TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ጵጥሮስ " አቋቁመናል ካሉት ውስጥ ሶስቱ #መታሰራቸውን የእንቅስቃሴው አስተባባሪ ነኝ ያሉ ዲያቆን አክሊሉ ዓለሙ የተባሉ ግስለሰብ ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

ሶስቱ አባቶች የታሰሩት " መንበረ ጴጥሮስ " አቋቁመናል የሚል መግለጫ ከሰጡ በኃላ ሸገር ከተማ አስተዳደር በሚገኘው ቢሯቸው እንደሆነ እኚሁ አስተባባሪ ተናግረዋል።

የታሰሩት ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማዕረጋቸውን ገፍፌዋለሁ ያለቻቸው አባ ገብረማርያም ነጋሳ፣ አባ ወልደ ኢያሱስ ኢፋ እንዲሁም አባ ወልደኢየሱስ ተስፋዬ እንደሆኑ ለመረዳት ተችሏል።

ሌሎችም አብረው የነበሩ ግለሰቦች መያዛቸውም ተነግሯል።

የሸገር ከተማ አስታዳደር ፖሊስ ስለጉዳዩ ምንም ያለው ነገር የለውም።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትላንት ተቋቁሟል የተባለውን " መንበረ ጴጥሮስ " አውግዛ ፤ አሁን በሕገወጥ ድርጊታቸው የቀጠሉትን ቡድኖች በፍርድ እንደምትጠይቅ አሳውቃለች።

በኦሮሚያ ክልል ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት በእነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የተመራ የ26 የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ተሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል።

ይህንን ሹመት ተከትሎም ቤተክርስቲያኗ በከፍተኛ ሁኔታ ያወገዘችና ግለሰቦቹንም የለየች ሲሆን ህገወጥ ባለችው ሹመት ላይ የተሳተፉ አካላትም ላይ እገዳ እና ማዕረጋቸውን የማንሳት ውሳኔ አሳልፋ ነበር።

እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በወቅቱ ቤተክርስቲያን " ህገወጥ ነው ! " ላለችው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ያደረሳቸው ፤ " ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረው 85% ከአንድ ወገን በመሆኑ፣ ያለው የውስጥ አሰራር ችግር፣ አባቶችን ከየአካባቢው ከማፍራት ይልቅ ከአንድ ወገን ብቻ የመሾም ችግር ፣  የሚመደቡት አባቶች የህዝቡን ባህል እና ቋንቋ ባለማወቃቸው ለምእመናን እምነት መዳከም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ መሆኑ ... " የሚሉና ሌሎች ምክንያቶች እንደነበሩ ይታወሳል።

ረጅም ጊዜ ከፈጀ አለመግባባት በኃላ በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች፣ ምክክር እና መግባባት፣ መንግሥትም ገብቶበት በቤተክርስቲያን በቀረበ ጥሪ እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን ጨምሮ ሎሎችም ብፁዓን አባቶች ወደ ቤተክርስቲያን ተመልሰው አሁን ላይ በስራ ላይ ይገኛሉ።

ከተወገዙት እና ከተለዩት ውስጥ ግን 4 አባቶች ጥሪውን ተቀብለው ያልመጡ ሲሆን አሁን 2015 ዓ/ም የተቋቋመ ነው ባሉት " የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ " መንበር መሰየም በማስፈለጉ " የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መንበረ ጴጥሮስ " አቋቁመናል ሲሉ በይፋዊ መግለጫ አሳውቀዋል።

ይህንን መግለጫ በሸገር ከተማ ከሰጡ በኃላ #መታሰራቸውን የእንቅስቃሴው አስተባባሪ ነኝ ያሉ ግለሰብ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
Tecno Spark 20 pro+ ! 

በአይነቱ ለየት ያለው አዲሱ ‘spark 20 pro+’ ስልክ ምርጫዎ ሲያደርጉ 256 ጂቢ ሚሞሪ ከ 16ጂቢ ኤክቴንድድ ራም ጋር በማጣመር፣ የፈለጉትን መተግበሪያ ወይም አፕ መጫን የሚያስችል ሲሆን (G99 ultimate processor) የተገጠመለት በመሆኑ የመረጡትን ጌም ሳይሳቀቁ መጫወት ያስችሎታል።

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Spark20pro+ #TecnoMobile #TecnoEthiopia
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy,
@CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com

Online Live class - Cisco CCNA Professional Networking Course Training & Certification Preparation.

Registration Date: Jan 12 to Feb.09, 2024
Class start date: Feb. 10, 2024.

Course Recognitions: CCNA trainees will receive 3 Certificate of Completion, 3 Letter of Merit, 3 Digital Badge that recognized and accepted in USA, Canada, and Europe, and you will award 58% CCNA certification exam discount voucher.

Mobile #: 0902-340070/0935-602563/ 0945-039478/
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
#ቅሬታ #ምላሽ

“ ... ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኞች ተብለው የወጡት ተመዝጋቢዎች አብዛኛዎቹ የባለ 2 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች ናቸው ” - የኪ ሃውሲንግ የቤት ዕጣ ቆጠቢ

“ ... ጥቂት ቁጥሮች ባለ 2 ብለን እኛ ሲስተም ላይ ጽፈናቸው ‘አይ እኔ የተመዘገብኩት ባለ 3 ነው’ ሊሉ ይችላሉ” - አቶ ቸርነት መንግስቱ (ከድርጅቱ)

ከሰሞኑን " Key Housing Finance Solution " የተሰኘ ተቋም የቤት ባለቤት ለመሆን ሲቆጥቡ ለነበሩ ሰዎች ዕጣ አውጥቶ ነበር።

ከተለያዩ ሴክተሮች በሚገኙ ልምድ ባላቸው አካላት ተዋቅሯል የተባለው " Key Housing Finance Solution " ከ15,000 በላይ ለሆኑ የቤት ቆጣቢ ተመዝጋቢዎች መካከል ለ60 ቆጣቢዎች / የቤት ዕድለኞች የመጀመሪያ ዙር ዕጣ አውጥቶላቸዋል።

ድርጅቱ በ77,280 ብር ቅድመ ቁጠባ ሰዎች የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ሞዴል ፕሮጀክት እንዳለው በገለጸው እና በተለያዩ መንገዶች ባስተዋወቀው መሰረት ነው ከ15,000 በላይ ቤት ፈላጊ ቆጣቢዎች ውስጥ #ለ60_ቆጣቢዎች / #ባለዕድለኞች ዕጣ ያወጣላቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ “Key housing Finanance Solution” የቤት ዕጣ ቆጣቢ፣ “ኪ ሃውሲንግን በተመለከተ እጣ አወጣጡ ላይ ስህተቶች የተሰሩ በመሆኑ ማብራሪያና እርማት ብንጠይቅም በሶሻል ሚድያም ሆነ በሌላ ምላሽ ልናገኝ አልቻልንም” የሚል ቅሬታ ደርሶታል።

ከተመዝጋቢዎቹ መካከል አንዷ በሰጡን ቃል፣ “ ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኛ ተብለው የወጡት ተመዝጋቢዎች አብዛኛዎቹ ባለ 2 ተመዝጋቢዎች ናቸው ” ብለዋል።

አክለውም ፣ “ ለዚሁም ብለን ' አትላስ ' በሚገኘው ዋና ቢሯቸው ማብራሪያ ለማግኘት ከአንዴም ሁለቴ ብንሄድም #በsystem ምክንያት ዕጣ አወጣጡ ላይ ችግር ያለበት መሆኑን ከማመን የዘለለ በቂ ምላሽ አልሰጡንም ” ሲሉ ድርጅቱን ወቅሰዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የቀረቡ ቅሬታዎች በዝርዝር ምን ይላሉ ?

- ዕጣው የደረሳቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ ካደረጉ በኋላ ቼክ በምናደርግበት ጊዜ ልዩነት አለው። 

- ልዩነት የተፈጠረው ባለ 3 ፣ ባለ 2 እና ባለ 1 መኝታ ቤት ነው ያዘጋጁት። ዕጣው ከመውጣቱ በፊት ካለው ዝርዝር ጋር ስናስተያየው ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኛ ተብለው የወጡት ተመዝጋቢዎች አብኞቹ ባለ 2 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች ናቸው።

- ከተመዝጋቢዎች ብዛት አንፃር #ባለ_3_መኝታ_ቤት ለ30 ሰዎች (50%)፣ ባለ 2 መኝታ ቤት ለ21 ሰዎች (35%)፣ ባለ 1 መኝታ ቤት ለዘጠኝ ሰዎች (15%) እንደሚወጣ ነበር ዕጣውን ከማውጣታቸው በፊት ሲገልጹ የነበረው።

- ባለ 3 መኝታ #ለ30_ሰዎች ብለው ካሰቡት ውስጥ ለ21 ሰዎች ነው የወጣው። የባለ 2 ደግሞ ለ21 ሰዎች ብለው ከገለጹት ለ29 ሰዎች ነው የወጣው። ባለ 1 መኝታ ቤት ደግሞ ለ9 ሰዎች ብለው ካሰቡት ለ10 ሰዎች ነው የወጣው። ይህ ማለት ይፋ ካደረጉት ፐርሰንቴጂ ጋር ግልፅ የሆነ ልዩነት አለው።

- በተጨማሪም ፤ ዕጣው ከመውጣቱ በፊት የታቀደው ፕላን በፐርሰት 50 በመቶ ባለ 3 መኝታ ቤት ፣ 35 በመቶ ባለ 2 መኝታ ቤት እንዲሁም ፣ 15 በመቶ ለባለ 1 መኝታ ቤት ብለው ነበር ያስቀመጡት። አክቹአል ሲወጣ ግን ወደ 35፣ 48፣ እና 17 ፐርሰቶች ተቀያይሯል።

- ከ15,000 በላይ ተመዝጋቢዎች 60 እደለኞች ብቻ መመረጣቸው ሳያንስ ይኸውም የ60 ሰዎች ዕጣ አወጣጥ ትክክል ያልሆነና ተዓማኒነት የጎደለው ነው።

- ሌላ ያስተዋልው የተመዝጋቢዎች ስም ዝርዝር ተብሎ የተመዘገበው ላይ እስከ አያት ድረስ በተመሳሳይ ደብል የሆኑ ስሞች አሉ” የሚሉ ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፤ የተነሳውን #ቅሬታ በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ የብሉዞን ማርኬቲንግ ማናጀርና የኪ ሃውሲነሰግ ቦርድ ሜምበር አቶ ቸርነት መንግስቴን አነጋግሯቸዋል።

እሳቸው ምን አሉ ?

ወደ ሲስተም ሲሞላ የታይኘ ኢረር ይኖረዋል። ባለ 2 የተመዘገበን ሰው ባለ 1 ብለህ ልትጽፍ ትችላለህ፣ ባለ 1 የተመዘገበን ባለ 3 ትላለህ። 

ይኼ ከሆነ ምናልባት ደንበኛው ራሱ ደግሞ ዕጣ ውስጥ ' መካተት ፤ አለመካተቱን ' እንዲያረጋግጥ ፣ እንዲህ አይነት የታይፕ ስህተቶች ተፈጥረው ከሆነ ታይቶ እንዲነገረን ፖስት አድርገንላቸዋል። 

በቴሌግራም ላይ ፖስት ካደረግን በኋላ ጥቂት ቁጥሮች ባለ 2 ብለን እኛ ሲስተም ላይ ፅፈናቸው ‘አይ እኔ የተመዘገብኩት ባለ 3 ነው’ ሊሉ ይችላሉ። እሱን ከውሉ ጋር ወዲያው ከሀርድ ኮፒው እናመሳክራለን። ሲስተሙ ላይ ይስተካከልላቸዋል። ምክንያቱም አዲስ ሲስተም ነው። መሞከሪያም ነው መስተካከል አለበት።

ፓስት ያደረግነው ቁጥር ሁሉም ማለት አይደለም የተወሰኑ ሰዎች ‘እንዲህ አስተካክሉልን’ ብለውናል። አስተካክለንላቸዋል። ‘አስተካክሉልን’ ያሉን ሰዎች ከተስተካከለላቸው በኋላ በቀጥታ ሰነዱን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው ያስረክብነው የተስተካከለውን። 

ቴሌግራም ላይ ፖስት የተደረገው ያልተስተካከለው የመጀመሪያው (አስተያዬት ለመሰብሰብ ፓስት የተደረገው) ነው። ዕጣ ከወጣ በኋላ ሰዎች ሂደው ሲያመሳክሩ ያን ያዩታል። ግን እነዛ ሰዎች እዚጋ እንዲስተካከልላቸው ሆኗል። ራሳቸው ባቀረቡት መሠረት ማለት ነው።

እንዲህ ካደረጋችሁ ፥ በተመዝጋቢዎች በኩል ብዥታ እንዳይፈጠር ለምን የተስተካከለውን በድጋሚ ፖስት አላደረጋችሁላቸውም ? ብሎ ቲክቫህ ጠይቋቸዋል።

ምላሻቸውም ፤ " ካለፈ በኋላ ፓስት ማድረግ እንችል ነበረ " ብለዋል።

ዕጣው ከመውጣቱ በፊት #የተስተካከለውን ሰነድ ፓስት ያላደረጉበትን ምክንያት ሲያስረዱ ፤ " የተጣራው ለአዲስ አበባ የምንሰጠው ሰነድ ነው። የአዲስ አበባን ዩኒቨርሲቲ Soft ware ከሰራበት በኋላ ነው እንጂ ኦዲት የምናደርገው ቀድመን ምን ይደረግ የሚለውን አናውቅም። ዜሮ፣ ዜሮ መሆኑን ብቻ ነው የምናየው " ሲሉ ተናግርዋል።

በተጨማሪ ...

ባለ 3 መኝታ ቤት ዕድለኛ ተብለው ዕጣ የወጣላቸው ተመዝጋቢዎች አብዛኛዎቹ ባለ 2 ተመዝጋቢዎች ናቸው ፤ ተብሎ ለቀረበው ቅሬታ ፦

° " ይህ #እውነት_አይደለም። ምክንያቱም ባለ 2 ተመዝግበው ባለ 3 እንዴት ይደርሳቸዋል ? የደረሰውስ እንዴት ይቀበላል ? የማይሆን ነገር ነው " ሲሉ መልሰዋል።

ዕጣ ከማውጣቱ በፊት ለባለ 3 ፣ ለባለ 2 እንዲሁም ለባለ 1 የቤት ዕድለኞች ያቀዱት ፐርሰንቴጂ ዕጣው ከወጣ በኋላ ተቀያይሯል ተብሎ ለተነሳው ቅሬታ ፦

° “ ቤቱን ገና አላስተላለፍንላቸውም። ገና በ18 ነው ቤቱን የሚረከቡት።

የሚረከቡትም በተባለው መሠረት ባለ 1 መኝታ ቤት ዘጠኝ ሰዎች፣ ባለ 2 መኝታ ቤት 21 ሰዎች፣ ባለ 3 መኝታ ቤት 30 ሰዎች ናቸው። ባልተዘጋጁ ቤቶች ዕጣ አናወጣም። ከየትስ እናመጣዋለን " ከሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ድርጅቱ ማብራሪያ ሊሰጥ ፈቃደኛ አልሆነም ተብሎ ለተነሳው ቅሬታ ፦

° “ ተወካይ ነን ብለው ለመጡ አባላቶች (የምር ተወካይ አይደሉም፤ የተወካይ ህጋዊ ሰነድ የላቸውም) ፤ ግን ነገሩ መልካም ስለሆነ ቢሮ ለእያንዳዱ ሰነድ ጭምር እያሳዬን ማብራሪያ ሰጥተናል ” ሲሉ መልሰዋል።

በተመሳሳይ ስም የተጠቀሱ " ዳብል " ተመዝጋቢዎች መኖራቸው ተከትሎ ለቀረበው ቅሬታ ፦

° " ... እንድ ተመዝጋቢ #ለብዙ_ሰዎች መመዝገብ ይችላል፣ ኮዱም ቢሆን ተመሳሳይ ሊሆን ይችላል " ሲሉ መልሰዋል።

በአዲስ አበባ ቲክቫህ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ ትግራይ ክልል ውስጥ በ5 መጠለያ ጣቢያዎች ከ900 በላይ ሰዎች ከምግብ እጦት እና ከመድሃኒት እጥረት ጋር በተያየዝ ሞተዋል ሲል የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አሳውቋል። የተቋሙ የመቐለ ቅርንጫፍ ፤ ረሃብ የሰው ህይወት መንጠቅ ከጀመረ ወራቶች መቆጠሩንም ገልጿል። * በሽረ * አክሱም * በአብይአዲ * በመቐለ * ዓዲግራት ባሉ መጠለያ ጣቢያዎች የሰው ህይወት በረሃብ እና በመድሃኒት እጥረት…
#FederalGovernment

የፌዴራል መንግሥት ከተለየዩ አካላት ጋር በመተባበር አስቸኳይ ሰብአዊ እርዳታ ለሚያስፈለጋቸው 3.8 ሚሊዮን ወገኖች እርዳታ ማድረሱን አሳውቋል።

ለሰብዓዊ እርዳታ በሦስት ተከታታይ ዙሮች 15 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አመልክቷል።

ከዚህ ውስጥ 40 በመቶውን የፌዴራል መንግሥት፣ 60 በመቶውን ደግሞ የዓለም ባንክ እንደሸፈነው ገልጿል።

በቀጣይ በድርቅ እና በተለያዩ ምክንያቶች ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ከ9 ሚሊዮን በላይ ሚሊዮን ወገኖች ተለይተው እርዳታውን ከጥር እስከ የካቲት ለማድረስ እየተሰራ ነው ብሏል።

ለዚህም 9.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ገልጿል።

" አስቸኳይ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ያልተቋረጠ ሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ እየሰራሁ ነው " ያለው ፌዴራል መንግሥት፤ " የክልል መንግሥታትም የሚጠበቅባቸውን ድርሻ እንዲወጡ " ብሏል።

ለተቸገሮች ወገኖች ለመድረስ የእርዳታ ድርጅቶችን ጨምሮ ሁሉም ወገኖች የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ መቅረቡን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

@tikvahethiopia
በመኪና የታገዘ ዝርፊያ . . .

እኚህ በፎቶው የምትመለከቷቸው ግለሰቦች፦
1. ናትናኤል አለሙ
2. አብደላ ሰኢድ
3. ቢያንያም መዝገበ አዲስ አበባ፣ ካዛንችስ ጠማማ ፎቅ አካባቢ ጉብኝት ሲያደርጉ ከነበሩ የውጭ ሀገር ሰዎች አይፎን ስልክ ቀምተው በመኪና (ከላይ በፎቶው በምትታየው ላዳ) ለማምለጥ ሲሞክሩ በአዲስ አበባ ፖሊስ እና በህብረተሰቡ ርብርብ እጅግ ከፍንጅ የተያዙ ናቸው።

አንደኛው ስልክ ቀሚ ፣ ሁለተኛው የተሽከርካሪውን በር ከፍቶ ሲጠባበቅ የነበረ ፣ ሶስተኛው ደግሞ ሹፌር ልክ ግብረአበሮቹ ወደመኪናው እንደገቡ በፍጥነት ለማምለጥ ጥረት ያደረገ ነው።

እንዲህ አይነት ተመሳሳይ የሆነ በመኪና የታገዘ የወንጀል ተግባር ከወራት በፊት " ቦሌ ሩዋንዳ " ጋር ተፈፅሞ እንደነበር አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

በወቅቱ ድርጊቱ የተፈፀመው ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ነበር " በቶዮታ ወያኔ ዲኤክስ " መኪና የነበሩ በቁጥር 4-5 የሚሆኑ ዘራፊዎች አንድ ሰው መንገድ ላይ አስቁመው በስለት እና በመሳሪያ አስፈራርተው ስልክ እና ገንዘብ ዘርፈው በፍጥነት መኪናውን እያሽከረከሩ ተሰውረዋል።

ከዛ በኃላ ዘራፊዎቹ ይያዙ አይያዙ የሚታወቅ ነገር የለም። የግል ተበዳይ ንብረትም አልተገኘም።

በፊት በፊት ዝርፊያ ሲፈፀም የሚሰማው በእግር ፣ ጨለማን ተገን በማድረግ ነበር አሁን አሁን ላይ ታርጋ ጭምር የለጠፈ መኪና በመጠቀም በእግሩ የሚሄድን ሰው በስለት በማስፈራራት፣ አንዳንዴም ሊፍት እንስጣችሁ በሚል ሆኗል።

እናተስ መሰል ነገር አጋጥሟቹ ይሆን ? ወይስ ያጋጠመው ሰው ታውቁ ይሆን ? ዝርፊያ ሲፈፀምባቸው የነበሩ መኪኖችን ትለይዋቸው ይሆን ? በ @tikvahethmagazine ላይ አጋሩን !

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DStv

📣 ሰምተዋል?

በማንኪያ ሲሉ በጭልፋ ፤ በጭልፋ ሲሉ በአካፋ!

👉 ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ድረስ ከሚጠቀሙት ፓኬጅ ከፍ ካሉ በእኛ ወጪ ወደ ቀጣዩ ትልቅ ፓኬጅ ለአንድ ወር ከፍ ይላሉ!

ይህ አገልግሎት ክፍያ ከፈፀሙ ከ48 ሰዓት በኋላ ተግባራዊ ይሆናል።

*ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን 

የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!

👇👇👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #StepUp
ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ!
=====================
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ስምና አርማ በመጠቀም በሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የሌብነት ተግባር የሚፈፅሙ አጭበርባሪዎች አሉ፡፡ 

በመሆኑም የባንኩን ትክክለኛ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች ብቻ በመከተል ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ያግኙ፤ ከአጭበርባሪዎች ይጠበቁ!

የባንኩ ትክክለኛ የማህበራዊ  ትስስር ገፆች፡
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• YouTube፡- https://www.youtube.com/commercialbankofethiopia
• LinkedIn፡- https://www.linkedin.com/company/commercialbankofethiopia
• Twitter፡- https://twitter.com/combankethiopia
• Telegram፡- https://t.me/combankethofficial
• Instagram፡- https://www.instagram.com/commercialbankofethiopia/
• tiktok:- https://www.tiktok.com/@combankethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ ፦ ከላይ የሚታዩት ተጠርጣሪዎች ተሽከርካሪ በመጠቀም እየተንቀሳቀሱ የማታለል ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ግለሰቦች እንደሆኑና አሁን ላይ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
                         
እንደ ፖሊስ መረጃ ፤ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች የሰሌዳ ቁጥር ኮድ " 3-B48631 አ.አ " በሆነ ተሽከርካሪ ወንጀል ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው።

ግለሰቦቹ  በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው 6 ኪሎ ዩኒቪርሲቲ አንደኛ በር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በፈፀሙት ወንጀል ነው የተያዙት።

ተጠርጣሪዎቹ ባንኮች ላይ ትኩረት አድርገው ሲንቀሳቀሱ የነበር ሲሆን ፤ በዚሁ አካባቢ በሚገኝ አንድ የባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ አንዱ ተጠርጣሪ ስራ አስኪያጁን የNGO አካውንት ለመክፈት እንደፈለገ ይነግረዋል።

ስራ አስኪያጁም አስፈላጊ መስፍቶችን ይነግረዋል ፤ በኃላም ፎቶና ሌሎች መስፈርቶችን አሟልቶ እመለሳለሁ ይላል። ቀጠል አድርጎ ድርጅታቸው በቅናሽ የሚሸጣቸው 53 ኢንች ሁለት ቴሌቪዥኖች ስላሉ የሚገዙ ከሆነ ይውሰዱ ሲል ይናግረዋል።

ስራ አስኪያጁ ቴሌቪዥን መግዛት እንደሚፈልግ ፤ እጁ ላይ ግን ያለው 3 ሺህ ብር እንደሆነና 12 ሺህ ተበድሮ 15 ሺህ ብር መስጠት እንደሚችል ይገልጻል። በዚህ ወቅት ተጠርጣሪው ችግር የለም ሌላ ጊዜ ቀሪውን ገንዘብ ወስዳለሁ ይላል።

ስራ አስኪያጁም ብሩን ሰጥቶ ቴሌቪዥኑን ለመረከብ አንድ የራሱን ሰው አብሮ ይልካል። ልክ ከባንክ እንወደጡ ከላይ ያለችው መኪና (የግብረአበሩ) ውስጥ ይገባሉ። ጥቂት ተጉዘው 6 ኪሎ ሲደርሱ ተጠርጣሪው ብሩን የያዘውን ሰው ብሩን ስጠኝ ብሎ ይቀበላል።

ሹፌሩ (ግብረአበር) መኪናውን ሲያቀዘቅዝ በሩን ከፍቶ ቴሌቪዥንኑን ሊያመጣ የተላከውን ሰው ወርውሮ ይጥለውና በፍጥነት ይነዱታል።

በወቅቱ በተሽከርካሪ በመንቀሳቀስ የወንጀል መከላከል ስራ ሲሰሩ የነበሩ የፖሊስ አባላት በደረሳቸው ጥቆማ ወንጀሉን ፈፅሟል የተባለውን ግለሰብ ከነ ግብራበሩ እና ሲጠቀሙበት ከነበረው መኪና ጋር ተከታትለው በቁጥጥር ስር አውለዋቸዋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
“ 12 የኦሮሚያ ሚሊሻዎች ተገድለዋል ” - የትፋቴ ቀበሌ ሊቀመንበር

“ እውነት ነው። እኔ እንደ ባለሙያ ሁለት ሰዎች የተመቱ አይቻለሁ ” - የዓይን እማኝ የጤና ባለሙያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ በትፋቴ ቀበሌ መንግሦት “ሸኔ” ብሎ የሚጠራቸው  ታጣቂዎች በድንገት አደረሱት በተባለ ጥቃት 12 የኦሮሚያ ክልል ሚሊሻዎች መገደላቸውን የዞኑ ሆስፒታል ባለስልጣንና የሆስፒታሉ ጤና ባለሙያ፣ የትፋቴ ቀበሌ ሊቀመንበርና የዓይን እማኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

የዓይን እማኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹት፣ 9ኙ ሚሊሻዎች እሬሳቸው ሆስፒታል አድሮ መሸኘቱን፣ 3ቱ ደግሞ በምዕራብ ጉጂ ዞን በጋላና አባያ ወረዳ ኤርጋንሳ ወይም ፃልቄ ቀበሌ መመለሳቸውን ነው።

ሚሊሻዎች ተገደሉ የሚባል መረጃ ደርሶናል እውነት ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምለሽ በኮሬ ዞን የትፋቴ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ መሐመድ ኪታሞ በሰጡት ቃል፣ “እውነት ነው ሚሊሻዎች ተገድለዋል” ብለዋል።

“ፃልቄ የሚባል አካባቢ (በገዳና ፃልቄ መካከል) ላይ 12 የኦሮሚያ ሚሊሻዎች ተገድለዋል” ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ድርጊቱ የተፈጠረው “ሰኞ ዕለት (ጥር 13 ቀን 2016 ዓ/ም) ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው ፤ “ሌሎች ታካሚዎችም አሉ። እኔ ከእነርሱ ጋር አይደለም የቆጠርኩት። የሞቱ ብቻ 12 ናቸው” ብለዋል።

ጥቃቱን ያደረሱት የ “ሸኔ” ታጣቂዎች ናቸው እንዴ ? ተብለው ሲጠየቁም፣ “አዎ የኦሮሚያ ሚሊሻዎች ከሸኔ ጋ ተገናኝተው” ብለዋል።

ስለ ጉዳዩ #ማረጋገጫ እንዲሰጡን ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የኬሌ ከተማ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ በለጠ በበኩላቸው ፤ “ እኛ ጋ በእርግጥ የህክምና አገልግሎት ለመቀበል የመጡ 2 በጥይት የተመቱ ነበሩ። ከዚያ ወጪ ዘጠኝ እሬሳ እንደመጣና በዚሁ እንዳለፈ ነው የምናውቀው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ መረጃው የደረሰኝ ሁለቱ ተወግተው መጥተው አገልገሎት አግኝተው እንደሄዱና ዘጠኙ እሬሳ ግቢ ገብቶ (ለማሳደር ከምሽቱ 3 በኋላ ነው ያመጧቸው” ያሉት ሥራ አስኪያጁ፣ “አሁን ያሉበትን ደረጃ ባናውቅም ሁለቱ ታክመው ነው የሄዱት” ሲሉ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ ስለ ጉዳዩ ጥያቄ ያቀረበላቸው የሆስፒታሉ የጤና ባለሙያ አቶ ገዛኸኝ እንደሻ በበኩላቸው፣ “እውነት ነው። እኔ እንደ ባለሙያ ሁለት ሰዎች የተመቱ አይቻለሁ። ታክመው ለተጨማሪ ህክምና ሂደዋል ጠዋት። የእነርሱ አመራርሮችም (የታካሚዎቹ) መጥተው ነበር” ብለዋል።

አክለውም፣ “የእኛ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ነው። የእነርሱ ደግሞ ኦሮሚያ ክልል ስለሆነ በአቅራቢያ በሚገኘው ዞን መጥተው ነበር ወደ እኛ፣ ሲታከሙ አድረው ሂደዋል። የተመቱት የኦሮሚያ ጉጂ ዞን ሚሊሻዎች ናቸው” ሲሉ አስረድተዋል።

ዘገባውን አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ዘንድሮ በመላ ሀገሪቱ የ " ኬጂ " ተማሪዎች እንግሊዝኛ ቋንቋ እየተማሩ አይደለም።

የመዋዕለ ህጻናት ተማሪዎች " ኤ፣ ቢ፣ ሲ፣ ዲ… " ን በዜማ መቁጠር፣ " ኤ ፎር አፕል፣ ቢ ፎር ቦል… " እያሉ ቃላት መመሥረትም አቁመዋል።

ከዚህ ዓመት ጀምሮ " ስፖክን ኢንግሊሽ " እና " ኢንግሊሽ ሊትሬቸር " ከ " ኬጂ " ተማሪዎች የትምህርት ዓይነቶች ውስጥ ተሰርዘዋል።

እንደ ቀድሞው በአማርኛ ሂሳብ፤ በእንግሊዝኛ " ማትስ " እያሉ የቁጥሮችን አጠራር በሁለት ቋንቋ መሸምደድም ቀርቷል።

የዘንድሮ የ " ኬጂ " ተማሪዎች ለአካባቢ ሳይንስ እና ለ " ጄኔራል ሳይንስ " ሁለት ደብተር አይዙም።

በአራት ዓመታቸው " ነርሰሪ " የሚገቡት ህጻናት፣ በ6 ዓመታቸው ከ " ዩ ኬጂ " ሲመረቁ የሚያውቁት ብቸኛ የፊደል ገበታ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውን እንዲሆን ተደርጓል።

ልጆችን እንግሊዝኛ በማስተማር ተመራጭ የሆኑት የግል መዋለ ህጻናት ከዚህ ዓመት ጀምሮ ሁሉንም ትምህርት የሚሰጡት በአካባቢው የአፍ መፍቻ ቋንቋ ብቻ ነው።

በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር አሠራር መሠረት ተማሪዎች እንግሊዝኛ ቋንቋን እንደ አንድ ትምህርት መማር የሚጀምሩት #አንደኛ_ክፍል ሲደርሱ ነው።

ከዚህ ዓመት ጀምሮ መተግበር የጀመረው ሥርዓተ ትምህርት ህጻናት የሚማሩትን ትምህርት በተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች (ሰብጀክት) አይከፋፍልም።

የኬጂ ተማሪዎች እንደ ቀድሞው ሂሳብ፣ አማርኛ ወይም አካባቢ ሳይንስ የሚባሉ የትምህርት ዓይነቶች አይኖሯቸውም። በትምህርት አይነቶች ፋንታ ህጻናቱ የሚማሩት " ጭብጦችን " ነው።

ለምሳሌ፤ የመጀመሪያ ዓመት የመዋለ ህጻናት ተማሪዎች ስድስት ጭብጦችን ይማራሉ። ከእነዚህ ጭብጦች ውስጥ፦
* ስለ እኔ፣ ስለ ቤቴ እና ስለ ቤተሰቦቼ
* ትምህርት ቤቴ እና አካባቢዬ የሚሉት ይገኙበታል።

የኬጂ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ከሚማሯቸው ጭብጦች ውስጥ ደግሞ ፦
* ዋሊያ
* ህዋ
* ተክሎች እና መጓጓዣ ተጠቃሽ ናቸው።

በአዲሱ ካሪኩለም መሠረት ህጻናቱ እንደ ቀድሞው አብዛኛውን ጊዜያቸውን ክፍል ውስጥ ቁጭ ብለው ከሰሌዳ እና ከደብተር ጋር እንዲፋጠጡ አይደረግም።

ዘንድሮ የኬጂ ተማሪዎች የሚማሩባቸው ዋነኛ መንገዶች ጨዋታ፣ መዝሙር እና ተረት ናቸው።

በአዲሱ ካሪኩለም የኬጂ ተማሪዎች እንግሊዝኛ እንዲማሩ አይደርግም። በእንግሊዝኛ ምንም ነገር የለም። ሁሉም ነገር በአፍ መፍቻ ቋንቋ ይሰጣል።

የኬጂ ትምህርት ይዘት መቀነስ ያላስደሰታቸው ወላጆችም ያሉ ሲሆን ተማሪዎች ከአቅማቸው በታች እንዲማሩ እያደረገ ነው ብለዋል።

በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶችም ከወላጆች ቅሬታ እየተቀበሉ መሆኑን የአዲስ አበባ የግል ትምህርት ቤቶች አሠሪዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ አበራ ጣሰው አሳውቀዋል።

የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ካሪኩለሙ በዝግጅት ላይ በነበረበት ወቅት የትምህርት ይዘቱ መቀነሱን እና የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት መውጣቱን በተመለከተ ማኅበሩ ተቃውሞ አስተያየት መስጠቱንም አስታውሰዋል።

የቅድመ አንደኛ ሥርዓተ ትምህርትን ካዘጋጁ ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ታደሰ ጃለታ ፤ " ቤተሰብ ልጁ እንግሊዝኛ ከቻለ፣ ፊደል ከቆጠረ ወይም መደመር ከቻለ ተምሯል፣ አድጓል ብሎ ያስባል። በህጻናት ደረጃ ትምህርት እርሱ አይደለም " ብለዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/BBC-AMAHRIC-01-24

Credit - #BBCAMAHRIC

@tikvahethiopia
#ኤርትራ

ኤርትራ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ቤርቦክን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረን አውሮፕላንን ከአየር ክልሏ ማስወጣቷ ተነግሯል።

የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ባየርቦክ ትላንት እንዳስታወቁት፤ ወደ ጂቡቲ ሲጓዝ የነበረው የጀርመን መንግስት አውሮፕላን ያለ እቅድ ሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዱን ገልጸለዋል።

ይህ የሆነ በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማለፍ ፍቃድ ባለማግኘቱ እንደሆነም አስታውቀዋል።

ሚኒስትሯ በ3 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለ3 ቀናት ጉብኝት ለማድረግ በጉዞ ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ጉብኝታቸውም ጂቡቲ ነበረች።

ሚኒስትሯ ፤ ያለ እቅድ በሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዳቸው በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ያለውን አለመረጋጋት ያመለክታል ብለዋል።

ትላንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው ለማደር የተገደዱት ሚኒስትሯ ዛሬ በጅቡቲ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።

የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ " አውሮፕላኑን በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማብረር ፈቃድ እንዳልተሰጠው ያወቅነው ትናንት ጠዋት ከበረራው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ ነበር " ብሏል።

አውሮፕላኑ #በበረራ_ላይ_እያለ ፈቃዱን ያገኛል ተብሎ በመወሰኑ ወደዚያ መሄዱንም ገልጿል።

ከቤርቦክ ጋር የተጓዙት ልዑካን ፤ አውሮፕላኑ እየበረረ ፈቃድ ማግኘት እንግዳ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

ቤርቦክን ፤ የሱዳን ጦርነት ጉዳይ እና የቀይ ባህር የመርከብ መንገድ ጉዳይ ትኩረት አድርጓል የተባለው የምሥራቅ አፍሪቃ ጉብኝታቸውን ነገ በደቡብ ሱዳን ያጠናቅቃሉ ተብሏል።

#AlAinNews #DW

@tikvahethiopia
" ከሶማሊያ ጋር የመዋጋት ፣ የመጣላት ፍፁም ፍላጎት የለንም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር #የመዋጋትም ሆነ የመጣላት ፍላጎት እንደሌላት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።

ዶ/ር ዐቢይ ይህን ያሉት ለፓርቲያቸው ማዕከላዊ ኮሚቴ ባቀረቡት ገለፃ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " የምንከተለው የዲፕሎማሲ ጉዟችን ክብርንና ጥቅምን ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። " ብለዋል።

" ሶማሊያ ከማንም በላይ የኢትዮጵያ ወንድም ዘመድ ጎረቤት ናት፤ ባለፉት 10 ዓመታት በሺሕ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በሶማሊያ ውስጥ የሶማሊያ ሰላም ለማስከበር የህይወት ዋጋ ከፍለዋል። " ሲሉ ገልጸዋል።

" ማንም ሀገር በዓለም ላይ ኢትዮጵያ የከፈለችውን ያህል የከፈለ የለም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " አግዛለው ብሎ መፎከርና ሄዶ መሞት ይለያያል " ብለዋል።

" ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ህዝብና መንግስት ጋር ለመጣላት ለመዋጋት ፍጹም ፍላጎት የላትም " ሲሉም ተደምጠዋል።

" አሁን በኢትዮጵያ ያለው መንግስት በሶማሊያ አንድነት የሚታማ መንግስት አይደለም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ታሪክ ሶማሊያዊያን አንድ እንዲሆኑ በንግግር ሳይሆን በተግባር የሰራ መንግስት ነው " ብለዋል።

" ከልባችን አንድ እንዲሆኑ ስለምንፈልግ የቀድሞው ፕሬዜዳንት ፈርማጆ ስልጣን ላይ እያሉ ከሱማሌላንድ ፕሬዜዳንት ቢሂ ጋር ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ ለማገናኘት በተደረገ መኩራ እንዲገናኙ አድርገን ውይይት ተደርጓል ፤ ሶማሊያ እና ኬንያ በድንበር ጉዳይ ሲጣሉ አለም ሲንጫጫ ፕሬዜዳንት ፈርማጆን ኬንያ ወስደን ከወንድማቸው ከፕሬዜዳንት ኡሁሩ ጋር እንዲነጋገሩ ጥረት አድርገናል፤ ለምን ? የነሱ ሰላም የኛ ስለሆነ " ሲሉ አስረድተዋል።

" ሶማሊያ እንደ ግጭት ሰፈር አድርጎ የመጠቀም ፍላጎት ከብዙ ኃይሎች ይነሳል፤ እኛ ለዓለም ህዝብ የቀይ ባሕር 'አክሰስ' ጥያቄያችን ህጋዊ መሆኑን አሳይተናል። ዓለም በሙሉ ይገባቸዋልኮ ግን፣ ግን ነው የሚለው ፤ የኛ ፍላጎት ባሕርን አክሰስ ማድረግ ብቻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከኢትዮጵያ መውሰድ ሲሆን ችግር የለውም፤ ለኢትዮጵያ መስጠት ነው ነውሩ ፤ ዲፕሎማሲያችን እንደዚያ ነው፤ አሁን መልኩን እየቀየረ ነው " ብለዋል።

" በእኛ እና ሶማሊያ መካከል ችግር ይፈጠራል ብዬ ባላስብም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " በሕዝቦች መካከል ጥላቻ እንዳይፈጠር ቁርሾ እንዳይፈጠር በተረጋጋና በሰከነ መንገድ ውጫዊ አክተር በሚያሰክን መንገድ መምራት ይጠይቃል " ሲሉ ተናግረዋል። #PP

@tikvahethiopia