TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትግራይ #መቐለ

" ስካይ ማይክሮፋይናንስ አ/ማ " የተሰኘ የቁጠባና የብድር የፋይናንስ ተቋም በይፋ ተመሰረተ።

የስካይ ማይክሮፋይናንስ ሰብሳቢ አቶ ግርማይ ካሕሳይ በይፋዊ የምስረታ ፕሮግራም ባሰሙት ንግግር ተቋሙ በመላ አገሪቱ መንቀሳቀስ የሚያስችለው ፍቃድ ከብሄራዊ ባንክ ማግኘቱንና ዘመኑ በሚጠይቀው ቴክኖሎጂ በመታገዝ የቁጠባ ፣ የገቢ ወጪ እንዲሁም ገንዘብ የመቀበል እና የማስተላለፍ የሃዋላ  አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል ።

የአንድ አክስዮን የሽያጭ ዋጋ አንድ ሺ ብር መሆኑና በግለሰብ 10,000 ፤ በተቋም 30,000 አክስዮኖች መግዛት እንደሚቻል ያብራሩት ሰብሳቢው ፤ ተቋሙ  በሚቀጥሉት ስድስት ወራት መደበኛ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ብለዋል። 

የትግራይ ክልል የፋይናንስ ፎረም አስተባባሪና የፕሮግራሙ የክብር እንግዳ  ዶ/ር መብራህቱ መለስ " የፋይናንስ እንቅስቃሴ በድህረ ግጭት ወቅት " በሚል ርእስ ባቀረቡት ፅሁፍ ከ1988 ዓ.ም ጀምሮ የፋይናንስ ተቋማት ምስረታ በመላ አገሪቱ መስፋፋቱንና ፤ በትግራይ እስከ 2013 ዓ.ም ድረስ  59 ቢሊዮን ብር የቆጠቡ ፤ ከ70 ሚሊዮን ብድር መስጠት የቻሉ 1074 ቅርንጫፍ ያላቸው 44 የፋይናንስ ተቋማት እንደነበሩ ገልፀው ፤ ተቋማቱ በተካሄደው ጦርነት ለከፍተኛ ጉዳት ተዳርገዋል ብለዋል።

ከሰላም ስምምነቱ በኋላ የፋይናንስ ዘርፉ በክልሉ መነቃቃት ማሳየት እንደጀመረ የዚሁ ማሳያ ስካይ ጨምሮ 45 የግል የፋይናንስ ተቋማት በምስረታ ላይ መሆናቸው ዶ/ር መብራህቱ አስታውቀዋል።

ባለፉት ሶስት የጦርነት አመታት የትግራይ የፋይናስ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ጉዳት ማስተናገዱንና ይህንን ለማዳንና ክልላዊና አገራዊ ፋይዳው እንዲጎለብት የፌደራል መንግስት የተለየ ትኩረት መስጠት ይገባዋል ብለዋል ዶ/ር መብራህቱ መለስ።  

የምስረታ ፕሮግራሙ ተሳታፊ  ወ/ሮ ለምለም ሃይሚካኤልና አቶ አስገዶም አሰፋ በሰጡት አስተያየት የተበታተነ ፋይናንስ በቁጠባ መልክ በማሰባሰብ መልሰው ለአገርና ህዝብ እድገት ብድር በመስጠት ኢኮኖሚው የሚደገፉ የግል የፋይናንስ ተቋማት የመንግስት ልዩ ትኩረትና ጥበቃ ይሻሉ ።  

በስካይ ማይክሮፋይናንስ አ/ማ ይፋዊ የምስረታ ፕሮግራም ባለ አክስዮኖች የሃይማኖት መሪዎች :  በፋይናንስ ዘርፍ የሚንቀሳቀሱ ተቋማት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን ለማወቅ ችለናል።

@tikvahethiopia
" በየትኛውም ዓለም ፤ በየትኛውም ሀገር ዋነኛው ቀጣሪ የግሉ ዘርፍ ነው " - አቶ ንጉሱ ጥላሁን

በአፍሪካ ሀገራት የስራ እድል ፈጠራዎች ላይ ባሉ ፈተናዎች እና ምቹ ሁኔታዎች ላይ የሚመክር የስራ ፈጠራ ማድረክ በአ/አ አፍሪካ ህብረት ግቢ ውስጥ ተጀምሯል።

ትላንት በነበረው መድረክ ላይ የተሳተፉት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በየአመቱ 2 ሚሊዮን አዳዲስ ስራ ፈላጊዎች እየተፈጠሩ ነው ብለዋል።

ለስራ ፈላጊ ዜጎች በተለያየ የስራ ዘርፍ ስራ ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ በውጭ ሀገርም ትልቅ እድል እንዳለ አሳውቀዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ " በየአመቱ በእቅድ ተይዞ ነው የሚሰራው።

ለምሳሌ በ2015 በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ100 ሺህ ዜጎች በውጭው አለም ለመፍጠር ነው የታቀደው፤ ከዙህ ውስጥ 85 በመቶ በቤት ውስጥ ስራ 15 በመቶ skilled የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ ነው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የዓመቱን ማጠቃለያ እንገመግማለን የአመቱን እቅድ እንደምናሳካ መረጃዎች ያሳያሉ።

ከዛ ባሻገር በውጭ ሀገር ገበያ በርካታ ፍላጎት አለ፤ 2 ሚሊዮን ያህል የስራ ገበያ ፍላጎት አለ።

በአንዳንድ ሀገራት ተወዳዳሪ ሆነን እስከተገኘን ድረስ ዋናው ብቃት ያለው ሰው ፣ ታታሪ ፣ ታማኝ ፣ ምርታማ የሆነ ፣ ስነምግባር ያለው ፤ ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሆነ ሰው ማዘጋጀት ከቻልን ሰፊ እድል አለ " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግሥት አዲስ ሰራተኞች የስራ ቅጥር እንደሌለ በገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ የተደረገውን ውሳኔ በተመለከተ አቶ ንጉሱ ተጠይቀው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ ስራ መፍጠር ያለበት መንግሥት ብቻ ነው የሚለው የቆየ አስተሳሰብ መቀየር አለበት ብለዋል።

" እኔ ምረዳው እውነታውም ጭምር መንግሥት ዋነኛ ስራ ቀጣሪ አይደለም። በየትኛውም ዓለም ፤ በየትኛውም ሀገር ዋነኛው ቀጣሪ የግሉ ዘርፍ ነው። መንግሥት የግሉ ዘርፍ ሁኔታዎችን እንዲመቻቹለት ማድረግ ነው የሚጠበቅበት ፤ ይሄንን የስራ እድል ለመፍጠር የማያስችሉ ፖሊሲዎች ፣ መመሪያዎችን አሰራሮችን ማውጣት ፣ የገንዘብ አቅርቦት እንዲሟላ ማድረግ ፣ የቴክኖሎጂ ትስስር ሽግግር እንዲኖር ማድረግ ፣ መሰረተ ልማት ማሟላት ፣ የገበያ ትስስር እንዲኖር ማድረግ የመንግስት ድርሻ ነው " ሲሉ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናግረዋል።

" እነዚህ ሁሉ የተሟሉ ሲሆኑ ፤ አገልግሎት ሲሟላ የግሉ ዘርፍ ይስፋፋል ያድጋል ፣ ኢንቨስትመንት ይሰፋል በዚህ ምክንያት የስራ እድል ይፈጠራል መንግሥት ሁሉንም ጀምሮ የሚጨርስ አይደለም። ዘንድሮ 3.1 ሚሊዮን የስራ እድሎች ተፈጥረዋል እስካሁን ከዚህ ውስጥ በመንግሥት መ/ቤቶች እና ተቋማት የተቀጠረው በጣም ዝቅተኛ ነው ከ3.1 ሚሊዮኑ መቶ ሺህ የማይሞላ ወደ 92 ሺህ ያህል ነው ከወረዳ እስከ ፌዴራል ድረስ ያለው ፤ በመንግሥት የስራ ዘርፍ ያሉት እድሎች ውስን ናቸው ጥቂቶች የሚገቡባቸው ናቸው ፤ ይልቁንም መንግሥት ማድረግ ያለበት ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሮ በርካታ ዜጎች የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው የሚያስችሉ ኢንተርፕራይዞች እንዲሰፉና እንዲያድጉ ማድረግ ነው " ብለዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ " በባለፈው ዓመት ከለየነው 6 ሚሊዮን የስራ ፈላጊ ፤ ወደ 650 ሺህ አካባቢው ምሩቅ ነው ፤ ይሄንን ምሩቅ ከቴክኒክና ሙያ እና ከዩኒቨርሲቲ የተመረቀ መንግሥት ሁሉም ቦታ ላይ አስገባዋለሁ ቢል ቦታው የለውም ፤ ይሄን ሁሉ ምሩቅ እና ስራ ፈላጊ መንግሥት ማድረግ ያለበት አሰልጥኖ አብቅቶ የገንዘብ አቅርቦት አመቻችቶ የስራ ቦታ አመቻችቶ የስራ ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቅበታል። " ሲሉ ተደምጠዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ተፈታኞች ፈተናውን ያለምንም ጭንቀትና ስጋት በጥንቃቄ ስሩ " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ያለምንም ጭንቀትና ስጋት ተረጋግተው እንዲወስዱ መልዕክቱን አስተለልፏል።

ሚኒስቴሩ ዛሬ የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ለተፈታኞች መልዕክት አስተላልፏል።

በዚህ መልዕክቱ ፤ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በተማሩት የትምህርት መስክ ከፍተኛ ግንዛቤ ያላቸውን ተመራቂዎች ለማፍራት እንዲቻል የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል። ከእነዚህም መካከል አንዱ የመውጫ ፈተና መስጠት እንደሆነ አመልክቷል።

ከዚህ ዓመት ጀምሮ በየትኛውም የትምህርት መስክና ከየትኛውም የአገራችን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ተከታትለው የሚወጡ ተማሪዎች በኦንላይን የመውጫ ፈተና እንዲወስዱ እየሰራ መሆኑና የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ቀንም በአገር አቀፍ ደረጃ ሰኔ 30 ቀን በጤናና ተጏዳኝ መስኮች መሰጠት መጀመሩን ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ ፈተናው በኦንላይን እንዲሰጥ ሲያደርግ በየደረጃው ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ የቆየ መሆኑንና አስፈታኝ ተቋማትም  ያደረጉትን ዝግጅት መገምገሙን ጠቁሟል።

ባደረገው ክትትልና ግምገማም ሁሉም ከፍተኛ ትምህርት  ተቋማት ፈተናውን ለመስጠት በሚያስችል ዝግጅትና ቁመና ላይ መሆናቸውን እንዳረጋገጠ ገልጿል።

በተጨማሪ ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የፈተና አዘገጃጀቱን በበላይነት ሲመራና ሲከታተል መቆየቱን ጥያቄዎቹ በየዘርፉ መምህራን እንዲዘጋጁና ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማድረግ ሥራ መስራቱን አስገንዝቧል።

ይህ የመውጫ ፈተና ሁሉንም  የቅድመ ምረቃ ድግሪ የሚሸፍን ነው ያለው ሚኒስቴሩ ፤ በዲጂታል መሰጠቱ ልዩ ያደርገዋል ብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅቱን ያጠናቀቀ መሆኑን ገልጾ ለተፈታኝ ተማሪዎችም ጥያቄዎቹ የተዘጋጁት በቆይታቸው ከተማሯቸው ርዕሰ ጉዳዮች መሆኑን ተገንዝበው ያለምንም ጭንቀትና ስጋት በጥንቃቄ እንዲሰሩ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
" ጥቃቱ በጣም አሳዛኝ ነው ለማን እንደሚነገርም አይታወቅም " - የአይን እማኝ

ትላንት ምሽት ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ መተከል ዞን፣ ግልገል በለስ ከተማ በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት በትንሹ ከ6 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአንይ እማኞች ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ አሳውቀዋል።

ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች መጎዳታቸው ተነግሯል።

አንድ የአይን እማኝ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ጥቃቱ በከተማው አቅራቢያ የተፈፀመ መሆኑንና የ6 ሰዎች አስክሬን ሲነሳ በአይናቸው መመልከታቸውን ገልጸዋል።

" እኛም የህግ አካል አልደረሰልንም ፤ በአይን ያየሁት የ6 ሰው ሲነሳ ነው ፤ መኪና ላይ ያለው ወደ መንደር 7 ሄዷል ስንት እንደሆነ አላወኩም " ብለዋል።

ሌላ አንድ የአይን እማኝ ደግሞ ታጣቂዎቹ በፈፀሙት ጥቃት ከዚህም ከፍ የሚል መሆኑን ገልጸዋል። እስከ ጥዋት ድረስ አስክሬን ሲሰበሰብ የቆሰሉ ሰዎችን የማንሳት ስራ ሲሰራ ነበር ብለዋል።

" ህዝብ እና ሽፍታ አንድ ላይ እየተቀመጠ የከባድ መሳሪያ ይዘው ይንቀሳቀሳሉ ፣ ሹፌር አስቁመ ይዘርፋሉ ፣ ህዝብን ይገድላሉ፣ ያስራሉ ይደበድባሉ ትላንት ደግሞ ህዝብን አዘናግተው ብዙ ሰው ፈጁ ፤ የገደሏቸው ሰዎች አስክሬን ሲለቀም ነበር ፤ እነሱ ቤት ገብተው የገደሉበት ቦታ ሌላው ደግሞ ጉዳት የደረሰባቸው ሆስፒታል ገብተው እየታከሙ ነው ፤ መለስተኛ ጉዳትም የደረሰባቸው አሉ ፤ ብዙ የሞቱ አሉ አስክሬናቸው ሲለቀም ነበር ከሰፈርም ከቤት ውስጥም እና በጣም አሳዛኝ ነው ለማን እንደሚነገርም አይታወቅም " ብለዋል።

የአይን እማኞቹ ጥቃቱን የተፈፀሙት በቅርቡ ከትጥቅ ትግል እራሳቸውን አግልለው በከተማው ቅርብ ርቀት በሚገኘው " ቻይና ካምፕ " የሰፈሩ ታጣቂዎች መሆናቸውን ለሬድዮ ጣቢያው ጠቁመዋል።

ጥቃቱን በተመለከተ የክልሉ / የዞኑ ኃላፊዎች ምላሻቸውን እንዲሰጡ ለማድረግ ጥረት ቢደረግም አለመሳካቱን ሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።

ከዚህ ቀደም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፖሊስ ኮሚሽን በመተከል ዞን ፤ በሁለት ወረዳዎች 90 የታጣቂ አባላት በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ትጥቃቸውን ለመንግስት ማስረከባቸውን ማሳወቁ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
ሲቢኢ ብር
ለፈጣን፣ ቀላል፣ አስተማማኝ የነዳጅ ክፍያ አገልግሎት!

***************

 ወደ ሲቢኢ ብር መተግበሪያ ‘Quick Pay’ በመግባት ‘Fuel Payment’ የሚለውን የአገልግሎት አማራጭ መርጠው
• የነዳጅ ቀጂውን የተመዘገበ ስልክ ቁጥር፣
• የሚገዙትን የነዳጅ ክፍያ መጠን፣
• የነዳጅ አይነት፣
• የሰሌዳ ቁጥርዎን፣ እና
• የሚስጥር ቁጥርዎን አስገብተው ክፍያውን በማከናወን ነዳጅ መቅዳት ይችላሉ፡፡

 ወይም ለነዳጅ ቀጂ ባለሙያው
• ሲቢኢ ብር የተመዘገቡበትን ስልክ ቁጥር ߹
• የሰሌዳ ቁጥርዎን ፣
• የሚቀዱትን ነዳጅ የገንዘብ መጠን አሳውቀው ግብይቱን ሲያስጀምሩ በሚደርስዎት አጭር መልእክት መሠረት የገንዘብ መጠኑን ትክክለኛነት አረጋግጠው የሚስጥር ቁጥርዎን በማስገባት እና ክፍያውን በመፈፀም ነዳጅ መቅዳት ይችላሉ።

ስለሲቢኢ ብር አገልግሎት በቂ መረጃ ለማግኘት ወደ 951 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ!

*********************
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለመጫን ወይም ለማዘመን፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
#MyWish

አስተማማኝ የሆነውንና ቱርክ ሰራሹን ኢሳን ሲልድ ባትሪን በተለያዩ አማራጮች ማለትም በ12V35AH፣ በ12V45AH፣ በ12V55AH፣ በ12V60AH፣ በ12V70AH፣ በ12V90AH፣ በ12V100AH፣በ12V120AH እና በ12V150AH በጅምላና በችርቻሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
0910041280  0911135133  0921612272  0911159234   0984733988  0941473413
ዋና መስሪያ ቤት፡ ሀይሌ ጋርመንት ወደለቡ መብራት በሚወስደው መንገድ ቅርንጫፍ፡ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ አጠገብ
ማይ ዊሽ ኢንተርፕራይዝ ኃላ/የተ/የግ/ማ 
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ: https://t.me/MYWISHENT
የካንሰር ህክምና . . . #በኢትዮጵያ

#ጥቁር_አንበሳ

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፤ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ መኖራቸውን አስታውቋል።

የሆስፒታሉ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ክፍል ኃላፊ ኤዶም ሰይፉ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" የተለያዩ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠብቁ ከ2013 መጨረሻ፣ 2014 ዓ.ም. እና 2015 ዓ.ም. ወረፋ ያልደረሳቸው አሉ፡፡

ይሁን እንጂ በየዕለቱ የሚመጡ ድንገተኛ የካንሰር ታካሚዎች በመኖራቸው በቅድሚያ ለእነዚህ ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ይደረጋል።

በሆስፒታሉ ቆይተው መታከም ይችላሉ ተብለው የተለዩት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ሕክምና ለማግኘት እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ ጥረት እየተደረገ ነው።

ለዚህ ወረፋ መብዛት ዋነኛ ምክንያት ብለው ያቀረቡት በሆስፒታሉ የሚገኘው መሣሪያ #አንድ ብቻ መሆኑን ነው።

በዚህ ዓመት ብቻ በተደረገው ማጣራት የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠበባቁ 5,000 ታካሚዎች ሲኖሩ፣ በማዕከሉ በቀን በአማካይ ከ300 በላይ ታካሚዎች ይስተናገዳሉ።

ከእነዚህ የካንሰር ታካሚዎች መካከል 70 በመቶ የጨረር ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ፣ ኬሞ ቴራፒ የሚያስፈልጋቸው የታካሚዎች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም ።

በማዕከሉ አገልግሎት ለማግኘት የ2014 ዓ.ም. እና በ2015 ዓ.ም. ሕክምና ለማግኘት የተመዘገቡ ደግሞ ከ10,000 በላይ ናቸው። "

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ_ስፔሻላይዝድ_ሆስፒታል

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክሊኒካል ኢንኮሎጂስት ዶ/ር አማረ የሺጥላ ምን አሉ ?

"  በሆስፒታሉ የሚሰጠው የካንሰር ሕክምና ኬሞ ቴራፒና ቀዶ ጥገና ነው።

የጨረር ሕክምና ለመጀመር የማሽን ተከላ ላይ እንገኛለን። 60 በመቶ የሚሆነው የካንሰር ታካሚ እስኪጠናቀቅ እየተጠባበቁ ነው።

በሆስፒታሉ ካንሰር ሕሙማን ሕክምና አንዱ የሆነው ኬሞ ቴራፒ ሕክምና ለማግኘት ወረፋ በዛ ከተባለ ከሳምንት አይበልጥም።

ይሁን እንጂ ለካንሰር ሕሙማን የሚሰጠው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለመጠባበቅ ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት ያስፈልጋል። "

#በሐሮሚያ_ዩኒቨርሲቲ_ሕይወት_ፋና_ሆስፒታል

በሐሮሚያ ዩኒቨርሲቲ ሕይወት ፋና ሆስፒታል በካንሰር ሕክምና ረዳት ፕሮፌሰር ሚካኤል ሻውል (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" በሆስፒታሉ የኬሞ ቴራፒና የጨረር ሕክምና ለካንሰር ሕሙማን እየተሰጠ ነው።

የጨረር ሕክምና ከተጀመረ ስድስት ወራት አስቆጥሯል ፤ የታካሚዎች መጠነ መጠበቅ ከሦስት ወራት አይበልጥም።

በሆስፒታሉ በዓመት እስከ 6000 የካንሰር ታካሚዎች ሕክምና ያገኛሉ። በተለይ ደግሞ ጨረር ሕክምና ከተጀመረ በኋላ የታካሚዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።

ሆስፒታሉ በምሥራቅ ኢትዮጵያ እስከ ቅርብ ጊዜያት ብቸኛው የካንሰር ሕክምና መስጫ በመሆኑ ከሶማሌላንድና ከሌሎች አገሮች እየመጡ አገልግሎት የሚያገኙ ነበሩ። "

Via Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia
በሻኪሶ ከተማ ሞቶ በሦስተኛው ቀን አስክሬኑ የተገኘው ወጣት ጉዳይ !

#ዋና_ነጥብ

- በሻኪሶ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ተወዳጅ ታምራት (ጆኒ) ከሞተ በሦስተኛው ቀን አስክሬኑ ተገኝቷል።

- በሟች ግድያ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት ጓደኞቹ ፍርድ ቤት የዋስ መብት ፈቅዶላቸዋል።

- ወደ ስምንት የሚሆኑ የሟች ቤተሰቦች " ሁከት ፈጥራችኋል " ተብለው ከታሰሩ 10 ቀን ሞልቷቸዋል። ፍርድ ቤት ግን አልቀረቡም።

#ዝርዝር_ጉዳይ

በጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የባጃጅ ሹፌር የሆነው ወጣት ተወዳጅ ታምራት (ጆኒ) ሚያዚያ 29 በአንድ ሰርግ ላይ ተገኝቶ ምሽት ላይ ከታየ በኋላ ሊገኝ አልቻለም።

ጓደኞቹ ጋር ይሆናል ተብሎ ቢታሰብም በ2ኛው ቀን ግን ከጓደኞቹ " ጆኒን አይታችሁታል " የሚል ጥያቄ ለወንድሞቹ ቀረበ።

በዚህ ጊዜ ታናሽ ወንድሙ ወደሚያድርበት ቤት ሄዶ የጆኒ ክፍል የተባለውን ቤት ከአንድ ጓደኛው ጋር ሰብሮ ይገባሉ። ጠፋ የተባለው ወንድሙም በአልጋው ላይ ህይወቱ አልፎ ያገኘዋል። በወቅቱ ፖሊስ ደርሶ አስክሬኑን ለምርመራ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይልካል።

ፖሊስ ለሆስፒታሉ በጻፈው ደብዳቤ ሟች በሰው እጅ በመደብደቡ ከሞተ በኋላ ቤት ውስጥ በማስገባት ከተደበቀ በጥቆማ አስክሬኑ ተገኝቷል ሲል ድብደባ መፈጸሙን ይገልጻል።

የዓይን እማኞችም አስክሬኑ ላይ የምት እንዲሁም በቤቱ የደም ምልክት መመልከታቸውን ጉዳዩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ቤተሰባችን ጠቁመዋል።

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ለፖሊስ በጻፈው የውጤት ሪፖርት አስክሬኑ ለምርመራ የቀረበው በከፍተኛ ደረጃ በመስበስ ላይ እንዳለ መሆኑን ይጠቅሳል። በአስክሬኑ ላይ ተለይቶ የሚታይ ጉዳት የለም ያለው ሪፖርቱ " የደረሰ ውስጣዊ ጉዳትም የለም " ሲልም አካቷል።

አክሎም የልብ የደም መጋቢ ቧንቧ ወደ ወስጣዊ የልብ ክፍል ሰርገው መግባታቸው የሞት መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ጠቁሞ፤  " ከአስክሬን የምርመራ ውጤት በመነሳት የሞቱን መንስኤ መወሰን አልቻልንም፤ ስለሆነም መርማሪ ፖሊስ አደጋ የተከሰተበት የምርመራ ውጤት ከሁኔታው ጋር ተያያዥነት ያላቸው ማስረጃዎችን እና ሌሎች ደጋፊ ማስረጃዎችን በመጠቀም ድምዳሜ ላይ እንዲደርስ ምክራዊ ሀሳባችንን እንገልጸለን " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

በግድያ ወንጀል የተጠረጠሩት ሁለት ጓደኞቹ እና የአንደኛው ተጠርጣሪ ልጅ እናት እና አባት በጊዜው በቁጥጥር ሥር ቢውሉም የዋስ መብታቸው በፍርድ ቤት መፈቀዱን የሰሙት የሟች ቤተሰብ " ይህ እንዴት ይሆናል " ብለው ለመጠየቅ በሄዱበት ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ሁኔታውን ካስረዱን ቤተሰባችን እንዲሁም ከተላኩልን የምስል ማስረጃዎች መመልከት ችለናል።

የሟች ወላጅ እናት እና አባት፤ 2 ታላላቅ ወንድሞቹ እንዲሁም የሟች አጎት ጨምሮ ወደ 8 ሰዎች " ሁከት በመፍጠር እና እስረኛ ለማስመለጥ " ተጠርጥራችኋል ተብለው ከታሰሩ ዛሬ 10ኛ ቀናቸው መሆኑን ሰምተናል። የሟች ቤተሰቦች እስካሁን ድረስ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡም ሰምተናል።

በሟች ግድያ የተጠረጠሩት ጓደኞቹና የአንደኛው ተጠርጣሪ ልጅ እናት እና አባት በእስር ላይ ይገኛሉ።

ጉዳዩን በሚመለከት ከአከባቢው ፖሊስ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

በጉዳዩ ላይ ፖሊስ የሚሰጠው ማብራሪያ ካለ የምናቀርብ ይሆናል።

@tikvahethiopia