TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.8K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#GERD

" ... በወንዞቻችን ለመጠቀም እና ድህነትን ለማስወገድ የምናደርገው ጥረት እራሳችንን እና ጎረቤቶቻችንን ጭምር ለመጥቀም እንጂ ማንንም ለመጉዳት እንዳልሆነ ለዓባይ ልጆች ሁሉ ለማረጋገጥ እፈልጋለሁ " - የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ ሀኃይለማርያም ደሳለኝ

@tikvahethiopia
#GERD

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንጨርሰዋለን። የታላቁ ህዳሴ ግድብን የምንጨርሰው ልጆቻችንን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስም እንደምንችል እንዲያውቁት ስለምንፈልግም ጭምር ነው " - የአሁኑ የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ

@tikvahethiopia
#GERD🇪🇹

" የታላቁ ህዳሴ ግድብ 3ኛውን የውሃ ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ ነው ፤ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ በትኩረት እየተሰራ ነው " - ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ

የመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ ፥ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው የምትገኘው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ያለምንም ፀጥታ ችግር እንዲከናወን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ሌ/ጀኔራል ደስታ " ሠራዊቱ የተሠጠውን ተልኮ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት መፈፀም በመቻሉ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ ግብአቶች በሰላም ተጓጉዘው እንዲደርሱ እና ሰራተኞችም ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ማድረግ ተችሏል " ብለዋል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ #3ኛውን_የውሃ_ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ሌ/ጀኔራሉ " የግድቡ ግንባታ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ በትኩረት እየሰራ ነው " ብለዋል።

አክለውም " የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ ዕድገታችንን ለማደናቀፍ #ከሱዳን ሰርገው የሚገቡ ኃይሎችን እየተከታተለ ሴራቸውን እያከሽፈው ይገኛል ፤ በቀጣይም ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ሲቪል አመራሮች ጋር ተቀናጅቶ ግዳጁን በአስተማማኝ ለመወጣት ዝግጁነቱ የላቀ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

#FDRE_Defense_Force🇪🇹

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#GERD

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 3ኛ ዙር ሙሌት ከመጪው ሐምሌ ወር አንስቶ መከናወን እንደሚጀምር አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልወደዱ የግድቡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊን ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ ወደ ግድቡ የሚፈሰው የውኃ መጠን ከሰኔ አጋማሽ ጀምሮ ከፍ እያለ ከሄደ በኋላ ወደ ግድቡ የሚገባውን ውኃ በመያዝ በሐምሌ ወር ሙሌቱ ይጀመራል ብለዋል ኃላፊው።

በዚህ ዓመት ወደ ግድቡ እንዲገባ የሚጠበቀውን የውኃ መጠን ለመያዝ የግድቡን ቁመት የመጨመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል። የውኃ ሙሌቱ ሲጀመር የግድቡ ቁመት በሚፈለገው መጠን እንደሚደርስ አስረድተዋል፡፡

ባለፈው ዓመት ሁለተኛው ዙር የውኃ ሙሌት በሰኔ ወር መጨረሻ ሲጀመር በነሐሴ ወር አጋማሽ እንደሚጠናቀቅ ተነግሮ የነበረ ቢሆንም፣ በዓመቱ በነበረው ከፍተኛ መጠን ያለው የዝናብ ፍሰት የተነሳ መጠናቀቁ የተበሰረው ሐምሌ 12 ቀን 2013 ዓ.ም. ነበር።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#GERD #ETHIOPIA 🇪🇹

🇪🇹 የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ አቶ መለስ ዜናዊ ፦

" ... ምንም የሚያጠራጥር ነገር የለም፤ ይሄ ግድብ ይሰራል።

ይሄን ግድብ የሚያቆም ምንም ኃይል የለም። "

🇪🇹 የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ ሀኃይለማርያም ደሳለኝ ፦

" ... በወንዞቻችን ለመጠቀም እና ድህነትን ለማስወገድ የምናደርገው ጥረት እራሳችንን እና ጎረቤቶቻችንን ጭምር ለመጥቀም እንጂ ማንንም ለመጉዳት እንዳልሆነ ለዓባይ ልጆች ሁሉ ለማረጋገጥ እፈልጋለሁ "

🇪🇹 የአሁኑ የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፦

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንጨርሰዋለን። የታላቁ ህዳሴ ግድብን የምንጨርሰው ልጆቻችንን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስም እንደምንችል እንዲያውቁት ስለምንፈልግም ጭምር ነው "

#ታላቁ_የኢትዮጵያ_ህዳሴ_ግድብ💪

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #GERD

" አሁን ላይ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የኮንቮይ ጉዞ ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ ችሏል " - ኢ/ር በላቸው ካሳ

የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቀጠና በተገኘው ሰላም የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተገልጿል።

የግድቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጂነር በላቸው ካሳ ፤ " በቀጠናው የተገኘው አስተማማኝ ሰላም የግድቡን የግንባታ ሂደት #እያፋጠነው ይገኛል " ሲሉ አሳውቀዋል።

" የፀጥታው ጉዳይ ለግድቡ ግንባታ መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ ተልዕኮውን በጀግንነት በመፈፀም በቀጠናው የከፈለው መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ያኮራ በታሪክ የሚኖር ነው  " ብለዋል።

ኢ/ር በላቸው፤ በቀጠናው በነበረው የሰላም ችግር ምክንያት ወደ ግድቡ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች ከሁለትና ከሶስት ቀን በላይ በመቆም መስተጓጎል ይፈጥር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ የኮንቮይ ጉዞ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ መቻሉን አስረድተዋል።

የግድቡን ግንባታ ዳር ለማድረስ ሌት ተቀን ሃያ አራት ሰዓት ያለ ዕረፍት የሚተጉ የግንባታዉ ሰራተኞች የአካባቢውን የሙቀት ሁኔታ ተቋቁመው ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን በደማቅ ሞራል እየተወጡ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

በስፍራው ከሚገኙ የሀገር መከላከያ አባላት የቀጠናውን ዘላቂ ሰላም በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ በማረጋገጥ ሰራዊቱ የተሰጠውን ግዳጅ በሞራል እየተወጣ እነደሆነ ተናግረዋል።

ሰራዊቱ የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ ፀረሠላም የሆኑ ኃይሎችን ፍላጎት በማምከን የግድቡን የፍፃሜ ትንሳኤ ለማብሰር ደከመኝ ሳይል ሀገራዊ ተልዕኮዉን እየተወጣ ነው ብለዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#GERD🇪🇹

" በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ

ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።

ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው ፣ በፀሎታቸው በስራው ለተሳተፉ ምስጋና አቅርበው " እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።

ለኢዜአ ቃላቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዳግሞ ፤ ባለፉት 4 ዓመታት የውሃ ሙሌት ስራውን ለማከናወን የሚያስችል በቂ የዝናብ መጠን መገኘቱን አስረድተዋል።

የውሃ ሙሌት ስራው በታችኛው ተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከናወኑን ገልጸዋል።

ለአብነትም በዘንድሮው ክረምት በግብጽ የሚገኘው የአሰዋን ግድብ ከበቂ በላይ ውሃ በመያዙ ምክንያት በግድቡ ማስተንፈሻ አማካኝነት ውሃ የማፋሰስ ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት የትብብር ምንጭ ከመሆን ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚያስከትለው ጉዳት እንደሌለ በተግባር ያመላከተ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡

አሁን ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመሩት ሁለቱ ተርባይኖች በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ እንደሚገቡ አሳውቀዋል።

4ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ በግድቡ ግንባታ ሂደት ሌላኛውን አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከዚህ በኋላ የሚኖሩት ስራዎች ከዚህ ቀደም ከተለፈባቸው የተሻሉ እንደሚሆኑ የጠቀሱት ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ ፤ " ይህ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ስኬት ነው " ብለዋል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው…
#GERD🇪🇹

ግድቡ ከዚህ በኃላ ውሃ አይዝም ?

" 4ኛና የመጨረሻው ሲባል ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት " - ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቅን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የመጨረሻ ሙሌት " ሲሉ መግለፃቸውን ተከትሎ በርካቶች " ግድቡ ከአሁን በኃላ ውሃ አይዝም ? " የሚል ጥያቄ ፈጥሮባቸዋል።

ይህንን በተመለከተ ቃላቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ፦

" አራተኛና የመጨረሻው የውሃ ሙሌት የተባለው  አራቱ ዙሮች ከፍተኛ የውሃ መጠን የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ነው።

በእነዚህ አራት ዙሮች ግድቡ መያዝ ያለበትን የውሃ መጠን መያዝ ችሏል።

አራተኛና የመጨረሻው ሲባልም ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት።

ይልቁንም ግድቡ #እየተጠናቀቀ በመሆኑ ፣ ከፍተኛ የውሃ መጠን ሳያስፈልግ ይከናወናል። "

Credit - Ethio FM 107.8

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው…
#GERD🇪🇹

ኢትዮጵያ በትላንትናው ዕለት አራተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት ማጠናቀቋን በይፋ ማሳወቋ ይታወሳል።

የውሃ ሙሌቱን በተመለከተ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ፤ የውሃ ሙሌት ስራው በታችኛው ተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከናወኑን መግለፃቸው አይዘነጋም።

በተለይ በዘንድሮው ክረምት በግብጽ የሚገኘው የአሰዋን ግድብ ከበቂ በላይ ውሃ በመያዙ ምክንያት በግድቡ ማስተንፈሻ አማካኝነት ውሃ የማፋሰስ ስራ ሲያከናወን መቆየቱን በመጠቆም ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት የትብብር ምንጭ ከመሆን ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚያስከትለው ጉዳት እንደሌለ በተግባር ያመላከተ ስለመሆኑ አብራርተዋል።

ግብፅ ግን በግድቡ ውሃ ሙሌት ዜና መበሳጨቷን የሚገልፅ መግለጫ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል አውጥታለች።

ኢትዮጵያ የግድቡን ውሃ ሙሌት ያከናወነችው መጋቢት 14፣ 2007 ዓ/ም ላይ በግብፅ ፣ ኢትዮጵያ ፣ ሱዳን የተፈረመውን የመርሆዎች ስምምነት በሚጥስ ሁኔታ ነው ብላለች ግብፅ።

" በተፈራረምነው የመርህዎች ስምምነት መሠረት በግድቡ አሞላል እና ኦፕሬሽን ላይ አስገዳጅ ስምምነት ሳይደረስ የውሃ ሙሌት ማድረግ የተከለከለ ነው " ስትል ገልጻለች።

" የኢትዮጵያ የአንድ ወገን እርምጃ በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች የተረጋገጡትን የታችኛው ተፋሰስ አገራትን ጥቅምና መብት እንዲሁም የውሃ ደኅንነታቸውን ያላገናዘበ ነው "  ብላለች።

በሥልጣን ሹኩቻ በርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የገባችው የታችኛው ተፋሰስ አገር ሱዳን የ4ኛው ዙር የውሃ ሙሌትን በተመለከተ እስካሁን ያለችው ነገር የለም።

ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ የሕዳሴ ግድብ ውሃ አሞላል እና ኦፕሬሽንን በተመለከተ በአዲስ አበባ፣ ካይሮ እና ካርቱም ተደጋጋሚ ድርድሮችን ያደረጉ ቢሆንም እስካሁን ከስምምነት መድረስ ሳይችሉ ቆይተዋል።

በቅርቡም ለሁለት ዓመት ያህል ተቋርጦ የቆየው ድርድር በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ በካይሮ ተካሂዶ ያለውጤት ተበትኗል። ይህ ውይይት በመስከረም 2016 በኢትዮጵያ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ተደርሷል።

ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱ እንዲሁም አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ፣ በታችኛው የተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንደማያደርስ በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
#GERD🇪🇹

" ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች " - ኢትዮጵያ

ባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን አዲስ አበባ ውስጥ የሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እንዲሁም ዓመታዊ የሥራ ሂደትን የተመለከተ መመሪያ ላይ የሦስትዮሽ ድርድር ሲያካሂዱ ነበር።

ድርድሩ ያለ ስምምነት ነው የተጠናቀቀው።

ኢትዮጵያ ምን አለች ?

- ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ እና በፍትሐዊ ድርድር የሶስቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ የመፍትሔ ሀሳብ ላይ ለመድረስ ያላትን ቁርጠኝነት ይዛ እንደምትቀጥል ገልጻለች።

- አራት ዙር ድርድር ተካሂዷል ፤ ይህ ድርድር የተካሄደው በጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና በፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ የጋራ መግባባት ነው።

- በአራት ዙሮች ኢትዮጵያ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ልዩነቶችን ለመፍታትና የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት አድርጋለች።

- ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች።

- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ አሞላል እና ዓመታዊ አሰራር መመሪያ እና ደንቦች ላይ የተደረገው ድርድር በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማመን ለመፍጠር እንጂ በአባይ ውሃ አጠቃቀም ላይ የኢትዮጵያን መብት ለመንጠቅ ያለመ አይደለም።

- ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በፍትሃዊና ምክንያታዊ አጠቃቀም መርህ ላይ በመመስረት የአሁንና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት ጥረቷን አጠናክራ ትቀጥላለች።

- አራተኛው ዙር ድርድር ከተጠናቀቀ በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ቻርተር እና የአፍሪካ ህብረት ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌን የሚጻረር መግለጫ ግብጽ አውጥታለች። ኢትዮጵያ በግብፅ በኩል የቀረበባትን የተሳሳተ መረጃ አትቀበለውም።

ግብፅ ምን እያለች ነው ?

* " ኢትዮጵያ የሦስቱንም አገራት ጥቅም ሊያስጠብቅ እና ሊያስማማ የሚችል የሕግም ሆነ የቴክኒክ መፍትሄዎችን ለመቀበል ዝግጁ አይደለችም " የሚል ነገር ይዛ ብቅ ብላለች።

* " የግድቡን አሞላል እና ኦፕሬሽን በቅርበት በመከታተል መብቴን አስከብራለሁ " ስትልም ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥታለች።

* ግብፅ " በግድቡ ምክንያት የትኛውም አይነት ጉዳት ቢደርስብኝ በዓለም አቀፍ ቻርተሮች እና ስምምነቶች መሠረት የውሃ ድርሻዬን እና ብሔራዊ ደኅንነቴን የመጠበቅ መብቴ የተጠበቀ ነው " ስትልም መግለጫ አውጥታለች።

🇪🇹 ኢትዮጵያ #በተደጋጋሚ ጊዜ አንዳቸውም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በአባይ ግድብ ምክንያት ጉዳት እንደማይደርስባቸው ይልቁንም እነሱኑ እንደሚጠቅም አሳውቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GRED🇪🇹 የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ 3ኛው እና 4ኛውን ተርባይኖች ሥራ መጀመራቸውን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አሳውቀዋል። " ሌሎቹ ዩኒቶች በተቀመጠላቸው እቅድ መሰረት በመከናወን ላይ ይገኛሉም " ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ " ወደታችኛው የአባይ ተፋሰስ ሀገራት ተጨማሪ ብስራት ከጉባ ተደምጧል " ብለው " የወንዝ ፍሰት ሳይስተጓጎል ከመቀጠሉም በተጨማሪ የግድቡ የውሃ ማስተንፈሻ በሮች ተከፍተው…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ETHIOPIA #GERD 🇪🇹

የታላቁ የሕዳሴ ግድብ መስሪያ ቤት ምን አለ ?

(ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት / አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የሰጠው ቃል)

- በቅርቡ 2 የግድቡ ተጨማሪ ተርባይኖች አገልግሎት በመጀመራቸው ከግድቡ የሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ወደ 1 ሺሕ 550 ሜጋዋት ከፍ ብሏል።

- ከዚሕ ቀደም ብሎ ሥራ የጀመሩ ሁለት ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 375 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫሉ።

- ከሰሞኑን የተመረቁት ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 400 ሜጋዋት ኃይል ያመነጫሉ።

- ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ከ5 ሺሕ ሜጋዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል።

- የግድቡ ግንባታ አሁን ወደ መጠናቀቁ ነው።

መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከፍተኛ ዋጋ የከፈለበት እና ብዙ ቢሊዮን ዶላር ያፈሰሰበት ግድብ ከአፍሪቃ ትልቁ የኃይል ማመነጫ ነው።

ቪድዮ ፦ PM OFFICE

#Ethiopia #AFP

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA #GERD 🇪🇹 የታላቁ የሕዳሴ ግድብ መስሪያ ቤት ምን አለ ? (ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት / አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የሰጠው ቃል) - በቅርቡ 2 የግድቡ ተጨማሪ ተርባይኖች አገልግሎት በመጀመራቸው ከግድቡ የሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ወደ 1 ሺሕ 550 ሜጋዋት ከፍ ብሏል። - ከዚሕ ቀደም ብሎ ሥራ የጀመሩ ሁለት ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 375 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫሉ።…
#GERD🇪🇹

ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ የላብና ደም አሻራ ያረፈበት የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ የአይን ብሌኑም ጭምር ነው።

ተማሪው ፣ ሰራተኛው ፣ ወጣቱ ፣ አዛውንቱ ለዚህ ግድብ ካለው ላይ ፤ ከሚበለው ቀንሶ ሰጥቶ ያሰራው ለትውልድ የሚያወርሰው ሀብቱና ቅርሱ ነው።

ይህ ግድብ ሀገር ውስጥ በየጊዜው በሚፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት ሀዘን፣ መከፋት፣ መበደል ሲመጣ እንኳን ሁሉም የውስጡን በውስጡ ይዞ " ሀገሬ ትቅደም " ብሎ ተጠናቆ በአይኑ ለማየት ሲል ብዙ ዋጋ የከፈለለት ነው።

በፖለቲካ አቋም፣ በሃሳብ፣ በአመለካከት እየተለያየ እንኳ የሀገሩን ጥቅምና ግንድቡን የሚነካበት ነገር ሲመጣ ሁሉን ጥሎ ሽንጡን ገትሮ የተራከረለት ፣ እስከመጨረሻው ድረስም ዋጋ የሚከፍልለት ነው።

ይህ ግድብ ገና ከመሰረቱ እንዳይገነባ ፤ ድጋፍም እንዳይመጣ ሲሯሯጡ የነበሩ ብዙ ናቸው።

እንዳይሳካ ያልፈነቀሉት ድንጋይ ፤ ያልሄዱበት ቦታ የለም። ግን አልሆነም ፤ ወደፊትም አይሆንም።

ዛሬም እነዚህ አካላት ለኢትዮጵያ እንደማይተኙ ግን ግልጽ ነው።

ኢትዮጵያ " የሰው ድርሻ አንድም አልነካም፤ የራሴን ግን እጠቀማለሁ " ማለቷ የሚያንጨረጭራቸው ሀገራት በግንባታው ወቅት ዛቻ ሲያዘንቡ ፣ እንዲቆም ለማስፈራራት ሲሞክሩ ፣ በአንድም በሌላ በዓለም አቀፍ መድረክ በውስጥ እና በይፋ ጫና ለማድረግ ሲሰሩ እንደከረሙ የአደባባይ ሚስጥር ነው።

ብዙ ብዙ ቢሞክሩም መክነው ቀርተዋል። አሁንም ግን ጩኸታቸው እንደቀጠለ ነው።

ለማደናቀፍ የሚደረገው ጥረትም እንደዛው እንደቀጠለ ነው።

አንዴ " የመሬት መንቀጥቀጥ ቢመጣ አይፈርሳል " ፤ አንዴ " ጥራቱ አስተማማኝ አይደለም ይደረመሳል " ፤ አልሆን ሲላቸው " በአየር እንመታዋለን ፣በቦንብ እናጋየዋለን " በማለት ብዙ ሲያወሩ ከርመዋል።

ከወሬ የዘለል ግን ምንም ማድረግ አይችሉም።

እዛው ያሉበት ሆነው የፈለጉትን ማሰብ ይችላሉ ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ እያለ ግን ማድረግ መንካት ግን ፈጽሞ አይቻልም።

#Ethiopia
#GERD
#TikvahEthiopia
#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ የላብና ደም አሻራ ያረፈበት የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ የአይን ብሌኑም ጭምር ነው። ተማሪው ፣ ሰራተኛው ፣ ወጣቱ ፣ አዛውንቱ ለዚህ ግድብ ካለው ላይ ፤ ከሚበለው ቀንሶ ሰጥቶ ያሰራው ለትውልድ የሚያወርሰው ሀብቱና ቅርሱ ነው። ይህ ግድብ ሀገር ውስጥ በየጊዜው በሚፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት ሀዘን፣ መከፋት፣ መበደል ሲመጣ እንኳን ሁሉም…
የግብፅ ነገር ?

ሀገራችን ኢትዮጵያ " እኔ ማንንም ሳልጎዳ የራሴን ሃብት እጠቀማለሁ " ብላ በራሷ የዓባይ ወንዝ ላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለመገንባት መሰረት ከጣለችበት ጊዜ አንስቶ ስትጮህ ፣ ስትዝት፣ ለማስፈራራት ስትሞክር የነበረችው ግብፅ ዛሬም ግድቡ ወደ መጠናቀቁ ደርሶም ዛቻና ቀረርቶዋን አላቆመችም።

ዛሬ ወደ ተመድ ፀጥታው ምክር ቤት አንድ ደብዳቤ ልካለች።

ሀገሪቱ በቅርቡ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ግድቡን ከጎበኙና ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ መግባታቸውን ካበሰሩ በኃላ ስለ ግድቡ ውሃ መያዝ እና ከሞላ ጎደል የሲቪል እና ኤሌክትሮ መካኒካል ስራ ወደ መጠናቀቁ መድረሱን በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ እጅግ አናዷታል፤ አንጨርጭሯታል።

ለጸጥታው ም/ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ላይም " በግብፅ መንግሥት ዘንድ ተቀባይነት የለውም " ብላለች።

ሀገሪቱ ግድቡን ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያን ጎረቤቶቿን ተንኳሽ አድርጋ ለማቅረብም ሞክራለች።

ኢትዮጵያ ስንት አመት ሙሉ ለሁሉም ጠቃሚ በሆነ መንገድ መፍትሄ ለማምጣት እንነጋገር እንስማማ ፤ መፍትሄ እንዲመጣ ቁርጠኛ ነኝ ስትል እንዳልከረመች ግብፅ እንደሁል ጊዜ ክሷ " ኢትዮጵያ ሌሎችን አግልላ የአንድ ወገን ፖሊሲ ታራምዳለች፣ መፍትሄ እንዲመጣም አትፈልግም " ብላለች።

ግብፅ ለጸጥታው ምክር ቤት በጻፈችው በዚህ ደብዳቤ ፤ " ኢትዮጵያ እየተከተለች ነው ያለችው ህገወጥ ፖሊሲ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ማለትም በግብፅ እና በሱዳን ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል " የሚል የተለመደውን ክሷን አቅርባለች።

" ጥቅሜን ለማስጠበቅ ሁሉንም አይነት ህጋዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ " ስትልም ዛቻዋን ገልጻለች።

" ሁኔታዎችን በቅርብ እየተከታተልኩ ነው " ያለችው ሀገሪቱ " ህልውናዬን እና የህዝቤን ጥቅም ለማረጋገጥ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር የተረጋገጡ ሁሉንም አይነት እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅቻለሁ ነው " ያለችው።

ግብፅ እንዲህ አይነት ዛቻ ስታሰማ ይህ የመጀመሪያ አይደለም። ገና ግድቡ መገንባት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እንዲሁ ስትል ነው የኖረችው።

ምንም እንኳን በቀጥታ ሞክራው ባታውቅም ኢትዮጵያን ይጠላሉ፣ ወይም ያዳክሙልኛል የምትላቸውን ኃይሎች በግልፅና በህቡ ስትደግፍ ፤ የግድቡን ስራም ለማደናቀፍ ስትሰራ ነው የኖረችው።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቅፍ ጫና ለማሳደር ሁሌም እንደተሯሯጠች ነው ፤ ግድቡ ግን ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። አሁን ላይም ወደመጠናቀቁ ነው። ግብፅ ዛቻዋን አላቆመችም፤ አርፋም አልተቀመጠችም። በምንም አይነት መንገድ ለኢትዮጵያ የምትተኛም አይመስልም። " ኢትዮጵያን ይጎዳል " የምትለውን ክፍተት ሁሉ ከመጠቀም ወደኃላ የምትመለስም አይደለችም።

የፈለገችውን ብትሞክር ፣ ብትዝት፣ ብታወራ በተግባርና በቀጥታ ግን ኢትዮጵያን መንካት ፈጽሞ አትችልም።

#TikvahEthiopia
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#GERD🇪🇹

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሶማሊያ ? ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ #ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲህ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት አሻክራለች። የሀገሪቱ ፕሬዜዳንትም በየጊዜው በተለይ ወደ ግብፅ ሲመላለሱ ነው የከረሙት። በቅርብ ደግሞ ግብፅ ሄደው ከፕሬዜዳንት አልሲሲ ጋር ወታደራዊ ስምምነት ፈጽመው ነው የመጡት። ትላንት ደግሞ የጦር መሳሪያዎችን የጫኑ ሁለት የግብጽ የጦር አውሮፕላኖች በሞቃዲሾ ገብተዋል።…
የግብፅ ነገር #2 ?

ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር በባህር በር ጉዳይ የመግባቢያ ስምምነት በተፈራረመች ወቅት ሰዓታት ሳይቆጠር ተቃውሞ ያሰማችው ግብፅ ነበረች።

ከሶማሊያ ጋር ተደዋውላም  " አይዞሽ እኔ አለሁልሽ፤ በማንኛውም መንገድ አብሬሽ ቆማለሁ " ብላት ነበር።

ባለስልጣናቶቿም ኢትዮጵያ ለሶማሊያን ስንትና ስንት የደም ዋጋ እንዳልከፈለች ዛሬ ደፍረው " ኢትዮጵያን እንዳለመረጋጋት ምንጭ " አድርገው ለመሳልም ሞክረዋል።

የኢትዮጵያን ስም እያነሱ ሲለፈልፉ ከርመዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ከኢትዮጵያ ጋር መቃቃር ውስጥ ገብተው ወደ ግብፅ ሲመላለሱ ነው የከረሙት።

በቅርብ ደግሞ " ከግብፅ ጋር ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረምን " ብለው ብቅ ብለዋል።

ይህ ተሰምቶ ብዙ ሳይቆይ የተለያዩ የጦር መሳሪያ ቁሳቁሶችን የያዙ የግብፅ ፕሌኖች ሞቃዲሾ ሲያርፉ እና ቁሳቁስ ሲያራግፉ ነው የከረሙት።

ሶማሊያ ደም አፍስሶ ዋጋ የከፈለላትን የኢትዮጵያ መከላከያ በATMIS እንዲቀጥል አልፈልግም ማለቷ ፤ ግብፅ ደግሞ በሶማሊያ ወታደሮቼን ማሰማራት ፈልጋለሁ ማለቷ አስገራሚ ነገር ሆኗል።

" እኛ የግብፅ ወታደር እንዲመጣ አንፈልግም፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ዋጋ ከፍለውልናል ፤ እንዳይወጡ " ያሉ የሶማሊያ የምክር ቤት ሰዎች እና ነዋሪዎች አደባባይ ወጥተው ድምጻቸውን አሰምተዋል።

ፕሬዝዳንቱ " ኢትዮጵያን በአቋማችሁ ደገፋችኋል " ያላቿውን ሰዎችን ከስራ ማባረር እንደተያያዙ ተሰምቷል።

ይኸው ቀጠናዊ ጉዳይ እንዳለ ደግሞ ግብፅ ሆዬ የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብን ጉዳይ በማንሳት " ማንኛውም አይነት እርምጃ ውስዳለሁ " ብላ ዛቻ ማሰማት ጀምራለች ፤ ምንም እንኳን የግብፅ ዛቻ አዲስ ባይሆንም።

እዛው ባለችበት በርቀት ሆና መዛት ፤ መጮህ ፣ ማውራት መብቷ ነው ኢትዮጵያን መንካት ግን ፈጽሞ አትችልም።

#TikvahEthiopia
#GERD🇪🇹

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA🇪🇹

" ልንከተለው የሚገባው ፖሊሲ አለመፍራት ነው ፤ ... አለመፍራት ሲባል ማንቀላፋት ማለት አይደለም " - አቶ መልስ ዜናዊ (የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ)

የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ፓርላማ ቀርበው ማብራሪያ ሲሰጡ በግብፅ ጉዳይ ተናግረው ነበር። ንግግራቸው የፓርላማ አባላትን ፈገግ ያሰኘ ደግሞም ጠንከር ያለ ነበር።

ምን ነበር ያሉት ?

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ፦

" ... የግብፅ መንግሥት #የጥፋት_መንገድ ለማንም እንደማይጠቅም ፤ ተከባብሮ እና ተጠቃቅሞ መኖር እንደሚቻል እንዲገነዘብ ማድረግ ነው ዋናው ስትራቴጂያችን።

አንዱ የግብፅ ስትራቴጂ ትልቅ ወታደር አስቀምጦ ማስፈራራት ነው ፤ ይሄን በተመለከተ ልንከተለው የሚገባው ፖሊሲ አለመፍራት ነው የሚሆነው ማለት ነው።

አለመፍራት ሲባል የቀረርቶ ጋጋታ ማስቀመጥ ማለት አይደለም፤ አለመፍራት ሲባል ማንቀላፋት ማለት አይደለም፤ አለመፍራት ሲባል በተጨባጭ በሀገራችን ላይ ሊቃጣ የሚችለው ወረራ ምን ያህል ነው ? ብሎ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፈተሽ ማለት ነው።

ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ሲፈተሽ የግብፅ ወረራ አደጋ በኢትዮጵያ ላይ በጣም ትንሽ ነው። ዜሮ ነው ማለት ግን አይቻልም። ነገር ግን በጣም ትንሽ ነው።

ስለዚህም በዚህ በጣም ትንሽ በሆነ አደጋ ምክንያት እንቅልፍ የምናጣበት ምክንያት የለም። ይሄ ማለት ዜሮ ሳላልሆነ ያቺ ትንሿን አደጋ ለመቋቋም ተጨማሪ የአቅማችንን ያህል ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል።

ይሄን የምናደርገው ግብፅ ይወረናል ብለን ቡራ ከረዮ ለማለት አይደለም። አደጋው በጣም ትንሽ ነው መፍትሄው በጣም ቀላል ነው ፤ መፍትሄው ተደጋግፎ መኖር ነው።

ዋናው ስትራቴጂያችን ላይ እየተረባረብን ምናልባት 5በመቶ እድልም ቢሆን 5በመቶ ትኩረት ሰጥቶ ለዚህ ጉዳይ የመከላከል አቅማችንን መገንባት ነው። "

#ETHIOPIA
#GERD🇪🇹

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ የላብና ደም አሻራ ያረፈበት የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ የአይን ብሌኑም ጭምር ነው። ተማሪው ፣ ሰራተኛው ፣ ወጣቱ ፣ አዛውንቱ ለዚህ ግድብ ካለው ላይ ፤ ከሚበለው ቀንሶ ሰጥቶ ያሰራው ለትውልድ የሚያወርሰው ሀብቱና ቅርሱ ነው። ይህ ግድብ ሀገር ውስጥ በየጊዜው በሚፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት ሀዘን፣ መከፋት፣ መበደል ሲመጣ እንኳን ሁሉም…
#ETHIOPIA🇪🇹

ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፦

" ሱዳን እና ግብፅ በጣም መደገፍ ያለባቸው ግድብ ነው።

ሰሞኑን በቀን እስከ 900 ሚሊዮን ሜትር ኪዩቢክ ውሃ በየቀኑ ይይዛል። ምን ማለት ነው በየቀኑ አንድ አንድ ቢሊዮን ከያዘ ይሄ አጠቃላይ አቅሙ 74 ቢሊዮን ስለሆነ በ74 ቀን ውስጥ ሙሉ ግድቡን መያዝ እንችላለን።

አንዳንዴ ሽርፍራፊ ስላለ በ100 ቀን ውስጥ ይሄ ግድብ ከ0 ተነስቶ ሙሉ መሆን ይችላል ፤ ያው በ100 ቀን ያን ያህል ውሃ አይገኝም ጊዜው ስለሚወጣ ስለሚወርድ ሃሳቡን ለመጨበጥ እንዲመቸን ነው።

በ100 ቀን እንደዚህ አይነት 10 እና 15 ግድቦች ኖረውን ውሃ ብንይዝ በማንኛውም ሰዓት የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ተጨማሪ ውሃ ቢያስፈልጋቸው ' ወንድሞቻችን ሆይ ለዚህ ለዚህ ጉዳይ እንደዚህ ፈልገናልና #እርዱን ' ብለው በቀላሉ መጠቀም ይችላሉ ፤ ምን ከሆነ ካለን ከያዝነው።

ዛሬ 4 ተርባይን ኢነርጂ እያመረተ ነው። ባለፈው ሁለት ነበር አሁን ሁለት ተጨምሮ እየሰራ ነው። ምናልባት በ3 ቢበዛ 4 ወር ዲሰምበር ላይ ተጨማሪ 3 ተርባይኖች ስራ ይጀምራሉ። ዲሰምበር ላይ፦
- 7 ተርባይን ኢነርጂ ያመርታል።
- በትንሹ 70 ወይም 71 ቢሊዮን ሜትር ኪዩቢክ ውሃ እንይዛለን።
- አንድ የማለቅ ማይልስቶን ያሳያል።

እስከ ሚቀጥለው ክረምት ድረስ ተጨማሪ የማጥራት ስራዎች ይኖራሉ አጠቃላይ ስራው ያልቃል ተብሎ የሚታሰበው የዛሬ ዓመት ክረምቱ ካለፈ በኃላ ሊሆን ይችላል።

ዲሰምበር ላይ አለቀ ብንልም ችግር የለውም የቀረው የብሪጁ ብቻ ነው ፤ ለብሪጁ ምሰሶ ቆሟል ብረቱን እየበየዱ ማሻገር ነው የቀረው ስራ። ያ ሲያልቅ የሲቪል ስራው 100% ይደርሳል።

የኤሌክትሮ መካኒካል ፔንስቶኩ ተገጥሟል፣ ታች ያለው አብዛኛው ስራ አልቋል ፤ ጄኔሬተሩን እያመጡ የመግጠም ስራ በገባባት ጊዜ ደረጃ ስለሚሄድ በሚቀጥሉት 6 ወራት አብዛኛው ነገር መልክ እየያዘ ይሄዳል።

ህዳሴን ከሞላ ጎደል ጨርሰነዋል። ከእንግዲህ በኃላ ህዳሴ ላይ ስጋት የለንም። ፋይናሻልም ሆነ ቴክኒካሊም ስጋት የለም።

ሊያደናቅፉን የሞከሩ ኃይሎች ገድለውን ሊሆን ይችላል፣ ሰዎችን አፈነውብን ሊሆን ይችላል፣ አንዳንድ መኪና ጎድተውብን ሊሆን ይችላል ግን አላቆሙንም ስራውን ጨርሰነዋል። ያሁሉ ጉልበት፣ ያሁሉ ገንዘብ፣ ያሁሉ ድካም ከንቱ ሆነ ማለት ነው።

ያ ገንዘብ እኛን ለመደገፍ አውለውት ቢሆን ኖሮ በተሻለ ቀና ትብብር ብዙ ነገር ጥቅም ላይ ሊውል ይችል ነበር። እኛ ለማደናቀፍ ገንዘብ መውጣቱ ተጨማሪ ሃብትና ጊዜ አባከኑ እንጂ አጠቃላይ ስራው እንዲቆም አላደረገውም።  "

https://youtu.be/8R7B3qPEB9U?feature=shared

#ETHIOPIA
#GERD🇪🇹

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA🇪🇹 ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፦ " ሱዳን እና ግብፅ በጣም መደገፍ ያለባቸው ግድብ ነው። ሰሞኑን በቀን እስከ 900 ሚሊዮን ሜትር ኪዩቢክ ውሃ በየቀኑ ይይዛል። ምን ማለት ነው በየቀኑ አንድ አንድ ቢሊዮን ከያዘ ይሄ አጠቃላይ አቅሙ 74 ቢሊዮን ስለሆነ በ74 ቀን ውስጥ ሙሉ ግድቡን መያዝ እንችላለን። አንዳንዴ ሽርፍራፊ ስላለ በ100 ቀን ውስጥ ይሄ ግድብ ከ0 ተነስቶ ሙሉ መሆን…
#GERD🇪🇹

ፕ/ር አታላይ አየለ ምን ነበር ያሉት ?

ኢትዮጵያ የሁለተኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ሙሌት ባከናወነችበት ወቅት በግብፅ ጉዳይ አንድ አስተያየት ሰጥተው ነበር።

ፕ/ር አታላይ አየለ ፦

" ግብፆች ' ግድቡን እንመታለን ' ምናምን የሚሉት ፣ የሚያስፈራሩት ነገር አለ።

የግድቡ ግዝፈት እንዲሁም ሚሰራበት ጥራት እውነት ለመናገር መቼውንም ቢሆን ተመቶ ይፈርሳል ተብሎ የሚታሰብ አይደለም።

እንደው ተሳክቶላቸው እንኳ ቢሆን የውሃ ሙሌቱ ልክ እንደ #ኒውኩሌር_ቦምብ ማለት ነው ለራሳቸው የሚሆነው ፤ ጠራርጎ ሜዴትራንያን ባህር ውስጥ ነው የሚጨምራቸው።

የቀድሞ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ' ግድቡን እኛ ሳንሆን እነሱ ናቸው የሚጠብቁት ' ብለዋል።

ስለዚህ ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያ ብዙ የሚያስጨንቃት አይደለም።

ቢፈልጉ ይደራደሩ በአካሄድ በሌሎች ጉዳዮች ፣ የውሃ ፣ አካባቢ ጥበቃና በሌሎች የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ። "

#TikvahEthiopia
#ETHIOPIA
#GERD🇪🇹

@tikvahethiopia