TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ላለፉት ስድስት ቀናት በመላ አገሪቱ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ተጠናቋል። 57 የመንግሥት እና 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ማስፈተናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከመውጫ ፈተናው ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉ ፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው…
#MoE

የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና እና የሪሚዲያል ማጠቃለያ ፈተና ውጤቶች መቼ ይፋ ይደረጋሉ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና እና የዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና መቼ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።

የትምህርት ሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ፥ የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ውጤት ከሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

በጣም ከዘገየ እስከ ሰኞ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ብለዋል፡፡

የመውጫ ፈተና ውጤት በቀጣይ ቀናት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ማስመረቅ ከመጀመራቸው በፊት ይፋ እንደሚደረግ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡

#TikvahEthiopia

Via @tikvahuniversity
#eQUB_APP

መልካም ዜና ለዕቁብተኞች! የዕቁብ ክፍያዎን ካሉበት ቦታ ሆነው ለአጠቃቀም ቀላል እና ምቹ በሆነው የዕቁብ መተግበርያ ከያሉበት ቦታ ሆነው ህልሞን ያሳኩ።

የዕቁብ መተግበርያን አሁን ይጫኑ👇
📱 Android - Google Play | 📱 iPhone - App Store

Telegram Channel: @equbapp

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 0116671717 ወይም 0116670404 ይደውሉ።
#DStvEthiopia

🔥 ከከባድ የምድብ ጨዋታዎች በጓላ የአወሮፓ ጨዋታ ቅዳሜ ምሽት ጥሎ ማለፍ ጫዋታዎች ይጀምራሉ!

🤔 ፉክክሩም አይሏል! እነማን ወደ ሩብ ፍፃሜ ያልፋሉ? የእናንተን አስተያየት ከስር አጋሩን!

ለናንተ ምርጡ ቡድንስ ማነው? መልሶቻችሁን ከስር አጋሩን!

በጀርመን የሚደረጉትን ደማቅ ጨዋታዎች በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች በወር ከ350 ብር ከጎጆ ፓኬጅ ጀምሮ ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#Euro2024onDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ላለፉት ስድስት ቀናት በመላ አገሪቱ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ተጠናቋል። 57 የመንግሥት እና 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ማስፈተናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከመውጫ ፈተናው ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉ ፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው…
#MoE

ትናንት የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ተሰርዞ በድጋሚ ይሰጣል ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው " የቴክኒክ ችግር " አጋጥሞት እንደነበር ገልጿል።

ተማሪዎች በበኩላቸው ቀደም ብሎ ፈተናው ወጥቶ በወረቀት እትም እና በPDF መሰራጨቱንና ተማሪዎችም ሰርተው መግባታቸውን አመልክተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ግን ፈተናው " የቴክኒክ ችግር " ስላጋጠመው ፈተናው በድጋሜ  በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጠዋት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እና ከሰአት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ይሰጣል ብሏል።

ምን አይነት የቴክኒክ ችግር እንደሆነ በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

ለፈተናው ተቀምጠው የነበሩ የፋርማሲ ተማሪዎች በየተፈተኑበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንዲወስዱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ተማሪዎች ምን አሉ ?

የጥዋቱም ይሁን የከሰዓቱ ፈተና ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ እንዴት እንደሆነ ባይታወቅም ወጥቶ ተማሪዎች በበድን ሰርተውት እንደገቡ ገልጸዋል።

ሌላው ፈተናው ከብሉፕሪነቱ ጋር እንደማይጣጣም ፤ ትምህርቱንም የሚመዝን ፈተና እንዳልወጣ አመልክተዋል።

የባለፉት ፈተናዎችን እንዳዩና የዚህ አይነት ፈተና ግን እንዳልነበር ጠቁመው ፈተናው ማስተካከያ እንዲደረግበት አሳስበዋል።

የ2016 ዓ/ም ፈተና ትላንት መጠናቀቁ ይታወሳል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የዘንድሮው ፈተና ከ220 በላይ ፕሮግራሞች ያለምንም ችግር Smoothly ነው የተሰጠው " ብሎ ነበር።

" ከፈተናዎቹ ጋር የተያያዘም ምንም አይነት Issue አላጋጠመንም፤ አንድም ቅሬታ ለትምህርት ሚኒስቴር አልደረሰም " ሲል ነበር ያስረዳው።

ሚኒስቴሩ ይህን ቢልም  ፤ በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው ፦
- የማኔጅመንት
- የማርኬቲንግ ማኔጅመንት
- የሀይድሮሊክና ውሃ ሃብት
- የቬተርነሪ ሜድስን
- የኸልዝ ኢንፎርማቲክስ ተማሪዎች ተማሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት እና ምክትል ፕሬዜዳንት በጋራ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ። ስራ መልቀቂያውን ያስገቡት ፤ " በፍትህ እና የዳኝነት ሰርዓቱ ለውጥ ለማምጣት ያሰብናቸው ፣ ያቀድናቸው የጀመርናቸው ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች ለማሳካት የሚያስችል ሁኔታ ማግኘት ስላልቻልን ነው " ብለዋል። ሰኞ ሰኔ 17/2016 ዓ.ም የተፃፈው የስራ መልቀቅያ ደብዳቤ በበርካታ የማህበራዊ…
#Update

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጥያቄያችን ለመመለስ ቃል ስለገባ የስራ መልቅቅያ ጥያቄያችን ትተነዋል " - የትግራይ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ያስገቡትን የመልቀቂያ ደብዳቤ እንደተውት አሳወቁ።

ፕሬዜዳንቱና ምክትል ፕሬዜዳንቱ ይፋ ባደረጉት መግለጫ ፤ ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም ያቀረቡት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ተከትሎ ሰኔ 18 /2016 ዓ.ም ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ውይይት ማደረጋቸውን ገልጸዋል።

በዚ ውይይት ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ለመመለስ ቃል በመገባቱ ስራ የመልቀቅ ጥያቄያቸውን እንደተውት አሳውቀዋል።

ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ምን እንደሆኑ በግልፅ ያላብራሩ ሲሆን ከላይ እስከ ታች የሚገኘው የፍርድ ቤት አካል ስራውን ተረጋግቶ እንዲሰራ መልእክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዜዳንቱና  ምክትል ፕሬዜዳንቱ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸው ተከትሎ የወረዳና የዞን ፍርድ ቤቶች ስራ የማቆም አድማ መምታት ጀምረው ነበር

ከክልሉ ፕሬዜዳንት ከተደረገው ውይይት በኃላ ችሎቶች ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በአካል ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

ከመቐለ ውጪ በመላው ክልል ያሉ ፍርድ ቤቶች መደበኛ አገልግሎት መስጠት መቀጠላቸው የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የፕሮቶኮል ሹም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
#ጎንደር

° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” - የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች

° “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ 


በአማራ ክልል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች፣ የውሃ ችግር እንደፈተናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የከተማው ነዋሪዎች በሰጡት ቃል፣ “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም። በአፋጣኝ መፍትሄ እንሻለን ” ብለዋል።

በከተማው የውሃ አቅርቦት እንደሌለ፣ በተለይ ህፃናት የውሃ ጥሙን መቋቋም እንዳልቻሉ፣ ሰው የክረምት ውሃ ለመጠጣት መገደዱን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል። 

ከዚህ ባለፈ ነዋሪዎች የጉርጓድ ውሃ በሰልፍ የመጠቀም ደረጃ እንደደረሱ አመልክተዋል።

ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አያል ፤ “ እውነት ነው። እንዲያውም ማህበረሰቡ ታጋሽ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ አሁን ዝናብ ስለዘነበ ትንሽ ይቀንሳል እንጂ በአንድ ወር ነው ሰው ውሃ ሲያገኝ የነበረው። ግድቡ ሙሉ ለሙሉ ቆሞ ነበር። አሁን ትንሽ ውሃ ስለያዘ ምርት ስለጀመርን አሁን ወደ 25 ቀን እየወረደ ነው ” ብለዋል።

የኢንተርን ሀኪሞቹን ቅሬታ በተመለከተ፣ “ ሆስፒታል ላይ ግን 24 ሰዓት ነው የምንሰጠው። መብራትና አጠቃላይ ምርት ቆሞ ካልሆነ አይቋረጥም ” ነው ያሉት።

“ የማህበረቡ ቅሬታ ግን እውነቱን ለመናገር ከቅሬታ ባለፈ ሌላ ነገር ቢሉም አይፈረድባቸውም ትክክል ናቸው ” ያሉት አቶ ወርቅነህ፣ “ እንደዚህ ትዕግስተኛ የሆነ ማህበረሰብ የለም ” ሲሉ ተናግረዋል።

ችግሩ ከቆዬ ለምን በወቅቱ መፍትሄ እንዳልተቸረው ሲያስረዱም፣ “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል። እንደዚህ አይነት ቻሌንጆች አሉብን ” ብለዋል።

ችግሩን ለመቀረፍ የገጠማችሁ ዋናው ችግር ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄ የፋይናንስ ችግር እንዳለባቸው ገልጸው፣ ምን ያህል በጀት እንደሚያስፈልግ ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

“ ችግሩን መነሻ ተደርጎ የአጭር፣ የአስቸኳይ፣  የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜያት ተብሎ ስራዎች እየተሰሩ ነው። አንዳንዶቹን ቶሎ እናጠናቅቃቸዋለን ” ብለዋል።

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚበጀውን በተመለከተ፣ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበው፣ ማህበረሰቡ ላሳየው ታጋሽነት ምስጋና አቅርበዋል። 

ለነዋሪዎቹ ከሚያስፈልገው የውሃ መጠን እየቀረበ ያለው ምን ያህሉ እንደሆነ፣ ምን ያህል ጉድጓድ እየተቆፈረ እንደሆነ፣ ችግሩን በተጨባጭ እስከ መቼ ለመቅረፍ እንደታሰበ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ  ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በሀገሪቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ የቀሰቀሰው የፋይናንስ ረቂቅ ሕግን እንደሚያስቀሩት / እንደማይፈርሙበት አስታውቀዋል። ሩቶ እዚህ ውሳኔ ላይ የተደረሱት ተቃውሞውን ተከትሎ ቢያንስ 20 ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ነው። ፕሬዜዳንቱ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ " ኬንያውያን በሕጉ ዙሪያ ያሰሙትን ተቃውሞ በደንብ ተከታትያለሁ፤ ስለዚህም ሕጉን እንደማይፈልጉት በግልጽ ተናግረዋል፤…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኬንያ

ምንም እንኳን ትላንትና የኬንያ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ በፋይናንስ ረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን እንደማያኖሩ እና ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንደተደረገ ቢያሳውቁም ዛሬም ተቃዋሚዎች አደባባይ ወጥተው ነበር።

ናይኖቢ ውስጥ የመንግስት ጸጥታ ኃይሎች አደባባይ በወጡ ተቃዋሚዎች ላይ አስለቃሽ ጪስ ተኩሰዋል።

ወደ ፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት የሚወስደውን መንገድ ዘግተውታል።

ዛሬም በከተማይቱ በርካታ የንግድ ተቋማት ባደረባቸው ስጋት በራቸውን ሳይከፍቱ ነው የዋሉት።

ከናይሮቢ በተጨማሪ ሞምባሳና ኪሱሙ ተቃዋሚዎች አደባባይ ወጥተው ነበር።

ትላንት ሩቶ ውሳኔያቸው ካሳወቁ በኃላ ተቃዋሚዎች ፦
- ቀጣይ ወዳሉበት ቤተመንግስት እንመጣለን። ይጠብቁን !
- ' ከሃዲ ፣ ወንጀለኞች ' እያሉ በቴሌቪዥን ለተናገሩት ዋጋ ይከፍላሉ
- ስልጣን የህዝብ ነው
- ለውሳኔው አርፍደዋል
- አሁን ደግሞ የስልጣን መልቀቂያ ለማስገባት ይዘጋጁ !
- ስልጣን ለመልቀቅ ይዘጋጁ የሚሉ መልዕክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ሲያሰራጩ ነበር።

ኬንያውያን የፋይናንስ ረቂቁን " ኑሮ ያስወድድብልናል ፣ የስራ አጥነት እጅግ በከፋበት ሰዓት ግብር መጨመር አይገባም ፣ ተደራራቢ ግብር በቃን " በሚል ነበር ተቃውሞ የጀመሩት።

በወጣቶች በተመሩ የጎዳና ላይ ተቃውሞዎች ቢያንስ 20 ሰዎች ህይወታቸውን እጥተዋል። ተቃውሞው እየበረታ ሲመጣም ሩቶ " በቃ ረቂቅ ሕጉን ትቼዋለሁ " የሚል ውሳኔያቸውን አሳውቀዋል።

#Kenya

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 22 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.me/BoAEth


#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa በሀዋሳ ከተማ የስፓርት ውርርድ ( #ቤቲንግ ) ቤቶች እየታሸጉ / እየተዘጉ ይገኛሉ። ይህ ተከትሎ የስፖርት ውርርድ ቤት ባለቤቶች " እንዴት የንግድ ፈቃድ እያለን ይዘጋብናል ? " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል። እነዚህ የስፖርት ውርርድ ቤቶች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክኒያቶች ተዘግተው የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ተከፍተው ነበር። አሁን ላይ ተመልሰው መዘጋት/መታሸግ መጀመራቸው…
#Update

" የስፖርት ውርርድ ቤቶችን የመዝጋትና የመክፈት አሰራር አድሎአዊነት የተንጸባረቀበት ነው " - ቅሬታ አቅራቢዎች

" የተከፈቱ ቤቶች ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያመጡ ናቸው " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ ያሉ የስፖርት ውርርድ ቤቶች  " ህጋዊ አይደሉም ፣ በብዛት  የተከፈቱበት አካባቢም የትምህርትና የመኖሪያ ሰፈር ነው " በሚል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቢዘጉም ከቀናት ቆይታ በኋላ ግን የተወሰኑት ተከፍተዉ ስራ ጀምረዋል።

ይህንን ተከትሎ ፥
- ለምን ሁሉም በህግና ስርአት እየሰራ እና ግብርም እየከፈለ እያለ በከፊል ተከፍቶ በከፊል ይዘጋል ?
- ቤቶቹን የመዝጋትና የመክፈት ስራን የሚሰራዉ የከተማው ፖሊስ አሰራሩ አድሏዊነት የታየበት ነው፤
- ገንዘብ ሰጥተው የሚያስከፍቱ ሰዎችም እንዳሉ እየተሰማን ነው ሲሉ የስፖርት ውርርድ ቤታቸው የተዘጋባቸዉ ግለሰቦች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የከተማዉ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ፥ አሁን ላይ ተከፍተዉ ወደስራ የተመለሱት ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያቀረቡ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

በተጨማሪም " ለሀገር ፈጽሞ ጥቅም የማይሰጠዉ የቨርቹዋል አሰራር አሁንም እንደተከለከለ ነው። ካሁን በፊት እንደህግ ያስቀመጥነዉ የመኖሪያ ቤትና የትምህርት ቤቶች ዙሪያ የተጣለዉ ክልከላ ዛሬም ቀጥሏል " ብለዋል።

ከዚህ ውጭ አከፋፈቱን በተመለከተ የሚነዛዉ ስም ማጥፋት አግባብ አለመሆኑን ገልጸዉ ማንኛዉም አካል ህጋዊ ሆኖ ከመጣ ድርጅቱን ማስከፈት እንደሚችል ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከኮሪደር ስራው ጋር በተያያዘ ከመገናኛ ወደ ቦሌ የሚወስደው መንገድ ከሃያት ሆስፒታል በኋላ ከነገ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ሙሉ ቀንና ምሽትን ጨምሮ ለማንኛውም አይነት ተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረግ ተገልጿል።

አሽከርካሪዎች ሃያት ሆስፒታል ጋር ሳይደርሱ በፊት እና ከሆስፒታሉ አጠገብ ያሉትን የቀኝ መታጠፊያዎችን እንዲጠቀሙ የአ/አ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ጥሪ አቅርቧል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#Ethiopia

" በ7 ቀናት ማስረጃ አቅርቡ ካልሆነ ሕጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " - የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 11 ፓርቲዎች በ7 ቀናት የሴትና የአካል ጉዳተኛ አባሎቻቸውን መረጃ እንዲያቀርቡ አሳሰበ።

የተባለውን የማይፈጽሙ ከሆነ ሕጋዊ የሆነ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አሳውቋል።

ቦርዱ ሀገሪቱ ውቅጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው ለሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከመንግሥት የሚመደብ የ2014፤ 2015 እና 2016 በጀትን አከፋፍሏል።

ይሀንን የበጀት ድጋፍ ለማከፋፈል በሕጉ ከተቀመጡ መሥፈርቶች መካከል የፖለቲካ ፖርቲዎች ያሏቸውን ሴት እና አካል ጉዳተኛ አባላት ቁጥር በቃለ-መኃላ አስደግፈው ማቅረብ ነው፡፡

በዚህም መሠረት ፥ 21 ፖለቲካ ፖርቲዎች በ2016 ዓ/ም ለቦርዱ ያሰወቁት የሴት እና የአካል ጉዳተኛ አባሎቻቸው በ2014 እና 2015 ዓ.ም ካቀረቡት ቁጥር አንጻር የተጋነነ ሆኖ ተገኝቷል።

በዚህም ምክንያት ፖርቲዎቹ የአባሎቻቸውን ሙሉ መረጃ ለቦርዱ እንዲያቀርቡ መጋቢት 25/2016 ዓ/ም አሳውቆ ነበር።

10 የፖለቲካ ፖርቲዎች የተለያዩ ምላሾችን የሰጡና በእጃቸው የሚገኙ መረጃዎችን አቅርበዋል።

11 ፖርቲዎች ማለትም ፦

➡️ የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት
➡️ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ
➡️ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ
➡️ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር
➡️ ብልጽግና ፓርቲ (ገዢው ፓርቲ)
➡️ ራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
➡️ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ
➡️ የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ
➡️ ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት
➡️ ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
➡️ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ግን በአንድ ዓመት ውስጥ ከ10,000 እስከ 900,000 የሴት አባላትና የአካል ጉዳተኛ አባላት ቁጥር ነው ያቀረቡት።

ፓርቲዎቹ ላቀረቡት ለዚህ ቁጥር ያላቸውን ማስረጃ እንዲያቀርቡ ቢጠየቁም እስካሁን ሳይሰጡ እንደቀሩ ተገልጿል።

በመሆኑም በ7 ቀን ውስጥ ማስረጃውን ካላቀረቡ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቦርዱ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
#አሜሪካ

ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ ፤ በሉዊዚያና ግዛት ከታች አንስቶ እስከ ዩኒቨርሲቲ ባሉ በሁሉም የመማሪያ ክፍሎች ውስጥ አስርቱ ትዕዛዛት እንዲለጥፉ ታዟል።

ትላንት ደግሞ የኦክላሆማ ግዛት በአስቸኳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንዲጀመር አዟል።

የግዛቱ ትምህርት ቢሮ በግዛቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች መጽሐፍ ቅዱስን በትምህርት ስርዓታቸው በአስቸኳይ እንዲያካትቱና እንዲያስተምሩ መመሪያ አስትላልፏል።

በግዛቱ የትምህርት የበላይ ተቆጣጣሪ ሪያን ዋልተርስ የተላከ መመሪያ " አፋጣኝ እና ጥብቅ ተፈጻሚነትን " የሚፈልግ አስገዳጅ ድንብ ነው ይላል።

ዋልተርስ " መጽሐፍ ቅዱስ ታሪካዊና ባህላዊ መሠረት ነው "  ብለዋል።

" ያለ መጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ እውቀት የኦክላሆማ ተማሪዎች የአገራችንን መሠረት በትክክል መረዳት አይችሉም " በማለት ነው በአስቸኳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንዲሰጥ መታዘዙን ያመለከቱት።

በግዛቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ይተገበራል።

ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ እያንዳንዱ ክፍል መጽሐፍ ቅዱስ ሊኖረው ይገባል ተብሏል። ሁሉም አስተማሪዎች በክፍሉ ውስጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ማስተማር እንዳለባቸው ታዟል።

የሲቪል መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግን ይህንን ውሳኔ ተቃውመዋል።

ሃይማኖት እና መንግሥት መለያየት አለባቸው ብለዋል።

አንድ መንግሥትን ከሃይማኖት መለያየት እንዳለበት የሚሰራ ተቋም ፥ " የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ሰንበት ትምህርት ቤቶች አይደሉም " ብሏል።

" ሪያን ዋልተርስ የተሰጠውን የመንግሥት ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም ሃይማኖታዊ እምነቱን በሌሎች ላይ ለመጫን እየተጠቀመበት ነው። ይህ እኛ ባለንበት ሊሳካ አይገባም " ብሏል ተቋሙ።

በአሜሪካ የሃይማኖት ነፃነትን ለማስጠበቅ የሚሰራው ኢንተርፌይዝ አሊያንስ ፤ " መመሪያው ግልጽ በሆነ መልኩ ሃይማኖትን መጫን ነው " ሲል ገልጾታል።

" እውነተኛ የእምነት ነፃነት ማለት የትኛውም የሃይማኖት ቡድን አመለካከቱን በሁሉም አሜሪካውያን ላይ እንዳይጭን መከላከል ነው " ብሏል።

#BBC #CNN

@tikvahethiopia
ባሉበት ሆነው በኮንፈረንስ ጥሪ በጋራ ያውጉ !

የቦታ ርቀት ሳይገድብዎ እንደልብዎ የሚወያዩበት የኮንፈረንስ ጥሪ አገልግሎትን በመጠቀም እስከ አምስት ሆነው በአንድ ላይ ይወያዩ፤ ይጨዋወቱ!

የመጀመሪያውን ስልክ ደውለው ደንበኛው መስመር ላይ እንዲጠብቅዎ በማሳወቅ ተጨማሪ ጥሪ ማድረግ (Add call) እስከ አምስት ሰው የሚፈልጉትን ያህል ካስገቡ በኋላ ለማገናኘት ‘Merge’ ወይም ‘conference’ የሚለውን በመጫን የስልክ ጥሪዎቹን ወደ አንድ ማምጣት ይችላሉ፡፡

ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት በ https://t.me/EthiotelecomChatBot 24/7 ያግኙን !

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና እና የሪሚዲያል ማጠቃለያ ፈተና ውጤቶች መቼ ይፋ ይደረጋሉ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና እና የዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና መቼ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል። የትምህርት ሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ፥ የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ውጤት ከሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ…
#Update

የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኳል።

የተማሪዎቹ ውጤት ዛሬ ለተቋማቱ መላኩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል።

በዚህም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የዘንድሮው የመውጫ ፈተና ለ57 የመንግሥት እና ለ124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ244 የቅድመ ምረቃ መርሐግብሮች መሰጠቱ ይታወቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቴፒ #አሽከርካሪዎች ° “ ከቴፒ ቡና ጭነን ለመውጣት ተከልክለን ከቆምን ወር ሊሞላን ነው ” - አሽከርካሪዎች ° “ ክልል ኮሚቴ አቋቁቁሞ ነገሩን እያጣራ ነው ”- ቡናና ሻይ ባለስልጣን የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይንቀሳቀሱ በመከልላቸው ያለምንም መፍትሄ ከሦስት ሳምንታት በላይ ለመቆም እንደተገደዱ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል። “ ለሥራ የምንወጣው ቤተሰቦቻችንንም ለማስተዳደር…
#Update

“ አሁንም ድረስ ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ ” - አሽከርካሪዎች 

“ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” - ቡናና ሻይ ባለስልጣን

ከቴፒ የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይወጡ ከዚህ ቀደም ተከልክለዋል ከተባሉት 24 ተሽከርካሪዎች መካከል 3ቱ አሁንም እንዳልተለቀቁ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ አንድ አሽከርካሪ፣ “ አሁንም ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ። ደቡብ ምዕራብ ቦንጋ ከተማ በቡናና ሻይ ባለስልጣን ግቢ ውስጥ አቁመዋቸዋል ” ብለዋል።

ሌሎችም አሽከርካሪዎች፣ በበኩላቸው ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተው፣ ተሽከርካሪዎቹ ቦንጋ የቆሙት ቴፒ ከወጡ በኋላ ቡናው ' Commercial ነው ’ ተብሎ መሆኑን አስረድተዋል።

የተለቀቁት ተሽከርካሪዎችም ቢሆኑ የተለቀቁት ከአንድ ወር መጉላላት በኋላ በመሆኑ በኑሮ ላይ ከባድ ጉዳት እንደገጠማቸው አስረድተው፣ “መጨረሻ ላይ ቡናው Local ነው ተብሎ ተለቀቅን፣ በዚህ ጉዳይ ሲጀመር መጠየቅ ያለበት ሹፌር አልነበረም” ብለዋል።

ከአሽከርካሪዎቹ በኩል ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ጥያቄ ያቀረበላቸው የቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻፊ ዑመር፣ “ ስንመረምር 3ቱ መኪና Local ብለው የጫኑት የExport ቡና ሆነ ” ብለዋል።

“ ስለዚህ የExport ቡና መሸጥ ህገ ወጥ ነው። አገርን ዶላር ማሳጣት ነው። 3ቱ መኪና እዛው ቆመው ነው ያሉት በፓሊስ እጅ ነው ” ሲሉ ተናግተዋል።

አቶ ሻፊ “ አሁን ላይ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” ብለው “ እንደዚህ ያደረጉ አካላትም ለህግ እንዲቀርቡ ለደቡብ ምዕራብ ደብዳቤ ፅፈናል ” ሲሉ አክለዋል። 

ትክክለኛ የችግሩ ምንጭ ማነው ? በማለት ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አቶ ሻፊ፣ “በሁሉም Side አለ” ብለዋል።

“ ላኪዎቹ የ Local አስመስለው Exportable ቡና ሲገዙ በጥሩ ዋጋ ስለሚሸጡ። ለአገር አያስቡም። አቅራቢው ደግሞ ቡናን በአፈርና ውሃ እያሸ ወደ Local እንዲገባ ስለሚያደርግ ችግር አለበት” ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው፣ “አሽከርካሪዎቹም ቢሆኑ እያወቁ ነው የተሻለ ዋጋ ስለሚከፈላቸው ቴፒ ሂደው የሚጭኑት። ሲጀመር የExports ቡና ማከማቻ፣ Localን ወደ Export የሚለየው አዲስ አበባ ነው። ቴፒ የሚያስሄዳቸው ነገር የለም” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ትግራይ

ግለሰቡ በአሰቃቂ የግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል።

ግድያው መቼና ? የት ተፈፀመ ? 

አሰቃቂ የግድያ ተግባሩ ግንቦት 17/2016 ዓ.ም ነው የተፈጸመው።

የተፈፀመበት ደግሞ በትግራይ ደቡባዊ ዞን ራያ ዓዘቦ ወረዳ ሀወልቲ ቀበሌ ዓዲ መጥሓን በተባለ ልዩ ቦታ ነው።

በግድያ ተግባር ተጠርጥሮ የሚፈለገው ግለሰብ ኣባዲ መሓሪ ረዳ ይባላል።

ግለሰቡ የአምስት ልጆች እናት የሆነች ባለቤቱ ወ/ሮ ዕፃይ ከበደ ገድሎ ከተሰወረ ከአንድ ወር በላይ ሆኖታል። 

የወ/ሮ ዕፃይ ቤተሰቦችና የራያ ዓዘቦ ወረዳ ፓሊስ በጋራ በግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ የተሰወረውን ኣባዲ መሓሪ ረዳ የተባለ ግለሰብ ያየውና ያለበት ቦታ የሚያውቅ 0996709824/0919548923 የሞባይል ቁጥሮች በመጠቀም መረጃ እንዲሰጣቸው ትብብር ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia