TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Alert🚨

የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል።

ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተያዘ ሰው #አለመኖሩን የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ አመልክቷል።

በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት እና ሞያሌን ጨምሮ በሌሎች የመግቢያ ቦታ ላይ የቁጥጥርና ማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።

በሽታው እስካሁን በ13 የአፍሪካ ሀገራት መከሰቱን እንዲሁም፣ 2,863 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው እና 517 ለህልፈት መዳረጋቸዉ መረጋገጡን የአፍሪካ ሲዲሲ መረጃ ያሳያል።

@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ። የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል። ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ…
#Alert🚨

ከተ.መ.ድ የጤና ኤጀንሲ እንደተገኘው መረጃ በቅርቡ ኤምፖክስ (Mpox) ለመጀመሪያ ጊዜ በ4 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ፦
- በጎረቤታችን ኬንያ ፣
- በቡሩንዲ ፣
- በሩዋንዳ
- በኡጋንዳ ተገኝቷል። ሀገራቱም ሪፖርት አድርገዋል። በነዚህ ሀገራት ውስጥ የታየው በሽታ በኮንጎ ካለው ጋር የተገናኘ ነው።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወይም Mpox በሽታ የሚከሰተው በቫይረስ አማካኝነት ነው።

ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። በወሲባዊ ግንኙነት ፣ በቆዳ ንክኪ ፣ በቅርብ ርቀት ሆኖ ማውራት/ መተንፈስ ፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ባለ የቅርብ ግንኙነት ይተላለፋል።

አሁን ላይ #ዋነኛዎቹ ናቸው የሚባሉት ሁለቱ የቫይረሱ ዝርያዎች Clade 1 - በማእከላዊ አፍሪካ ውስጥ ያለ ፤  Clade 1b - እጅግ በጣም አደገኛ የሆነው አዲስ የቫይረሱ ዝርያ ነው።

@tikvahethiopia
🏆የመጀመሪያውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በኦልድትራፎርድ ስታዲዮም ማን ዩናይትድ ከፉልሃም ጋር የሚያደርጉትን ፍልሚያ አርብ ነሐሴ 10 ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በSS Premier League እና SS Liyu ቻናል በሜዳ ፓኬጅ በቀጥታ ይከታተሉ!

⚽️ዩናይትድ ከኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ ሽንፈት በኋላ የዓመቱን የመጀመሪያ 3 ነጥብ ለማሸነፍ ይጫወታል!

🤔እናንተስ ከሊጉ የትኛውን ተጫዋች ለማየት ጓግታችኋል?

ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን  ወደ ሜዳ ያሳድጉ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት በቀጥታ ይከታተሉ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
ሴንት ማርክ ኢንተ. ስኩል ለ 2017 ዓ.ም ባካበት ነው የ12 ዓመት በላይ የመማር ማስተማር ልምድ ጥራት ያለውን የት/ት አሰጣጣችንን ተደራሽ ለማድረግ 22 ከሚገኘው ዋና ጊቢ በተጨማሪ በመገናኛ ፣ ጎተራ እና መሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅቱን ጨርሷል።

👉 እንዳያመልጦዎ የቀረን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀድመው ይመዝገቡ

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን  0912506470/71 ይደውሉልን

ለልጅዎ የሚገባ ት/ት ቤት
ሴንት ማርክ ኢንተ. ስኩል
Follow us : Telegram - https://t.me/SaintMarkSchool
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዕለታዊ

አንዱ አሜሪካን ዶላር ዛሬ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 103.9699 መግዣው ፤ በ114.6788 መሸጫ ተቆርጦለታል።

በግል ባንኮችም፥ ከ103 ብር አስንቶ (መግዣው) እስከ 117 ብር ድረስ እየተሸጠ ነው።

(የዛሬ ነሐሴ 9 የውጭ ሀገር ምንዛሬ ዋጋ ዝርዝር ከላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia " መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ አድርጉልኝ ፤ ፕሬዜዳንታችንንም እዛው ሊወጡ ሲሉ ይቅርታ ጠይቂያለሁ አሁንም ይቅርታ ደግሜ ደጋግሜ ጠይቃለሁ !! " - አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ምን አሉ ? " የብር ጉዳይ አይደለም። ለእኛ (ለአሰልጣኞች) እየተሰጠን ያለው Value የተለያየ ነው። እኔ አስተማሪ ነበርኩ ፤ በአስተማሪነት ለ9 ዓመት አገልግያለሁ የጠላሁት ማንም…
#Update

አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ፣ የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ከኢትዮጵያ መንግሥት የተበረከተላቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት " አልቀበልም " ብለው መልሰው ከመድረክ መውረዳቸው ይታወሳል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር " ገንዘቡ ወደ መንግስት ካዝና ተመላሽ ይሆናል። ምክንያቱም ስጦታ በግድ ውሰዱ ስለማይባል " ሲል ለኤፍ ኤም 97.1 ተናግሯል።

አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ፤ ለሙያውና ለአሰልጣኞች የሚሰጠው ክብር ዝቅ ያለ በመሆኑ በስሜታዊነት ያንን ነገር እንዳደረጉ በዚህም ፕሬዜዳንቷን እና መላው የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ መጠየቃቸው ይታወሳል።

አሰልጣኙ ገንዘቡን ካላስተካከሉት እንደማይቀበሉም ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ መናገራቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#Gambella

ከ6 አመት በላይ ጋምቤላ ክልልን ሲመሩ የቆዩት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ከስልጣናቸው ተነስተው አዲስ ፕሬዚዳንት ዛሬ ተሹሟል።

የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድን የክልሉ ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

ወ/ሮ አለሚቱ የዛሬው ሹመት እስኪሰጣቸው በኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን አገልግለዋል።

በክልሉ ም/ቤት " የአመራር ለውጥ ያስፈለገበት ምክንያት በሠላም እና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ዘርፍ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም የተቀመጡ አቅጣጫዎች ውስንነቶች በመታየታቸው ነው " ተብሏል።

የቀድሞው ፕሬዜዳንት አቶ ኡመድ ሌላ የፓርቲ ተልዕኮ እንደሚሰጣቸውም ተሰምቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ ጋትሏክ ሮን (ዶ/ር) ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።

@tikvahethiopia
🔈 #የሰራተኞችድምጽ

° " በየጊዜዉ የደመወዝ መዘግየቱ ህይወትን ከባድ አድርጎብናል " - የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሰራተኞች

° " አሁን ላይ ችግሩ ተቀርፏል ከዚህ በኋላ የደሞዝ መዘግየት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም " -ምላሽ የሰጡን አመራር


" የደመወዝ መዘግየት ፈተና ሆኖብናል " ያሉ የደቡብ ሬዲዬና ቴሌቪዥን ሰራተኞች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።

" ደመወዝ በየወቅቱ ሳይከፈል አይደለም እየተከፈለን እንኳን ኑሮ ከባድ ሆኖብናል " የሚሉት ሰራተኞቹ " በተለያዬ ምክኒያት በ25 ወይም በ26 የሚገባዉ ደሞዝ እስከሁለት ሳምንት እየዘገዬ መግባቱ ችግር እየፈጠረብን ነው " ብለዋል።

" አሁን ላይ የሀምሌ ወር ደሞዛችን ባለመግባቱ ቤት አከራዮቻችን ሽሽት ላይ ነን " የሚሉት ሰራተኞቹ " ኑሮን ደግሞ የምታዉቁት ነው " በማለት የሚመለከታቸዉ አካላት ለችግራቸው ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

በጉዳዩ ላይ ስሜ አይጠቀስ ብለዉ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ አንድ የድርጅቱ አመራር " አሁን ላይ ከሶስቱ ክልሎች ማለትም ከደቡብ ኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያና ከመእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሶ የበጀት መልቀቅና ገንዘብ የማዘዋወር እንቅስቃሴ ተጀምሯል " ሲሉ ተናግረዋል።

ከሶስቱ ክልሎች በተጨማሪ የሲዳማ ክልል ገና ዉሳኔ ላይ አለመድረሱን የገለጹት ኃላፊው ከነሱም ጋር ያለው ሁኔታ ቀስ ብሎ በውይይት መፍትሄ እንደሚፈለግለትና ከዚህ በኋላ ችግር ይኖራል ብለው እንደማያስቡ ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም የዚሁ ተቋም ሰራተኞች ከደመወዝ ጋር በተያያዘ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሰማታቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Tigray
 
መምህርቷ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።

በትግራይ፣ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ ነሀሴ 7/2016 ዓ.ም ሌሊት ጭካኔ የተሞላበት እጅግ አሰቃቂ ግድያ ተፈፅሟል።

አስቃቂ ግድያ የተፈፀመባት መምህርት ብርኽቲ ተስፋማርያም ትባላለች።

የትግራይ መምህራን ማህበር በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ በአባሉ ላይ በተፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት ዘግናኝ ግድያ የተሰማው ጥልቅ ሃዘን ገልጿል።

የዚህ እጅግ አሰቃቂ የወንጀል ተግባር ፈፃሚዎች በአስቸኳይ ተጣርተው ተመጣጣኝ ቅጣት እንዲጣልባቸውም ጠይቋል።

ሟች መምህርት ብርኽቲ ተስፋማርያም ከሑመራ ተፈናቅለው ከባለቤታቸውና 3 ልጆቻቸው በእንዳስላሰ ከተማ ይኖሩ እንደነበር ማህበሩ አመልክቷል።

" የሟች ባለቤት ቤት ውስጥ አለማደሩ ያጠኑና ያረጋገጡ ግፈኞች ነሀሴ 7/2016 ዓ.ም መምህርትዋ ልጆችዋ ፊት አርደው ገድልዋታል " ብሏል የመምህራን ማህበሩ።

" ይህ አስነዋሪ የግፍ ተግባር የትግራይ ህዝብ መልካም እሴት የሚፃረርና የሚያጎድፍ ሰይጣናዊ ተግባር ነው " ያለው መገለጫው " የፍትህ አካላት የአሰቃቂ ተግባሩ ፈፃሚዎች በማጣራት የህግ የበላይነት እንዲያረጋግጡ እንጠይቃለን " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ፣ የግድያ ተግባሩ የሚመለከት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ወደ እንዳስላሰ ሽረ ፀጥታና ፓሊስ ፅህፈት ቤት ስልክ ደውሏል።

የከተማው ፓሊስ ዋና አዛዥ የሆነ ኢንስፔክተር አወጠሀኝ ፣ የወንጀል ተግባሩ የማጣራት ጉዳይ በሃላፊነት የያዙት የወንጀል ማጣራት ሃላፊ መሓሪ ኪዳነ ደውሎ የሁለቱም የእጅ ስልካቸው አይነሳም።

ይሁን እንጂ ከከተማው የፀጥታ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ በሪሁ ባገኘነው መረጃ በሟችዋ መምህርት ላይ የተፈፀመው የወንጀል ተግባር የሚያጣራ ከጸጥታ ከፖሊስና የህግ አካላት የተውጣጣ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ ይገኛል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
#Ethiopia

" በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ያሉ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በመንግስትም ሆነ በታጣቂዎች በኩል እውነተኛ ከልብ የመነጨ ፍላጎት የለም።

በሁለቱ ክልሎች ባለው ግጭት ምክንያት ንጹሃን እየሞቱ፣ እየተፈናቀሉ፣  እየታገቱ እና ንብረታቸው እየወደመ ነው።

መንግስትም ሆነ በጫካ ያሉ አካላት ይህንን እያወቁ ችግሮቻቸውን በንግግር ለመፍታት ግን ፍላጎት የላቸውም።

ይህም መንግስት እየመራሁት ነው፣ ጫካ ያሉ አካላት ደግሞ እየታገልኩለት ነው ለሚሉት ህዝብ ያላቸውን ምልከታ ያሳያል።

በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ማድረግ ብቻውን መፍትሄ አያመጣም።

ሰላም የሚመጣው እውነተኛ ሰላም በመሻት እና በፖለቲካ ውሳኔም ጭምር ነው።

አሁን በመንግስት እና በታጣቂዎች መካከል እየታየ ያለው ግን መናናቅ እና አንዱ አንዱን ለማሸነፍ የሚደረግ ትግል ነው።

ይህ ደግሞ ንጹሀን ዜጎች ባሉበት ስቃይ እንዲቀጥሉ አድርጓቸዋል። "
- ደስታ ዲንቃ (የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ)

#ShegerFMRadio

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WachemoUniversity ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በስድስት ወራት ብቻ ለአንድ ሰው የ1 ሺህ 496 ቀን አበል / 1 ሚሊዮን 56 ሺህ 854 ብር አበል የተከፈለበት ግቢ ነው። የዚሁ ተቋም ፕሬዝዳንቱን እና ምክትል ፕሬዜዳንቱን ጨምሮ ሌሎችም ኃላፊዎቹ በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነግሯል። @tikvahethiopia
#WachamoUniversity

#በከባድ_የሙስና_ወንጀል የተጠረጠሩት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በአጠቃላይ በ6 ግለሰቦች ላይ የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ።

የክስ መመስረቻውን የፈቀደው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው።

ተጠርጣሪዎቹ ፦
1ኛ. የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሀብታሙ አበበ አጊሾ ( ዶ/ር)፣
2ኛ. የዩኒቨርሲቲው አካዳሚና ምርምር ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ታምራት ታገሰ ተኮራ (ዶ/ር)፣
3ኛ. ኮንትራክተር የሆነው ደሳለኝ አስረዳ፣
4ኛ. የዩኒቨርሲቲው የግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ ሙላቱ ኤርትሮ ጡንዳዳ፣
5ኛ. የዩኒቨርሲቲው የፋይናንስ ዳይሬክተር ማርቆስ ዮሃንስ ረገዮ እና
6ኛ. የቀድሞ የአዋሽ ባንክ ሆሳህና ቅርጫፍ ስራ አስኪያጅ የነበረው መለሰ ግርማ ኤርጋኖ ናቸው።

የዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ምን ይላል ?

ተጠርጣሪዎች በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፣ ለንግስት ኢሌኒ መታሰቢያ ሆስፒታል የኦክስጂን ማምረቻ ለማስገንባት መቀመጫውና ዋናው መ/ቤቱን ካናዳ ቶሮንቶ ካደረገ " ኤ. ኤ. ኤምዲ. ቴክኖሎጂ ኢንካ " ለተባለ ድርጅት የመንግስትን የግዢ መመሪያው ባልጠበቀ መንገድ በ5 አመት አፈጻጸሙ እየታየ መከፈል የሚገባውን አሰራሩን በመተላለፍ በውል ላይ የተዘረዘሩ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ባልተሰሩበት ሁኔታ ለድርጅቱ የ57 ሚሊየን 383 ሺህ 956 ብር ከ72 ሳንቲም ለታለመለት አላማ ሳይውል በመክፈል ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል።

የውል ማስከበሪያ የውሉን ጠቅላላ ዋጋ 10 ከመቶ ማለትም 117 ሚሊየን 10 ሺህ 859 ብር ከ60 ሳንቲም የውል ማስከበሪያ ሳይቀርብ እና ስራውም በውል ላይ በተገለጸው ጊዜ ሳይጠናቀቅ በመቅረቱ ይህ የውል ማስከበሪያ ዋስትና ቀርቦ ቢሆን ኖሮ ለመንግስት ገቢ መደረግ የነበረበትን ጥቅም አሳጥተዋል።

" ደሳለኝ አስረደ የግንባታ ስራዎች ተቋራጭ " የመምህራን መኖሪያ ቤት ሁለት (2) ህንጻ ግንባታ ስራ ግንቦት 2013 ዓ/ም እና ጥር 2016 ዓ/ም ላይ በተገባው ውል መሰረት ለዚሁ ህንፃ ተቋራጭ በተጋነነ ዋጋ በመስጠት 272 ሚሊየን 170 ሺህ 210 ብር ከ60 ሳንቲም ያለአግባብ ለተጨማሪ የግንባታ ወጪ መደረጉ ፤ ክፍያ በመፈጸም በዚህ ልክ በመንግስት ላይ ጉዳት በማድረስና ለውለታ 26 ሚሊዮን ብር ጥቅም ማስገኘትና ማግኘት።

በዝምድና እንዲሁም በትውውቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባለቤት እህት እና ሌሎች 2 ሰራተኞች ባልሰሩት ስራ በአበል መልክ የዩኒቨርሲቲውን ገንዘብ ያለአግባብ በመመዝበር ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።

ተጠርጣሪዎቹ ከሌሎች እስካሁን ድረስ እጃቸው ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣሪዎች ጋር በመመሳጠር በመንግስት ላይ 487 ሚሊየን 333 ሺህ 912 ብር ከ78 ሳንቲም ጉዳት እንዲደርስና ለሌሎች ያልተገባ ጥቅም እንዲያገኙ ተደርጓል።

ዐቃቤ ሕግ 15 ቀን የክስ መመስረቻ እንዲሰጠው ፍርድ ቤትን ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቆች ዋስታና ጠይቀዋል።

ፍ/ቤት የተጠርጣሪዎችን ዋስትና በማለፍ ለዐቃቤ ሕግ የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

Via https://telegra.ph/FBC-08-15

@tikvahethiopia
#Infinix_Note40_Pro_Plus

ኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G ከዘመኑ ጋር አብሮ የዘመነ ዓለም የደረሰባቸውን ቴክኖሎጂዎች በአንድ ላይ ያጣማረ ለርሶ ሚገባ ዘመናዊ ስልክ ነው፡፡

#Note40Et #Note40Pro #Note40 #Note40ProPlus #InfinixEt
#MesiratEthiopia

🌟 ፋይናንስ ትንበያ እና በጀቲንግ ስልጠና 🚀

የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም ያዘጋጀው የኦንላይን ፋይናንስ ትንበያ እና በጀቲንግ ስልጠና ላይ ይሳተፉ!

ቀን፡ ነሃሴ 10, 2016
ከቀኑ 8:00 - 11:00 ሰዓት

👉 አሁኑኑ በ https://forms.gle/ArtHvGNn2YxuDBst9 ይመዝገቡ!
--