TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.8K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Ethiopia

ዛሬ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ፥ በፓሪስ ኦሎምፒክ በወንዶች ማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው ጀግናው አትሌት ታምራት ቶላ 7 ሚሊዮን ብር እና የወርቅ ኒሻን ሽልማት አበርክተዋል።

ለሀገራቸው የብር ሜዳልያ ላመጡት አትሌት ትግስት አሰፋ፣ አትሌት በሪሁን አረጋዊ እና አትሌት ፅጌ ዱጉማ ለእያንዳንዳቸው የ 4 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቷል፡፡

የታምራት ቶላ እና ትግስት አሰፋ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ የሁለት ሚልዮን ብር ሽልማት ቢሰጣቸውም ለመቀበል ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

አሰልጣኙ ፥ " ፕሬዝዳንታችን እኛ አሰልጣኞች ለረጅም ጊዜ ለፍተናል ፣ ልፋታችንን አይመጥንም " ብለዋል።

" እኔ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ የወርቅና የብር ሜዳሊያ እንዲሁም ዲፕሎማ አስመጥቼ፤ ለዚህ ሀገር ተጋድዬ ለእኔ ሁለት ሚሊዮን ብር የስድብ ያህል ስለሆነ እርሶን ካላስከፋዎት ይህንን ሽልማቴን መመለስ እፈልጋለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።

" የሚመጣውን ሁሉ እቀባለለሁ " ሲሉም ተናግረዋል።

ቪድዮ ፦ ኢቢሲ መዝናኛ

Via @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ድርጅቱ ጉባኤውን እንዳያካሂድ እንቅፋት የሚሆን ከድርጅቱ የተፈለፈለ ከፍተኛ አመራር አለ " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)

የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ለሁለት የከፈለውና በብሔራዊ ምርጫ ቦርድም እውቅና የተነፈገው የህወሓት 14ኛ ጉባኤ መክፈቻ ዛሬ ተደርጓል።

የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በመክፈቻው ባሰሙት ንግግር ምን አሉ ?

ሊቀመንበሩ " ድርጅቱ ህጋዊ እውቅና እንዳያገኝና ጉባኤው እንዳያካሂድ እንቅፋት የሚሆን ከድርጅቱ የተፈለፈለ #ከፍተኛ_አመራር አለ " ብለዋል።

" በፓርቲያችን ውስጥ ተፈልፎሎ ያደገ፣ ፓርቲያችን ለመበተን እየሰራ ያለው የጥፋት ቡድን ያደረገውና አሁንም እያደረገው ያለው እንቅስቃሴ፥ በየሰዓቱ እየፈጠረው ባለው ማደናገርያ ሁኔታችን ከመጥፎ ወደ ከፋ ደረጃ ተሸጋግሯል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይህንም ለማስቆም በዘላቂነት ለመቀየር ብቸኛ መፍትሔው 14ተኛ ጉባኤ ማካሄድ እና ማካሄድ ብቻ ነው " ብለዋል።

" ህወሓት አድኖ ህዝብ ከጥፋት መታደግ የጉባኤው ዋነኛ አላማ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።

" የድርጅቱና የህዝቡ የተሟላ ድህንነት ማረጋገጥ በሚችል መልኩ በዴሞክራሲያዊ ውይይትና ክርክር ብቃት ያላቸው አመራሮች መምረጥ ይገባል " ሲሉ ተደምጠዋል።

" የአሁኑ ጉባኤ ለድርጅቱ የሞት የሽረት ጉዳይ ነው " በማለት አክለዋል።

" ህወሓት ፈረሰ ማለት የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ፈረሰ ማለት ነው " ብለው " በዚህ ግዜ ህወሓት ከፈረሰ የፕሪቶርያው ስምምነት አይኖርም ብቻ ሳይሆን ከነአካቴው ታሪክ ሆኖ ይረሳል ማለት ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ከፈረሰ የትግራይ ህዝብ ለበይ አሳልፎ መስጠት ማለት ነው " ሲሉም ተናግረዋል።

" ስለዚህ እነዚህ ችግሮችና አደጋዎች ለመፍታት ነው ጉባኤአችን በዚህ ፈታኝ ወቅት ለማድረግ የፈለግነው ብቻ ሳይሆን የግድም ልናደርገው የተገደድነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#ጉምሩክ

° “ ጉምሩክ ኮሚሽን አዋጅን በደብዳቤ ሽሮ ከእጥፍ በላይ ቀረጥ ‘ ክፈሉ ’ እያለን ነው ” - አስመጪዎች

° “ ከአፈጻጸም አኳያ ምን ሊያስቸግረን ይችላል ? የሚለውን ውይይት እየተደረገ ነው ” - ጉምሩክ ኮሚሽን

የጉምሩክ ኮሚሽን ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ምክንያት በማድረግ ከተቀመጠው አዋጅ ውጪ የቀረጥ ክፍያ እየጠየቃቸው መሆኑን አስመጪ ነጋዴዎች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አቤት ብለዋል፡፡

ነጋዴዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ ጉምሩክ እስከዛሬ የሚሰራበት አዋጅ ነበር።

አዋጁ፣ ‘ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡም ሆነ ከአገር የሚወጡ እቃዎች የቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ የሚሰላው ስለእቃዎቹ የቀረበው የእቃ ዲክላራሲዮን በተመዘገበበት ቀን በብሔራዊ ባንክ የተገለጸውን የገንዘብ ምንዛሪ በመጠቀም ይሆናል ’ ይላል፡፡

ግን አዋጁን በደብዳቤ ሽረው ‘እቃው በተመዘገበበት ሳይሆን እቃው ከጉምሩክ መልቀቂያ ባገኘበት ቀን ባለው ሬት ተሰልቶ ልዩነቱን እንዲከፍሉ>’ የሚል አዲስ መመሪያ አውጥተዋል፡፡

አዋጅ በደብዳቤ ይሻራል ወይ ? ግን ሽረውት ቅሬታ ለማቅረብ ከዋና መስሪያ ቤት ስንሄድ የተወሰንን ነጋዴዎች ተሰባስበን ቅሬታ ለማቅረብ በነበርንበት ጥያቄችንን ሳይሰሙን ፌደራል ፖሊስ መጣ የተሰበሰበውን ሰው እንዳለ በመኪና ጭኖ ይዟቸው ሄደ ፤ ወደ 40 ነጋዴዎችን፡፡

አዋጅን የሚያክል ነገር በአንድ ደብዳቤ ተሽሮ፣ ' ወደ ኋላ ተመልሳችሁ ክፈሉ ' የሚል አሰራር አመጡ፡፡

ሲቀጥል ጭማሪው እጅግ በጣም የተጋነነ ነው፡፡ በ57 ብር የተመዘገበን እቃ 100 በላይ ብር ክፈሉ እያሉ ነው፡፡ ከእጥፍ በላይ ነው የሚጠይቁት።

ለምሳሌ ፦ የቀድሞ የተመዘገበው ቀረጥ 2 ሚሊዮን ብር ከነበረ አሁን በእጥፍ 4 ሚሊዮን ብር ይሆናል፡፡ ጉምሩክ ያሉት ኦፊሰሮች እንኳ የሚሰሩበት ሲስተም የላቸውም፡፡ ' ዝም ብላችሁ አቻኩሏቸው ' ተብለው እቃችን እናዳለ ተይዟል ” ብለዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የነጋዴዎቹን ጥያቄና ቅሬታ ይዞ ለምን እንደዚህ ሆነ? ሲል የጠየቃቸው የኮሚሽኑ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥጠዋል፡፡

ምን አሉ ?

“ እንደሚታወቀው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ አስፈጻሚ ተቋማት የራሳቸውን ሚና አላቸው፡ አንዱ አስፈጻሚ ተቋም ጉምሩክ ኮሚሽን ነው፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን የተለያዩ ህጎችን ያስፈጽማል፡፡ አንዱ የብሔራዊ ባንክ ጋር ተያይዞ ያሉ ህጎችን የሚያስፈጽም ነው፡፡

በምን መልኩ መስተንግዶ መሰጠት እንዳለበት ውይይቶች ሲደረጉ ቆይቶ ነበር፡፡ ያ ሰርኩላር ከዛ ጋር በተያያዘ ነው የመጣው፡፡ ሰርኩላሩ አጠቃላይ ነገሮችን የያዘ ነው፡፡

ከተጠቀሱት የተወሰኑ ጉዳዮች ላይ አስመጪዎች ዋናው መስሪያ ቤት (አዲስ አበባ) አካባቢ ቅሬታውን ለማሰማት እንደመጡ ሰምቻለሁ፡፡

ከምን አንጻር ነው ይሄ ሰርኩላር ? ለሚለው ተጨማሪ ውይይቶች የሚያስፈልጉ ከሆነ ውይይቶች እየተደረጉ ነው፡፡ አጠቃላይ ሰርኩላሩን አንልም ሰርኩላሩ ተፈጻሚ ነው የሚሆነው፡፡ ግን ያነሷቸው ጉዳዮች ታይው ምላሽ ይሰጣል፡፡

በኋላ ብዙ አመጪዎችን ማወያየት እንደተቻለም ከአመራሮች ያገኘሁት መረጃ አለ፡፡

ግን አንዳንዴ እንዲሁ በጋራ መጥቶ አቤቱታዎችን የማሰማት ሁኔታዎች ሲኖሩ እዚያ አካባቢ ያሉትን ነገሮች ጸጥታ የማስከበር ሥራዎች ተሰርተው ሊሆን ይችላል፡፡

በኋላ ላይ ግን የተወሰኑ አስመጪዎችን በማናገር ያላቸውን ቅሬታ ኮሚሽኑ እንደሚያየው፣ ተገቢነት ያለው ከሆነ ሊፈታ፣ ከህግ አንጻር የሚያስኬድም ከሆነ በዚያው ሊቀጥል የሚችልበት እድል እንዳለ ነው የሰማሁት፡፡

አስመጪዎቹ የሚያነሳቸውን ጉዳዮችን ኮሚሽኑ ተረድቷል፡፡

ከህግ አንጻር ምን መሆን ነው ያለበት ? ከአፈጻጸም አኳያስ ምን ሊያስቸግረን ይችላል? የሚለውን ውይይት እየተደረገ ነው ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ጉዳዩ ከምን እንደሚደርስ ኮሚሽኑን ጠይቆ ምላሽ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia

🎁 በተወዳጆቹ ሜጋ ጥቅሎች ለወራት ያለሃሳብ ዳታ እንጠቀም! ለ90 እና ለ180 ቀን የሚቆዩትን ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎች በM-PESA በመግዛት እስከ 500 ብር የሚደርስ ቅናሽ አግኝተን ፏ እንበል! 🌐🤳 ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት!⚡️

🤖 የቴሌግራም ቦታችንን https://t.me/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
  
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#ዮናታን_ቢቲ_ፈርኒቸር
Yonatan BT Furniture

Conference table and Office table in different sizes
የውበት እና የጥራት ዳር ድንበር!


አድራሻችን፦
1. ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251 995 27 2727
2. ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251 957 86 8686
3. ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251 993 82 8282
👉 Telegram:  https://t.me/yonatanbt_furniture
👉 Instagram: https://www.instagram.com/yonatanbtfurniture/
👉 Facebook:  https://www.facebook.com/profile.php?id=100087238034736
👉 TikTok: https://www.tiktok.com/@yonatanbtfurniture
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ድርጅቱ ጉባኤውን እንዳያካሂድ እንቅፋት የሚሆን ከድርጅቱ የተፈለፈለ ከፍተኛ አመራር አለ " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ለሁለት የከፈለውና በብሔራዊ ምርጫ ቦርድም እውቅና የተነፈገው የህወሓት 14ኛ ጉባኤ መክፈቻ ዛሬ ተደርጓል። የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በመክፈቻው ባሰሙት ንግግር ምን አሉ ? ሊቀመንበሩ " ድርጅቱ ህጋዊ…
#TPLF

' ህወሓት ' ውስጥ እየሆነ ያለው ምንድነው ?

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከትግራዩ ጦርነት በፊት እንደ ህጋዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ስር ተመዝግቦ ይንቀሳቀስ ነበር።

ነገር ግን  ቦርዱ ፓርቲው " ኃይልን መሰረተ ያደረገ የአመጽ ተግባር ላይ ተሰማርቷል " በሚል ሰርዞታል።

የተወካዮች ምክር ቤትም ፓርቲውን " ሽብርተኛ ድርጅት " ሲልም ፈርጆት ነበር።

ደም አፋሳሹና አስከፊው ጦርነት እንዲያበቃ ፕሪቶሪያ ላይ ስምምነት ሲፈረም አንዱ ፈራሚ ይኸው ህወሓት ነበር።

በስምምነቱ ላይ ፓርቲው የተለጠፈበት የሽብርተኝነት ፍረጃ እንደሚፋቅ በግልጽ ሰፍሯል።

በዚህ መሰረት ከወራት በፊት ድርጅቱ ከሽብርተኛነት ተሰርዟል።

ነገር ግን የምዝገባው ጉዳይ ሌላ ነው።

ክፍፍሉ እና ' የቀደመ ህጋዊ ሰውነት ይመለስልኝ ' ጥያቄ ምንድነው ?

ህወሓት የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኃላ በውስጥ የኃይል ሽኩቻ ላይ ነበር።

አመራሮቹም ቀስ በቀሰ በሂደት የለየለት መከፋፈል ውስጥ ገብተዋል።

ምንም እንኳን በይፋ ባይወጣም ግልጽ ክፍፍል ይታይ ነበር።

ይህም በአቶ ጌታቸው ረዳ እና በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ቡድኖች መካከል ነው።

ባለፉት ወራት እጅግ በርከታ ስብሰባዎች ተደርገው የነበረ ቢሆንም ልዩነቶች ግን እየሰፉ እንጂ እየጠበቡ ሲሄዱ አልታዩም።

ከአንድነት ይልቅ መከፋፈሉ እና ሽኩቻው ጨምሮ ታይቷል።

በዚህ ሂደት ላይ ግን ህወሓት ፥ " ህጋዊ ሰውነታችን ወደነበረበት እንዲመለስ " የሚል ጥያቄ ለምርጫ ቦርድ ይቀርባል (ሚያዚያ ወር ላይ)።

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግን አንድ በአመጽ ተግባር ላይ ተሳትፎ የሰረዘውን ፓርቲ የቀደመው ህልውና መመለስ የሚያስችልበት የሕግ ድንጋጌ የለውም። በዚህም ጥያቄውን ሳይቀበለው ይቀራል።

ህወሓትንና ሌሎችንም ለመመዝገብ በሚል አዋጅ እስኪሻሻል ተደርጓል።

ህወሓትም ዳግም " ህጋዊው ሰውነቴ ወደነበረበት ይመለስ " ሲል በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረጽዮን በኩል ጥያቄ ያቀርባል።

በእርግጥ ሁሉም አመራሮች " የነበረው ህልውና ይመለስ " የሚለው ላይ ልዩነት የላቸውም።

የተሻሻለው አዋጅም ግን በአመጽ ተሳትፎ ለተሰረዘ ፓርቲ የቀደመ ህልውናውን መመለስ የሚያስችል የህግ ድንጋጌ አልያዘም።

ይህን ተከትሎም ቦርዱ " #በልዩ_ሁኔታ " በሚል ፓርቲውን መዝግቦታል።

ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልም ወደ አዲስ አበባ ሄደው ከምርጫ ቦርድ የተሰጠውን " በልዩ ሁኔታ " መመዝገቡን የሚገልጽ ህጋዊ የሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ፈርመው ወስደው መቐለ ሄደዋል።

ከዚህ በኃላ መቐለ ሄደው በሰጡት መግለጫ " እኛ ይሄን አንቀበልም ፤ የጠየቅነው ሌላ የተሰጠን ሌላ ነው " ሲሉ መግለጫ ሰጥተዋል።

" እኛ እንደዛ አልነበረም የተነጋገርነው ፤ የተባልነውም እንደዛ አልነበረም " የሚል ነገር አንስተዋል።

የእውቅና ምስክር ወረቀቱን ፈርመው ከወሰዱ በኃላ  " ከምቀደው ብዬ ነው ይዤው የመጣሁት " ብለዋል። ምዝገበውን እንደማይቀበሉት እና እንደተመዘገቡም እንደማይቆጠር ነው የገለጹት።

እነ አቶ ጌታቸው ረዳ በምስክር ወረቀቱ ጉዳይ ምንድነው አቋማቸው ?

- በምዝገባ ጉዳይ ለምርጫ ቦርድ የተላከው ደብዳቤ ማእከላዊ ኮሚቴ የማያውቀው በግለሰቦች የተላከ ነው።

- የተወሰኑ ግለሰቦች ናቸው ከድርጅቱ አሰራር ውጪ በቡድን በመሆን የፈረሙት እንጂ እኛ ለምዝገባ ብለን የፈረምነው ማንኛውም ሰነድ የለም።

- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ' ህወሓት ' ን አስመልክቶ ለተወሰኑ ግለሰቦች የሰጠው እውቅና #የተጭበረበረ በመሆኑ ዳግም ሊያጤነው ይገባል ... የሚል ነው።

ጉባኤው ?

የህወሓት ፅህፈ ቤት እና ማህተምን የተቆጣጠረው የነ ዶ/ር ደብረጾን ገ/ሚካኤል ቡድን ክፍፍሉ እና ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለው ልዩነት ሳይፈታ ለጉባኤ ዝግጅት ሲያደርግ ነበር።

በጣም አጭር ጊዜ ውስጥም የጉባኤ ተሳታፊ ለይቶ ጉባኤ ማካሄድ ጀምሯል።

ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው አንዱ የህወሓት ቁጥጥር ኮሚሽን " አካሄዱን የጠበቀ አይደለም " በማለት ራሱን አግልሏል።

አቶ ጌታቸው ያሉበት 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " እኛ የለንበትም " ብለው ራሳቸውን አግልለዋል።

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ባለው አሰራር አንድ ህጋዊ ፓርቲ ጠቅላላይ ጉባኤ ከማድረጉ ከ21 ቀናት በፊት ለቦርዱ ማሳወቅ እንዳለበት ይገልጻል።

በመሆኑንም ፤ የቦርዱን አሰራር ያልተከተለ ፣ ቦርዱ ባልተገኘበት የሚደረግ ጉባኤ ላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን እውቅና እንደማይሰጥ አሳውቋል።

ህወሓት ግን መቐለ ላይ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድና በርካታ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በሌሉበት ጉባኤ እያካሄደ ነው።

ጉባኤ ማድረግ ምድነው ጥቅሙ ?

አንድን ጉባኤ ህጋዊ የሚያደርገው በሚመለከተው አካል እውቅና አግኝቶ አሰራሩን ተከትሎ ሲካሄድ ነው።

የፓርቲዎችን ጉዳይ የሚመለከተው ምርጫ ቦርድ በመሆኑ " አካሄዱ ትክክል አይደለም። እውቅናም አልሰጥም " ባለበት ሁኔታ ጉባኤ ቢደረግ ተሰብስቦ ከመበተን ውጭ ውጤት የለውም የሚሉ አሉ።

ዶ/ር ደብረጽዮን ግን ፥ " ህወሓትን አድኖ ህዝብ ከጥፋት መታደግ የጉባኤው ዋነኛ አላማ ነው " ብለዋል።

" የድርጅቱና የህዝቡ የተሟላ ድህንነት ማረጋገጥ በሚችል መልኩ በዴሞክራሲያዊ ውይይትና ክርክር ብቃት ያላቸው አመራሮች መምረጥ ይገባል "ም ብለዋል።

" የአሁኑ ጉባኤ ለድርጅቱ የሞት የሽረት ጉዳይ ነው " እንደሆነ ገልጸዋል።

አቶ ጌታቸው ፍጹም መግባባት ሳይሰረግበት እየተካሄደ ያለ መሆኑን ያነሳሉ።

የጉባኤው ውጤት ምን ሊሆን ይችላል ?

ጉባኤ ማድረግ ምን ችግር ላይፈጥር ይችላል።

ጉባኤውን ተከትሎ የሚተላለፉ ውሳኔዎች እውቅና ስለማያገኙ ሌላ ጭቅጭቅ እና ልዩነት መፍጠሩ ይጠበቃል።

ጉባኤው ላይ በእነ አቶ ጌታቸው እና ቡድናቸው ምትክ ሌሎች የመምረጥ ነገር ካለ ይበልጥ ነገሩ ይከራል።

አቶ ጌታቸውም " #ይቃወሙናል " የሚሏቸውን አመራሮች ለማስወገድ የሚደረግ ጉባኤ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጉባኤው የሚያመጣው የግጭት ስጋት አለ ?

በትግራይ ፖለቲካውን የሚከታተሉ አካላት አሁን ላይ በተጨባጭ የሚታይ የግጭት ስጋት የለም ባይ ናቸው።

ጉባኤውን ተከትሎ ምርጫ ተደርጎ ፤ አመራሮችን የማስወገድ ነገር ከመጣ ግን በሂደት ጭቅጭቁና ንትርኩ መጨመሩ እንደማይቀር ያነሳሉ።

በፓርቲው ጉዳይ ከፌዴራል መንግሥት ጋር ያለው ልዩነት የመስፋት እድል ሊኖረው እንደሚችል ይገልጻሉ።

በፓርቲው ያሉት አንጃዎች የራሳቸው ደጋፊ ስላላቸው ልዩነታቸው በሰፋ ቁጥጥር በሂደት ወደ ኃይል እርምጃ እንዳይሄዱ ያሰጋል።

አሁን ላይ ግን በተጨባጭ የሚታይ የግጭት ስጋት ግን የለም።

#ትግራይ : ትግራይ ከአስከፊው ጦርነቱ በቅጡ ሳታገግም ፣ ብዙ ተጎጂ ባለበት ፣ ገና ተጠያቂነት ባልተረጋገጠበት ፣ ብዙ እገዛ የሚፈልግ ባለባት ፣ ተፈናቃይ ተሟልቶ ባልተመለሰበት ... ሌሎችም ብዙ ስራዎች ባልተሰሩበት ይህ የጉባኤ እና ምዝገባ ጉዳይ የህዝብ አጀንዳ እንዲሆን መደረጉ በርካቶችን ያስቆጣ ሆኗል። ይህ ጉዳይ ቀስ በቀስ በሂደት መሄድ እንደሚችልና መቅደም ያለባቸው ህዝባዊ ጉዳዮች መቅደም እንደነበረባቸው የሚያነሱ ብዙዎች ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ዛሬ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ፥ በፓሪስ ኦሎምፒክ በወንዶች ማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው ጀግናው አትሌት ታምራት ቶላ 7 ሚሊዮን ብር እና የወርቅ ኒሻን ሽልማት አበርክተዋል። ለሀገራቸው የብር ሜዳልያ ላመጡት አትሌት ትግስት አሰፋ፣ አትሌት በሪሁን አረጋዊ እና አትሌት ፅጌ ዱጉማ ለእያንዳንዳቸው የ 4 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቷል፡፡ የታምራት…
#Ethiopia

" መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ አድርጉልኝ ፤ ፕሬዜዳንታችንንም እዛው ሊወጡ ሲሉ ይቅርታ ጠይቂያለሁ አሁንም ይቅርታ ደግሜ ደጋግሜ ጠይቃለሁ !! " - አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ

አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ምን አሉ ?

" የብር ጉዳይ አይደለም።

ለእኛ (ለአሰልጣኞች) እየተሰጠን ያለው Value የተለያየ ነው።

እኔ አስተማሪ ነበርኩ ፤ በአስተማሪነት ለ9 ዓመት አገልግያለሁ የጠላሁት ማንም ለሙያው ቦታ የሚሰጥ ሰው የለም።

በሀገራችን ላይ ለሙያ የሚሰጠው ክብር በጣም የሞተ ነው።

ይሄ መሆን የለበትም ሞያውን እንዴት እናሳድገው ፣ አትሌቲክሱ ወደቀ ውጤታችን ጠፋ ይባላል እዚህ ጋር ደግሞ አሰልጣኝ ይጠፋል። አትሌትን ያደረሱ አሰልጣኞች ይጠፋሉ። ስንቶቹን አሰልጣኞች እያጣን ነው።

እዚህ ጋር የሚሰጠው value ቅር ያሰኘኝ። እኔ ለታምራት የሰጡትን ኒሻን ሸልመንሃል ቢሉኝ ይሻል ነበር።

ለኔ ስሙ ይሻለልኛል። መኪና ሰጠንህ ብለው ህዝብ መሃል ተናግረው ቁልፍ እዛ ጋር ሰጥተው መኪናውን ባይሰጡኝ እና ሁለት ሚሊዮኑን ቢሰጡን ደስተኛ ነኝ።

አሁን እያልን ያለነው ለኛ የሚሰጠው value ፣ ሞራል ከገንዘቡ ይበልጣል ነው።

የገንዘብ ጉዳይ አይደለም። እኔ እኮ ከካምፓኒዎች ጋር ሰራለሁ፣ በአትሌቶች ማናጀርነት ሰራለሁ እኔ ገንዘቡ ችግሬ አይደለም። ድህነንትንም አውቀዋለሁ በድህነቴም እኖራለሁ።

የታምራት 7 ሚሊዮን ሽልማት ለኔ ይሰጠኝ እያልኩ አይደለም። ግን እኔ ከታምራት እኩል መልፋቴን፣ ከታምራት እኩል መድከሜን Value መሰጠት አለበት ነው።

እንደ ገና ልዩ ተሸላሚ ተብሎ መሸለም ያለበት ሲሳይ ለማ እንዴት አልተሸለመም ? እኔ እንዴት አድርጌ ሲሳይን አሳምኜ ፣ ታምራትን አሳምኜ ደክመን በስንት መከራ ነው ውጤቱ የመጣው። ይሄ ውጤት በስንት መከራ እንደመጣ እናውቃለን።

እኔ ጥዋት ኤርፖርት ስደርስ በጣም ነው የተሰማኝ። ሁሉም እዛ የነበረው የሚጠራው ሜዳሊያ ያመጡትን ልጆች ብቻ ነው። ሁሉም የሚጠራው ገመዶን ብቻ ነው።

' ና ገመዶ እዚህ ጋር ተቀመጥ ' ከኔ በፊት እኮ ትላንት ያኮራን ሁሴን ሽቦ አለ ፣ ትላንት በሜዳሊያ ያስደሰተን ሀጂ አዲሎ አለ፣ ትላንት ሜዳሊያ የሰጠችን አማኔ አለች። እዛ ጋር የትዕግስት ብር የአማኔ ትግል ነው። እነሱን ለይተው በጣም ነው ያስለቀሰኝ። ለነሱ በተሰጠው ክብር እምባዬን ነው የለቀኩት።

እኔን ብቻ ነው ሲጠሩ የነበረው ለምን እኔን ብቻ ይጠሩኛል ?

ይሄ ለአሰልጣኝ እየተሰጠ ያለው ክብር ከሚገባው በላይ ያንሳል። አትሌቶችም ይረሳሉ።

እኛ እያለን ያለው የሚሰጠው value ካልተስተካከለ አትሌቲክሱን ይገለዋል። ይስተካከል ነው።

እኔ የገለጽኩበት አይነት ስህተት ነው። አዎ ! እዛ መሆን አልነበረበትም። ግን አንዳንዴ ጊዜ unconscious ሆነህ እንዲህ ታደርጋለህ። ሰው ልትመታም ትችላለህ፣ ልታብድም ትችላለህ።

እኔ በውስጤ የተንጸባረቀው በፊት የነበሩ ችግሮች በሙሉ ጭንቅላቴ ውስጥ አንጸባርቀው ነው።

ያ ግን ቤተመንግስት መሆኑና ህዝቡን በማስቀየሜ የኢትዮጵያን ህዝብ በሙሉ በጣም ይቅርታ ጠይቃለሁ። ፕሬዜዳንታችንንም እዛው ሊወጡ ሲሉ ይቅርታ ጠይቂያለሁ አሁንም ይቅርታ ደግሜ ደጋግሜ ጠይቃለሁ።

የሞያ ጓደኞቼንም ይቅርታ ጠይቃለሁ።

ሰው ይሳሳታል ፤ ከስህተቱም ይታረማል።

ህዝቡ ለሙያ ክብር እንዲሰጥ መደገፍ አለበት። እኔ አስተማሪ በነበረኩ ሰዓት በጣም ያመኝ ነበር አስተምረህ ፣ የሆነ ቦታ  አድርሰህ ዶክተር ይሆናል አንተ እዛው ነው ያለኸው ገጠር ነው ያለኸው የትምህርት እድል የለው፣ ከስራ ከወጣ የሚኖርበት የለውም በቃ እዛው ተገሎ ሙያው ተረግጦ ይሄዳል ይሄ መሆን የለበትም።

ገንዘቡን አሁንም ቢሆን አልቀበልም ፤ ካስተካከሉት እቀበላለሁ።

እኔ ሀገሬ ደመወዝ ከፍላኝ አታውቅም ፣ ደመወዝ ተከፍሎኝ አያውቅም። አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ ኦሎምፒክ የሁለት ወር ደመወዝ ከፍሎናል። እኛ የምንሰራው በራሳችን ለሀገራችን ነው የምንሰራው፤ በፍጹም አይከፋንም።

ለባለሙያ የሚሰጠው ክብር እኔ አፈረጥኩት እንጂ መፍረጡ አይቀርም ነበር። ከኔ በፊት የተሸለሙትም እኮ ውስጣቸው ቅጥል ብሏል። በውስጣቸው ይዘውት ነው።

ቀጥሎ በማሰልጠኑ እቀጥልበታለሁ። "


ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ የአሰልጣኙ ቃል ለሸገር ኤፍ ኤም ስፖርት የተሰጠ መሆኑን ይገልጻል።

#CoachGemedoDedefo #Ethiopia

@tikvahethiopia
#Egypt #Somalia : የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ' ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ' ብለው ግብፅ ይገኛሉ።

የፕሬዜዳንቱ ቢሮ እንዳለው በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸው በማጠናከር ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ጋር መክረዋል።

ስምምነታቸው ይዘቱ ምን እንደሆነ በዝርዝር ባይታወቅም ሀገራቱ #ወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል ስምምነትም ተፈራርመዋል።

ግብፅ በሞቃዲሾ ኤምባሲ መክፈቷም ተነግሯል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ወደ ፕሬዜዳንትነት ስልጣን ከመጡ በኃላ ከግብፅ ጋር የተለየ ወዳጅነት ለመመስረት ሲሰሩ ታይቷል።

በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላና ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነቷ ከሻከረ በኃላ ወደ ግብፅ ብዙ ጊዜ እየተመላሳለሱ ይገኛሉ።

Photo Credit - Villa Somalia

Via @thiqahEth
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ' ህወሓት ' ውስጥ እየሆነ ያለው ምንድነው ? ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከትግራዩ ጦርነት በፊት እንደ ህጋዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ስር ተመዝግቦ ይንቀሳቀስ ነበር። ነገር ግን  ቦርዱ ፓርቲው " ኃይልን መሰረተ ያደረገ የአመጽ ተግባር ላይ ተሰማርቷል " በሚል ሰርዞታል። የተወካዮች ምክር ቤትም ፓርቲውን " ሽብርተኛ ድርጅት " ሲልም ፈርጆት ነበር። ደም አፋሳሹና አስከፊው…
#Update

ሰባት የትግራይ የሲቪክ እና የንግድ ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ ፤ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ጥረት ማድረጋቸውን ነገር ግን ጥረታቸው አለመሳካቱን አሳውቀዋል።

በህወሓት አመራሮች የተፈጠረው መለያየት በድርጅቱ ዙሪያ ብቻ ተወስኖ እንዲቀር አሳስበዋል።

" ፓለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት አልሞ ህዝብ ለመከፋፈል የሚደረገው ጥረት ብፅኑ እናወግዛለን " ብለዋል።

ማህበራቱ ህዝቡ የፓለቲከኞች መሳሪያ ሆኖ ደህንነቱና አንድነቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

" የትግራይ የፀጥታ ሃይሎችም የልዩነት ፈጣሪ ከሆኑ ፓለቲከኞች ሳይወግኑ የህዝብ ደህንነት መጠበቅ ይገባቸዋል " በማለት አሳስበዋል። 

ማህበራቱ ፤ በፓለቲከኞቹ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በመፍታት በኩል በአገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች የሚጠበቅባቸው ሃላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የሲቪክና ንግድ ማህበራቱ ፦
1. የትግራይ ስቪል ማሀረበረሰብ ጥምረት :
2. የትግራይ ህዝባዊ ግንኙነት ምክር ቤት
3. ጥላ የምዕራብ ትግራይ ስቪክ ማህበረሰብ ማህበር
4. የትግራይ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት
5. የትግራይ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት
6. ግርዓልታ የፓለሲ ጥናትና ስልጠና ስቪክ ማህበር
7. ማሕበር ምውሓስ ሰላምን ልምዓትን ዶብን ወሰንን ትግራይ ናቸው።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 
#Infinix_Note40_Pro_Plus

የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G አጅግ ፈጣን እና በአለማችን የመጨረሻው የኔትወርክ ቴክኖሎጂ የሆነውን የ5G ኔትወርክ ማስጠቀም ሲያስችል በተለይም ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ስራዎችን በስልካቸው በሚከውኑ ሰዎች ተመራጭ የሆነውን የ Mediatek Dimesnty 7020 ፕሮሰሰርን የተገጠመለት ፈጣን ስልክ ነው፡፡

#Note40Et #Note40Pro #Note40 #Note40ProPlus #InfinixEt
TIKVAH-ETHIOPIA
የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ? የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እና የተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ አበባው ደሳለው ፦ " የመንግስት ኃላፊዎች በተለያየ ጊዜያት በተደጋጋሚ ስለ ሀገራዊ ምክክር እና ስለ ሽግግር ፍትህ ሲያነሱ ይደመጣል። ነገር ግን ከሀገራዊ ምክክር እና ከሽግግር ፍትህ በፊት መቅደም ያለባቸው ነገሮች አሉ። ከነዚህ ውስጥ አንደኛውና ዋነኛው የእምነት ግንባታ ነው። መንግስት በህዝብ…
" መኖሪያ ቤታቸው የገቡት ትላንት ከምሽቱ 4 ሰዓት ገደማ ነው " - ቤተሰቦች

ከ6 ወራት በፊት " ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታፍነው " መወሰዳቸው የተነገረላቸው የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ሀብታሙ በላይነህ ትላንት ተይዘው ከነበረበት መለቀቃቸውን ቤተሰቦቻቸውን ዋቢ በማድረግ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

የአብን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ ሀብታሙ፤ ደብዛቸው የጠፋው ከየካቲት 22፤ 2016 ጀምሮ ነበር።

በዕለቱ በአዲስ አበባ 4 ኪሎ አካባቢ " ሰው ላግኝ ብሎ ከቤት እንደወጣ አልተመለሰም ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ለ6 ወራት ያህል ያለበት ሳይታወቅ ቆይተዋል " ሲሉ አንድ የቅርብ ምንጭ  አስረድተዋል።

የአማራ ክልል የምክር ቤት አባሉ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አያት አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው የገቡት ትላንት ከምሽቱ 4 ሰዓት ገደማ መሆኑን ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

አቶ ሀብታሙ በላይ እስካሁን ድረስ የት እንደቆዩና የነበሩበትን ሁኔታ በተመለከተ ግን በዚህ ጊዜ መናገር እንደማይፈልጉ ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የአቶ ሀብታሙን መለቀቅ አረጋግጣል።

የቆዩበት እና ሌሎችንም ዝርዝር ጉዳዮች በተመለከተ " ገና ቃላቸውን እንዳልሰጡ " አስረድቷል።

ሰኔ መጨረሻ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ምንም እንኳን ምላሽ ባይሰጥበትም የአቶ ሀብታሙ ጉዳይ በአብን የምክር ቤት ተመራጭ አቶ አበባው ደሳለው ተነስቶ እንደነበር ይታወሳል።  #EthiopiaInsider

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ከእዚህ በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ የ '' ቤቲንግ '' ወይም የስፖርት ውርርድ ቤት አይኖርም ሲል የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ማሳወቁን ሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ዘግቧል።

የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ ፤ " በተጠናቀቀው 2016 የበጀት ዓመት በከተማዋ የሚገኙ 4,118 የቤቲንግ (የስፖርት ውርርድ) ቤቶችን ዘግተናል፤ ከዚህ በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ የውርርድ ወይም ቁማር ቤት አይኖርም " ብለዋል፡፡

" የቤቲንግ ቁማር ስራን በዚህ ከተማ ላይ ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም " አስረድተዋል፡፡

" ልጆቻችን አዕምሯቸው በቁማር ምክንያት እየተበላሸ ነው ፤ እቃም ጭምር ከቤት እየተሰረቀ እየተሸጠ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" ለትዳር ፊቺ ጭምር መነሻ ሆኗል እየተባለ ቅሬታ ሲነሳ ነበር፤ ምላሽ ተሰጥቶታል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ማሸጉ ግብ አይደለም፤ በዘርፉ ላይ ተሰማርተው ሲሰሩ የነበሩ ሌላ ስራ ቀይረው እንዲሰሩ ትዕዛዝ ተላልፏል " ብለዋል።

አቶ ሚደቅሳ ከበደ ፥ " ቤት አከራይተው የነበሩ አከራዬችም ለሌላ ንግድ ወይም አገልግሎት በማከራየት አንዲጠቀሙ ተደርጓል " ሲሉ መናገራቸውን ሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

በዚህ ጉዳይ ላይ የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር የሚሰጠውን አስተያየት ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ' ህወሓት ' ውስጥ እየሆነ ያለው ምንድነው ? ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከትግራዩ ጦርነት በፊት እንደ ህጋዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ስር ተመዝግቦ ይንቀሳቀስ ነበር። ነገር ግን  ቦርዱ ፓርቲው " ኃይልን መሰረተ ያደረገ የአመጽ ተግባር ላይ ተሰማርቷል " በሚል ሰርዞታል። የተወካዮች ምክር ቤትም ፓርቲውን " ሽብርተኛ ድርጅት " ሲልም ፈርጆት ነበር። ደም አፋሳሹና አስከፊው…
#TPLF

በአመራሮች መካከል ከፍተኛ ክፍፍል የፈጠረውና በምርጫ ቦርድ እውቅና የተነፈገው የህወሓት ጉባኤ ዛሬ በዝግ ሲመክር ውሏል።

በዛሬ ውሎው የአዘጋጅ ኮሚቴ ሪፓርት አቅርቦ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በሙሉ ድምፅ ማፀደቁ ተሰምቷል። 

ከመላው ትግራይ በድምፅ መሳተፍ ከሚገባቸው 950 ጉባኤተኞች 785 ማለትም 83% ተገኝተዋል ተብሏል።

የተለያዩ ወረዳዎች በድምጽ የሚሳተፍ ሰው እንዳላኩ ተሰምቷል።

ከዛሬው የዝግ ስብሰባ በኃላ ድርጅቱ ባሰራጨው መረጃ ፤ " በጉባኤው አንሳተፍም ያሉ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ስህተታቸው በማረም ወደ ጉባኤው በመግባት ሃሳቦች ለማቅረብ ዝግጁ ከሆኑ በሩ ክፍት ነው " ብሏል።

የህወሓት የ14ኛው ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋይ ገ/እግዚአብሔር  " በኮሚቴው ስራ ውስጥ የሚታዩ ጣልቃ የመግባት ፣ ከፕሮግራም ውጪ ስብሰባ መጥራት፣ ውሳኔዎችን መጠምዘዝ የመሳሳሉ ተግባራት እንዲታረሙ ለመስራት ብሞክርም  አልተሳካም " በማለት ደብዳቤ ፅፈው ከሃላፊነት ራሳቸው ስለማግለላቸው  መዘገባችን ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ደግሞ በዛሬው ዕለት የወጡ አንዳንድ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ጉባኤውን የተቃወሙ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ቁጥር ጨምሯል ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የዚን መረጃ ትክክለኝት ለማጣራት ያደረገው ጥረት አልተሳካም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF በአመራሮች መካከል ከፍተኛ ክፍፍል የፈጠረውና በምርጫ ቦርድ እውቅና የተነፈገው የህወሓት ጉባኤ ዛሬ በዝግ ሲመክር ውሏል። በዛሬ ውሎው የአዘጋጅ ኮሚቴ ሪፓርት አቅርቦ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በሙሉ ድምፅ ማፀደቁ ተሰምቷል።  ከመላው ትግራይ በድምፅ መሳተፍ ከሚገባቸው 950 ጉባኤተኞች 785 ማለትም 83% ተገኝተዋል ተብሏል። የተለያዩ ወረዳዎች በድምጽ የሚሳተፍ ሰው እንዳላኩ ተሰምቷል። ከዛሬው…
#TPLF

ከህወሓት ከፍተኛ አመራር አንዱ የሆኑት የማይጨው ከተማ ከንቲባ አቶ የማነ ንጉስ ለዶቼ ቨለ በሰጡት ቃል ፤ " ጉባኤው የተወሰነ ቡድን ለማጥቃት በችኮላ የተጠራ ነው " ብለዋል።

በዚህም እሳቸው ጨምሮ በርካቶች ተቃውሞዋቸውን በመግለፅ ከመድረኩ መቅረታቸውን አመልክተዋል።

የህወሓት ማእከላዊ ቁጥጥር ኮምሽን ሊቀ መንበር አቶ ተክለብርሃን አርአያ ትላንት በሰጡት መግለጫ ፥ " 14ተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተብሎ የተጀመረው ስብሰባ ህወሓትን ወደከፋ ችግር የሚያስገባ ነው " በማለት ጉባኤውን አውግዘዋል።

አቶ ተክለብርሃን ፥ " አንድነታችን ይዘን ፣ የፕሪቶርያው ውል ማእከል አድርገን፣ ለአላዊነታችን አረጋግጠን በተጨማሪም አንድ ላይ በመንቀሳቀስ ሕጋዊ እውቅናችን መልሰን ሊደረግ የሚገባው ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይህ ጉባኤ ግን ወደ ቅርቃር ውስጥ የሚያስገባን ነው " ብለዋል።

" ተግባብተን ወደ አንድ መንገድ መጥተን ልናደርገው ይገባ የነበረ ነው። ላይ ያለው አመራሩ ብቻ ሳይሆን ታች ያለው አባልም ጭምር መግባባት የፈጠረበት ሊሆን ይገባ ነበር " ማለታቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

@tikvahethiopia