TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Photo የጥምቀት በዓል እየተከበረ ይገኛል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዘንድ ፤ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ የጥምቀተ ባህር ስፍራዎች ቀሳውስት እና ሊቃውንት ለምዕመናን ትምሕርት ሰጥተው፣ ጸሎት ተደርጎ እና ጥምቀተ ባሕሩ ተባርኮ ሥርዓተ ጥምቀቱ ተካሂዷል። አሁን ላይ በዛሬው ዕለት የሚገቡ ታቦታትን የማስገባት ስነስርዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን…
ቅዱስ ፓትርያርኩ ምን አሉ ?

ዛሬ በአዲስ አበባ ' ጃንሜዳ ' ባሕረ ጥምቀት በነበረው የጥምቀት በዓል አከባበር ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈው ነበር።

ከቅዱስነታቸው መልዕክት መካከል የሚከተለው ይገኝበታል ፦

" ... እኛን የላከ እግዚአብሔርም ሆነ፣ ከሱ የተላክን እኛ ለሰው ልጆች ሁሉ የምናስተላልፈው መልእክት “ንስሐ ግቡ” የሚለው ነው፡፡

በእውነት ንስሐ ከገባን ጠቡ፣ ግድያው፣ ዘረፋው፣ መለያየቱ ይቆማል ፤ በምትኩ ደግሞ ፍቅር፣ አንድነትና ወንድማማችነት ይሰፍናል፤ መከባበር፣ መተማመን፣ መስማማትና ይቅር ባይነት የበላይነቱን ያገኛል፤ ውጤቱም ሰላምና ዕድገት ይሆናል፤ የእግዚአብሔርን ቃል የምትሰማ ነፍስ ካለች እኛ የምንነግራት ይኼና ይኼ ብቻ ነው።

ከንስሐና ከፍቅር ውጭ በእግዚአብሔር ስም የሚናገር መልእክተኛ ካለ እሱ የእግዚአብሔር መልእክተኛ አይደለም፤  እባካችሁ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች የእግዚአብሔርን ቃል በሰላምና በሰላም ብቻ ለሕዝቡ እናድርስ፤ ሕዝቡም የእግዚአብሔርን ቃል በትክክል ሰምቶ ለሰላም ይታዘዝ፡፡

ሌላው የጥምቀት በዓል ዋና መልእክት “ያለው ለሌለው ያካፍል” የሚለው ትእዛዘ እግዚአብሔር ነው፡፡ ዛሬ ብዙ ወገኖቻችን ሕፃናት፣ እናቶች፣ እኅቶችና አረጋውያን በረኃብ ተቈራምደው ዕለተ ሞታቸውን ሲጠብቁ እያየን ነው፡፡

ወገኖቻችን በረኃብ እንዲህ እየሞቱ #እንደባዕድ ዝም ብለን የምናይ ከሆነ ክርስቲያንነቱ ጥያቄ ውስጥ አይገባምን ? ስለሆነም ኢትዮጵያውያንም ሆን የዓለም ማኅበረ ሰብ በሙሉ በጽኑ ረኃብ ለተጠቃው ሕዝባችን እጃቸውን እንዲዘረጉ በዚህ አጋጣሚ በእግዚአብሔር ስም ጥያቄያችንን እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር በዚሁ ዕለት እኛን ለመቀበል ሰማያዊ በሩን እንደከፈትልን እኛ ኢትዮጵያውያንም አእምሮአችንን ከፍተን ለመረዳዳት ለሰላም፣ ለፍቅር ለይቅርታ ለአንድነትና ለእኩልነት ተጠቃሚነት በርትተን እንድንሰራ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላፋለን፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም በሁለቱም የትምህርት መስኮች እያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች ፈተናው እንዲሰጥ ተወስኗል፡፡

የተፈጥሮ ሣይንስ ፦
እንግሊዝኛ፣
ሒሳብ፣
ፊዚክስ፣
ኬሚስትሪ፣
ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት

የማኅበራዊ ሣይንስ፦
እንግሊዝኛ፣
ሒሳብ፣
ታሪክ፣
ጂኦግራፊ፣
ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት

ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የተፃፈው ሰርኩላር፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝግጅትንም ያብራራል።

በዚህም የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ከ12ኛ ክፍል ብቻ ፈተናው የሚዘጋጅ ሲሆን ሌሎች የትምህርት አይነቶች ከ9-11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንደሚሆን ያትታል።

ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ወደፊት ጥናት ተጠንቶ እስከሚለይ ድረስ በነበረው አሠራር መሠረት ውጤት ተደምሮ የሚገለጽ መሆኑንም ገልጿል።

የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያውቁት እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

የ2016 ዓ/ም ብሔራዊ ፈተና መቼ ሊሰጥ ታቅዷል ?

የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ከዚህ ቀደም ሰጥተው በነበረ ማብራሪያ ፤ የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ግንቦት ወር ላይ እንዲሰጥ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው።

ሚኒስትሩ ፤ የዚህ ዓመት ፈተና ድብልቅ / ሃይብሪድ መሆኑንም በወቅቱ ገልጸው ነበር።

ድብልቅ ፈተና ማለት ግማሹ #ኦንላይን (የኢንተርኔት ችግር የሌለባቸው አካባቢዎች) ፤ የኢንተርኔት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከዚህ ቀደም ሲሰጥ በነበረበት አካሄድ #በወረቀት ለመስጠት ነው እቅዱ።

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ ሰጥተውት በነበረው ማብራሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ምንም እንኳን የመግዛት አቅም ባይኖረውም ለፈተናው የሚሆኑ #ታብሌቶችን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመነጋገር ለፈተናው ጊዜ በመውሰድ ፈተናውን በድብልቅ እንደሚሰጥ አሳውቀዋል።

የ2016 ዓ/ም ፈተና ድብልቅ በሆነ መንገድ እንዲሰጥ የሶፍትዌር ስራው መጠናቀቁንም ይፋ አድርገው ነበር።

የዘንድሮው ምዝገባ በኦንላይን እንደሚሆን ተፈታኞች በአካል ተገኝተው ፎቶ እንዲነሱ እንደሚደረግ እና በዚህ ረገድ ቁጥጥሩ ጠበቅ እያለ እንደሚሄድ ሚኒስትሩ ከወራት በፊት መግለፃቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መዘገቡ አይዘነጋም።

#ምንጭ@tikvahuniversity (ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ)

#ድብዳቤው ፦ ከክልል የትምህርት ቢሮዎች የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IGAD ዛሬ በኡጋንዳ፣ ኢንቴቤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት (ኢጋድ) መሪዎች ስብሰባ ይደረጋል። ስብሰባው ትኩረት ከሚያደርግባቸው ጉዳዮች አንዱ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረው ውጥረት ነው። ሌላው የሱዳን ጦርነት ነው። ለኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ እስካሁን ድረስ በታወቀው ፦ የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር የጅቡቲው ፕሬዜደንት ኢሳሜል ኦማር ጌሌህ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት…
#Update

ከቀናት በፊት ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ጋር ግኙነት እንዳቋረጠ የገለፀው በጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን የሚመራው የሱዳን መንግሥት ዛሬ ከኢጋድ አባልነት መውጣቱን አሳውቋል።

የሱዳንን ብሔራዊ ጦር የሚመራው የሱዳን መንግሥት ኢጋድ በኡጋንዳ ኢንቴቤ አድርጎት በነበረው አስቸኳይ ስብሰባ የተፋላሚውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ በስብሰባው እንዲሳተፉ መጋበዙ ‘የሃገሪቱን ሉላዊነት ጥሷል’ በማለት ከኢጋድ ጋር ያለውን ግንኙነት አቋርጦ ነበር።

ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ባወጣው መግለጫ ከኢጋድ አባልነት ሀገሪቱ መውጣቷን ይፋ አድርጓል።

ምንጭ ፦ አልጀዚራ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ግብፅ #ሱማሊያ

በግብፁ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ግብዣ የተደረገላቸው የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ግብፅ ካይሮ ገብተዋል።

ሁለቱ ፕሬዜዳንቶች በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሏል።

የኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት በተፈረመ ማግሥት " ከሶማሊያ ጎን እቆማለሁ " ብላ በስምምነቱ ላይ ተቃውሞ ያሰማቸው ግብፅ ነበረች።

ከዚህም ባለፈ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት በስምምነቱ ተቃውሞ ዙሪያ ቀደመው ስልክ ከደወሉላቸው መሪዎች አንደኛው ፕሬዜዳንት አልሲሲ እንደነበሩ አይዘነጋም።

ፕሬዜዳንት አልሲሲም ከቀናት በኃላ ፕሬዜዳንቱ ወደ ኤርትራ ባቀኑበት ወቅት ግብፅን እንዲጎበኙ ጥሪ አድርገውላቸው የነበረ ሲሆን በዚሁ ጥሪ መሰረት ለሁለት ቀን ጉብኝት ትላንት ምሽት ካይሮ ገብተዋል።

ግብፅ ፤ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 የባህር በር እንዲኖራት እድልን ይሰጣል ከተባለውና ከሶማሌላንድ ጋር ከተደረገው የመግባቢያ ስምምነት ወዲህ ኢትዮጵያን የሚወነጅሉ አስተያየቶችን ስትሰጥ የነበረ ሲሆን ከሰሞኑን " ኢትዮጵያን በአካባቢው የአለመረጋጋት ምንጭ እየሆነች ነው " የሚል ንግግር በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል ተናግራለች።

ኢትዮጵያም ግብፅ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል ለተናገረችው ንግግር በአምባሳደር መለስ አለም በኩል ፤ " ኢትዮጵያን በአለመረጋጋት መንስኤነት መክሰስ በአንድ ቃል ለመግለፅ #ቧልት ነው፤ የዘመኑ ቀልድ ተብሎ ሊቀመጥ ይችላል። " በሚል የመልስ ምት ሰጥታታለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Grade12NationalExam

ከዚህ ቀደም በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ሲሰጡ ከነበሩ የትምህርት አይነቶች መካከል ሥነ ምግባርና የሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) በዘንድሮው ዓመት 2016 ዓ/ም #አይሰጥም

የሥነምግባር እና ሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) ፈተና ያልተካተተው በሁለቱም የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች ነው።

ይህ ፈተና ለምን በብሄራዊ ፈተናው ላይ እንዳልተካከተተ / እንዳይካተት ውሳኔ እንደተለለፈ ትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው ዝርዝር ማብራሪያ የለም።

በሌላ በኩል ፤ ባለፉት ዓመታት ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሳይሰጥ የቆየው #የኢኮኖሚክስ ትምህርት በዚህ ዓመት 2016 ፈተና ላይ ተካቷል።

በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እኩል ስድስት ትምህርቶችን ይወስዳሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ፤ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ሶኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ፈተና ሲወስዱ የማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ ፣ ጂኦግራፊ ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ፈተና የሚወስዱ ይሆናል።

በዚሁ ዝርዝር መሰረት ከሁለቱም ዘርፎች የሥነ ዜጋና ሥነምግባር (Civics and Ethical Education) ትምህርት የወጣ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ላይ ባለፉት ዓመታት ሳይሰጥ የቀረው ኢኮኖሚክስ ተካቷል።

ፈተናው የሚሰጥበት ትክክለኛውና ቁርጥ ያለው ቀን ባይታወቅም እንደ ከዚህ ቀደሞቹ ዓመታት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (#ዩኒቨርሲቲዎች) በማስገባት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
#DStv

📣 ሰምተዋል?

በማንኪያ ሲሉ በጭልፋ ፤ በጭልፋ ሲሉ በአካፋ!

👉 ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ድረስ ከሚጠቀሙት ፓኬጅ ከፍ ካሉ በእኛ ወጪ ወደ ቀጣዩ ትልቅ ፓኬጅ ለአንድ ወር ከፍ ይላሉ!

ይህ አገልግሎት ክፍያ ከፈፀሙ ከ48 ሰዓት በኋላ ተግባራዊ ይሆናል።

*ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን 

የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!

👇👇👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #StepUp
#CBE

CashGo (ካሽ ጎ)

ከውጭ ሀገራት ገንዘብ መላኪያ የሞባይል መተግበሪያ
===========================
በሞባይል ስልክዎ አማካኝነት ቪዛና ማስተር ካርድዎን በመጠቀም

• ከውጭ ሀገር በቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ወይም ወደ ሲቢኢ ብር ሂሳብ መላክ ይችላሉ፣ አሊያም
• ተቀባዩ ከ1900 በላይ በሚሆኑት የባንካችን ቅርንጫፎች መቀበል ይችላሉ!
**
የCashGo ሞባይል መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ይጠቀሙ።

• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo&hl=en&gl=US

• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/cashgo/id1559346306
TIKVAH-ETHIOPIA
" በምጥ የተያዘችን እናት ሊያመጣ ሲሄድ በተተኮሰበት ጥይት ተመቶ ህይወቱ አልፏል " - የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር   የአምቡላንስ ሼፌሩ በተተኮሰበት ጥይት #ተገደለ። በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን ‘የእምባስነይቲ ቅርንጫፍ’ የአምቡላንስ ሹፌር አቶ ወልዱ አረጋዊ በርሀ የወላድ እናትን ህይዎት ለማዳን እያሽከረከረ ባለበት ሰዓት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰበት…
#UPDATE 

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ያወጣውን የሃዘን መገለጫ ዋቢ በማድረግ ጥር 3 /2016 በትግራይ ማእከላዊ ዞን ‘የእምባስነይቲ ቅርንጫፍ’ የአምቡላንስ ሹፌር አቶ ወልዱ አረጋዊ በርሀ የወላድ እናትን ህይወት ለማዳን እያሽከረከረ ባለበት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ማለፉ መዘገባችን ይታወሳል።

የቀይ መስቀል የአምቡላንስ ሹፌሩ እንዴት ለህልፈት እንደበቃ የሚያትት ከትግራይ ማእከላዊ ዞን ፤ እንዳባፃሕማ ወረዳ፤ ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ፓሊስ የደረሰን የምርምራ ወጤት እንደሚከተለው አቅርበናል።

አቶ ወልዱ አረጋዊ የሚነዳት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በእምባስነይቲ እንዴት ተመታች ? ሹፌሩስ እንዴት ለህልፈት ተዳረገ ? 

ፖሊስ ፤ አከባቢው ህጋዊ ያልሆነ ትጥቅ በተምቤን ትግራይ ክልል አድርጎ ወደ ሰቆጣ አማራ ክልል የሚተላለፍበት እንደሆነ በጥናትና ክትትል ቀደም ብሎ እንደደረሰበት ይገልጻል።

ስለሆነም ጥር 2/2016 ቀን ላይ በአምባስነይቲ ነበለት በተምቤን ወደ ሰቆጣ 80 መሳሪያ ከነተተኳሹ በሌሊት እንዲተላለፍ እየተደሎተ መሆኑ መረጃ እንደደረሰው አመልክቷል።

ገዢና ሻጮች ወደ እምባስነይቲ ዕዳጋ ዓርቢ ነበለትና አከባቢው መግባታቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።

ፓሊስ በአከባቢው ከሚገኙ ሌሎች የፀጥታ ሃይሎች በመቀናጀት መሳሪያው ከገዢና ሻጭ እንዲሁም አሻሻጭ ደላሎች እጅ በፈንጅ ለመያዝ በተጠንቀቅ ቆመ። 

ፓሊስ ቀን ላይ ገዢና ሻጭ እንዲሁም አሻሻጭ ደላሎች ያረፉበት ሆቴል የሚዘዋወሩባቸው ቤቶችና ተመሳሳይ ጉዳዮች ሲከታተለ ውሎ አመሸ። 

ፓሊስ ከአከባቢው ተገዝቶ የሚጓጓዘው መሳሪያ ከነተተኳሹ በመኪና እንደሚጓጓዝ መረጃው ቢደርሰውም፤ መኪናዋን የሚያሽከረክራት ሹፌርና የመኪናዋ ዓይነት አልለየም ነበር።

ይህ በእንዲህ እያለ አቶ ወልዱ አረጋዊ የሚነዳት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር  አምቡላንስ በወሊድ ምጥ የተያዘች እናትን ከአከባቢው የተሻለ ህክምና ወዳለበት ከተማ ለመውሰድ በእምባስነይቲ ነበለት ዓዲ ፌላ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ተገኘች። 

ከሌሊቱ 5:00 ሰዓት ፓሊስና ሌሎች የፀጥታ አካላት ህጋዊ ያልሆነ ትጥቅ ከትግራይ ወደ አማራ ክልል ለማሸጋገር የምትበረው መኪና ከነግብረአበሮችዋ ለመያዝ በተጠንቀቅ እያሉ አምቡላንስዋ ተከሰተች።

አቶ ወልዱ አረጋዊ የሚነዳት አምቡላንስ የወላጅ እናት ህይወት ለመታደግ በጉዞ ሳለች በድቅድቅ ጨለማ በአሳቻ ቦታ " ቁም ! " የሚል የፀጥታ አካላት ትእዛዝ እንደተሰጣት ፖሊስ ገልጿል።

ፖሊስ ፤ ሟች " ቁም " የሚለውን ወታደራዊ ትእዛዝ ሳይቀበል በመቅረት አምቡላንስዋን መንዳቱን ቀጠለ ይላል።

" ቁም !ቁም !ቁም " የሚለው ድምፁ እንጂ መልኩ የማይታየው ከድብቅ ቦታ የሚሰማው ማስጠንቀቅያ ትእዛዝ ቀጠለ። ሟች አምቡላንስዋ አላቆማትም ። አንደኛ ኬላ አልፎ ሁለተኛ ኬላ ደርሶ ለማለፍ ሲሞክር አምቡላንስዋ ተተኮሰባት ሟችም ተተኮሰበት። መኪናዋ ቆመች ፤ የወልዱ ህይወትም በዚህ መንገድ ተቀጠፈ።

ይህ አደጋ ካጋጠመ በኃላ ቀን ሙሉ በድብቅ የፓሊስና ሌሎች የፀጥታ አካላት ክትትል የዋለችው ህጋዊ ያልሆነ መሳሪያ የጫነችው መኪና ተከትላ እንደመጣች ፖሊስ ገልጿል።

መኪናዋ ከተወሰኑት ግብረ አበሮች ከጫነችው ህጋዊ ያልሆነ መሳሪያና ተተኳሽ ጭምር በፀጥታ ሃይሎች ቁጥጥር ስር ዋለች። 

በአምቡላንስዋ የነበሩና ከአደጋው የተረፉ ሃኪሞች ሟች ቁም ሲባል ለምን እንዳልቆም አስመልክቶ ከፓሊስ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ቃል፤ እንዲቆም የተጠየቀበት ቦታ ከከተማ ውጪ እንዲሁም ጨለማ ስለነበር #ዘራፊዎች መስለውት ለማምለጥ እሰቦ ነው ብለዋል።

አቶ ወልዱ አረጋዊ ባለትዳርና የ6 ልጆች አባት ነበር።

#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ

@tikvahethiopia
#ቤኒሻንጉልጉሙዝ

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ወደ አዲስ አበባም ሆነ ወደ አጎራባች አካባቢዎች የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ምክንያት ዝግ በመሆኑ፣ ለከፍተኛ ሕክምና ሪፈር የሚጻፍላቸው ሕሙማን ሕክምና ባለማግኘታቸው ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ፡፡

ከአሶሳ ከተማ ተነስቶ ወደ መተከልና ኦሮሚያ ክልል የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ችግር ምክንያት በመዘጋቱ ሕሙማን የከፋ ችግር ውስጥ ወድቀዋል።

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶፊያ አወት ምን አሉ ?

- ከአጎራባች ሱዳን ፈልሰው የመጡ ስደተኞችና ምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ የሠፈሩ ዜጎች ሙሉ ለሙሉ የሕክምና አገልግሎት የሚያገኙት አሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል በመሆኑ፣ ሆስፒታሉ አገልግሎት ለመስጠት ከአቅሙ በላይ ሆኖበታል።

- ሆስፒታሉ ከፍተኛ የሆነ የሕክምና ግብዓት እጥረት አለበት።

- ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ሕክምና እንዲያገኙ ሪፈር የሚጽፍላቸው ሕሙማን አቅም ያላቸው ብቻ የአየር ትራንስፖርት ተጠቅመው የሕክምና አገልግሎት እያገኙ ነው።

- በክልሉ አብዛኛውን ነዋሪ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለ ሲሆን፣ ወደ አዲስ አበባ ከተማም ሆነ ወደ ሌሎች አጎራባች አካባቢዎች በአየር ትራንስፖርት ሄደው ለመታከም የገንዘብ ችግር ስለሚገጥማቸው ሞታቸውን የሚጠባበቁበት ሁኔታ ተፈጥሯል።

- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቁጥር አንድ ከሚባሉት ሆስፒታሎች ውስጥ አንዱ ነው። በአሁኑ ወቅት በቀን ከ150 በላይ ለሆኑ ሕሙማን አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡

- ለሆስፒታሉ የሚቀርበው መድኃኒትና ሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት ጭራሽ የማይመጣጠን ነው።

- በፀጥታ ችግር ምክንያት መድኃኒት እየቀረበ ያለው በአየር ትራንስፖርት ነው።

- በአየር ትራንስፖርት መድኃኒት ቢመጣም ቶሎ ቶሎ የሚያልቅ በመሆኑ መድኃኒት ለመግዛትም ሆነ ለመድኃኒት ማጓጓዣ ሆስፒታሉ ከፍተኛ ወጪ እያወጣ ይገኛል።

- ሆስፒታሉ የቀዶ ጥገና፣ የማዋለድ፣ የዓይን ሕክምናና ሌሎች አገልግሎቶችን ይሰጣል።

- ከዚህ በፊትም የፀጥታ ችግር ባልነበረበት ወቅት ሕሙማንን በፍጥነት በአምቡላንስ በማመላለስ አገልግሎት ይሰጥ ነበር፤ ይሁን እንጂ የፀጥታ ችግር በክልሉ በመባባሱ አምቡላንሶች እንደ ልብ ተንቀሳቅሰው አገልግሎት እንደማይሰጡ ሆኗል። ከዚህ ቀደም አንድ አምቡላንስ በታጣቂ ኃይሎች መቃጠሉንና ውስጥ የነበሩ ሕሙማንና ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለም ደበሎ ምን አሉ ?

* በክልሉ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ ስድስት ሆፒታሎች አሉ፡፡ ሆስፒታሎቹ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት የግብዓት ችግር ገጥሟቸዋል።

* በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት አገልግሎት ለመስጠት ተቸግረዋል።

* የመድኃኒትም ሆነ ሌሎች የሕክምና ግብዓቶችን በተመለከተ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር በአየር ትራንስፖርት እያስገባን ቢሆን ችግሩ ግን ከፍተኛ ነው።

* በክልሉ የሕክምና አገልግሎቶች የሚሰጡ ሆስፒታሎች ለሕሙማን ሪፈር ሲጽፉ አብዛኞቹ ሕሙማን በአየር ትራንስፖርት ሄደው ለመታከም ይቸገራሉ፤ በዚህ ምክንያት እዚያው ሕክምናቸውን ለመከታተል ተገደዋል።

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ለዓለም ዋንጫ ታልፍ ይሆን ?

የኢትዮጵያ #ከ20_ዓመት_በታች ሴት ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን ከሞሮኮ አቻው ጋር በአዲስ አበባ ፤ አበበ ቢቂላ ስታዲየም እያደረገ ይገኛል።

ብሔራዊ ቡድኑ ከሳምንት በፊት ከሜዳው ውጪ ያደረገውን የማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ በሞሮኮ የ2ለ0 ተሸንፏል።

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታውን በድምር ውጤት የሚያሸንፍ ከሆነ በቀጥታ ኮሎምቢያ ለምታዘጋጀው የ2024 ዓለም ዋንጫ ውድድር ያልፋል።

በ " አበበ ቢቂላ ስታዲየም " እየተካሄደ ያለውን ጨዋታ በቲክቫህ ስፖርት መከታተል ይችላሉ ፦ https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x

በተጨማሪ በቀጥታ ለመመልከት ፦ https://www.youtube.com/live/fGyiYbhaj-k?si=_DGAQyXg1Oo7q5u_

ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ እና የሞሮኮ እግር ኳስ ቡድን አባላት (Tikvah Ethiopia Sport Image)

@tikvahethiopia @tikvahethsport