TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.6K photos
1.41K videos
203 files
3.86K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሐምሌ19

የፀጥታ ኃይሎች ዝግጅት ምን ይመስላል ?

(ሀዋሳ - ቅዱስ ገብርኤል)

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ጸጥታ እና ፖሊስ መምሪያ ከነገ በስቲያ ሐምሌ 19 የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓልን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የበዓሉን ታዳሚዎች ደህንነት ለማረጋገጥ አስተማማኝ ዝግጅት መደረጉን አሳውቋል።

የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በሠላም፣ በፍቅርና በመተሳሰብ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ እንዲከበር የህብረተሰቡ ሚና ወሳኝ መሆኑ ገልጿል።

በተለይም በከተማዋ በሚገኙ ሆቴሎች እና የትራንስፖርት አገልግሎቶች ላይ ጥብቅ ፍተሻ በማድረግ ለበዓሉ በሰላም መጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉ ተጠቁሟል።

ሀዋሳ ከነገ በስቲያ በሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ንግስ በዓል እጅግ በጣም ከፍተኛ የሰው ቁጥር ታስተናግዳላቸው ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
#ሐምሌ19

የፀጥታ ኃይሎች ዝግጅት ምን ይመስላል ?

(ቁልቢ ገብርኤል)

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ፤ በዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል ንግስ በዓል ላይ የሚታደሙ ምዕመናንን እና እንግዶችን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ አስተማማኝ ዝግጅት መደረጉን አሳውቋል።

ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የምስራቅ እና የምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ፣ የሐረሪ ክልል ፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ተቀናጅተው በቂ ዝግጅት አድርገዋል።

የንግስ በዓሉ ታዳሚዎች መጨናነቅ በሚበዛባቸው ቦታዎች ላይ በተለይ የደብሩ መግቢያና መውጫ በሮች አካባቢ የኪስ ቦርሳቸውን ፣ ሞባይላቸውን እና ሌሎች ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ እንዲይዙ ፖሊስ አሳስቧል።

አሽከርካሪዎች ወደ ንግስ በዓሉ ሲመጡ #ከኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_መለያ ወይንም ከህጋዊው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በስተቀር ሌላ ለፖለቲካ ማራመጃ የሚሆን ዓርማና ምልክት ይዞ መገኘት እንደማይቻል አሳስቧል።

በንግስ በዓል ላይ ሶስት ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያ እና የወንጀል ድርጊት ተጠርጣሪዎች ሲያዙ ውሳኔ ለመስጠት ዐቃቤ ህግና ጊዜያዊ ፍርድ ቤት ተቋቁሟል።

የበዓሉ ታዳሚዎች አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥማቸው በስልክ ቁጥር 0256665056 መጠቆም እንደሚችሉ ፖሊስ ገልጿል።

የአካባቢው የመሬቱ አቀማመጥ ዳገታማ፣ ቁልቁለታማና ጠመዝማዛ በመሆኑ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግና ደንብ አክብረው በማሽከርከር ከአደጋ እንዲጠበቁ ተብሏል።

ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ባለው ዋናው የተሸከርካሪ መንገድ ላይ ከባድ መኪና ማለፍ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።

#ENA

@tikvahethiopia