TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.86K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ስፖርተኞች ያረፉበት ሆቴል እየተከተሉ አልጋ በመያዝ ስርቆት ሲፈጸሙ ነበር " - የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ

የሲዳማ ክልል ጸጥታ ኃይል " ስፈልጋቸው የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ይዛለሁ " አለ።

በቁጥጥር ስር የዋለቱ ተጠርጣሪዎች ስፖርተኞች ያረፉበት ሆቴል እየተከተሉ #አልጋ_በመያዝ ስርቆት ሲፈጹም የነበሩ እንደሆነ የጸጥታ ኃይሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ገልጿል።

ካሁን በፊት በተመሳሳይ አይነት መንገድ ስርቆት ፈጽመዉ ሀዋሳ ከተማን በመልቀቃቸዉ ሳይያዙ ቢቆዩም ከሰሞኑ ከተማውን ሲረግጡ ጀምሮ በተደረገ ክትትል መያዛቸዉን የክልሉ ጸጥታ ቢሮ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ " ከገንዘብ አንስቶ ስማርት ስልኮች ከባጃጅ እስከ መኪኖች ድረስ ተደራጅተዉ የሚዘርፉና ከሀገር ውጭ ዶላር ተመድቦላቸው የዘረፋ ተግባር የሚፈጽሙ መሆናቸውን " የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ሀሚድ አህመድ  ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ዳይሬክተሩ ፤ በከተማው የተተከሉ ካሜራዎችና የተሰማሩ የጸጥታ አካላት ሲከታተሏቸዉ ቆይተዉ እንደተለመደው ስፖርተኞች ያረፉበት ሆቴል በማረፍ የዘረፋ ተግባራቸውን ለመፈፀም ሲሞክሩ እጅ ከፈንጅ መያዛቸዉን አስረድተዋል።

ግለሰቦቹ እንዲህ ያለዉን ተግባር ለመፈጸም እንዲችሉ ከሁለት መቶ በላይ ማስር ቁልፎችን እንዲሁም ሲያዙ ህገወጥ የውጭ ሀገር ገንዘቦች እና በርካታ ስልኮች እንዲሁም የባንክ ቼኮች መያዛቸዉን ገልጸዋል።

አሁን ላይ ጉዳያቸው በህግ ተይዞ ምርመራ እየተደረገ ሲሆን ወደፊት የወንጀል ምርመራው እና የፍርድ ሂደቱንም ሆነ የተጠርጣሪዎችን ሰንሰለት በተመለከተ ዝርዝር መረጃ የሚሰጥ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
" የስምምነት ሃሳቡ ተቀባይነት ካገኘ #ኢትዮጵያ የተረጋጋ እና ተገማች የባህር ሀብት ተደራሽነት ይሰጣታል " - ኮሪር ሲንግኦኢ

ኬንያ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ቀጠናዊ የባህር ላይ ስምምነት ሃሳብ ማቅረቧን ሮይተርስ ዘግቧል።

ኬንያ የስምምነት ሃሳቡን ያቀረበችው ፤ ከጅቡቲ እና ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት ኢጋድ ጋር በመመካከር ነው።

ይህ ስምምነት ወደብ የሌላቸው ሀገራት በንግድ እንዴት ወደብ መጠቀም እንደሚችሉ የሚገዛ መሆኑን የኬንያ የውጭ ጉዳይ ዋና ጸሃፊ ኮሪር ሲንግኦኢ ተናግረዋል።

ኢጋድ የባህር ሃብትን ለመጋራት የሚያስችል ስምምነት መፍጠር እንደሚችልም ገልጸዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ትላንት ከኬንያ አቻቸው ዊሊያም ሩቶ ጋር በኬንያ ዋና ከተማ ለውዝግቡ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ላይ መወያየታቸው ተሰምቷል።

በውይይቱ መጨረሻም " ቀጠናው የተረጋጋ እንዲሆን ለማድረግ ከሁሉም አካላት ጋር መገናኘታችንን እንቀጥላለን " ሲሉ ሲንግኦይ ተናግረዋል።

የናይሮቢ መፍትሄ ተቀባይነት ካገኘ ኢትዮጵያ የተረጋጋ እና ተገማች የባህር ሀብት ተደራሽነን ስለሚሰጥ የንግድ ስራዋን ያለምንም እንቅፋት እንድትፈጽም እንደሚያደርግ እና የሶማሊያን የግዛት አንድነት እንደሚያከብርም አክለዋል።

ኮሪር ሲንግኦኢ ፥ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ሃሳቡን እያጤኑበት ነው ያሉ ሲሆን " መሪዎቻቸው ሂደቱን ወደፊት ለማራመድ ተገናኝተው እንዲመክሩበት ተጠይቀዋል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የሮይተርስ / ዶቼ ቨለ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋኖ መሪዎችና አባላት መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ፤
- ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣
- አቤኔዜር ጋሻው አባተ
- ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት " ፋኖ " ቡድን አባላት በከተማው " የሽበር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቃሰቀሱ " መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል እንደደረሱባቸው ገልጿል።

ዛሬ " ሚሊኒየም አዳራሽ " አካባቢ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ " እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆን በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ ሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ተኩስ መክፈታቸውን " አመልክቷል።

በዚም ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት አቤነዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል  መገደሉን ገልጿል።

ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የፈኖ አባለቱ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበርም በማለታቸው  እንደገደሏቸው አመልክቷል።

አቶ እንደሻው ሲያሽከርክሯት የነበረቸው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ  80457 በጥይት ጉዳት እንደረሰባት አዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋኖ መሪዎችና አባላት መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ፤ - ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣ - አቤኔዜር ጋሻው አባተ - ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት " ፋኖ " ቡድን አባላት በከተማው " የሽበር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቃሰቀሱ " መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል…
“ በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም ” - አዲስ አበባ ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ በፋኖና በፓሊስ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሲቪልና ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ፣ በሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

የ“ፋኖ” አመራርና አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ ከፀጥታ አካላት ተኩስ እንደከፈቱ፣ በ “ፋኖ” በኩል ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ አንድ በቁጥጥር ስር እንደዋለ፣ በመንግሥት በኩል ሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ በንጹሐን በኩል ደግሞ አንድ አሽከርካራ እንደተገደለ፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል፣ “ የተገደሉት የ “ፋኖ” ቡድን አመራርና አባላት ናቸው። አመራሩ ናሁሰናይ አንዳርጌ ነው። ሌላው አቤኔዘር ጋሻው የተባለው ነው፣ እዛው ቦታው ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሂወቱ አልፏል። ሀብታሙ አንዳርጌ ግን ምንም አልሆነም በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።

የ “ፋኖ” አመራርና አባላት የነበራቸውን እንቅስቃሴ ሲያስረዱም ኮማንደሩ፣ “ በከተማው ውስጥ ነው የሚንቀሳቀሱት የነበረው። በከተማው ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ጥፋቶች ለማጥፋት ነው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበረው ” ነው ያሉት።

አክለውም፣ “ እነርሱን ለመያዝ በተደረገው ሂደት ቦሌ ወረዳ 3 ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የሚባሉ ሁለት የፓሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ከእነርሱ (“ፋኖ”) በተተኮሰ ጥይት ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ እሱም ብቻ አይደለም አንድ አሽከርካሪ እንዲጭናቸው ሲያስገድዱት ‘አልተባበርም’ ስላለ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ሞቷል። የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታውት በጥይት መትተውታል። ሙሉ ለሙሉ ጉዳት ደርሶበታል። ሰውየው ግን ምንም የሆነው ነገር የለም ” ነው ያሉት።

“ ማኀበረሰቡ ከፓሊስና ከፀጥታ አካላት የሚተላለፉ መረጃዎችን በቁም ነገር ማዳመጥ፣ አካባቢውን ማዬት መቻል አለበት። በሰላምና በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም። እነዚህ ሰዎች መካከላችን አሉ። ይሄ አንዱ ማሳያ ነው። ቦሌ መሀል ከተማው ላይ እንግዲህ እየኖሩ ነው የነበረው ” ብለዋል ኮማንደር ማርቆስ።

“ እነዚህ ሰዎች መንፈስ አይደሉም። በተሽከርካሪያቸው ሲወጡ ሲገቡ ይታያሉ። ግን ፓሊስ በራሱ ነው ሲከታተተል የነበረው ” ያሉት ኮማንደር ማርቆስ፤ አሁንም ማህበረሰቡ አካባቢውን መጠበቅ አለበት ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
ባህር ማዶ ከሚኖር ወዳጅ ዘመድ በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎትን ገንዘብ በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሃዋላ በኩል እስከ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ሲቀበሉ 20% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፤ የዕድል ጨዋታ በመጫወት የአየር ሰዓት ይሸለማሉ!

ለተጨማሪ መረጃ ማስፈንጠሪያውን bit.ly/3ArwoEO ይጫኑ

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
የኤርትራ መንግሥት 46 እስረኞችን ለቀቀ።

በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።

የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።

በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።

እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።

በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።

የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

" ... የተኩስ ልውውጡ የነበረው ከሚሊኒየም አዳራች በሰንሻይን በኩል ወደ ቦሌ መድኃኒዓለም በሚያስወጣው መንገድ ነበር " - የአካባቢው ነዋሪዎች

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቦሌ በፖሊስ እና ፋኖ አባላት መካከል የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች አድርጎ ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ወደ ሚያስወጣው መንገድ ላይ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ገልጸዋል።

በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት እና አንድ መንገደኛ ህይወታቸው ጠፍቷል። ሁለት የፖሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፥ " ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ ወቅት እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው " ብለዋል።

" ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።

ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃላቸው ፥ ቦሌ በነበረው የፋኖ አባላቱና እና የፖሊስ ተኩስ ልውውጥ ፦
- ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ #ሞቷል
- አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፤
- ሀብታሙ አንዳርጌ የተባለ የፋኖ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር ውሏል።

ከዚህ ባለፈ ፦
° አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ባለመኪና ‘#አልተባበርም’ ስላሉ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ገድለውታል።
° የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታወት በጥይት መተውታል " ሲሉ ተናግረዋል።

በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ በኩል ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

@tikvahethiopia