሐዲስ 118
ጀዳህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "መረጋጋት ከአሏህ ነው፥ ችኮላ ከሸይጧን ነው"። عَنْ جَدِّهِ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ الأَنَاةُ مِنَ اللَّهِ وَالْعَجَلَةُ مِنَ الشَّيْطَانِ ‏"‏

ኢማም አሥ ሡዩጢይ ሠነዱን ሐሠን ብለውታል። መቸኮላችን ዋጋ እያስከፈለን ነው፥ ሰው እስከ ማስገደል ድረስ ወንጀል የሚያሠራው ይህ ችኮላ ነው። በዕውቀት እና በማስረጃ እስከምናረጋግጥ ድረስ ዝም ማለቱ ነጻ ያወጣል፦
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 37 ሐዲስ 87
ዐብደላህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ዝም ያለ ነጻ ሆነ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم "‏ مَنْ صَمَتَ نَجَا ‏"‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1 ሐዲስ 80
አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን መልካም ይናገር ወይም ዝም ይበል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ مَنْ كَانَ يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الآخِرِ فَلْيَقُلْ خَيْرًا أَوْ لِيَصْمُتْ

የምእመናን አርአያ እና የሥነ ምግባር ባለቤት የሆኑት ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" "በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን መልካም ይናገር ወይም ዝም ይበል" ብለው በአጽንዖት እና በአንክሮት ዘክረውናል። አምላካችን አሏህ ሰውን ከመጉዳት እና ከሕሊና ጸጸት ይጠብቀን! ተረጋግተው በማስረጃ እና በዕውቀት ከሚያረጋግጡት ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ተጸጸተ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

65፥11 አላህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ

አምላካችን አሏህ ሁሉንም "ነገር" ዐዋቂ ነው፥ "ሸይእ" شَيْء ማለት "ነገር" ማለት ሲሆን ይህም ነገር አጠቃላይ ፍጥረትን ሁሉ ያጠቃልላል፦
65፥11 አላህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ

አሏህ አንድ ነገር ከመከሰቱ፣ ከመሆኑ፣ ከመደረጉ፣ ከመከናወኑ በፊት ያለውን ሩቅ ነገር እና አንድ ነገር ከተከሰተ፣ ከሆነ፣ ከተደረገ፣ ከተከናወነ በኃላ ያለውን ግልጹን ነገር ሁሉ ዐዋቂ ነው፦
64፥18 ሩቁን ነገር ግልጹንም ሁሉ ዐዋቂው አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ عَالِمُ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ الْعَزِيزُ الْحَكِيمُ

"አማሬ ኲሉ" ማለት "ሁሉን ዐዋቂ" ማለት ነው፥ መለኮት "ሁሉን ዐዋቂ" ነው። በባይብል አንዱ አምላክ "ሁሉን ዐዋቂ" ነው፦
1 ዮሐንስ 3፥20 አምላክ ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና "ሁሉንም ያውቃል"። ὅτι μείζων ἐστὶν ὁ Θεὸς τῆς καρδίας ἡμῶν καὶ γινώσκει πάντα.

ቅሉ ግን አንድ ማንነት በሠራው ሥራ ከተጸጸተ ያንን ሥራ ከመሥራቱ በፊት ስለማያውቅ ሁሉን ዐዋቂ አይደለም። ለምሳሌ፦ ሰው በሚሠራው ሥራ ይጸጸታል፦
ዘጸአት 13፥17 አምላክ፦ "ሕዝቡ ሰልፉን ባየ ጊዜ እንዳይጸጽተው እና ወደ ግብፅ እንዳይመለስ" ብሎአልና። אָמַ֣ר אֱלֹהִ֗ים פֶּֽן־יִנָּחֵ֥ם הָעָ֛ם בִּרְאֹתָ֥ם מִלְחָמָ֖ה וְשָׁ֥בוּ מִצְרָֽיְמָה׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "እንዳይጸጽተው" ለሚለው የገባው ግሥ " ፐን ዪንናኼም" פֶּֽן־ יִנָּחֵ֥ם ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "ናኻም" נָחַם ነው። የእስራኤል ሕዝብን የፈርዖንን ሠራዊት ሰልፍ ባየ ጊዜ ከግብፅ መውጣቱ ጸጽቶት ወደ ግብፅ መመለስ ከከጀለ በመውጣቱ ይጸጸት ነበር፥ የእስራኤል ሕዝብን ሰው ስለሆነ የወደፊቱን ሰማያውቅ በሠራው ሥራ ሊጸጸት ስለሚችል ፈጣሪ እንዳይጸጸቱ መክሯቸዋል። ሰው የወደፊቱን ሁሉን ዐዋቂ ስላልሆነ በሚሠራው ሥራ ይጸጸታል፥ የሰው ተቃራኒ አምላክ ደግሞ የወደፊቱን ሁሉን ዐዋቂ ስለሆነ በሚሠራው ሥራ አይጸጸትም፦
ዘኍልቍ 23፥19 ሐሰትን ይናገር ዘንድ አምላክ ሰው አይደለም፥ ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ አይደለም። לֹ֣א אִ֥ישׁ אֵל֙ וִֽיכַזֵּ֔ב וּבֶן־אָדָ֖ם וְיִתְנֶחָ֑ם
1 ሳሙኤል 15፥29 የእስራኤል ኃይል አይዋሽም አይጸጸትምም፤ እርሱ ይጸጸት ዘንድ ሰው አይደለምና። וְגַם֙ נֵ֣צַח יִשְׂרָאֵ֔ל לֹ֥א יְשַׁקֵּ֖ר וְלֹ֣א יִנָּחֵ֑ם כִּ֣י לֹ֥א אָדָ֛ם ה֖וּא לְהִנָּחֵֽם׃

ሁለቱም አናቅጽ ላይ "መጸጸት" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ ሥርወ-ቃሉ "ናኻም" נָחַם እንደሆነ ልብ አድርግ! ነገር ግን ከዚያ በተቃራኒው ያህዌህ በሠራው ሥራ እንደተጸጸተ ባይብሉ ይናገራል፦
ዘፍጥረት 6፥6 ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ ተጸጸተ፤ በልቡም እጅግ አዘነ። וַיִּנָּ֣חֶם יְהוָ֔ה כִּֽי־עָשָׂ֥ה אֶת־הָֽאָדָ֖ם בָּאָ֑רֶץ וַיִּתְעַצֵּ֖ב אֶל־לִבֹּֽו׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "ተጸጸተ" ለሚለው የገባው ግሥ "ይዪንናኼም" פֶּֽן־ יִנָּחֵ֥ם ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "ናኻም" נָחַם ነው፥ ያህዌህ የተጸጸተ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ ነው። የሠሩትን ወንጀል ዓይቶ "ከመነሻው ሰው መፍጠር አልነበረብኝም" ብሎ በሠራው ሥራ ተጸጸተ፥ መጸጸት ለሁሉን ዐዋቂ አምላክ የተገባ ባሕርይ አይደለም።
በእርግጥ "ናኻም" נָחַם የሚለው ቃል "ተጸጸተ" ብቻ ሳይሆን "አዘነ" "ራራ" "አጽናና" "ረዳ" "ተቆጣ" የሚል ፍቺ ይኖረዋል፥ ይህንን ይዘን፦
፨"ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ "አዘነ"
፨ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ "ራራ"
፨ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ "አጽናና"
፨ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ "ረዳ"
፨ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ "ተቆጣ"
ትርጉም ይሰጣልን? እራሱ በሠራው ሥራ ማዘን፣ መራራት፣ መጽናናት፣ መርዳት፣ መቆጣት ትርጉም አይሰጥም፥ ነገር ግን እራሱ በሠራው ሥራ ተጸጽቷል። ይህ የፈጣሪ ባሕርይ በፍጹም አይደለም፥ "አምላክ ይጸጸት ዘንድ የሰው ልጅ አይደለም" "እርሱ ይጸጸት ዘንድ ሰው አይደለም" ከሚሉት አናቅጽ ጋር ከመጋጨት አልፎ በመላተም ይፋጫል። የሚያሳዝነው "ያህዌህ ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ ተጸጸተ" ብሎ የሚነግረው ያህዌህ ወይም ሙሴ ሳይሆን ማንነቱ በውል የማይታወቅ ሰው ነው፥ ይህ ውሉ የማይታወቅ ሰው ንግግር ይዘን እንደ አምላክ ቃል መሞገት አግባብ አይደም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
መውሊድ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥3 ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ

“መውሊድ” مَوْلِد‎ የሚለው ቃል "ወለደ" وَلَدَ ማለትም "ወለደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ልደት” ማለት ነው፥ "የልደት ቀን፣ ቦታ እና በዓል እራሱ "መውሊድ" مَوْلِد‎ ይሉታል። በተለይ ነቢያችን”ﷺ” ተወለዱት ተብሎ የሚከበርበት ቀን "መውሊድ" مَوْلِد‎ ይባላል፥ ይህንን የመውሊድ እሳቤ ለማወቅ ከዝንባሌ ነጻ ሆነን ስለ ሸሪዓችን ጠንቅቀህ ማወቅ ይጠበቅብናል። መፍረድ ያለብንም ከአሏህ በወረደው ሸሪዓህ ብቻ ነው፦
5፥48 በመካከላቸውም አሏህ ባወረደው ሕግ ፍረድ። فَٱحْكُم بَيْنَهُم بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ

“ሑክም” حُكْم የሚለው ቃል”ሐከመ” حَكَمَ ማለትም “ፈረደ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን ፍርድ” ወይም “ሕግ” ማለት ነው፥ “አሕካም” أَحْكَام‎ ማለት ደግሞ የሑክም ብዙ ቁጥር ሲሆን “ሕግጋት” ማለት ነው። በኢሥላም አሕካም በአምስት ዋና ዋና ክፍል ይከፈላል፥ እነርሱም፦ “ፈርድ” فَرْد‎ “ሙስተሐብ” مُسْتَحَبّ‎ “ሙባሕ” مُبَاح‌‌‎ “መክሩህ” مَكْرُوه‎ እና “ሐራም” حَرَام ናቸው። አምላካችን አሏህ ሐላል ያላደረገውን ነገር ሐላል ማድረግ ዝንባሌን መከተል ነው፦
5፥48 እውነቱም ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን አትከተል፡፡ ከእናንተ ለሁሉም ሕግን እና መንገድን አደረግን፡፡ وَلَا تَتَّبِعْ أَهْوَآءَهُمْ عَمَّا جَآءَكَ مِنَ ٱلْحَقِّ ۚ لِكُلٍّۢ جَعَلْنَا مِنكُمْ شِرْعَةًۭ وَمِنْهَاجًۭا

እዚህ አንቀጽ ላይ “ሕግ” ለሚለው ቃል የገባው “ሺርዓህ” شِرْعَة ሲሆን “ሸሪዓህ” شَرِيعَة ማለት እራሱ “ትክክለኛ ሕግ” ማለት ነው። “ዒባዳህ” عِبَادَة ማለት “አምልኮ” ማለት ሲሆን ዒባዳህ አሏህ ዘንድ ተቀባይነት የሚያገኝባቸው ሥስት ሸርጦች አሉት፥ እነርሱም፦ ኢማን፣ ኢኽላስ እና ኢትባዕ ናቸው። “ኢትባዕ” إِتْبَاع‎ የሚለው ቃል “አትበዐ” أَتْبَعَ ማለትም “ተከተለ” ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን የተወረደውን “መከተል” ማለት ነው፥ ያለ ኢትባዕ ማንኛውም ዒባዳህ ተቀባይነት የለውም። ኢትባዕ ቁርኣን እና ሐዲስ ላይ በተቀመጠው ብቻ ዒባዳህን መፈጸም ነው፦
6፥106 ከጌታህ ወደ አንተ የተወረደውን ተከተል፡፡ اتَّبِعْ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِن رَّبِّكَ
7፥3 ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ

“ተከተሉ” የሚለው ቃል “ኢተቢዑ” اتَّبِعُوا ሲሆን “ኢትባዕ” ማለት ከአሏህ ወደ ነቢያችን”ﷺ” የተወረደውን ብቻ መከተል ማለት ነው፥ ሙሥሊም የተወረደውን ብቻ ሲከተል ሁለት ዒድ ብቻ ያከብራል። “ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። ነቢያችን”ﷺ” የነገሩን ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻ እና ብቻ ናቸው፥ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፤ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው"። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏
አሥ ሠለፉ አስ ሷሊሑን የሚያከብሩት እነዚህን ሁለቱን በዓላት ብቻ ነበር። እነዚህ ሦስት ትውልድ፦
፨፦ የመጀመሪያው ትውልድ “ሰሓቢይ” صَحَابِيّ ሲባሉ የነቢያችን”ﷺ” ውድ “ባልደረባ”companion” ናቸው፣
፨፦ ሁለተኛው ትውልድ “ታቢዒይ” تَابِعِيّ ሲባሉ ለጥቆ ያሉ ናቸው፣
፨፦ ሦስተኛው ትውልድ “ታቢዑ አት-ታቢዒን” تَابِع التَابِعِين ሲባሉ ሠልሶ ያሉ ናቸው። እነዚህ ሦስት ትውልድ “አሥ-ሠለፉ አስ-ሷሊሑን” ٱلسَلَف ٱلصَالِحُون ማለትም “መልካሞቹ ቀደምት” ይባላሉ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 83, ሐዲስ 72
ዒምራን ኢብኑ ሑሰይን እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”ከእናንተ ምርጡ የእኔ ትውልድ ነው፥ ቀጥሎ ያሉት እነርሱን የሚከተሉት ነው፥ ለጥቆ ያሉት የሚከተሉትን የሚከተሉ ናቸው”። قَالَ سَمِعْتُ عِمْرَانَ بْنَ حُصَيْنٍ، يُحَدِّثُ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ خَيْرُكُمْ قَرْنِي، ثُمَّ الَّذِينَ يَلُونَهُمْ، ثُمَّ الَّذِينَ يَلُونَهُم

አሥ-ሠለፉ አስ-ሷሊሑን በመንሀጃቸው ውስጥ ስለ መውሊድ  አላስተማሩም፥ መውሊድን አልተገበሩትም። “መንሀጅ” مَنْهَج ማለት “ፍኖት” “ፋና” “መንገድ” ማለት ነው። በታሪክ እንደሚታወቀው ለመጀመርያ ጊዜ "የነቢያችን”ﷺ”  የልደት ቀን" ተብሎ መከበር የተጀመረው ግብፅ ውስጥ በፋጢሚዩን በአራተኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ ነው፥ የጀመሩትም ክርስቲያኖች ከሚያከብሩት "ልደት" ኮርጀው ነው። ክርስቲያኖች ደግሞ የሚያክብሩት ከመጽሓፋቸው ተፈቅዶላቸው ወይም ታዘው ሳይሆን ከፓጋን ኮርጀው ነው። ስለ ገና ይህንን ጽሑፍ ይመልከቱ፦ https://t.me/Wahidcom/3665

ስለዚህ ሦስተኛ በዓል መውሊድ መጤ እና ቢድዓ ነው፥ “ቢድዓህ” بِدْعَة የሚለው ቃል “በደዐ” بَدَعَ ማለትም “ፈጠረ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ፈጠራ” ማለት ነው። ቢድዓህ የኢትባዕ ተቃራኒ ነው፥ “ቢድዓህ” ማለት አላህ ሳያዘን እና ሳይፈቅድልን ዝንባሌአችንን ተከትለን የምናደርገው አዲስ አምልኮ ማለት ነው። ያለ ኢትባዕ የአሏህን ውዴታ ለመፈለግ ተብሎ የሚደረግ ማንኛውም አዲስ አምልኮ ቢድዓህ ነው፦
ሡነን ነሣኢ መጽሐፍ 19, ሐዲስ 23
ጃቢር ኢብኑ ዐብደላህ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ኹጥባቸው ላይ እንደተናገሩት፦ “አሏህ የመራውን ማንም አያጠመውም፥ አሏህ ያጠመመውን ማንም አያቀናውም። ከንግግር ሁሉ በላጩ የአሏህ መጽሐፍ ነው፥ ከመመሪያ ሁሉ በላጩ የሙሐመድ መመሪያ ነው። ከሁሉ የተጠላ ነገር ቢድዓህ ነው፥ ቢድዓህ ሁሉ ጥመት ነው። ጥመት ሁሉ የእሳት ነው"። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ فِي خُطْبَتِهِ يَحْمَدُ اللَّهَ وَيُثْنِي عَلَيْهِ بِمَا هُوَ أَهْلُهُ ثُمَّ يَقُولُ مَنْ يَهْدِهِ اللَّهُ فَلَا مُضِلَّ لَهُ وَمَنْ يُضْلِلْهُ فَلَا هَادِيَ لَهُ إِنَّ أَصْدَقَ الْحَدِيثِ كِتَابُ اللَّهِ وَأَحْسَنَ الْهَدْيِ هَدْيُ مُحَمَّدٍ وَشَرُّ الْأُمُورِ مُحْدَثَاتُهَا وَكُلُّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ وَكُلُّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ وَكُلُّ ضَلَالَةٍ فِي النَّارِ

ከሁሉ የተጠላ ነገር ቢድዓህ ነው፥ ቢድዓህ ሁሉ ጥመት ነው። ጥመት ሁሉ የእሳት ከሆነ ካየን ዘንዳ ቢድዓህ የሚያራምድ ማንኛውም ሰው "ተብዲዕ" تَبْدِيع ከተደረገበት “ሙብተዲዕ” مُبْتَدِع ይባላል። ቢድዓህ ደግሞ ምንጩ ዝንባሌን መከተል ነው፥ በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፦
79፥40 በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ፥ وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَى
79፥41 ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَىٰ

አምላካችን አሏህ ዝንባሌ ከመከተል ይጠብቀን! ከቢድዓህ እርቀን በኢትባዕ ብቻ እርሱን የምናመልክ ያርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
10ኛ ዙር የነሕው ደርሥ

በወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" 10ኛ ዙር የነሕው ደርሥ!

አን-ነሕው" اَلنَّحْو ማለት "ሰዋስው"grammar" ማለት ሲሆን የቁርኣንን እና የጥንቱን የአነጋገር ዘይቤ በዐማርኛ እና በእንግሊዝኛ በተደገፈ መልኩ ለሃይማኖት ንጽጽር መማር የምትፈልጉ ሁሉ ቦታው ክፍት ነው። ደርሡ (ትምህርቱ) የሚፈጀው 7 ወር ኢንሻሏህ ሲሆን ሦስት ተርም አለው።

፨ የመጀመሪያው ተርም ዐጽመ-አሳብ በኢሥም ላይ የሚያውጠነጥኑ ሲሆኑ 11 ናቸው፥ እነርሱም፦
1. ኢሥሙል ማዕሪፍ፣
2. ኢሥሙል ዐለም፣
3. ኢሥሙል ጂንሥ፣
4. ኢሥሙል ዐደድ፣
5. ኢሥሙ አድ-ደሚር፣
6. ኢሥሙል ኢሻራህ፣
7. ኢሥሙል መውሱል፣
8. ኢሥሙል ኢሥቲፍሃም፣
9. ኢሥሙል ሚልክ፣
10. ኢሥሙል ወስፍ፣
11. ኢሥሙ አዝ-ዘርፍ ናቸው።

፨ የሁለተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በፊዕል ላይ የሚያውጠነጥኑ ሲሆኑ 7 ናቸው፥ እነርሱም፦
1. ሸኽስ፣
2. ዐደድ፣
3. ጂንሥ፣
4. ተወቱር፣
5. ሲጋህ፣
6. ሓላህ፣
7. ጁምላህ ናቸው።

፨ የሦስተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በሐርፍ ላይ የሚያውጠነጥኑ ሲሆኑ 7 ናቸው፥ እነርሱም፦
1. ሐርፉል ጀር፣
2. ሐርፉል አጥፍ፣
3. ሐርፉ አት-ተፍሲል፣
4. ሐርፉል መስደሪይ፣
5. ሐርፉ አን-ነፍይ፣
6. ሐርፉል ሐስድ
7. ሐርፉ አሽ-ሸርጥ ናቸው።

ደርሡ በሳምንት አንዴ የሚለቀቅ ሲሆን በሁለት ሳምንት አንዴ የሁለቱ ሳምንት ጥያቄ ፈተና ይኖራል። ፈተናው ከ 10 የሚወሰድ ሲሆን ከ 6-10 ማምጣት ይጠበቅባችኃል። ከ 6 በታች ሦስት ጊዜ ካመጣችሁ በሰርተፍኬት አናስመርቅም።

ለመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩት አድሚናት በውስጥ ያናግሩ!
እኅት ጀሙቲ፦ http://t.me/JemutiMenhajself34
ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu
እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe
አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa
እኅት አበባ፦ http://t.me/selemtewa

ቦታ ሳይያዝ ይመዝገቡ! መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንልዎ!
ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
ዲኑል ኢሥላም

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥19 አሏህ ዘንድ ሃይማኖት ኢሥላም ነው፡፡ إِنَّ الدِّينَ عِندَ اللَّهِ الْإِسْلَامُ

አምላካች አሏህ በተለያየ ዘመነ መግቦት"dispensation" መልእክተኛ ልኳል፥ ያ የሚላከው ማንንም መልእክተኛ በአሏህ ፈቃድ አማኞች ሊታዘዙት እንጂ አልተላከም፦
4፥64 ማንንም መልእክተኛ በአሏህ ፈቃድ ሊታዘዙት እንጂ አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن رَّسُولٍ إِلَّا لِيُطَاعَ بِإِذْنِ اللَّهِ

"ኢዝን" بِإِذْن ማለት "ፈቃድ" ማለት ሲሆን አንድ አማኝ የተላከው መልእክተኛ መታዘዝ የአሏህ ፈቃድ ነው፥ በዚህም ኑሕ፣ ሁድ፣ ሷሊሕ፣ ሉጥ፣ ሹዕይብ፣ ዒሣ ወዘተ "ታዘዙኝ" በማለት ይናገራሉ፦
26፥108 26፥126 26፥144 26፥163 26፥169 3፥50 አሏህንም ፍሩ! ታዘዙኝም፡፡ فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ታዘዙኝ" ለሚለው የገባው ቃል "አጢዑኒ" أَطِيعُونِ ነው፥ አምላካችን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" መታዘዝ እንዳለብን ሲናገር "መልእክተኛውን ታዘዙ" በማለት ነው፦
24፥56 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፣ ምጽዋትንም ስጡ፣ መልእክተኛውን ታዘዙ! ለእናንተ ሊታዘንላችሁ ይከጀላልና፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ وَأَطِيعُوا الرَّسُولَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዘዙ" ለሚለው የገባው ቃል "አጢዑ" أَطِيعُوا እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ሰዎች ለአሏህ "ታዘዙ" የተባሉበት ትእዛዝ ግን ለእርሱ ብቻ አምልኮታዊ መታዘዝ ነው፦
22፥34 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ ታዘዙ! ለአሏህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ

"አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው" ካለ በኃላ "ለእርሱም ብቻ ታዘዙ" በማለት ያስቀምጣል፥ እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዘዙ" ለሚለው የገባው ቃል "አሥሊሙ" أَسْلِمُوا ሲሆን ለእርሱ በብቸኝነት የሚቀርብ አምልኮ ነው፦
39፥54 «ቅጣቱም ወደእናንተ ከመምጣቱ እና ከዚያም የማትረዱ ከመኾናችሁ በፊት ወደ ጌታችሁ በመጸጸት ተመለሱ፡፡ ለእርሱም ታዘዙ!፡፡ وَأَنِيبُوا إِلَىٰ رَبِّكُمْ وَأَسْلِمُوا لَهُ مِن قَبْلِ أَن يَأْتِيَكُمُ الْعَذَابُ ثُمَّ لَا تُنصَرُونَ

አሁንም እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዘዙ" ለሚለው የገባው ቃል "አሥሊሙ" أَسْلِمُوا ነው፥ "ኢሥላም" إِسْلَام ማለት እራሱ "መታዘዝ" ማለት ነው፦
3፥19 አሏህ ዘንድ ሃይማኖት ኢሥላም ነው፡፡ إِنَّ الدِّينَ عِندَ اللَّهِ الْإِسْلَامُ

ለአሏህ ብቻ በውጥን የሚደረግ መታዘዝ "ኢሥላም" إِسْلَام ይባላል፥ "ኢሥላም" إِسْلَام የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ‎ ማለትም "ታዘዘ" "ተገዛ" "አመለከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መታዘዝ" "መገዛት" "ማምለክ" ማለት ነው።
"ዲን" دِين የሚለው ቃል "ዳነ" دَانَ ማለትም "ሃይመነ" "ደነገገ"  "ፈረደ" "በየነ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ሃይማኖት" "ፍትሕ" "ፍርድ" "ሕግ" "መርሕ"doctrine" ማለት ነው፥ አሏህ ዘንድ ያለው ሃይማኖት ኢሥላም ነው። አንድ ማንነት ለአሏህ ብቻ በአምልኮ ሲታዘዝ "ሙሥሊም" مُسْلِم ይባላል፦
3፥84 «እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» በል፡፡ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ
2፥136 «እኛም ለእርሱ ታዛዦች ነን» በሉ፡፡ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ
29፥46 በሉም «በዚያ ወደ እኛ በተወረደው ወደ እናንተም በተወረደው አመንን፡፡ አምላካችንም አምላካችሁም አንድ ነው፡፡ እኛም ለእርሱ ታዛዦች ነን» وَقُولُوا آمَنَّا بِالَّذِي أُنزِلَ إِلَيْنَا وَأُنزِلَ إِلَيْكُمْ وَإِلَـٰهُنَا وَإِلَـٰهُكُمْ وَاحِدٌ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُسْلِمُون ነው፥ "ሙሥሊም" مُسْلِم ማለት በነጠላ "ታዛዥ" ማለት ሲሆን ብዙ ቁጥሩ "ሙሥሊሙን" مُسْلِمُون ነው። ታዲያ ቀደምት ነቢያት ሙሥሊሞች አይደሉምን? ዲናቸውስ "ፈጣሪ አንድ አምላክ ነው" ተብሎ ፈጣሪን ብቻ በአምልኮ መታዘዝ አይደለምን? እንዴታ።
ወደ እኛም የተወረደው እና ወደ መጽሐፉ ሰዎች የተወረደው ግልጠተ መለኮት ጭብጡ የአንድ አምላክ አስተምህሮት ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ

አሏህ ከጥንት ጀምሮ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" ብሎ ለሚልከው ነቢይ የሚገልጠው ይህ ግልጠት ነው፥ "የምናወርድ" ለሚለው የገባው ቃል "ኑሒ" نُوحِي ሲሆን የሚወርድለት "ወሕይ" وَحْي ነው። ስለዚህ የቀደሙት ነቢያት ሙሥሊም ነበሩ፦
5፥44 እነዚያ "ትእዛዝን የተቀበሉት" ነቢያት በእነዚያ አይሁዳውያን በኾኑት ላይ በእርሷ ይፈርዳሉ፡፡ يَحْكُمُ بِهَا النَّبِيُّونَ الَّذِينَ أَسْلَمُوا لِلَّذِينَ هَادُوا

በግሥ መደብ "ትእዛዝን የተቀበሉት" ለሚለው የገባው ቃል "አሥለሙ" أَسْلَمُوا ሲሆን በስም መደብ "ሙሥሊም" مُسْلِم ነው። የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በእኛ እና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ኾነች ቃል ኑ፦
3፥64 በል፦ "የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በእኛ እና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ኾነች ቃል ኑ፡፡ قُلْ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ تَعَالَوْا إِلَىٰ كَلِمَةٍ سَوَاءٍ بَيْنَنَا وَبَيْنَكُمْ

ይህቺ የጋራ ትክክለኛ ቃል አሏህን እንጂ ሌላን ላናመልክ፣ በእርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአሏህ ሌላ ጌቶች አድርጎ ላይዝ ነው፦
3፥64 እርሷም፦ "አሏህን እንጂ ሌላን ላናመልክ፣ በእርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአሏህ ሌላ ጌቶች አድርጎ ላይዝ ነው"። أَلَّا نَعْبُدَ إِلَّا اللَّهَ وَلَا نُشْرِكَ بِهِ شَيْئًا وَلَا يَتَّخِذَ بَعْضُنَا بَعْضًا أَرْبَابًا مِّن دُونِ اللَّهِ

"ረብ" رَبّ ማለት "ጌታ" ማለት ነው፥ የረብ ብዙ ቁጥር "አርባብ" أَرْبَابً ሲሆን "ጌቶች" ማለት ነው። አሏህን በአምልኮቱ እና በጌትነቱ መታዘዝ ኢሥላም ሲሆን ይህንን ሐቅ ካስተባበሉ ሑጃህ እንዲቆምባቸው እኛ ሙሥሊሞች መኾናችንን መስክሩ በሏቸው፦
3፥64 ምቢ ቢሉም፡- "እኛ ሙሥሊሞች መኾናችንን መስክሩ" በሏቸው፡፡ فَإِن تَوَلَّوْا فَقُولُوا اشْهَدُوا بِأَنَّا مُسْلِمُونَ

አምላካችን አሏህ በዲኑል ኢሥላም ያጽናን! ሙሥሊም አድርጎ ወደ እርሱ ይውሰደን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ወንድ እና ሴት

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

53፥45 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድን እና ሴትን ፈጠረ፡፡ وَأَنَّهُ خَلَقَ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ

ሐቅን መሸጥ፣ መሸቀጥ እና መሸቃቀጥ የለመዱ ሚሽነሪዎች "ቁርኣን ወንድን እንጂ ሴትን ሰው አይላትም" በማለት ዓይነ መጭማጫ ሆነው ጥቅስን በቅጡ እና በአግባቡ ሳያነቡ እና ሳይረዱ ያንሸዋርራሉ። ቁርኣንን ሳያጠኑ ከላይ ከላይ እያንኮበከቡ ለሚያጠናብሩ ደግነታችን መሬት ስለማይነጥፍ መልስ እንሰጣለን።
"ኑጥፋህ” نُّطْفَة ማለት "የፍትወት ፈሳሽ"sexual fluid" ማለት ነው፥ ይህምም የፍትወት ፈሳሽ የወንዱ የዘር ሕዋስ"sperm cell" እና የሴቷ የእንቁላል ሕዋስ"egg cell" ነው። አምላካችን አሏህ ሰውን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ሕዋስ እንደፈጠረ ይናገራል፦
76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ሕዋስ ፈጠርነው፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ

የወንዱ 23 ነጠላ ሕዋስ"haploid" እና የሴቷ 23 ነጠላ ሕዋስ"haploid" በተራክቦ ጊዜ አምሻጅ ይሆናል፥ “አምሻጅ” أَمْشَاج ማለት “ቅልቅል"diploid" ማለት ነው። ከዚህ ቅልቅል የፍትወት ሕዋስ ድቅለት"fertilization" ፅንስ ይፈጠራል፥ "ሚን" مِن ማለት "ከ" ማለት ሲሆን "ሚን" የሚለው መስተዋድድ "ኑጥፋህ" ከሚለው መነሻ ላይ መምጣቱ በራሱ የሁለቱን ተቃራኒ ጾታ የሚያመለክት ነው። እዚህ አንቀጽ ላይ "ሰው" ለሚለው የገባው ቃል "አል ኢንሣን" الْإِنسَان ሲሆን ከሁለቱንም የፍትወት ሕዋስ ማለትም ከወንድ የፍትወት ሕዋስ እና ከሴት የፍትወት ሕዋስ የተፈጠረውን ሰው አመላካች ነው፥ ከወንድ የፍትወት ሕዋስ እና ከሴት የፍትወት ሕዋስ የተፈጠረውን ሰው ሌላ ቦታ ላይ ወንድ እና ሴት ይለዋል፦
53፥45 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድን እና ሴትን ፈጠረ፡፡ وَأَنَّهُ خَلَقَ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ
53፥46 ከፍትወት ሕዋስ በምትፈሰስ ጊዜ፡፡ مِن نُّطْفَةٍ إِذَا تُمْنَىٰ

"ኢዛ" إِذَا ማለት "ጊዜ" ማለት ነው፥ ይህም የተራክቦን ጊዜ ያሳያል። "ቱምና" تُمْنَىٰ ወይም "ዩምና" يُمْنَىٰ የግሥ መደብ ሲሆን "የምትፈሰስ" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "መኒይ" مَّنِىّ ማለትም "የፍትወት ሕዋስ" ማለት ነው። ከፍትወት ሕዋስ የተፈጠረው ሰው ወንድ እና ሴት ነው፦
75፥36 "ሰው" ልቅ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን? أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَن يُتْرَكَ سُدًى
75፥37 የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ሕዋስ አልነበረምን? أَلَمْ يَكُ نُطْفَةً مِّن مَّنِيٍّ يُمْنَىٰ
75፥38 ከዚያም "የረጋ ደም" ሆነ፥ ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡ ثُمَّ كَانَ عَلَقَةً فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
75፥39 "ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድ እና ሴትን አደረገ"፡፡ فَجَعَلَ مِنْهُ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ

"ሚን-ሁ" مِنْهُ ማለት "ከእርሱ" ማለት ሲሆን "ከ" የሚል መስተዋድ ያለበት ተሳቢ ስለሆነ "እርሱ" የተባለው ዐውደ ንባቡ ላይ ያለው "መኒይ" مَّنِىّ የሚለውን ተክቶ የመጣ ነው፥ እዚህ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሁለት ዓይነቶችን ወንድ እና ሴትን" የሆነን ሰው ከመኒይ እንደፈጠረ ሲናገር ከላይ ደግሞ ሰውን "ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ሕዋስ ፈጠርነው" ማለቱ "ሰው" የሚባሉት ወንድ እና ሴት መሆናቸውን ፍንትው አርጎ ያሳያል። የአባት ሀብለ በራሂ"paternal chromosome" ግማሽ 23% የእናት ሀብለ በራሂ"maternal chromosome" 23% ተገናኛተው 46% ሀብለ በራሂ ሕዋስ"diploid" ሆነው ይዋሐዳሉ፦
49፥13 እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድ እና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَاكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሰዎች" ለሚለው የገባው ቃል "አን ናሥ" النَّاس ሲሆን ከወንድ እና ከሴት የተፈጠሩትን ወንድ እና ሴት ያመለክታል፥ ሰዎች ከሴት ተፈጥረው ሳለ "ሰው ካሆነች ሴት ሰዎች ተፈጠሩ" ማለት ቂልነት ነው። አሏህ ከወንድ አደም እና ከሴት ሐዋ ብዙ ወንዶችን እና ሴቶችን የፈጠረ ነው፦
4፥1 እናንተ ሰዎች ሆይ! ያንን ከአንዲት ነፍስ የፈጠራችሁን፣ ከእርስዋም መቀናጆዋን የፈጠረውን፣ ከእነርሱም ብዙ ወንዶችን እና ሴቶችን የበተነውን ጌታችሁን ፍሩ፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ اتَّقُوا رَبَّكُمُ الَّذِي خَلَقَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ وَخَلَقَ مِنْهَا زَوْجَهَا وَبَثَّ مِنْهُمَا رِجَالًا كَثِيرًا وَنِسَاءً

"እናንተ ሰዎች ሆይ" የሚለው ይሰመርበት! “ከእነርሱም” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ሚንሁማ” مِنْهُمَا ሲሆን “ሙሰና” مُثَنًّى ነው። “ሚንሁማ” مِنْهُمَا ሁለቱን ጥንድ የሚያሳይ ሲሆን ከእነርሱ ማለትም ከአደም እና ከሐዋ ብዙ ወንዶችን እና ሴቶችን ፈጠረ፥ አሏህ እነዚህ ወንዶችን እና ሴቶችን "እናንተ ሰዎች ሆይ" ይላቸዋል። "አዝዋጅ أَزْوَاج ማለት "ጥንዶች"pairs" ማለት ነው፦
78፥8 ጥንዶች አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡ وَخَلَقْنَاكُمْ أَزْوَاجًا

እነዚህ ጥንዶች ወንድ እና ሴት እንደሆኑ ተፍሢር ኢብኑ ዐባሥ፣ ተፍሢር ኢብኑ ከሲር እና ተፍሢር ጀላለይን ገልጸውታል፥ ሴት ከወንድ ሰው ተፈጥራ ሳለ "ሰው አይደለችም" ማለት ጅላንፎነት ነው። ስለዚህ "በቁርኣን "ሴት ሰው ናት" የሚል የለም" የሚል ሙግት ዕውር ድንብር የሆነ ጸለምተኛ ሙግት"Pessimistic Approach" ነው።
በአሁን ሰዓት የሙሥሊም ዐቃቢያን ዕቅበተ ሥራ ብዙ ክርስቲያኖችን እየናጠ ስለሆነ ቆፍጠን ብለን ኢንሻላህ እናስተምራለን። ሚሽነሪዎች ሆይ! ዛሬ ብዙ ወደ ኢሥላም የመጡ ሺ በክንፉ ሺ በአክናፉ የተባለላቸው ኅሩያን እና ንዑዳን የከፍታቸው ምሥጢር በመተናነስ መጠየቃቸው ነውና በቅንነት ጠይቁ እንጂ እልህ አትጋቡ! ሙግት ማለት በእንካ ሰላንቲያ መጎናተል እና መጋፈር ሳይሆን ኩታ ገጠም በሆኑ አርስት ላይ አንጡራ ሙግት"metropolitan argument" ማንሸራሸር ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አምላከ አበው

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ

"አብ" ማለት "አባት" ማለት ነው፥ "አበው" የአብ ብዙ ቁጥር ሲሆን "አባቶች"ማለት ነው። እዚህ ጽሑፍ ላይ "አበው" ስል ጥንት የነበሩትን ነቢያት አብርሃምን፣ ይስሓቅን እና ያዕቆብ ወዘተ ለማመልከት ነው፥ "አምላከ አበው" ማለት "የአባቶች አምላክ" ማለት ነው።
አምላካችን አሏህ የጥንት አባቶች አምላክ ነው፥ ቁርኣን የአሏህ ንግግር ነው። አምላካችን አሏህ በሡረቱ አጥ ጧሀ ላይ "ቁርኣንን በአንተ ላይ እንድትቸገር አላወረድንም" በማለት ዐውዱ ይጀምራል፦
20፥2 ቁርኣንን በአንተ ላይ እንድትቸገር አላወረድንም፡፡ مَا أَنزَلْنَا عَلَيْكَ الْقُرْآنَ لِتَشْقَىٰ

እዚህ ዐውድ ላይ አሏህ በሁለተኝም መደብ "አንተ" የሚላቸው ተወዳጁ ነብያችንን”ﷺ” ነው፥ በመቀጠል አሏህ ለተወዳጁ ነቢያችን”ﷺ” "የሙሣም ወሬ በእርግጥ መጥቶሃል" በማለት ይናገራል፦
20፥9 የሙሣም ወሬ በእርግጥ መጥቶሃል፡፡ وَهَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ مُوسَىٰ

አሏህም ሙሣን ጠራውና "የሚወረድልህንም ነገር አዳምጥ" አለው፥ ይህ የወረደለት የአሏህ ንግግር ሲሆን ይህም የወረደው ንግግር፦ "እኔ አሏህ እኔ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለምና አምልከኝ" የሚል ነው፦
20፥11 በመጣም ጊዜ «ሙሣ ሆይ» በማለት ተጠራ፡፡ فَلَمَّآ أَتَىٰهَا نُودِىَ يَٰمُوسَىٰٓ
20፥13 «እኔም መረጥኩህ፤ የሚወረድልህን አዳምጥ፡፡ وَأَنَا اخْتَرْتُكَ فَاسْتَمِعْ لِمَا يُوحَىٰ
20፥14 እኔ አሏህ እኔ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትንም እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي

ሙሣን ጠርቶ "እኔ አሏህ እኔ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለምና አምልከኝ" ብሎት እንደነበር ለተወዳጁ ነቢያችንን”ﷺ” በሁለተኛ መደብ የሚነግራቸው አሏህ እራሱ ስለሆነ "ከጡር ቀኝ ጎን በኩልም ጠራነው፤ ያነጋገርነውም ሲኾን አቀረብነው" በማለት ይናገራል፦
19፥52 ከጡር ቀኝ ጎን በኩልም ጠራነው፤ ያነጋገርነውም ሲኾን አቀረብነው፡፡ وَنَٰدَيْنَٰهُ مِن جَانِبِ ٱلطُّورِ ٱلْأَيْمَنِ وَقَرَّبْنَٰهُ نَجِيًّۭا

"ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" የሚለው መገሰጫ ወደ ተወዳጁ ነቢያችን”ﷺ” የወረደ እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት አበው የወረደ መገሰጫ ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ

አንዱ አምላክ የጥንት አበው አሏህ እያሉ ይጠሩ እንደነበር የዐረቢኛ ባይብል ላይ ብዙ ቦታ ተጠቅሷል። ለምሳሌ፦ አሏህ ለኢብራሂም፦ "አሏህ እኔ ነኝ" እንዳለው ተቀምጧል፦
ዘፍጥረት 5፥7 ይህችን ምድር ትወርሳት ዘንድ እንድሰጥህ ከከለዳውያን ዑር ያወጣሁህ አሏህ እኔ ነኝ" አለው።
وَقَالَ لَهُ: «أنَا هُوَ اللهُ الَّذِي أخْرَجَكَ مِنْ أُورِ الكِلْدَانِيِّينَ لِيُعْطِيكَ هَذِهِ الأرْضَ مِلْكًا.»

አሏህ ፈጣሪ ካልሆነ ለምን በዐረቢኛ ላይ "አሏህ እኔ ነኝ" እንዳለ ሰፈረ? ዐረብ ክርስቲያኖች "አሏህ" ሲሉ እውነት አሏህ የሚለው ቃል ፈጣሪን ለማመልከት ሳይገባቸው ቀርተው ነው? ለይስሐቅም አሏህ ተገለጠለት ይለናል፦
ዘፍጥረት 26፥2 አሏህ ተገለጠለት እና እንዲህ አለው፦ “ወደ ግብፅ አትውረድ፥ እኔ በምልህ ምድር ተቀመጥ እንጂ።
فَظَهَرَ اللهُ لِإسْحَاقَ وَقَالَ لَهُ: «لَا تَنْزِلْ إلَى مِصْرٍ. بَلِ امْكُثْ فِي الأرْضِ الَّتِي سَأقُولُ لَكَ عَنْهَا.

"መገለጥ" ማለት "መታወቅ" ማለት ነው፥ ለይስሐቅ "እኔ በምልህ ምድር ተቀመጥ እንጂ" እያለው የሚያናግረው አሏህ እንደሆነ መገለጹ ስህተት ነውን? አሏህ ለያዕቆብ "የአባትህ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ እኔ ነኝ" አለው፦
ዘፍጥረት 28፥13 አሏህም፦ "የአባትህ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ እኔ ነኝ" አለው።
فَقَالَ اللهُ: «أنَا إلَهُ أبِيكَ إبْرَاهِيمَ، وَإلَهُ إسْحَاقَ.

ከተወዳጁ ነቢያችን”ﷺ” በፊት አሏህ የሰበከ ከሌለ ለምን "አሏህ አለ" "እኔ አሏህ ነኝ" የሚል ቃል ባይብል ላይ ሰፈረ? አሏህ ሙሴን፦ እኔ አሏህ ነኝ" ብሎታል፦
ዘጸአት 6፥29 እርሱም ሙሴን፦ እኔ አሏህ ነኝ፤ እኔ የምነግርህን ሁሉ ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖን ንገር" ብሎ ተናገረው።
قَالَ لَهُ: «أنَا اللهُ. قُلْ لِفِرعَونَ مَلِكِ مِصْرٍ كُلَّ مَا أقُولُهُ لَكَ.»

በዚህ ሙግት ስናቆራጥጣቸው "የእኛ አሏህ እና የእናንተ አሏህ ይለያያል፥ የእኛ አሏህ አንድም ሦስት ነው፤ የእናንተ አሏህ አንድ ብቻ ነው" ይሉናል። ጥሩ!
፨ አንደኛ ሁለት አሏህ በህልውና የለም፥ ስለ አሏህ ሁለት ሰዎች የተለያየ መረዳት ቢኖራቸው አሏህ ሁለት ሆኖ ሳይሆን መረዳታቸው ብቻ ይለያያል።
፨ ሁለተኛ ከክርስቲያኖች በፊት ያሉ አይሁዳውያን ወጥ በሆነ አቋም አሏህ ጥንት የነበረው የአባቶች አምላክ መሆኑን ይቀበላሉ፥ በተጨማሪም "አሏህ አንድ ብቻ ነው" ብለው ሲያምኑ በተቃራኒው "አንድም ሦስት ነው" የሚለውን ክፉኛ ይቃወማሉ።
፨ ሦስተኛ አሏህ ፈጣሪ መሆኑን ከተቀበላችሁ እና ከጥንት ነቢያት ማስተማራቸውን መቀበላችሁ "ይበል" የሚያስብል ንግግር ነው፥ አሏህ የሚለው ስም ለጣዖት አገልግሎት የዋለበት አንድም የሐራዊ ሆነ የወጋዊ ዘገባ የሌለ ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የባዕድ አምላክ ስም ቢሆን ኖሮ ባይብል ላይ ለነቢያት አምላክ ስም አርገው አይጠቀሙም ነበር።

አምላከ አበው አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
በወንድም ተውፊቅ አል ሐበሺይ
ሡረቱል አንቢያ 21፥21-35
ኢሬቻ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ "እኔንም ብቻ አምልኩኝ"፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ

አምላካችን አሏህ መለኮት ነው፥ “መለኮት” ማለት "ሁሉን ነገር የሚሰማ፣ ሁሉን ነገር የሚመለከት፣ ሁሉን ነገር የሚያውቅ፣ ሁሉን ነገር የፈጠረ፣ በሁሉን ነገር ላይ ቻይ" ማለት ነው። እርሱ በእኔነት የሚናገር ነባቢ እና ሕያው መለኮት ነው፥ አምላካችን አሏህ ብዙ አናቅጽ ላይ “አምልኩኝ” እያለ በመጀመሪያ መደብ ይናገራል፦
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ "እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ"፡፡ إِنَّ هَٰذِهِۦٓ أُمَّتُكُمْ أُمَّةًۭ وَٰحِدَةًۭ وَأَنَا۠ رَبُّكُمْ فَٱعْبُدُونِ
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ "እኔንም ብቻ አምልኩኝ”፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ

"እኔንም ብቻ አምልኩኝ" የሚለው ይሰመርበት! "አምልኩኝ" ለሚለው የገባው ቃል "አዕቡዱኒ" ٱعْبُدُونِ ሲሆን አምላካችን አሏህ ጥንት ለነበሩ ነቢያትም "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት የሚናገር አምላክ ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ ”የምናወርድለት” ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ

ሰው የተፈጠረበት ዓላማ እና ዒላማ የአምልኮ ሐቅ የሚገባውን አሏህን ብቻ ለማምለክ ነው፥ አንድ ሙሥሊም በጌታው አምልኮን ማንንም ሆነ ምንንም ማጋራት የለበትም፦
51፥56 ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
18፥110 «በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا

"ዒባዳህ" عِبَادَة ማለት እራሱ "አምልኮ" ማለት ነው። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ስለ ኢሬቻ ትንሽ እንበል? “ኢሬቻ” ማለት “አምልኮ” ማለት ሲሆን “ገልማ” ማለት “ቤተ አምልኮ” ማለት ነው፥ ኢሬቻ ገልማ ውስጥ በጭፈራዎቹ እና በፌሽታዎች የሚከበር በዓል ነው። ኢሬቻን የምትለዋ ቃል የምትወክለው እርጥብ ሣር ወይም አበባ በማቅረብ “መሬሆ” ማለትም “መዝሙር” መዘመሩን ነው፥ "ኢሬቻ ባህል እንጂ ሃይማኖት አይደለም" ለምትሉ ስመ ሙሥሊም ይህንን ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን?

“ዋቃ” ማለት እኮ “አምላክ” ማለት ነው፥ "ዋቃ ጉራቻ" ማለት "ጥቁር አምላክ" ማለት ሲሆን "ዋቃ ጉራቻ" እያሉ ለወንዙ፣ ለተራራው፣ ለሐይቁ የሚደረገው የሁሉ አምላክነት”Pantheism” እሳቤ ባዕድ አምልኮ ነው። በዚህ አምልኮ ውስጥ ልመና፣ ምስጋና፣ ስለት፣ ስግደ፣ የእድርድ መሥዋዕት የመሳሰሉት ይካሄዳሉ፥ ዛፍ ቅቤ በመቀባት መለማመን፣ ማመስገን፣ መሳል፣ መስገድ ባዕድ አምልኮ ካልሆነ ምንድን ይሆን?

እንደውም “ቃሊቻ” የሚለው ቃል የተገኘው “ቃሉ” ከሚለው እንደሆነም ይነገራል፥ “ቃሉ” የተባሉት መሪዎች ከአጋንንት ጋር እየተነጋገሩ ሺርክ እንደሚያደርጉ የዚህ ባዕድ አምልኮ ነጻ የወጡ ሰዎች ይናገራሉ።
ይህንን አምልኮ የሚፈጽሙ ምዕመናኑ “ሚሤንሣ” ሲባሉ እምነቱን የሚመሩት ካህናቱ “ቃሉ” ይባላሉ፥ ፓለቲካውን “ሲርነ ገዳ” ሲባል ፓለቲካውን የሚመሩት መሪዎች ደግሞ “አባ ገዳ” ይባላሉ።

የዚህ ባዕድ አምልኮ ስም "ዋቄፈና" ሲባል ይህንን እምነት የሚከተል ሰው ደግሞ “ዋቄፈታ” ይባላል፥ ይህ እምነት አምልኮውን የሚፈጽመው በተራራ እና በሃይቅ ወዘተ ነው። “ቱሉ” ማለት “ተራራ” ማለት ሲሆን “ቱሉ ጩቋላ(የዝቋላ ተራራ) “ቱሉ ፊሪ” “ቱሉ ኤረር” እየተባለ ወደ ስምንት ተራሮች ላይ አምልኮ ይፈጸማል፥ “ሆረ” ማለት “ሃይቅ” ማለት ሲሆን “ሆረ አርሰዴ” “ሆረ ፊንፊኔ” “ሆረ ኪሎሌ” እየተባሉ ሰባቱ የዋቃ ሃይቆች ላይ አምልኮ ይፈጸማል።

ይህንን የባዕድ አምልኮ በዓል በዓመት ሁለት ጊዜ ይከበራል፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ሙሥሊም የሚያከብረው በዓል ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ብቻ እና ብቻ ናቸው፦
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፤ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው"። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏

ይህ እምነት ታሪካዊ ዳራው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ3000 ቅድመ ልደት እንደተጀመረ እና ጅምሩ የአንድ አምላክ አስተምህሮት እንደነበር ይገመታል ይነገራል፥ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 2007 ድህረ ልደት በተደረገው የሕዝብ እና ቤቶች ቆጠራ ከኦሮሞ ሕዝብ ወደ 3.3 በመቶ የሚደርሰው ሕዝብ የዚህ እምነት ተከታይ ነበር። በአሁኑ ጊዜ ይሄ ቁጥር ወደ 3 በመቶ ዝቅ እንዳለ ይነገራል፥ አንዳንዶች ደግሞ፦ “አብዛኛው ዋቄፈናን ከእሥልምና ጋር ወይንም ከክርስትና ጋር ቀይጦ ነው የሚያመልከው” ይላሉ። ይህ ስህተት ነው፥ ምክንያቱም የሚያመልኩት ዋቃ አንድም ቀን እንዴት መመለክ እንዳለበት አልነገራቸውም። ደግሞም “አይናገርምም” ይላሉ፥ እነርሱም ባወጡት ሰው ሠራሽ አምልኮ ያመልኩታል።

"የመውሊድ በዓል ቢድዓህ ነው፥ የገና እና የፋሲካ በዓል ሐራም" ብለህ እየተቃወምክ ኢሬቻ ላይ መሳተፍ እና በዓሉን ማክበር በምን ሞራልህ እና ስሌትህ ነው "ሐላል ነው፥ ባህል ነው" የምትለው? ስለዚህ እዚህ እምነት ውስጥ ያላችሁ ዋቄፈታዎች የነቢያት አምላክ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። ሙሥሊሞች ሆናችሁ ይህንን በዓል ባለማወቅ የምታከብሩም እና የምታመልኩ ካላችሁ በንስሓ ወደ አሏህ ተመለሱ! አሏህ ወደ እርሱ በመጸጸት ለሚመለሱት ይቅር ባይና አዛኝ ነው፦
2፥160 እነዚያ ከመደበቅ የተጸጸቱና ሥራቸውን ያሳመሩም የደበቁትን የገለጹም ብቻ ሲቀሩ፡፡ እነዚህም በእነርሱ ላይ ጸጸታቸውን እቀበላለሁ፤ እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ ነኝ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ تَابُوا وَأَصْلَحُوا وَبَيَّنُوا فَأُولَـٰئِكَ أَتُوبُ عَلَيْهِمْ ۚ وَأَنَا التَّوَّابُ الرَّحِيمُ

"እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ ነኝ" ብሎ የተናገረን አምላክ በብቸኝነት ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም ቤተ መጣጥፍ ብዙ ሰዎች እያነበቡ እየተለወጡበት ይገኛል። ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ይህንን ቤተ መጣጥፍ ከ 37 ሺህ ወደ 100 ሺህ ለማስገባት የእናንተ ሼር ማድረግ እና እርብርብ ይጠይቃል። ሊንኩ ይህ ነው፦
https://t.me/Wahidcom

ይህንን ቻናል በተሻለ ረብጣ አሳብ ለማረቅ እና ለማሳለጥ የምትፈልጉ በኮሜንት ክፍል ውስጥ አስተያየታችሁን ማስፈር ትችላላችሁ።

ጥሪአችን ሰዎች አንዱን አምላክ በብቸኝነት እንዲያመልኩ ነው፦
24፥55 በእኔ ምንን ነገር የማያጋሩ ሆነው ያመልኩኛል፡፡ ከዚያም በኋላ የካደ ሰው እነዚያ እነርሱ አመጸኞች ናቸው፡፡ يَعْبُدُونَنِي لَا يُشْرِكُونَ بِي شَيْئًا ۚ وَمَن كَفَرَ بَعْدَ ذَٰلِكَ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْفَاسِقُونَ
ዐቂዳህ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا

"ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለው ቃል "ዐቀደ" عَقَدَ ማለትም "ቋጠረ" "ያዘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መቋጠር" "መያዝ" ማለት ነው፥ "ዐቃኢድ" عَقَائِد ደግሞ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፦
113፥4 “በየተቋጠሩ” ክሮች ላይ ተፊዎች ከኾኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፡፡ وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "የተቋጠሩ" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቀድ" عُقَد እንደሆነ ልብ አድርግ!  ለምሳሌ፦ የጋብቻ ቃል ኪዳን "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاح ተብሎ ይጠራል፦
2፥237 ለእነርሱም መወሰንን በእርግጥ የወሰናችሁላቸው ስትኾኑ ሳትነኳቸው በፊት ብተፈቷቸው ካልማሩዋችሁ ወይም ያ "የጋብቻው ውል" በእጁ የኾነው ባልየው ካልማረ በስተቀር የወሰናችሁት ግማሹ አላቸው፡፡ وَإِن طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِن قَبْلِ أَن تَمَسُّوهُنَّ وَقَدْ فَرَضْتُمْ لَهُنَّ فَرِيضَةً فَنِصْفُ مَا فَرَضْتُمْ إِلَّا أَن يَعْفُونَ أَوْ يَعْفُوَ الَّذِي بِيَدِهِ عُقْدَةُ النِّكَاحِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "የጋብቻው ውል" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاحعُقَد ነው፥ ስለዚህ አንድ ሰው እኔን፡- "ዐቂዳህ" ምንድነው? ብሎ ቢጠይቀኝ ጥያቄው፡- በልብህ አምነህ የያዝከው እና የቋጠርከው ምንድነው? ማለቱ ነው።
ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ሸሪዓዊ ፍቺው ደግሞ "አንቀጸ እምነት" "ዶግማ" ማለት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን "መሠረት" "መርሕ" "አንቀጸ እምነት"creed" ማለት ነው፦
ሡነን አድ ዳርሚይ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 231
ዐብዱር ረሕማን ኢብኑ አባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ":እንዲህ አሉ፦ "የሙሥሊም ልብ በሦስት ጉዳይ "አያምንም" ጀነት የሚገባበት ቢሆን እንጂ፥ እኔም፦ "ምንድን ናቸው? አልኩኝ። እርሳቸው፦ "ለአሏህ ብሎ በኢኽላስ መሥራት፣ ለአሚር ቅን ምክር መስጠት እና ጀመዓን አጥብቆ መያዝ"። عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ أَبَانَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ :" لَا يَعْتَقِدُ قَلْبُ مُسْلِمٍ عَلَى ثَلَاثِ خِصَالٍ إِلَّا دَخَلَ الْجَنَّةَ "، قَالَ : قُلْتُ : مَا هُنَّ؟، قَالَ : إِخْلَاصُ الْعَمَلِ لِلَّهِ، وَالنَّصِيحَةُ لِوُلَاةِ الْأَمْرِ، وَلُزُومُ الْجَمَاعَةِ،

እዚህ ሐዲስ ላይ "የዕተቂዱ" يَعْتَقِدُ የሚለው "ዩእሚኑ" يُؤْمِنُو በሚል የመጣ ነው፥ ቁርኣን ላይ "ኢማን" إِيمَان የሚለው "ኢዕቲቃድ" اِعْتِقَاد ማለት ነው፦
5፥89 አሏህ በመሐላዎቻችሁ በውድቁ አይዛችሁም፥ ግን መሐላዎችን "ባሰባችሁት" ይይዛችኋል፡፡ لَا يُؤَاخِذُكُمُ اللَّهُ بِاللَّغْوِ فِي أَيْمَانِكُمْ وَلَـٰكِن يُؤَاخِذُكُم بِمَا عَقَّدتُّمُ الْأَيْمَانَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሰባችሁት" ለሚለው የገባው ቃል "ዐቀድቱም" عَقَّدتُّم ሲሆን "በወጠናችሁት" ማለት ነው፥ "ዐቅድ" عَقْد ማለት በልብ ውስጥ ያለ "ውጥን" ማለት ሲሆን በልብ ውስጥ የሚቀመጥ ውጥን ደግሞ እምነት ነው።
አርካኑል ኢማን "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ናቸው፥ "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ማለት "ዶግማዊ"dogmatic" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ

"ነፍይ" نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማጽደቅ” ማለት ሲሆን ኢስባት "ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ነው፦
2፥256 “በጣዖት የሚክድ እና በአሏህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ገመድ በእርግጥ ያዘ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا

“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ በጣዖት መካድ ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه በአሏህ ማመን ነው፥ ከአርካኑል ኢማን አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "አመንቱ ቢላህ" آمَنْتُ بِاللَّه ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለውን ጠንካራ የአሏህን ገመድ መያዝ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ይባላል፦
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا

"ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ ገመድ ሰዎች ከጀሀነም እሳት ጉድጋድ አፋፍ ላይ እያሉ ተንጠንጥለው የሚድኑበት ገመድ ነው፦
3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا

አርካኑል ኢሥላም "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ናቸው፥ "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ማለት "ዶግማውያን"dogmatism" ማለት ነው። ከአርካኑል ኢሥላም አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ነው፥ ሙሉ ሁለንተናውን ለአሏህ የሰጠ ሙሥሊም ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ

እዚህ አንቀጽ "የሚሰጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሥሊም" يُسْلِمْ እንደሆነ ልብ አድርግ! ስለዚህ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ማለት "ሁለተኛ ወይም ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ" ሳይሆን የመጀመሪያ እና ዐቢይ የዲን ቅርንጫፍ ነው፥ "ዐቂዳህ ምንድን ነው? ሲባል "እርሱ ሁለተኛ እና ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ ነው" ብሎ ከመናገር በላይ የሚያሳፍር ነገር የለም። አምላካችን አሏህ ፈሣድን ከሚያስፋፉ ኢሕዋኑል ሙፍሢዱን ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
Video
ቴሊቲስሞስ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ

"ቴሎ" θέλω ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን ስለ "ፈቃድ" ያለው እሳቤ "ቴሊቲስሞስ" θελητισμός ይባላል፥ "ፈቃድ" ምንነትን"essence" ሳይሆን ማንነትን"person" ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ለምሳሌ፦ እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ሰው የሚለየው በምንነቱ ሳይሆን በማንነቱ ነው፥ እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ሰው የሚለየው በማንነቱ ስለሆነ እያንዳንዱ ሰው የራሱ "ፈቃድ" አለው። ፈጣሪ የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ መለኮታዊ ፈቃድ አለው፦
ሉቃስ 22፥42 ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ። πλὴν μὴ τὸ θέλημά μου ἀλλὰ τὸ σὸν γινέσθω.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ነው፥ ኢየሱስ አብን "አንተ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "አንተ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። ኢየሱስ ሰው ስለሆነ የሰው ማንነት እስካለው ድረስ "የእኔ ፈቃድ" ሲል "እኔ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "እኔ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ እና አብ ሁለት የተለያየ ፈቃድ ያላቸው ማንነቶች ናቸው፦
ዮሐንስ 5፥30 የላከኝን ፈቃድ እንጂ የእኔን ፈቃድ አልሻምና። ὅτι οὐ ζητῶ τὸ θέλημα τὸ ἐμὸν ἀλλὰ τὸ θέλημα τοῦ πέμψαντός με.

እዚህ አንቀጽ ላይ ላይ ሁለት ጊዜ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ሲሆን አብ እና ወልድ ሁለት የተለያየ"distinct" ፈቃዶች ያላቸው ናቸው። "ፈቃድ" ምንነትን ታሳቢ ቢያደርግ ኖሮ በምድር ላይ ያለው ሰው ሁሉ በምንነት አንድ ስለሆነ አንድ ፈቃድ ብቻ ይኖረን ነበር፥ ነገር ግን እውነታው እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት የሚለይበት እራሱን የቻለ የራሱ ፈቃድ አለው።

፨ በአገራችን የፕሮቴስታንት ዐቃቢ እምነት ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌ በአንድ ትምህርታቸው ላይ ዮሐንስ 5፥30 ሲያብራሩ፦ "ሁለት ፈቃድ አለ፥ ፈቃድ የሚባለው ነገር ማንነትን ሲገልጽ ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ ነውና እዚህ ጋር "የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና" በማለት ሁለት ፈቃድን ያሳያል" ብለዋል።

፨ አሜሪካዊ የክርስትና ዐቃቢ እምነት እና የሥነ መለኮት ምሁር ዊልያም ሌን ክሬግ"William Lane Craig" የተባሉት "Reasonable Faith" በሚል ድረ ገጻቸው ሦስቱ አካላት ሦስት ፈቃድ እንዳላቸው አስቀምጠዋል፦
"አንድ የማንነት ጠንካራ እሳቤ የራስ ንቃተ ሕሊና፣ ውጥን እና ፈቃድ ማዕከል እንዳለው ካረጋገጥን ያንን ተከትለን የሥላሴ አካላት ሦስት ፈቃዳት እንዳላቸው አስባለው"።
784 Monothelitism and the Trinity May 22, 2022
https://www.reasonablefaith.org/question-answer/P50/monothelitism-and-the-trinity

"ፈቃድ ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው ዘመናዊ የፕሮቴስታንት እሳቤ እኔ የምቀበለው እሳቤ ሲሆን ምናልባት ቀደማይ እና ታሪካዊ ፕሮቴስታንት ይህንን እሳቤ የሚቀበል አይመስለኝም።
"አብ እና ወልድ በውጫዊ ግብር ይለያያሉ፣ ሁለት የተለያየ ፈቃድ ስላላቸው አብ ላኪ ወልድ ተላኪ በመሆን የተለያየ የሥራ ድርሻ አላቸው" የሚለው የሎዶቂያው ኤጲስ ቆጶስ አቡሊናርዮስ ነው፥ ይህም እሳቤ በ381 ድኅረ ልደት በቆስጠንጢኒያ ጉባኤ ተወግዟል። የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ፊላታዎስ እና የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናስዮስ ሦስቱ አካላት አንድ ፈቃድ እንዳላቸው ተናግረዋል፦
ሃይማኖተ አበው 105፥1 "ሦስቱ አካላት በመለኮት አንድ ናቸው፥ አንድ ባሕርይ፣ አንድ መንግሥት፣ አንድ አሳብ፣ ፈቃድ ናቸው"።
ሃይማኖተ አበው 111፥4 "እኛ መለኮትን እና መንግሥትን ወደ መክፈል አንገባም፥ አንድ መለኮት፣ አንድ ባሕርይ፣ አንድ ፈቃድ፣ አንዲት ውድ፣ ሦስት አካላት እና ሦስት ገጻት ብለን በጎላ በተረዳ እናስተምራለን እንጂ"።

ሌላው በ 680 ድኅረ ልደት በ 3ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ ግብጽ እና ሶሪያ እንደ ሰደድ እሳት ተዛምቶ የነበረውን የልሙጥ ፈቃድ ሙግት ለማውገዝ የተሰበሰቡበት ነው፥ "ሞኖ ቴሊቲስሞስ" μόνο θελητισμός ማለት "ልሙጥ ፈቃድ" ወይም "ሞኖ ቴሌቲዝም"Mono thelitism" ሲሆን "ዲያ ቴሊቲስሞስ" δυο θελητισμός ማለት "ሁለት ፈቃድ" ወይም "ዲያ ቴሌቲዝም"Dyo thelitism" ማለት ነው። 3ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤው "ኢየሱስ ልሙጥ ፈቃድ ብቻ አለው" የሚለው ትምህርት አውግዞ በተቃራኒው "ኢየሱስ ሁለት ፈቃድ አለው" የሚለው እሳቤ አጽድቋል፥ "አንድ ነጠላ ማንነት"person" አንድ ፈቃድ አለው" በሚል መርሕ ከሄደን ኢየሱስን ሁለት ማንነት ያረገዋል። ካቶሊካውያን፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ እና ፕሮቴስታንት የሚያራምዱ "ዲያ ቴሊቲስሞስ" δυο θελητισμός ሲሆኑ የጽብሓውያን ኦርቶዶክስ"Oriental Orthodox" የሚያራምዱት ደግሞ "ሚያ ቴሊቲስሞስ" μία θελητισμός ነው፥ "ሚያ ቴሊቲስሞስ" μία θελητισμός ማለት "አንድ ፈቃድ" ወይም "ሚያ ቴሌቲዝም"Mia thelitism" ማለት ሲሆን "ከሁለት ፈቃድ አንድ ፈቃድ ሆነ" የሚል ነው።

እንደ ዲኑል ኢሥላም አስተምህሮት ኢየሱስ አንድ ልሙጥ የሰው ባሕርይ"human nature" ያለው ሰዋዊ ማንነት"human person" ሲሆን ያለው ፈቃድ ደግሞ ሰዋዊ ፈቃድ"human will" ነው። እንግዲህ አምላካችን አሏህ ስለ ዒሣ ምንነት እና ማንነት በቁርኣን የነገረን ቃል እውነተኛ ቃል ነው፦
19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ

“የምተሩነ” يَمْتَرُونَ ማለት “የሚከራከሩበት” ማለት ሲሆን ብዙ ሰዎች በዒሣ ምንነት እና ማንነት ቢከራከሩበትም አሏህ ስለ ዒሣ የነገረን ግን እውነተኛ ንግግር ነው፥ “ሂ” هِ ማለትም “እርሱ” የተባለው ዒሣ ሲሆን “እርሱ” በሚለው መነሻ ቅጥያ ላይ “ፊ” فِي የሚል መስተዋድድ ሲኖር “ስለ”about” በሚል የመጣ ነው፦
"That is Jesus, son of Mary. And this is a word of truth, “about” which they dispute".

አምላካችን አሏህ በዒሣ ዙሪያ የሚወዛገቡትን ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም