TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" በቅርቡ 10 ኤጲስ ቆጶሳትን እንሾማለን "

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ ሌላው ፈተና ነው የተባለው በትግራይ ክልል የሚገኙ ሊቃነጳጳሳት እንቅስቃሴ ጉዳይ አሁንም መቀጠሉ ተነግሯል።

በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በትግራይ ያሉ አባቶች ቤተ ክህነት ማቋቋማቸውን ማሳወቃቸው ይታወቃል።

ሊቃነ ጳጳሳቱ በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ፤ " በቅርቡ 10 ኤጲስ ቆጶሳትን እንሾማለን " ብለዋል።

በቅርቡ 10 ኤጲስ ቆጶሳትን በአገር ውስጥና በውጭ እንደሚሾም የተናገሩት ሊቃነ ጳጳሳቱ አዲሶቹ ተሿሚዎች በቅርብ ጊዜ ውስጥም ወደ ሥራ ይገባሉ ሲሉ ማሳወቃቸውን ትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

በትግራይ ክልል የሚገኙት ሊቃነ ጳጳሳት መሥርተነዋል ያሉትን ቤተ ክህነት ካቋቋሙበት ጊዜ ጀምሮ ስለ ኤጲስ ቆጶሳት ሢመት ጉዳይ ያሉት ነገር ባይኖርም አሁን ላይ ኤጲስ ቆጶሳትን እንደሚሾሙ አሳውቀዋል።

ተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ፤ በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ጠቅላይ ጽ/ቤትም ሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ሙከራ ማድረጉን ነገር ግን እንዳልተሳካ ዘግቧል።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሥር በትግራይ በሚገኙ አኅጉረ ስብከት መካከል የነበረው ግንኙነት መቋረጡን ይታወቃል።

በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል በትግራይ ክልል ለሚገኙ ብፁዓን አባቶች የግንኙነት ማስቀጠያ ደብዳቤዎች ሲጻፉ ቢቆዩም ውጤት ግን ሊያመጡ አልቻሉ።

በቅርቡም ቅዱስ ሲኖዶስ ከብፁዓን አባቶች፣ ከሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ከታዋቂ ሰዎችና ከምዕመናን የተወጣጣ ኮሚቴ ሰይሞ የነበረ ሲሆን ግንኙነቱን ለማስቀጥል ያመች ዘንድ አንድ ልዑክ ወደ ትግራይ እንደሚልክ ተነግሮ ነበር፤ ነገር ግን ከዚህ በኃላ የተሰማ አዲስ ነገር የለም።

@tikvahethiopia
የአሜሪካ ጦር በሶማሊያ የአየር ድብደባ አካሄደ።

ባለፈው ቅዳሜ ዕለት የአሜሪካ ጦር የ " አልሸባብ " ታጣቂዎችን ኢላማ ያደረገ አዲስ የአየር ድብደባ ማፈፀሙ ተረጋግጧል።

የአሜሪካ ጦር በሰጠው ማረጋገጫ ጥቃቱ የተፈፀመው በደቡብ ሶማሊያ መካከለኛው ጁባ ግዛት ፣ ጅሊብ ከተማ ሲሆን ጥቃቱ ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር በመተባበር የተፈፀመ ነው ተብሏል።

የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቶች በጥቃቱ የተገደለ / የተጎዳ ሲቪል እንደሌለ አመልክተዋል።

በጥቃቱ ከፍተኛ የ " አልሸባብ " አዛዦች ኢላማ መደረጋቸውን በተመለከተ ምንም የተባለ ነገር የለም።

ጅሊብ ፤ ከሞቃዲሾ በስተደቡብ ምዕራብ 385 ኪሎ ሜትር (239 ማይል) ርቃ የምትገኝ በ " አልሸባብ " ይዞታ ስር ያለች ከተማ ናት።

@tikvahethiopia
የስዕል ተስዕጦ ላላቸው የቀረበ ዕድል!

ሪድም ዘጀኔሬሽን USAID ጋር በመተባበር ዕድሜያቸው ከ18 -29 ለሆኑ ወጣቶች በቡድን ሆነው የሚሳተፉበት የስዕል ውድድር አዘጋጅቷል። ውድድሩ በሁሉንም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ 80 የሚሆኑ ወጣቶች ክህሎታቸውን ተጠቅመው ስለሰላም በጋራ እንዲሰሩ የሚያግዝና መልዕክት የሚያስተላልፉበት ነው።

ምዝገባው ከዛሬ ግንቦት 14 እስከ18 ድረስ የሚቆይ ሲሆን ተሳታፊዎች በሥራ ሰዓት በሪድም ቢሮ በአካል ወይም በኦላይን https://forms.gle/rQr7ojZ8jXkCrkA18 ላይ መመዝገብ ይችላሉ።

አንደኛ ለሚወጣው የሥዕል ሥራ የ60,000 ብር ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን፤ ሁለተኛ ለወጣው አሸናፊ ደግሞ የ40,000 ብር ሽልማት ያስገኛል። በማኅበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላገኘው የሥዕል ሥራ ደግሞ የ10,000 ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል።

ስለውድድሩ ዝርዝር መረጃና ለመሳተፍ ስለሚያስፈልጉ መስፈርቶች በቀጣዩ ሊንክ ይጠቀሙ https://telegra.ph/Call-for-Applicants-05-22

ለተጨማሪ መረጃ  0930098219 / fisehat@rtgethiopia.org ላይ ይጠይቁ።
#EthiomartShopping

ሴኩሪቲ ካሜራ ሽያጭና ነፃ ገጠማ : 0911582926

security camera CCTV (ባለ 4 አና ባ 8 ካሜራ) ለቤትዎ፤ ለድርጅት፤ ለሱቅ፤ ለፋርማሲ፤ ለዳቦ ቤት፤ ለቡቲክ፤ ለህንጻዎ ፤ ለመጋዘንዎ አና ለንብረትዎ የአመታት ልምድ ባለው ድርጅታችን ሴኩሪቲ ካሜራ ያስገጠሙ።

- 4 ካሜራዎች :- 4 ባለ 20 ሜትር ኦሪጂናል የካሜራ ኬብሎች  35,000 ብር
-8 ካሜራዎች :- 8 ባለ 20 ሜትር ኦሪጂናል የካሜራ ኬብሎች 50,000 ብር

ቦሌ መድሀንያለም ቤዛ ህንጻ 208
#ሱዳን

የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ እና ሱዑዲ አረቢያ አደራዳሪነት የተኩስ ማቆ ስምምነት ላይ ማድረሳቸው ቢነገርም እንደ ከዚህ በፊቶቹ ስምምነቶች ሁሉ ተጥሶ ካርቱም ትላትናም በፍንዳታ ስትናጥ መዋሏን ቪኦኤ ዘግቧል።

የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ከሰኞ ምሽት ለአራት ሩብ ጉዳይ ይጀምራል የተባለና ለሰባት ቀናት የሚቆይ ነበር።

ተኩስ ኡቅም ላይ ተደረሰ በተባለ በደቂቃዎች ውስጥ የአየር ድብደባ እና የተኩስ ልውውጥ እንደነበር የዓይን እማኞች ተናግረዋል። በሰሜን ካርቱም ውጊያ ሲካሄድ፣ ከካርቱም በሥተ ምስራቅ ደግሞ የአየር ድብደባ እንደነበር ዘገባው ጠቁሟል።

በአንዳንድ የካርቱም ክፍሎች ደግሞ፣ የሚያስጨንቅ ጸጥታ ሰፍኖ እንደነበር እና ነዋሪዎቹም የሰላም ስምምነቱ ውጊያውን ያስቆማል በሚል ተስፋ አድርገው እንደነበር ተነግሯል።

ነዋሪዎች ሕይወት አድን ርዳታ እንዲደርስ እና ወደ ጦር አውድማነት ከተቀየረችው ካርቱም በሕይወት ለመውጣት እንደሚሹም ታውቋል ሲል ቪኦኤ በዘገባው ገልጿል።

እስካሁን ድረስ ከ1,000 በላይ ሰዎች የሞሩ ሲሆን ከሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። 250 ሺሕ የሚሆኑትን ደግሞ #ኢትዮጵያን ጨምሮ የተሻለ ሰላም እናገኛለን ወዳሉባቸው ጎረቤት አገራት ሸሽተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአስቸኳይ መስጂዶችን ማፍረስ አቁሙ ፤ የፈረሱትንም በፍጥነት መልሳችሁ አሰሩ ፤ ህዝበ ሙስሊሙንም በይፋ ይቅርታ ጠይቁ " - የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዲሱ "በሸገር ከተማ " መስጂዶች እየፈረሱ መሆኑን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም አሳሰበ። ምክር ቤቱ ለኦሮምያው ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ…
#Update

የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በሸገር ከተማ እየተካሄደ ያለውን የመስጂድ ፈረሳ አጥብቆ እንደሚቃወም በመግለፅ ድርጊቱን አውግዟል።

በመላው ኦሮሚያ በሚገኙ መስጂዶች የጁመዐ ኹጥባ በሸገር ከተማ የተደረገውን መስጂዶችን የማፍረስ ዘመቻን በማውገዝ እንዲሆንም ጥሪ አቅርቧል።

የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ይህን ያለው ትላንት በፅህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው።

ምክር ቤቱ በመግለጫው ፤ አዲሱ የሸገር ሲቲ ማስተር ፕላን " ሆን ተብሎ " በሚመስል መልኩ  መስጂድ ያለባቸው አካባቢዎች ከፕላኑ ላይ እንዲወገዱ የተደረገ ነው ብሏል።

በዚህ መልኩ በተጠና ሁኔታ እስካሁን ከ19 በላይ መስጂዶች መፍረሳቸውን በመጥቀስ የፈረሱ መስጂዶች መልሰው መገንባት እንዳለባቸው የሚመለከተውን አካል አሳስቧል።

በተጨማሪ በመላው ኦሮሚያ በሚገኙ መስጂዶች የፊታችን ጁምዓ የሸገር ሲቲ አስተዳደር ያደረገው መስጂዶችን የማፍረስ ዘመቻ በኹጥባ እንዲያወግዙ እና ለህዝበ ሙስሊሙ ጉዳዩን አስመልክቶ ትክክለኛ መረጃ እንዲሰጡ አቅጣጫ አስቀምጧል።

ህዝቡ አንድነቱን ጠብቆ በጋራ ጉዳዩን እንዲያወግዝ እና ዱዓም እንዲያደርግ ም/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዎች መግለጫ ጥሪ አቅርቧል።

ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ደብዳቤ መፃፉና በደብዳቤው በሸገር ከተማ እያፈረሱ ስላሉ መስጂዶች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ መጠየቁ የሚዘነጋ አይደለም።

ፎቶ ፦ ዛውያ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
#በቆጂ

በቀናት በፊት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በቆጂ ከተማ የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ጥቃት 4 ሰዎች መገደላቸውን እና ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ የነበሩ እስረኞችን ማስመለጣቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ጋዜጣው ቃላቸውን ሰጡኝ ያላቸው የአይን እማኞች ፤ አርብ ዕለት ከምሽት 4 ሰዓት እስከ ለሊት 8 ሰዓት ከፍተኛ ተኩስም ከተማ ውሥጥ ይሰማ እንደነበር ገልጸው ፤ በማግስቱ ግን የፌዴራል ፖሊስ ወደ ከተማው መግባቱን ተከትሎ ተኩስ እንደቆመ አመልክተዋል።

የአይን እማኞቹ ተኩስ የከፈቱት መንግሥት " ኦነግ ሸኔ እያለ የሚጠራቸው የታጠቁ ቡድኖች መሆናቸውን ገልጸው ፤ ለሊት በነበረው ተኩስ አንድ የአካባቢው የሚሊሻ አሰልጣኝን ጨምሮ ነዋሪዎች መገደላቸውን አሳውቀዋል።

አንድ የሚሊሻው አሰልጣኝ የቅርብ ጓደኛ ነኝ ያሉ የአይን እማኝ ፤ ታጣቂዎቹ " ይህንን ቤት ከምናፈነዳው አንተ ብትወጣ ይሻላል " በማለት በለሊት ከመኖሪያ ቤቱ አስወጥተው እንደገደሉት ጠቁሟል።

ታጣቂዎቹ በከተማው ተኩስ የከፈቱት በእስር ቤት ያሉ ታራሚዎችን ለማስፈተት መሆኑን የገለፁት ነዋሪዎች የሚሊሻ አባሉንና ከነዋሪዎችን ሰው ከገደሉ በኃላ በከተማው ወደሚገኝ አንድ የፖሊስ ጣቢያ ሰብረው በመግባት ታሳሪዎችን ከእስር አስወጥተው መውሰዳቸውን ነዋሪዎች ለጋዜጣው ገልጸዋል።

ጋዜጣው ከከተማው ከንቲባ ምላሽ ለማግኘት የድምፅ እንዲሁም ፅሁፍ መልዕክት በመላክ ሙከራ ቢያደርግም ምላሽ ለማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።

የበቆጂውን ጥቃት በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ የበቆጂ ቤተሰብ አባላት ተመሳሳይ መልዕክቶች መላካቸውን ተመልክተናል።

ጆ የተባለ የቤተሰባችን አባል አርብ ከምሽቱ 5:30 ጀምሮ ከተማው ውስጥ ከባድ የተኩስ ድምፅ እንደነበር እና ተኩሱ ቢያንስ ከ1 ሰዓት በላይ እንደቆየ ጠቁሟል።

ሌላ ኤቢ የተባለ የቤተሰባችን አባል በበኩሉ ፤   በአርሲ ዞን በቆጂ ከተማ መንግስት " ሸኔ " ብሎ የሚጠራው አካል በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት በመክፈት 20 የሚደርሱ የህግ ታራሚዎችን አስለቅቋል ሲል ገልጿል።

የተኩስ ልውውጡ ከበድ ያለ እንደነበር የገለፀው ይኸው የቤተሰባችን አባል ከበቆጂ ከተማ ወጣ ባለ ስፍራ በከተከፈ ድንገተኛ ጥቃት ሁለት የኦሮሚያ ፖሊስ አባላት መገደላቸውን ጠቁሟል።

ከዚህ በተጨማሪ ስሜ ፥ የተባለ የበቆጂ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል በቆጂ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የታጠቀ ኃይል ፖሊስ ጣብያ ሰብሮ እስረኞችን ማስመለጡንና ወዳልታወቀ ቦታ እንደወሰዳቸውን ጠቁሟል። በጥቃቱ ወደ ሶስት ፖሊሶችን እንዲሁም ሌሎች ሰዎችም መገደላቸውን አመልክቷል።

የበቆጂ ከተማን በተመለከተ ስለተከፈተው ጥቃት እና ስለደረሰው ጉዳት በመንግስት በኩል የተሰጠ መረጃ የለም።

ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ፣ እንዲሁም በወለንጪቲ ከተማ የታጠቁ ኃይሎች ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት ተኩስ በመክፈት ሰዎችን መግደላቸውና እስረኞችን ከማስመለጥ ሙከራ ማድረጋቸው መነገሩ አይዘነጋም።

የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አበበ ገረሱ በበቆጂ ጨምሮ በቢሾፍቱ፣ ወለንጪቲ ስለተፈፀሙት ጥቃቶች ከሪፖርተር ጋዜጣ ተጠይቀው  " የተባለውን ዓይነት የተደራጀ ጥቃት በየትኛውም አካባቢ አልተፈፀመም " ያሉ ሲሆን " አልፎ አልፎ #ሽፍታ ወይም #ሌባ ሊኖር ይችላል እንጂ ጥቃት የሚባል ነገር የለም። ሁሉም አካባቢ ሰላም ነው " ብለዋል።

Credit :  Reporter Newspaper , Tikvah Bokoji Family (Sem, Joh, Ab Via @tikvah_eth_BOT)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ሀገሪቱ ካሏት 47 ሽህ ገደማ ትምህርት ቤቶች 99 በመቶዎቹ አመቺ አይደሉም። በተሰራው ምዘና አራት ትምህርት ቤቶች ብቻ ከፍተኛውን ደረጃ አሟልተዋል። 86 በመቶ የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም 71 በመቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፍፁም ከደረጃ በተታች ናቸው። በትምህርት ምዘናና ጥናት ውጤት ከ4ተኛ ክፍል 20 በመቶዎቹ…
የትምህርት ማስረጃ ማጣራት . . .

የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለህ/ተ/ም/ቤት የተናገሩት ፦

" በሁሉም #የፌደራል_ተቋማት የሰራተኞችን ማህደር መመርመር ጀምረናል። ምን ያህሉ እውነተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዞ ነው ? ምን ያህሉ አይደለም የሚል ምርመራ እያካሄድን ነው፤ ከራሳችን ጀምረን።

ማህበረሰቡ ልክ እንደፈተናው [የ12ተኛ ክፍል ፈተና] እንዲያውቅልን የምንፈልገው ከአሁን በኋላ በተጭበረበረ ድግሪ፤ በተጭበረበረ ዲፕሎማ የሚሰራ ስራ አይኖርም የሚለውን ለማሳወቅ ነዉ። በዚህ ዓመት እሱን እንጨርሳለን ብለን እናስባለን። "

Credit : #AlAIN

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ

ለግብይትዎ የብርሃን ኤቲኤም ካርድን በመጠቀም ጊዜዎን ይቆጥቡ፤ ድካምዎን ያቅልሉ!

አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !

Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.me/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#MyWishEnterprise

DEVELON (ዲቬሎን) የሚለው አዲሱ የዱሳን ስያሜ የ Develop (“ማደግ”) እና Onward (“ወደፊት”) ቃላቶች ውህድ ሲሆን፤ በኮንስትራክሽን ማሽነሪ ዘርፍ ያሳረፍነዉን ትልቅ አሻራ በማጎልበት በጎ ነገሮችን ይዘን “ወደፊት ለማደግ” ያለንን ምኞት ያንፀባርቃል።

• ከአዲሱ የብራንድ ስያሜ ለዉጥ ውጭ ምንም አይነት ውጫዊ ገፅታም ሆነ ውስጣዊ የማሽኑ አካላት ላይ ለውጥ አልተደረገም።
 
• ኦርጅናል መለዋወጫ፣ አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና እና ተደራሽነት ያለው የጥገና አገልግሎት መለያችን ናቸው።

ማይ ዊሽ ኢንተርፕራይዝ ኃላ/የተ/የግ/ማ ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡ https://t.me/MYWISHENT 
+251-913-356384  +251-912-710661  +251-910-626917  +251-928-414395
+251-911-606068  +251-922-475851  +251-935-409319  +251-911-602664
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል " - ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ ሰጥተዋል። ምን አሉ ? - የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ #በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል። - ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ…
#Update

የግንቦት 2015 ዓ.ም የርክበ ካህናት ጉባኤ ባለ  10 ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።

ዛሬ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥቷል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ምን አለ ?

ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያኗ አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት እና መንፈሳዊ ዕድገት ትኩረት በመስጠት ለቤተ ክርስቲያናን እና ለሀገር ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን ማሳለፉን አሳውቋል።

ከተላለፉ ውሳኔዎች መካከል ፦

- በመላው አገራችን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ካሉ ተቋማት ጋራ የሚሠራ፣ በሀገሪቱ መንግሥትም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የሚኖረው የሰላም ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

- በትግራይ ክልል በሚገኙት አህጉረ ስብከት ተቋርጦ የነበረው መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ግንኙነትን በተመለከተ ቀደም ሲል በቅዱስ ሲኖዶስ ተሠይሞ በሥራ ላይ የሚገኘው ልዑክ የጀመረውን እንቅስቃሴ እንዲቀጥል የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትን በማነጋገር ተልዕኮውን እንዲፈጽም ምልዓተ ጉባኤው መመሪያ ሰጥቷል፡፡

- በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በትግራይ ክልል የሚገኙ ወገኖቻችን ያሉበትን ከፍተኛ ችግር ታሳቢ በማድረግ አስቸኳይ የሆነ ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ #ሃያ_ሚሊየን ብር ድጋፍ እንዲደረግ ተወስኗል።

- በወቅታዊ ችግር ምክንያት በመላው ሀገራችን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን ሁሉ በአጠቃላይ ችግሮቹን በጥናት በመለየት፣ ቤተ ክርስቲያኗ ምእመናን ልጆቿን በማስተባበር ሁለንተናዊ ሰብዓዊ ድጋፍ፣ የማጽናናትና የመጎብኘት መርሐ-ግብሮች እንዲደረጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

- መቐለ የሚገኘው የቅዱስ ፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ የሠራተኞችን ደመወዝና የሥራ ማስኬጃ በጀት እንዲለቀቅና በ2016 በጀት ዓመት ተማሪዎችን በመቀበል መደበኛ የሆነ የመማር ማስተማሩ የሥራ ሂደት እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥቷል፡፡

- በኦሮምያ ክልል በሚገኙ አህጉረ ስብከት ተፈጥሮ በነበረው ወቅታዊ ችግር ምክንያት በአህጉረ ስብከትና በአብያተ ክርስቲያናት አገልግሎት ስለተቋረጠ፣ በርካታ ምእመናንና ካህናት በእስርና እንግልት ላይ ስለሚገኙ በዚሁ መነሻነት ችግሮች እንዲቀረፉና ወደ መደበኛው የአሠራር መዋቅር እንዲመለስ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን በመሠየም ከፌዴራልና ከኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት ጋር በመወያየት ችግሮች እንዲፈቱ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

- የመንፈሳዊ ኮሌጆች መከፈት እና የአብነት ትምህርት ቤቶችን ማጠናከር በተመለከተ በኢሉ አባቦራ የመቱ ፈለገ ሕይወት የነገረ መለኮት መንፈሳዊ ኮሌጅ እንዲከፈት የተፈቀደ ሲሆን በሌሎች አህጉረ ስብከት ሊከፈቱ የታሰቡ ኮሌጆችን እና የአብነት ት/ቤቶችን መሠረታዊ ጥናት ተደርጎ ለ2016 ዓ.ም. የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ መመሪያ ሰጥቷል፡፡  

- ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ ክፍት በሆኑና በተደራቢነት በተያዙ፣ ጉልህና አንገብጋቢ ችግር ባለባቸው በኦሮምያ ክልልና በደቡብ ክልል ባሉ አህጉረ ስብከት ላይ 9 ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስመራጭ ኮሚቴ ሰይሟል፡፡ ወደፊትም ተደርበው በተያዙና አስፈላጊ በሆኑ አህጉረ ስብከት እንደአስፈላጊነቱ በመንበረ ፓትርያርክ ተጠንቶ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia