ትምህርት ሚኒስቴር
94.7K subscribers
272 photos
2 videos
81 files
40 links
ቀዳሚ የተማሪዎች የመረጃ ምንጭ 🇪🇹
Share and Support Us🙏

ማስታወቂያ ለማስነገር በዚህ ያናግሩን
@Adis_probot
Download Telegram
#MoE

ከሁለት ሳምንት በኋላ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በተመለከተ መጠናቀቅ ያለባቸውን ጉዳዮች ያላከናወኑ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝግጅቶቻቸውን እንዲያጠናቅቁ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

የመጀመሪያ ዲግሪ የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 03 እስከ 08/2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ አንዳንድ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተማሪዎቻቸው በቂ መረጃ  ያላደረሱ፣ ተማሪዎቹ የትና መቼ እንደሚፈተኑ ያላሳወቁ፣ ተማሪዎቻቸው ፈተናውን ከሚወስዱባቸው የመንግሥት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ያልተወያዩና መሰል ጉድለት እንዳለባቸው ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

በመሆኑም ክፍተቶቹ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲታረሙ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ተፈታኝ ተማሪዎች መረጃ ባለማግኘታቸው ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ተቋማቱ ኃላፊነት ይወስዳሉ ብሏል ሚኒስቴሩ።

ለማንኛውም ድጋፍና ማብራሪያ፦
          
ጡሪ ጭምዴሳ      0911-78-04-97           
ታምራት ከበደ       0913-56-67-17
ብሩክ አሰፋ           0913-30-77-30
አዲስ አለማየሁ     0913-71-57-72
ፋሲል ፀጋዬ           0911-33-56-83

@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
#MoE

ከ2016 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ሊሰጥ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች ቅበላን በተመለከተ በላከው ደብዳቤ እንዳሳወቀው፥ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና (Graduate Admission Test) ይሰጣል።

ሚኒስቴር ባደረገው ክትትልና ግምገማ "ጥቂት በማይባሉ የመንግሥትና የግል ትምህርት ተቋማት የድህረ ምረቃ ለመማር የሚያመልክቱ ተማሪዎች ምንም አይነት የመመዘኛና የመግቢያ ፈተና እንዳማይወስዱ" ለማወቅ መቻሉን ገልጿል፡፡

በመሆኑም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በ2016 ዓ.ም ተማሪ የሚቀበሉባቸውን የድህረ-ምረቃ ፕሮግራሞች (የፀደቁና ፈቃድ የተሰጣቸው) ዝርዝር እስከ ነሐሴ 20/2015 ዓ.ም እንዲያሳውቁ ተብሏል።

ተቋማቱ የተልዕኮና ትኩረት ልየታን መሰረት በማድረግ ለድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች ማስታወቂያ በማውጣትና በመመዝገብ ዕጩ ተማሪዎቻቸውን እስከ መስከረም 10/2016 ዓ.ም ሚኒስቴሩ ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና (Graduate Admission Test) ለተቀራራቢና ተመሳሳይ ፕረግራሞች በጋራ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፈተና ማዕከል ከመስከረም 20 እስከ 28/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

(ሚኒስቴሩ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የጻፈው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።)
@Adis_Media
@Adis_Media
#MoE

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ከሚማሩት ትምህርት ውጪ ወደ ተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሔደው ለሚያደርጓቸው የተግባር ላይ ልምምዶች የሚደረግ ወጪ÷ ከምርቃት በኋላ በሚከፍሉት የወጪ መጋራት ውስጥ እንዲካተት ጥናት መጀመሩ ተገለጸ፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የወጪ መጋራት (Cost Sharing) መመርያ መሠረት ወደ መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቀላቀሉ አዳዲስ ተማሪዎች÷ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ተመርቀው እስኪወጡ ድረስ፣ መንግሥት ለምግብና ለመኝታ ያወጣውን ወጪ በሚገቡት ውል መሠረት ከምርቃት በኋላ ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተደንግጓል፡፡

ተማሪዎች ወደ ተግባር ልምምድ ሲወጡ ለሚቆዩባቸው ጊዜያት ለሚኖራቸው የተግባር ላይ ትምህርት፣ ከምረቃ በኋላ ከወጪ መጋራት ጋር ተደምሮ እንዲከፍሉ ለማድረግ የትምህርት ሚኒስቴር ዕቅድ መያዙንና ጥናት መጀመሩን፣ በትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ተሾመ ዳንኤል ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡

ሐሳቡ በጥናት ላይ መሆኑንና ዓላማውም ወደፊት ተማሪዎች የተግባር ላይ ልምምድን ትኩረት ሰጥተው እንዲማሩ ለማድረግ በማሰብ የታቀደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ይሁን እንጂ ለክፍያው የልማት አጋር ድርጅቶች ለትምህርት ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ትስስር የሚመድቡት ገንዘብ ስለሚኖር፣ ከዚህ ገንዘብ ለወጪ መጋራት ሊከፈል የሚችልበት አሠራርም ሊዘረጋ እንደሚችልም አስረድተዋል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
#MoE

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተናን በኦንላይን የሚወስዱ ተፈታኞች በክላስተር የተዘጋጀ ማስፈንጠሪያ (URL) ላይ በመግባት እንዲለማመዱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

ከስር የተቀመጡት ማስፈንጠሪያዎች ተፈታኝ ተማሪዎች የሚለማመዱበት ሲሆን የፈተናው ዕለት ደግሞ መፈተኛ ይሆናሉ።

Note:

እስካሁን Username እና Password ያለገኛችሁ ተፈታኞች፤ ከትምህርት ቤት አስተባባሪዎች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ክላስተር አንድ

አዲስ አበባ፦ https://c2.exam.et
ሲዳማ ክልል፦ https://c2.exam.et
ትግራይ ክልል፦ https://c2.exam.et

ክላስተር ሁለት

ደቡብ ም/ኢ/ክልል፦ https://c3.exam.et
ጋምቤላ ክልል፦ https://c3.exam.et
አማራ ክልል፦ https://c3.exam.et

ክላስተር ሦስት

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፦ https://c4.exam.et
ሀረሪ ክልል፦ https://c4.exam.et
አፋር ክልል፦ https://c4.exam.et
ኦሮሚያ ክልል - 1
• አዳማ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• አጋሮ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• አምቦ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ አርሲ፦ https://c4.exam.et
• ምዕራብ አርሲ፦ https://c4.exam.et
• አሰላ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ባሌ፦ https://c4.exam.et
• ባቱ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቤሾፍቱ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቦረና፦ https://c4.exam.et
• ቡሌ ሆራ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቡኖ በደሌ፦ https://c4.exam.et
• ዶዶላ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ባሌ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ቦረና፦ https://c4.exam.et
• ጉጂ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ሐረርጌ፦ https://c4.exam.et
• ምዕራብ ሐረርጌ፦ https://c4.exam.et
• ሆለታ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ሆሮ ጉዱሩ፦ https://c4.exam.et
• ኢሉባቦር፦ https://c4.exam.et

ክላስተር አራት

ድሬዳዋ ከተማ፦ https://c5.exam.et
ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል - 2
• ጅማ፦ https://c5.exam.et
• ጅማ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ቄለም ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• ማያ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• መቱ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሞጆ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሞያሌ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ነጆ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ነቀምት ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሮቤ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሰንዳፋ በኬ፦ https://c5.exam.et
• ሻኪሶ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሻሸመኔ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሸገር ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሸኖ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ምስራቅ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• ሰሜን ሸዋ (ኦሮሚያ)፦ https://c5.exam.et
• ደቡብ ምዕራብ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• ምስራቅ ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ጉጂ፦ https://c5.exam.et
• ወሊሶ ከተማ፦ https://c5.exam.et

@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister