TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56K photos
1.4K videos
202 files
3.79K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዕለታዊ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ? 💵 US Dollar #CASH Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 #TRANSACTION Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 💷 Pound Sterling #CASH Buying ➡️ 91.5537 Selling ➡️ 93.3848 #TRANSACTION Buying ➡️ 96.0811 Selling…
#ዕለታዊ : የዶላር ዋጋ ጨምሯል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዱ የአሜሪካ ዶላር በ77 ብር ከ1280 ሳንቲም እየተገዛ በ78 ብር ከ6706 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል።

ፓውንድ ስተርሊንግ በተመሳሳይ ጨምሯል።

አንዱ በፓውንድ በ94 ብር ከ3071 ሳንቲም እየተገዛ በ96 ብር ከ1932 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

ትላንት መጠነኛ መውረድ አሳይቶ የነበረው ዩሮ ዛሬ ጨምሮ አድሯል። አንዱ ዩሮ በ83 ብር ከ3754 ሳንቲም እየተገዛ በ85 ብር ከ0429 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

ከመንግስታዊ ባንክ ውጭ በግል ባንኮችም የዶላር ዋጋ ጨምሯል።

ለአብነት ወጋገን ባንክ አንዱን የአሜሪካ ዶላር በ77 ብር ከ7401 ሳንቲም እየገዛ በ79 ብር ከ2949 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

ዩሮ 82 ብር ከ6591 ሳንቲም እየገዛ በ84 ብር ከ3123 ሳንቲም እየሸጠ ሲሆን ፓውንድ ስተርሊንግ በ93 ብር ከ6991 ሳንቲም እየገዛ በ95 ብር ከ5731 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

በአንጻሩ ኦሮሚያ ባንክ ዶላርን ጨምሮ ዩሮ እና ፓውንድ ስተርሊንግ ትላንት ሲጠቀምበት በነበረው ተመን ነው ዛሬም የቀጠለው።

በዚህም አንዱ ዶላር በባንኩ በ74 ብር ከ7382 ሳንቲም እየተገዛ በ76 ብር ከ2329 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

ዩሮ በ81 ብር ከ0386 እየተገዛ በ82 ብር ከ6593 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል።

ፓውንድ ስተርሊንግ በ92 ብር ከ6021 ሳንቲም እየተገዛ በ94 ብር ከ4542 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

በገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን / Floating exchange rate ወይም ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በሚያደርጉ ነጻ ድርድር የውጭ ምንዛሬ መግዛት እና መሸጥ እንዲችሉ የሚፈቅደው አሰራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ባንኮች የየራሳቸውን ዕለታዊ ምንዛሬ አውጥተው እየተጠቀሙ ናቸው።

ዝርዝር ዕለታዊ ምንዛሬ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባውን አድርጎ ዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተደረገውን የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በማጽደቅ ለሕ/ተ/ም/ቤት እንዲላክ ወስኗል።

ምክር ቤቱ ምን አለ  ?

- የተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት የ1.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያስገኝ ነው። ከዚህ ውስጥ 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በእርዳታ፣ 500 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደግሞ በብድር መልክ የተገኘ ነው፡፡

- የፋይናንስ ድጋፉ ፦
° የኢትዮጵያ መንግሥት የማክሮ ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የጀመራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ለማስፈጸም
° ለሥራ ፈጠራ፣
° የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር፣
° የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመቅረፍ፣
° የመዋቅር ማስተካከያ ለማድረግ እንዲሁም የፌደራል መንግሥት የ2ዐ17 ዓ.ም በጀትን በቀጥታ ለመደገፍ የሚውል ነው፡፡

- ብድሩ ከወለድ ነፃ ፣ የ6 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ38 ዓመታት ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው። ከአገራችን የብድር አስተዳደር ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣምም ነው።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግዳሮቶቹ ምንድናቸው ?

ጠንካራ ጎኑን በሚመለከት በስፋት ከብሔራዊ ባንክ ሰነድ ላይ መረዳት ይቻላል።

ስለ ተግዳሮቶቹ ደግሞ የባንክ ጉዳዮች ባለሙያው ሙሴ ሸሙ ተከታዩን ሙያዊ ትንተና አቅርበዋል።


ከአስተያየታቸው መካከል ፦

- ገበያ መር (Free Floating) የውጭ ምንዛሪ ስርዓት በተረጋጋ፣ በቂ አቅርቦት እና ምርታማነት እውን በሆነበት ኢኮኖሚ ላይ ተመስርቶ ካልተተገበረ በስተቀር ውጤታማነቱ አስተማማኝ አይደለም።

- እጅግ የናረ ፍላጎት እና የአቅርቦት እጥረት ያለበት ኢኮኖሚ ገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ተመኑ ላይ ሲተገበር የውጭ ምንዛሪው ዋጋ የሚዋዠቅና በከፍተኝ ደረጃ የሚለዋወጥ ባህርይ ስለሚኖረው የምንዛሬ ተመኑ ከየት ተነስቶ የት ሊያደርስ እንደሚችል መገመት ያዳግታል። 

- እንደሚታወቀው ኢኮኖሚያችን የሚያመነጨው የውጭ ምንዛሪ መጠን ዝቅተኛና ፍላጎታችን የሚያጠረቃ ስላልሆነ የውጭ ምንዛሪውን ተመን ለገበያ ውድድር ብቻ መተዉ፣ የማያቋርጥ የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ንረትና ጡዘት ሊያስከትል ይችላል። 

- የብር የመግዛት አቅም መዳከምን ተከትሎ አገልግሎት፣ የጉልበት ዋጋን ጨምሮ፣ አቅርቦት/ ፍጆታ ነዳጅና ማዳበርያ... ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ስለሚያሳዩ ኑሮ በከፍተኛ ደረጃ ሊንር ይችላል። 

- በሰላም እጦት ምክንያት ኢኮኖሚው በምርታማነት፣ በኤክስፓርት፣ በነጻ ግበይትና እንቅስቃሴ ስለማይደገፍ አቅርቦት ተዳክሞ የዋጋ ንረቱ ተባብሶ ሊቀጥል ይችላል። "

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Mushe-Semu-07-31

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና  (NGAT) ምዝገባ ከሐምሌ 24 እከ ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም የሚካሄድ እንደሆነ ገልጿል።

የድህረ ምረቃ ፕሮግራም መማር ፍላጎቱ ያላቸው የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት በ
https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዕለታዊ : የዶላር ዋጋ ጨምሯል። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዱ የአሜሪካ ዶላር በ77 ብር ከ1280 ሳንቲም እየተገዛ በ78 ብር ከ6706 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል። ፓውንድ ስተርሊንግ በተመሳሳይ ጨምሯል። አንዱ በፓውንድ በ94 ብር ከ3071 ሳንቲም እየተገዛ በ96 ብር ከ1932 ሳንቲም እየተሸጠ ነው። ትላንት መጠነኛ መውረድ አሳይቶ የነበረው ዩሮ ዛሬ ጨምሮ አድሯል። አንዱ ዩሮ በ83 ብር ከ3754…
ዶላር ዛሬ ከሰዓት ጨምሯል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥዋት የነበረው የዶላር ዋጋ ዛሬ ከሰዓት ጨምሯል።

ባንኩ አንዱን ዶላር በ80 ብር ከ0203 ሳንቲም እየገዛ በ81 ብር ከ6207 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

በተመሳሳይ ፓውንድ ስተርሊንግም ጨምሯል።

አንዱን ፓውንድ ስተርሊንግ በ97 ብር ከ8436 ሳንቲም እየገዛ በ99 ብር 8005 እየሸጠ ነው።

ዩሮ 86 ብር ከ5019 ሳንቲም እየገዛ በ88 ብር ከ2320 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

(ሌሎች የከሰዓት የውጭ ምንዛሬ ዝርዝሮችን ከላይ ተመልከቱ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶላር ዛሬ ከሰዓት ጨምሯል። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥዋት የነበረው የዶላር ዋጋ ዛሬ ከሰዓት ጨምሯል። ባንኩ አንዱን ዶላር በ80 ብር ከ0203 ሳንቲም እየገዛ በ81 ብር ከ6207 ሳንቲም እየሸጠ ነው። በተመሳሳይ ፓውንድ ስተርሊንግም ጨምሯል። አንዱን ፓውንድ ስተርሊንግ በ97 ብር ከ8436 ሳንቲም እየገዛ በ99 ብር 8005 እየሸጠ ነው። ዩሮ 86 ብር ከ5019 ሳንቲም እየገዛ በ88 ብር ከ2320…
#ዕለታዊ : የጠዋቱ እና የከሰዓቱ የምንዛሬ ለውጥ ምን ይመስላል ? (በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)

💵 የአሜሪካ ዶላር !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ዶላር መግዣው 77 ብር ከ1280 ሳንቲም ፤ መሸጫው 78 ብር ከ6706 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ዶላር መግዣው 80 ብር ከ0203 ሳንቲም ፤ መሸጫው 81 ብር ከ6207 ሳንቲም ሆኗል።

💷 ፓውንድ ስተርሊንግ !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው 94 ብር ከ3071 ሳንቲም ፤ መሸጫው 96 ብር ከ1932 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው 97 ብር ከ8436 ሳንቲም መሸጫው 99 ብር ከ8005 ሳንቲም ሆኗል።

💶 ዩሮ !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ዩሮ መግዣው 83 ብር ከ3754 ሳንቲም መሸጫው 85 ብር ከ0429 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ዩሮ መግዣው 86 ብር ከ5019 ሳንቲም መሸጫው 88 ብር ከ2320 ሳንቲም ሆኗል።

#UAE ድርሃም !

➡️ ጠዋት ፦ 1 ድርሃም መግዣው 18 ብር ከ7954 ሳንቲም ፤ መሸጫው 19 ብር ከ1713 ሳንቲም ነበር።

➡️ ከሰዓት ፦ 1 ድርሃም መግዣው 19 ብር ከ5002 ሳንቲም ፤ መሸጫው 19 ብር ከ8902 ሳንቲም ሆኗል።

የውጭ ምንዛሬ በገበያው መወሰን / Floating exchange rate / የሚባለው ይኸው ነው። የውጭ ምንዛሬው በፍጥነት መለዋወጥ የሚታይበት ነው።


#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
ተጨማሪ በጀት ለፓርላማ ሊቀርብ ነው።

የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ድርጅቶች ያገኘውን ድጋፍ እና ብድር የያዘ ተጨማሪ በጀት በቅርቡ ለፓርላማ አቅርቦ እንደሚያስጸድቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል።

ይህ የተናገሩት ዛሬ በነበረው የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ ወቅት ነው።

ተጨማሪ በጀቱ ፦

➡️ ለዝቅተኛ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች ለሚደረግ የደመወዝ ጭማሪ፣

➡️ ለነዳጅ ድጎማ፣

➡️ ለዘይት ድጎማ፣

➡️ ለማዳበሪያ እና መድኃኒት ድጎማ የሚውል መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

ፎቶ፦ ፋይል

#EthiopianInsider #HoPR #Ethiopia

@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia

🎁በተወዳጆቹ ሜጋ ጥቅሎች በሽ በሽ እንበል! ለ90 እና ለ180 ቀን የሚቆዩትን ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎች በM-PESA በመግዛት እስከ 500 ብር የሚደርስ ቅናሽ አግኝተን ፏ እንበል! 🌐🤳 ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት!

🤖 የቴሌግራም ቦታችንን https://t.me/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
   🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
TIKVAH-ETHIOPIA
" የ6 ሰዎችን ማግኘት አልተቻለም  "- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ ኪንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ የደረሰዉን የመሬት መንሸራተት አደጋ በተመለከተ ክልሉ ዛሬ ወቅታዊ መረጃ ሰጥቶ ነበር። በዚህም መግለጫ " የቀበሌዉን ማህበረሰብ ቁጥር ለመለየት በተደረገ የቤት ለቤት ቆጠራ ስድስት ሰዎች አልተገኙም " ብሏል። አሁንም አስክሬን ፍለጋዉን እንደቀጠለ ጠቁሟል። በሌላ በኩል ፤ እስካሁን…
#Update

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የቀሪ ሰዎችን አስክሬን የማፈላለጉ ሥራ ማብቃቱን ዛሬ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት አሳውቋል።

ያልተገኙ ሟቾችን የመፈለጉ ሥራ ያበቃው አደጋው ከተከሰተበት ከባለፈው ሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ እስከ ትናንት ድረስ የቁፋሮ ሥራው ሲካሄድ ከቆየ በኋላ እንደሆነ ጠቁሟል።

በፍለጋው የ243 ሰዎች አስክሬን በማግኘት በክብር እንዲያርፍ ሲደረግ፤ የ6 ሰዎች እስክሬን ግን እስከ ትናንት ተፈልጎ አለመገኘቱን አሳውቋል።
#DW

@tikvahethiopia
#ምንዛሬ

የዛሬው ከሰዓት የግል ባንኮች የምንዛሬ ዋጋ ምን ይመስላል ?

ዶላር እና ዩሮን ጨምሮ ሌሎች የውጭ ምንዛሬዎች በጣም ጨምረዋል።

ለአብነት እንመልከት ፦

➡️ አቢሲንያ ባንክ
💵 ዶላር መግዣው 79.8507 ፤ መሸጫው 82.2462
💶 ዩሮ መግዣው 86.3185 ፤ መሸጫው 88.9081
💷 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው 97.6361 ፤ መሸጫው 100.5652
🇦🇪UAE ድርሃም መግዣው 19.4589 ፤ መሸጫው 20.0426

➡️ ሲንቄ ባንክ
💵 ዶላር መግዣው 81.2399 ፤ መሸጫው 82.8647
💶 ዩሮ መግዣው 87.5402 ፤ መሸጫው 89.2910
💷 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው ፤98.3822 ፤ መሸጫው 100.3498
🇦🇪 UAE ድርሃም መግዣው 18.9165 ፤ መሸጫው 19.2948

➡️ ቡና ባንክ
💵 ዶላር መግዣው 80.0203 ፤ መሸጫው 82.8212
💶 ዩሮ መግዣው 83.4588 ፤ መሸጫው 87.1690
💷 ፓውንድ ስተርሊንግ መግዣው 94.4014 ፤ መሸጫው 98.5980
🇦🇪 UAE ድርሃም መግዣው 18.4140 ፤ መሸጫው 19.6508

#Floating_exchange_rate

@tikvahethiopia
🔈 #የዜጎችድምጽ

" የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተለይ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ (ዶላር እና ሌሎች ምንዛሬዎች መውጣት መውረድ) ገበያውን እንደሚያናጋው የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ።

በተለይም ሁኔታው በዝቅተኛ ማህበረሰብ ክፍል / ዝቅተኛ የወር ገቢ ያለው ዜጋ ላይ የሚያሳድረው ጫና ከፍተኛ እንደሚሆን ለማንም ግልጽ ነው።

ነገር ግን የአንዳንድ ነጋዴዎች ተግባር ብዙዎችን ያበሳጨ ፣ ያስቆጣ ሆኗል።

' የማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ ተደርጓል ' ከመባሉ ከወራት በፊት ያስገቡትን ምርት ፣ ቁሳቁስ በተለይ የምግብ ግብዓት ላይ ጭማሪ ለማድረግ ሲጥሩ ተስተውሏል።

እነዚህ ነጋዴዎች እዚሁ ከማህበረሰቡ ጋር አብረው የማይኖሩ ይመስል ያለ አንዳች ምክንያት በዚህ ልክ ራሳቸውን ክፉኛ ወደው ወገናቸውን ለመጉዳት የሚሄዱበት ርቀት አሳፋሪም ጭምር ነው።

አንዳንዶቹ ምርት ደብቀው " የለም " ማለትም ጀምረዋል።

ለመሆኑ ማሻሻያ ሳይደረግ በፊት ያስገቡት እና መጋዘን ውስጥ ያስቀመጡትን ምርት፣ ቁሳቁስ ላይ " ዶላር ጨምሯል " በማለት  ፦
° በምን አግባብ ነው ዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉት ?
° ለምንስ ነው ከገዛ ወገናቸው ምርት የሚደብቁት ?
° እነሱስ የሚኖሩት ከህብረተሰቡ ጋር አይደለም ?
° አብረው ደስታንና ሀዘንን ችግርን የሚጋሩት ከዚሁ ህዝብ ጋር አይደለም ? ፤
° ነገ አንድ ነገር ቢሆኑ የሚደርስላቸው ይኸው ዛሬ ዋጋ እየጨመሩ የሚያሰቃዩት ህዝብ አይደል ?

ህዝቡ ከዛሬ ነገ ምን ይጠብቀኛል ፤ ኑሮው እንዴት ልገፋው ነው ብሎ በተጨነቀበት በዚህ ወቅት መሰረታዊ አቅርቦትን መደበቅ እና ዋጋ መጨመር ምን አይነት የጭካኔ ተግባር ነው ? ምን አይነት ስግብግብነትስ ነው ?

ይህ የነጋዴዎች ተግባር ጭንቀት ላይ ጭንቀት የሚጨምር እጅግ የሚያስተዛዝብ ነው። እንዲህ ያለ ወቅት መረዳዳት እና መተዛዘን ሲገባ ትርፍ ለመሰብሰብ መሮጥ አሳፋሪ ነው።

ከምንም በላይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው ነዋሪ ጫናው እንደሚበረታበት እየታወቀ ፣ እንደሚያሰቃየው እየታወቀ መቶ አመት ለማይኖር ህይወት በወገን ላይ እንዲህ መጨከን ተገቢ አይደለም።

ከላይ የሚወርደውን ሁሉ በማይችል ጫንቃው የሚሸከመው በዝቅተኛ ገቢ የሚኖረው የሀገሬው ህዝብ ነው። "

(በናውስ የሐሳብ መድረክ)

የሐሳብ መድረኩን ይቀላቀሉ :
https://t.me/NousEthiopia/36

Via
@nousethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF " ጉባኤ በማካሄድ የሚፈጠር ግጭት አይኖርም  " - የህወሓት ሊቀመንበር የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) ዛሬ ሀምሌ 20/2016 ዓ.ም በክልሉ ለሚገኙ የመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተው ነበር።  በዚህም ፥ ከ2 ቀናት በፊት አዲስ አበባ ድረስ በመሄድ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስተር አብይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር…
#Tigray #TPLF

" እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?  "  - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክተው ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር።

አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?

- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት የትግራይ ህዝብ እና ህልውና ያዳነና ያስቀጠለ ነው።

- ሁሉም የትግራይ ችግሮች ከውጭ ተፅእኖ ነፃ ናቸው ባይባልም በአመዛኝ ውስጣዊ ፓለቲካዊ ችግሮች ናቸው ያሉት። ውስጣዊ ችግሮቻችን ባይጠልፉን የፕሪቶሪያው ስምምነት በፈጠረው እድል በርካታ ለውጦች ይታዩ ነበር።

- ውስጣዊ ፓለቲካዊ ድክመታችን ሰከን ብለን መመርመር አለብን፤ ከጥፋት ለጥቂት ያመለጠ ህዝብ መልሰን ወደ ጦርነት እንዳናስገባው በሃላፊነት መንፈስ መንቀሳቀስ አለብን።

- ጉባኤ መካሄድ የለበትም ያለ የለም ፤ አሁን ያለው ሩጫ ግን ስልጣን ለመቆጣጠርና ከተጠያቂነት ለማምለጥ ያለመ ነው።

- ህወሓት መዳን የሚችለው በጭቅጭቅ ሳይሆን በሳልና ተራማጅ ሃሳብ በማመንጨት ነው።

- እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30/2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር ቢሆንም ፍትህ ሚንስቴር በደብዳቤ አስቀርቶታል። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?

- " ከፌደራል መንግስት ጥሩ መግባባት ደርሰናል ተስማምተናል " ይባላል እንጂ መሬት ላይ ጠብ የሚል ነገር የለም። አዲስ አበባ በመሄድ የሚስማሙትና እዚህ የሚነገረን የተለያየ ነው፤ ይህ ካድሬው ሊያውቀው ይገባል።

- የተጀመረው ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ተግባር ከተጨማሪ ግጭት ቂምና ቁርሾ በፀዳ መልኩ እንዲፈፀም እየሰራን ነው።

- በእርስ በርስ ሽኩቻ ባሳለፍናቸው ጊዚያቶች ፀፀት ተስምቶን ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ለመመለስና የፕሪቶሪያው ስምምነት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈፀም በተቀናጀ የአመራር ጥበብ መስራት ይጠበቅብናል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
" ተማሪዎችን አወዳድሬ ነው የምቀበለው " - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

የራስ-ገዝ ዩኒቨርሰቲ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በራሱ ፖሊሲና መስፈርት ፤ ምዘናና የክፍያ ስርዓት ተማሪዎችን አወዳድሮ እንደሚቀበል አሳውቋል።

በመደበኛ፣ በማታና በርቀት በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ አመልካቾች በቅርቡ ዝርዝር ማስታወቂያ እንደሚያወጣ ገልጿል።

ዝርዝር ማስታወቂያውን ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF " እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?  "  - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክተው ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር። አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ? - የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት…
#Tigray

" ትግራይ በሁለት ቡድን በተከፈለ ገዢ መታመስ  ይበቃት !! " - ሦስት የትግራይ ፓርቲዎች

ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ፣ ውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት) ፣ባይቶና ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ አስመልክተው በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም " ስልጣኑ ከመጠበቅ አልፎ አርቆ ማሰብ የማይችለው ስርዓት ችግሮቹ ወደ ህዝብ ለማላከክ የሚያደርገው ሸፍጥ በጊዜው መታረም አለበት " ብለዋል።

" የትግራይ ችግር መፍትሄ የሚያገኘው ተጠያቂነት ያለው የመንግስት ስርዓት ሲኖር ነው " ያሉት ፓርቲዎቹ " ይህ የሚሆነው ደግሞ ሁሉን አቀፍ ምክር ቤት ሲቋቋም ብቻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል። 

ፓርቲዎቹ በስም ያልጠቀሱትና " ፀረ ህዝብ " ያሉት ሃይል ችግሮቹን ወደ ህዝብ ለማጋባት የሚያደርገው ሸፍጥና አስመሳይነት ተቀባይነት የለውም መታረም አለበት በማለት አስጠንቅቀዋል። 

" የትግራይ ህዝብ ለስልጣናቸው ህልውና በማሰብ ብቻ ወደ አደገኛ እልህ ከገቡት ገዢ ቡድኖች ራሱ በማራቅ አድነቱ ጠብቆ ሊታገላቸው ይገባል " ብለዋል።

" ትግራይ በሁለት ቡድን በተከፈለ ገዢ መታመስ ይበቃት ! " ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።

" ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ የቅድምያ ቅድምያ መታየት ያለበት አጀንዳ መሆን ይገባዋል " ያሉት ፓርቲዎቹ " የተጀመረው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት " ሲሉ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia