TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Gambella : በጋምቤላ ክልል 4 ወረዳዎች የጎርፍ አደጋ ተከስቷል።

ከ16 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቀያቸዉ ተፈናቅለዋል።

በሀገሪቱ ደጋማ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብ ፦
- በጎግ፣
- በላሬ፣
- በጆርና
- በዋንቱዋ ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከስቶ ነው ወገኖቻችን የተፈናቀሉት።

ተፈናቃዮቹን ለጊዜዉ ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ ተደርጓል ተብሏል።

የጎርፍ አደጋዉ በቤት ዉስጥ ባሉ ቁሳቁሶች እንዲሁም በቁም እንስሳትና በሰብል ላይም ጉዳት ማድረሱን ገልፀዋል።

የጎርፍ መጥለቅለቁ በሚቀጥሉት ጊዜያት ከዚህ የከፋ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ተብሏል። ለዚህም ነዋሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅትና ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንዲያደርጉ የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር አሳውቋል።

#GambellaRegionPressSec.

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

" ህወሓት 50 ዓመታታት ያስመዘገበ እንደ አዲስ መመዝገብ የሌለበት አንጋፋ የፓለቲካ ድርጅት ነው " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)


የህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)  ዛሬ እሁድ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም " ህወሓት 50 ዓመታታት ያስመዘገበ እንደ አዲስ መመዝገብ የሌለበት አንጋፋ የፓለቲካ ድርጅት ነው " ብለዋል።

ሊቀመንበሩ ፤ " የህወሓት ህጋዊነት የመመለስ ጉዳይ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ጎን ለጎን እንጂ አሁን የተጀመረ አይደለም " ያሉ ሲሆን " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሁለቱ ተፈራራሚዎች እርስ በራሳቸው እውቅና እንደሚሰጣጡ ይደነግጋል " ብለዋል።

የህወሓት ህጋዊነትን ለመመለስ የተካሄደ በርካታ ውይይቶችን ተከትሎ ድርጅቱና ሌሎች የሚያካትት አዲስ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ የሚመለከት የተሻሻለ አዋጅ እስከ ማውጣት መደረሱ አብራርተዋል።

" የተሻሻለው በአመፅ ድርጊት የተሳተፉ የፓለቲካ ፓርቲዎች መልሶ ስለ መመዝገብ የሚመለከት አዋጅ ህወሓት ወደ ቀደመው እውቅናዋ ሊመልስ አይችልም " ያሉት ደብረፅዮን (ዶ/ር) ፥ " ስለሆነም ህወሓት ወደ ነባር እውቅናው ይመለሳል እንጂ እንደ አዲስ አይመዘገብም " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ህወሓት እንደ አዲስ መመዝገብ ማለት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ማፍረስ ማለት ነው " በማለትም ተናግረዋል።

" የአፍሪካ ህብረት ታዛቢዎች በተገኙበት ህወሓት ወደ ነባሩ እውቅና ለመመለስ ነው ስምምነት የተደረሰው " ሲሉ ገልፀዋል። 

ሊቀመንበሩ ህወሓት ጉባኤ ስለሚያካሂድበት ጊዜ ቁርጥ ያለ ቀንና ቦታ በመግለጫቸው አልጠቆሙም።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ፥ ከቀናት በፊት ለህወሓት " በልዩ ሁኔታ " ሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ መስጠቱ ይታወሳል።

ቦርዱ ነሀሴ 3 ባወጣው መግለጫ ድርጅቱ በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን የሚገልጸው ድብደቤ ከደረሰው ቀን አንስቶ ባሉት 6 ወራት የቦርዱ ታዛቢዎች በተገኙበት ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ ያዛል።

ህወሓት ግን ነሀሴ 4/2016 ዓ.ም " የተሰጠኝ የምዝገባ ውሳኔ ከተካሄዱት የሁለትዮሽ ወይይቶችና መግባባት ወጪ ነው ስለሆነ ወደ ነባሩ እውቅናዬ የማይመልስ ውሳኔ አልቀበልም " ብሎ መግለጫ አውጥቷል።

ዛሬ ደግሞ የድርጅቱ ሊቀመነንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፤ " ህወሓት 50 ዓመታታት ያስመዘገበ እንደ አዲስ መመዝገብ የሌለበት አንጋፋ የፓለቲካ ድርጅት ነው፤ ህጋዊ ሰውነታችን ይመለሳል እንጂ እንደ አዲስ አንመዘገብብም " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
#NewsAlert #Tigray

" የህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላለልተወሰነ ጊዜ የድጋፍም ይሁን የተቋውሞ ሰልፍ ማድረግ ተከልክሏል " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ ምክትል ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ ከሰዓት መግለጫ ሰጥተዋል።
 
በዚህም ፤ " ፓለቲካዊ አለመግባባት ወደ ማንኛውም የፀጥታ አደጋ እንዲሸጋገር አንፈቅድም " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" የህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላለልተወሰነ ጊዜ የድጋፍም ይሁን የተቋውሞ ሰልፍ ማድረግ ተከልክሏል " ያሉት ጀነራል ታደሰ ወረደ " ፓለቲካዊ ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት አለበት " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ በቀላል እና ከባባድ ወንጀሎች ተሳትፈዋል ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የማዋል ኦፕሬሽን መጀመሩ ይታወሳል።

ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረዳ በዛሬ መግለጫቸው ላይ በህግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦችና ብዛታቸውን ባይገልጹም " የህግ የበላይነት ለማስከበር የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል " ሲሉ አሳውወዋል።

የዘንድሮ የአሸንዳ በዓል አከባበርና የህወሓት ጉባኤ ከመካሄድ ጋር ተያይዞ  የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ተገቢ እና ጥብቅ የፀጥታ ስራ ይሰራል ሲሉም ተናግረዋል።

በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ እና እየከረረ መሄዱ በርካቶችን ያሳሰበ ጉዳይ ሆኗል።

ሁኔታው የፀጥታ ስጋት ደቅኗል የሚሉ አልጠፉም።

ሌ/ጄነራል ታደሰ ግን ፓለቲካዊ ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለበት ፤ ማንኛውም ልዩነት ወደ ፀጥታ አደጋ እንዲሸጋገር የጸጥታ አካሉ እንደማይፈቅድ አስጠንቅቀዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

Photo Credit - TG TV

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF "ሊካሄድ በታቀደው ጉባኤ አልሳተፍም ! " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር ፕሬዜዳንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ ዛሬ ዓርብ ነሀሴ 3/2016 ዓ.ም ለህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፣ ለድርጅቱ የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ተኽለብርሃን ኣርኣያ በፃፉት ደብዳቤ በጉባኤው እንደማይሳተፉ አረጋግጠዋል። ፕሬዜዳንቱ በደብዳቤያቸው…
#TPLF

" ህወሓትን ለማፍረስ አልሞ በሚካሄደው ጉባኤ አንሳተፍም !! " - የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት

ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 14 የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በህወሓት ጉባኤ ላይ እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል።

" ህወሓት ለማፍረስ አልሞ በሚካሄደው ጉባኤ አንሳተፍም " ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል።

" በጥቂት ቡድኖች ማን አለበኝነት የተዘጋጀና የጉባኤው ከፍተኛ ስልጣን ያለው የማእከላዊ ኮሚቴ አመራር ያልወሰነው፣ የድርጅታችን የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ውድቅ ያደረገው ፣ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ መግባባት ያልተደረሰበትና ትግራይ ከጫፍ አስከ ጫፍ ያልተወከለበት የጠባብ ቡድን ጥቅም ለማስከበር ብቻ ባለመ ጉባኤ አንሳተፍም " ብለዋል።

በጉባኤው " አንሳተፍም " ያሉት 14ቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ፦
1. ጌታቸው ረዳ
2. በየነ ምክሩ
3. ክንደያ ገ/ህይወት
4. ሓጎስ ጎዶፋይ
5. ሰብለ ካህሣይ
6. ብርሃነ ገ/የሱስ
7. ሰለሞን መዓሾ
8. ሺሻይ መረሳ
9. ሃፍቱ ኪሮስ
10. ረዳኢ ሓለፎም
11. ነጋ ኣሰፋ
12. ገ/ሕይወት ገ/ሄር
13. ሩፋኤል ሽፋረ
14. ርስቁ ኣለማው ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF : " ህወሓትን ለማፍረስ አልሞ በሚካሄደው ጉባኤ አንሳተፍም " ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ጉባኤውን ተከትሎ ለሚመጣው ነገር እኛ የለንበትም " ብለዋል።

ጉባኤው " በጥቂት ቡድኖች ማን አለበኝነት " የተዘጋጀ ፦
- የጉባኤው ከፍተኛ ስልጣን ያለው የማእከላዊ ኮሚቴ አመራር ያልወሰነው
- የድርጅቱ የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ውድቅ ያደረገው
- ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ መግባባት ያልተደረሰበትና
- ትግራይ ከጫፍ አስከ ጫፍ ያልተወከለበት፤ ነጻ ያልወጡ አካባቢዎች ባሉበት ነው ብለዋል።

" ጉባኤው የጠባብ ቡድን ጥቅም ለማስከበር ብቻ ያለመ ነው ፤ እኛ ደግሞ በዚህ ላይ አንሳተፍም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ህወሓትን እና የትግራይ ህዝብ ወደ ከፋ አደጋ የሚያጋልጥ ያልተረጋጋ ጉባኤ ማካሄድ የጠባብ ቡድኑ ጥቅምን ከማረጋገጥ ያለፈ እርባና የለውም " ሲሉም ገልጸዋል።

14ቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት " ህወሓትን እና የትግራይ ህዝብ ወደ ሌላ የተወሳሰበ ቀውስ በሚከት በጠባብ ቡድን የተዘጋጀው ጉባኤ አንሳተም " ብለው " ጉባኤውን ተከትሎ ለሚፈጠረው ማንኛውም ነገር ተጠያቂው ይኸው ቡድን መሆኑ እናስታውቃለን " ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ያሉበት 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ጠባብ ቡድን " እያሉ የገለጻቸውን ጥቂት ቡድኖች በስም አልገለጿቸውም።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ከኦሎምፒክ ውድድር ጋር በተያያዘ ገና ከጅምሩ አንስቶ ጭቅጭቅ ፣ ቅሬታ ፣ ንትርክ ፣ በሚዲያ በኩል የኃይል ምልልስ የነበረበት ነው። የስፖርት ቤተሰቡ ሆነ ዜጋው የነበረውን ነገር በአንክሮ ሲከታተል ነበር። " እስቲ እዛው ፓሪስ ላይ ሲደርሱ ነገሮችን ጸጥ ይላሉ፣ ለሀገር ክብር ሲሉ ሁሉም በስምምነት ያለ ጭቅጭቅና ቅሬታ ይሰራሉ " ቢባልም ዛሬም ድረስ ቅሬታዎች እንደ ጉድ እየተሰሙ ነው።…
#Ethiopia

አትሌቲክሳችን ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገዋል። ይህ መሆን ያለበት ደግሞ በትክክለኛ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ነው።

የኦሎምፒክ ውጤቱ አንገት የሚያስደፋ ነው።

በጭቅጭቅ፣ በንትርክ፣ በየሚዲያ ላይ በሚደረግ ምልልስ የተጀመረው የፓሪስ ውድድር ኢትዮጵያን የማይመጥን እጅግ ዝቅ ያለ ውጤት ተመዝግቦበት አልቋል።

ጥፋት ከደረሰ እና ውጤት ከጠፋ በኃላ የሚቀርብ ይቅርታ ተቀባይነት የለውም።

የሚያስፈልገው ሁሉም የአትሌቲክሱ ቤተሰብ ቁጭ ብሎ በእርጋታ መክሮ ፤ ስር ነቀል ለውጥ ማምጣት ብቻ ነው።

ሁሉም ዜጋ በየፊናው የተሰማውን ብስጭት፣ ንዴት እየገለጸ ነው። ይህ የሚጠበቅ ነው። ምክንያት ? ሀገሩ ነው፣ ክብሩ ነው። የሚጠብቀውን ሳያገኝ ሲቀር ህዝቡ ያዝናል ፣ይበሳጫል።

እውነትም " ለሀገራችን ክብርና ፍቅር አለን " የሚሉ የአትሌቲክሱ አካላት በእርጋታ ፣ በንግግር ችግሮች እንዲፈቱ ያድርጉ።

ይህም በመሪዎች እና አመራሮች ደረጃ " ለጠፋው ውጤት ፣ ዝቅ ላለው የህዝባችን ክብር ኃላፊነት እንወስዳለን ፤ ይህ የመጣው ስላልሰራን ነው " ብሎ ቦታ መልቀቅን ፤ ለሌላው እድል መስጠትን ያካትታል።

በአትሌቶች ዘንድም የውጤታችን መጥፋት እንዴት እንደተከሰተ ፤ ምናልባት የተሻሉ አትሌቶችም ካሉ ለነሱ ቦታ እያስረከቡ መሄድም እንዲቻል በጥልቀት መገምገም ይገባል።

በአትሌቶች እና አሰልጣኞች መካከልም ተግባብቶ እንደ አንድ ሀገር ዜጋ በቡድን አለመስራት ችግርም ካለ መፈተሽ አለበት።

ከምንም በላይ ግን ዘርፉን የሚመሩትን አካላት እና እዛ አካባቢ ያሉትን በሙሉ በጥልቀት መገምገም ይገባል።

በአጠቃላይ ስር ነቀል ለውጥ መምጣት አለበት።

ህዝቡ የሚፈልገው ክብሩ እንዲመለስለት ብቻ ነው ፤ ሙያውን የሚያውቅ በቦታው ተገኝቶ ለውጥ አምጥቶ በሀገሩ ውጤት ተደስቶ ማየት ነው።

የሚዲያ ምልልስ ፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ በዚህ መሃል ደግሞ የሚፈጠር የውጤት ውድቀት ህዝብን ፍጹም አይመጥንም።

ጉዳዩ ሙያዊነውና ለባለሙያዎቹ እንተወው ፤ እውነት ግን " የሀገራችን ክብር ይመለከተናል " የሚሉ የሀገር ጉዳይ ብቻ አላማቸው ከሆነ ሌላ ፍላጎት ከሌላቸው ጭቅጭቅ እና ንትርክ ትተው ቁጭ ብለው መነጋገር አለባቸው። ኃላፊነት መውሰድም አለባቸው።

በአሁኑ ውጤት ያልተበሳጨ፣ ያላዘነ ፣ አንጀቱ ያላረረ ዜጋ የለም በዚህም ደግሞ በስሜታዊነት አስተያየቱን እየሰጠ ነው። ለውጥ እንዲመጣ ወደ ክብራችን እንድንመለስ ጥያቄ እያቀረበ ነው።

ነገር ግን አንዳንድ አስተያየቶችም ጥንቃቄ ይፈልጋሉ የአትሌቶችን ስነልቦና እንዳይጎዳ።

ባለፈው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና " ያለእናተ ሰው የለም ፤ ጀግኖች " እያልን ያወደስናቸውን ልጆች ዛሬ ውጤት በመጥፋቱ በብስጭት እና ሀዘን ስሜት ያልተገባ ቃል እንዳንናገር መጠንቀቅ ይገባል።

ዳግም ህዝቡ በሚኮራበት #አትሌቲክስ እንዳያዝን እና እንዳይበሳጭ ተነጋግሮ ስር ነቀል ለውጥ መምጣት አለበት።

ህዝቡ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ክብሩ እንዲመለስለት ይፈልጋል፤ አራት ነጥብ !

ስር ነቀል ለውጥ ለኢትዮጵያ  🇪🇹 አትሌቲክስ !


#የሐሳብ_መድረክ @nousethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Bangladesh : ለ15 ዓመታት ያህል ባንግላዴሽን የመሩት ሺህክ ሀሲና የተነሳባቸውን ጠንካራ ተቃውሞ ተከትሎ ሀገር ጥለው  ጠፍተዋል። የተቆጡ ተቃዋሚዎችም ወደ ሚኖሩበት ቤተመንግስት በኃይል ሰብረው በመግባት ወረው በመኖሪያ ቤታቸው እንዳሻቸው እየፈነጩበት ነው። ግማሹ አልጋ ላይ ፣ ግማሹ በየክፍሉ እየዞረ እቃቸውን ይፈትሻል፣ ግማሹ ይጨፍራል። ከመንግሥት የስራ ኮታ ስርዓት ጋር በተያያዘ ተማሪዎች…
#Bangladesh

ተማሪዎች በቀሰቀሱትና በኃላም ሌላውም ዜጋ በተቀላቀለው የመንግሥት የስራ ኮታ ተቃውሞ ምክንያት ስልጣናቸውን ለቀው ከሀገር ወጥተው የሄዱት የቀድሞ የባንግላዴሽ ጠ/ሚኒስትር ሼኪህ ሀሲና ከስልጣን እንዲወርዱ " የአሜሪካም እጅ አለበት " ማለታቸውን ' ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ' አስነብቧል።

ልጃቸው ግን " ውሸት ነው " ሲል አጣጥሏል።

ሀሲና አሁን ላይ ሀገራቸውን ጥለው ህንድ ነው ያሉት።

እሳቸው ናቸው የተናገሩት ብሎ ' ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ' እንዳስነበበው ሀሲና ፤ " የደም መፋሰስ እንዳይፈጠርና እሱን ላለማየት ስልንነው ስልጣን የለቀቅኩት " ብለዋል።

" በተማሪዎች እሬሳ ላይ ተረማምደው ስልጣን መያዝ ፈልገው ነበር ግን እኔ ያንን አልፈቀድኩም፤ በዚህም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣኔን ለቅቂያለሁ " ሲሉ መግለጻቸውን አስነብቧል።

ሀሲና " የሴንት ማርቲን ደሴትን ሉዓላዊነት አሳልፌ ብሰጥና ፤ አሜሪካ የቤይ ኦፍ ቤንጋልን እድትቆጣጠር ብፈቅድ ኖሮ በስልጣን ላይ እቆይ ነበር " ማለታቸውን ገልጿል።

አሜሪካ ተቃውሞ ማቀናበሯንና ይህን ያደረገችው የአገዛዝ ለውጥ አድርጋ ፍላጎቷን ለማሟላት እንደሆነ እንደጠቆሙ ነው ' ታይም ኦፍ ኢንዲያ ' ያስነብበው።

አሁን ላይ አሜሪካ የሚኖረው ልጃቸው ሳጂብ ዋዜድ ፤ " እናቴ ከስልጣን መልቀቋን በተመለከተ የሰጠችው መግለጫ ተብሎ በጋዜጣ ታትሞ የወጣው ሙሉ በሙሉ ውሸትና የተቀናበረ ነው፤ ከራሷ እንዳረጋገጥኩት ዳካን ከመልቀቋ በፊትና በኃላ ምንም መግለጫ እንዳልሰጠች ነው " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ሀሲና ባንግላዴሽ ፓርላማ " አሜሪካ በሀገሪቱ የአገዛዝ ለውጥ ለማድረግ እየሞከረች ነው " በማለት አሜሪካንን ወንጅለው ነበር።

ሴንት ማርቲን ደሴት ከ1971 (እ.አ.አ) አንስቶ በባንግላዴሽን ፖለቲካ ትልቅ ተጽእኖ ያላት ትንሽዬ ግን በጣም ወሳኝ ደሴት ናት።

ቦታው ከቤይ ኦፍ ቤንጋል ያለው ርቀት እንዲሁም ከማይናማር ጋር ያለው የባህር ወሰን በስፍራው ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ፍላጎት እንዲኖር አድርጓል።

' ቤይ ኦፍ ቤንጋል ' ን ለመቆጣጠር እንዲሁም የህንድ ውቂያኖስ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ጭምር ለመከታተል ፤ ስትራቴጂክ የሆነ ስፍራ ነው።

በዚህም በቀጠናው ኃይሏን ለማጠናከር የተሟላ ቁጥጥር እንዲኖራትና በቻይና ላይም የበላይነት ለመውሰድ አሜሪካ ወታደራዊ ቤዟን ለማቋቋም እንደምትፈልግ ይናገራል።

አሜሪካ ግን ከበርካታ ዓመታት በፊት ይህንን ቦታ እንደማትፈልገው እና በስፍራው ወታደራዊ ቤዝ እንዲኖርት እቅድ እንደሌላት አሳውቃ ነበር።

#TikvahEthiopia #TimesofIndia

@tikvahethiopia
Jasiri Talent Investor welcomes bold and brave aspiring women entrepreneurs from Ethiopia,🇪🇹🇷🇼 ready to lead and innovate. Jasiri is more than a program—it's your opportunity to rise as a future leader. We remove barriers that hinder the success of new businesses. Jasiri will support you from Ideation to Venture Creation, by providing funding, coaching, strategic advisory, and guidance in the complex space of innovation.
Apply for Cohort 7 today at jasiri.org/application

For more information join our telegram channel https://t.me/jasiri4Africa
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF : " ህወሓትን ለማፍረስ አልሞ በሚካሄደው ጉባኤ አንሳተፍም " ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ጉባኤውን ተከትሎ ለሚመጣው ነገር እኛ የለንበትም " ብለዋል። ጉባኤው " በጥቂት ቡድኖች ማን አለበኝነት " የተዘጋጀ ፦ - የጉባኤው ከፍተኛ ስልጣን ያለው የማእከላዊ ኮሚቴ አመራር ያልወሰነው - የድርጅቱ የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ውድቅ ያደረገው…
 #TPLF : የህወሓት የፅህፈት ቤት ሃላፊና የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ብሔር  የህወሓት ማእከላዊ  የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት በጉባኤ እንዲሳተፉ በፃፉት ደብዳቤ " 14ኛው የህወሓት ጉባኤ ነሃሴ 7/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 3:00  ጀምሮ በመቐለ የሰማእታት ሓወልት አዳራሽ ይካሄዳል " ይላል።

ይሁን እንጂ የደርጅቱ ማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ከ2 ሳምንት በፊት ከሚካሄደው ጉባኤ ራሱ ማግለሉ ይታወሳል።

የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበርና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ማንአለበኝነት የተጠናወተው ጠባብ ቡድን " ያሉት አካል " ጉባኤ ንድሕነት ! "  በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው ጉባኤ እንደማይሳተፉ አስታወቀዋል።

" ጉባኤውን ተከትሎ ለሚመጣ ነገር እኛ የለንበትም " ብለዋል።

አንዳንድ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣  ምክትል ሊቀ-መንበሩ የሚገኙባቸው 14 ፒቲሽን የፈረሙ የማእከላይ ኮሚቴ አባላት ጨምሮ በመስዋእት ፣ ከደርጅቱ በመልቀቅ ፣ በህመም እና በሌሎችም ምክንያቶች ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ጉባኤ በርካታ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት አይሳተፉም።

በርካታ የማእከላዊ ኮሚቴ ማለትም ከ50 በመቶ በላይ አለመሳተፍ ደግሞ የደርጅቱ ህልውና እጅጉ የሚጎዳ የሚሉ በርካታ አስተያየቶች በመንሸራሸር ላይ ናቸው።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
 
TIKVAH-ETHIOPIA
 #TPLF : የህወሓት የፅህፈት ቤት ሃላፊና የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ብሔር  የህወሓት ማእከላዊ  የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት በጉባኤ እንዲሳተፉ በፃፉት ደብዳቤ " 14ኛው የህወሓት ጉባኤ ነሃሴ 7/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 3:00  ጀምሮ በመቐለ የሰማእታት ሓወልት አዳራሽ ይካሄዳል " ይላል። ይሁን እንጂ የደርጅቱ ማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ከ2 ሳምንት በፊት ከሚካሄደው ጉባኤ ራሱ…
#TPLF

ሰባት የመቐለ ከተማና ሁለት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ከፍተኛ ካድሬዎች " ጠባብ ቡድን " ሲሉ በጠሩ አካል ተጠርቷል ባሉት የህወሓት ጉባኤ እንደማይሳተፉ አስታወቁ።

አመራሮቹ ፤ " ባሁኑ ወቅት የሚካሄደው ጉባኤ ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚያመዝን ላለመሳተፍ ወስነናል " ብለዋል።

በጉባኤው እንዳማይሳተፉ በደብዳቤ ያስታወቁ የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎች ፦

1. ነጋሽ ኣርኣያ - የመቐለ ጀተማ የህወሓት ፅህፈት ቤት ሃላፊ 
2. ሓለፎም ገ/ህይወት  - የሓድነት ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
3. ኤልያስ ኪሮስ  -  የዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
4. እያሱ ተካ  -  የዓይደር ከፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
5. ኣስመላሽ ብርሃኑ  - የዓዲ ክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ (መቐለ)
6. ፍጹም ለገሰን - በትግራይ ማእከላዊ ዞን የዓዴት ወረዳ አስተዳዳሪ 
7. ሓጎስ ንጉስ - የዓዴት ወረዳ የአደረጃጀት ሃላፊ ናቸው።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Drone : በቻይና ግዙፍ የተባለ ለሲቪል አገልግሎት የሚውል / የጭነት አገልግሎት የሚሰጥ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ተሰርቶ የሙከራ በረራ መደረጉ ተሰምቷል።

ባለመንታ ሞተር የሆነው እና 2 ሜትሪክ ቶን መሸከም ይችላል የተባለው ይህ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ትላንት ነው  ሙከራ ያደረገው።

በሙከራ በረራው ድሮኑ ለ20 ደቂቃ በደቡብ ምዕራብ ሲቹዋን ግዛት መጓዙም ተነግሯል።

ሁሉ ነገሩ የተሳካ እንደሆነ ተሰምቷል።

ድሮኑን የሰራው ' ሲቹዋን ቴንግደን ሳይ-ቴክ ኢኖቬሽን ኩባንያ ' ነው እንደሆነ ከሲጂቲኤን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ቻይና በዓለም ላይ ከፍተኛ የሰው አልባ አውሮፕለን (ድሮን) ሰሪ ሀገር ናት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#FederalGovernment #TPLF

" አላስፈላጊ እና ሕዝብን የማይጠቅም፣ ትርጉም አልባ ንትርክን አስወግደን ለሕዝብ ረብ ያላቸው ጉልህ የሰላም እና የልማት አጀንዳዎች ላይ ልናተኩር ይገባል " - የፌዴራል መንግሥት ኮሚኒኬሽን

የፌዴራል መንግሥት ኮሚኒኬሽን በህወሓት ጉዳይ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህ መግለጫ ፦

- ህወሓት እንዴት ሕጋዊ ሰውነቱን ሊያጣ እንደቻለ ወደኃላ መለስብሎ አስታውሷል ፤

- የፕሪቶሪያ ስምምነት ሲፈጸም የፌዴራል መንግሥት በስምምነቱ የገባው ግዴታ የህወሓት የሽብርተኝነት ፍረጃ እንዲነሣ ሂደቱን የማሣለጥ ኃላፊነት (የስምምነቱ አንቀጽ 7 (2) (C)) እንደሆነ ፤

- የፌዴራል መንግሥት የህወሓትን የሕግ ሰውነት እና የምዝገባ ጉዳይ በተመለከተ በፕሪቶሪያ ስምምነት ውስጥ የወሰደው የተለየ ኃላፊነት ወይም ግዴታ እንዳልነበር፤

- ህወሓት በፕሪቶሪያ ስምምነት እንቀጽ 7 (1) (A) መሠረት የሀገሪቱን ሕገ መንግሥት፣ ሕጎች፣ የፌዴራል ተቋማትን እና ሌሎች ሕገ መንግሥታዊ ተቋማትን ሥልጣን የማክበር ግዴታ መግባቱም ፤ ስለዚህ ሕወሐት የሀገሪቱን የፖለቲካ ፖርቲዎች የምዝገባ ሕግ እና የምርጫ ቦርድን ሥልጣን በማክበር የመሥራት ግዴታ እንዳለበት ... ገልጿል።

የፌዴራል መንግሥት በመግለጫው ፤ ህወሓት ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት ስለተኬደባቸው መንገዶች ፣ ውይይቶች ፤ በህወሓት እና ምርጫ ቦርድ በኩል ስለተነሱት ልዩነቶች አብራርቷል።

ድርጅቱ ሕጋዊ ሰውነት እና ዕውቅና እንዲኖረው ለቦርዱ የትብብር ጥያቄ ስለማቅረቡም አስታውሷል።

እንዲሁም አዋጅ እስከማሻሻል በደረሰ እርምጃ ድርጅቱ ወደ ህጋዊ መስመር እንዲገባ ለማድረግ የተኬደበትን ርቀት ገልጿል።

ይህን ተከትሎ ህወሓት ሕጋዊ ሰውነት እና ዕውቅና ለማግኘት የሚጠበቅበት የፓርቲ ሰነዶቹን ማለትም የፓርቲውን ፕሮግራም እና ሕገ ደንብ፣ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ሰነዶችን ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማቅረብ በተሻሻለው አዋጅ መሠረት ተመዝግቦ ሕጋዊ ሰውነት እንዳገኘ አሳውቋል።

በመሆኑም " የምዝገባ እና የህግ ሰውነትን ጉዳይ በዚህ በመቋጨት፤ የሁሉም ባለድርሻ አካል ርብርብ ሰላምን በማጽናት፣ በመልሶ ግንባታ እና በልማት አጀንዳ ላይ ሊሆን ይገባል " ብሏል።

ፌዴራል መንግሥት"  አላስፈላጊ እና ሕዝብን የማይጠቅም፣ ትርጉም አልባ ንትርክን አስወግደን ለሕዝብ ረብ ያላቸው ጉልህ የሰላም እና የልማት አጀንዳዎች ላይ ልናተኩር ይገባል " ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia