TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትፈለጋለች

በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ ቡራዩ ክፍለ ከተማ አንዲት እንጀራ እናት ሁለት ልጆችን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደሏ እየተፈለገች መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

ስለጉዳዩ የቡራዩ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምርያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ባልደረባ የሆኑት ዋና ሳጅን ቀነኒሳ ታደሰ ምን አሉ ?

ዋና ሳጅን ቀነኒሳ ታደሰ ፦

" ወንጀሉ የተፈፀመው ቅዳሜ ሚያዝያ 28/2015 ዓ.ም. በከታ ወረዳ ልዩ ስሙ ሦስተኛ ቡራዩ በሚባል ስፍራ ነው።

ወንጀሉ የተፈፀመው ሌሊት ነው። ሁለት ሕጻናት በአሰቃቂ ሁኔታ በእንጀራ እናታቸው ተገድለዋል ተገኝተዋል።

ተጠርጣሪዋ ነጋሴ ከበደ ብሩ የምትባል ስትሆን፣ የባለቤቷን ሁለት ልጆች አንገታቸውን ቀልታ፣ በተኙበት ብርድ ልብስ አልብሳ እሳት ለኩሳባቸው አምልጣለች። "

የልጆቹ አባት የሆኑት አቶ ጌታሁን ባልቻ ምን አሉ ?

በአካባቢው የሚገኝ ቄራ የሚሰሩ ሲሆን ግድያው በተፈፀመበት ዕለት ማምሻውን ከባለቤታቸው ጋር በልጆቻቸው ጉዳይ ተነጋግረው እንደነበር ገልጸዋል።

አቶ ጌታሁን ባልቻ ፦

" በልጆቼ ጉዳይ ተነጋግረን ነበር። በዚህም ምክንያት እንለያይ ተባብለን፤ እርሷም ‘እኔ እሄዳለሁ፣ አንተ እዚህ ትኖራለህ’ አለችኝ።

ምሽት ላይ ስንነጋገር ዛቻም ሆነ ለእንደዚህ አይነት አሰቃቂ ድርጊት ያበቃል ብዬ የምጠረጥረው ጠቋሚ ነገር አላየሁም።

ሌሊት ከዘጠኝ ሰዓት በኋላ ወደ ቤት ስመለስ የቤቱ በር ክፍት ነበር። ወደ ውስጥ ስገባ እሳት ይነዳል። ልጆቼን አልጋ ላይ ሳያቸው ጭሱ አፈነብኝ ብዬ ሮጬ ወደ ውጪ አወጣኋቸው። በወቅቱ ትልቁ ልጄ ተቃጥሏል። ትናሿ ልጄንም አወጣኋት። ወደ ውጪ ካወጣኋቸው በኋላ እነርሱ ላይ ወድቄ ራሴን ሳትኩኝ።

ልጆቼን መጀመሪያ ሳያቸው በሕይወት ያሉ መስሎኝ ነበር ፤ ያሟሟታቸውን ሁኔታ ራሴን ከሳትኩበት አንድ ቀን በኋላ ነው ከአካባቢ ነዋሪዎች እና ከፖሊስ የሰማሁት።

ልጆቼን ማሳደግ እፈልጋለሁ እንለያይ አልኳት. . . እኔ እሄዳለሁ አንተ እዚህ ትኖራለህ አለችኝ። ይህንን ብቻ ነው የተናገረችኝ። እንደዚህ ዓይነት ድርጊት በልጆቼ ላይ፣ ቤተሰቤ ላይ፣ እንስሳትም ላይ ታደርጋለች ብዬ አላሰብኩም። "

በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት የአቶ ጌታሁን ልጆች አንደኛው የ13 ዓመት ወንድ ሲሆን፣ ሌላኛዋ ደግሞ የ4 ዓመት ተኩል ሴት ናቸው።

ሁለቱም አንገታቸው ተቀልቶ ነው የተገደሉት።

አቶ ጌታሁን በ2013 ዓ.ም የልጆቻቸውን እናት በሞት ካጡ በኋላ ባለፈው ታኅሣሥ ነበር ከተጠርጣሪዋ ጋር የተጋቡት።

ሲጋቡም የልጆቻቸውን ሁኔታ ገልፀው፣ ተማምነው ነበር የተጋቡት።

ከዚያ በኋላ እዚያው ቡራዩ አካባቢ " ሽሮ ቤት " ከፍታ ስትሰራ ቆይታለች።

ነዋሪነቷም እዚያው ቡራዩ አካባቢ ኤጀርሳ ጎሮ የሚባል አካባቢ ነው።

ተጠርጣሪዋ እየተፈለገች ነው ...

ፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ የሁለት ህፃናትን ነፍስ ያጠፋችውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ለማዋል እያፈላለጋት ይገኛል።

በቁጥጥር ስር የዋሉ የቤተሰቦቿ አባላትም አሉ።

ከሰበታ እስከ አንቦ ድረስ ከተጠርጣሪዋ ጋር የሚመሳሰሉ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችም አሉ።

መረጃው #የቢቢሲ_አማርኛ እና የቡራዩ ፖሊስ ነው።

@tikvahethiopia
#big5construct

በቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ ላይ በመሳተፍ ታላላቅ የግንባታው ዘርፍ ተቋማትንና ባለሙያዎችን ያግኙ።

ልዩ ልዩ የግንባታው ዘርፍ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና ዘላቂነት ያላቸው መፍትሔዎችን እንዲሁም የወደፊቱን የኢትዮጵያ የግንባታ ዘርፍ አቅጣጫ አብረውን ያቅዱ!

የንግድ እና የግንባታ ፍላጎቶችዎን የሚያሟሉ ከ100 በላይ የሀገር ውስጥ እና ዓለምአቀፍ ተቋማት እና ባለሙያዎችን ለማግኘት ዕድሉን ይጠቀሙበት!

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ገፆቻችንን  ይቀላቀሉ፡ https://t.me/big5ethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

አፖሎን ተጠቅመው ቪዛ ካርድ ሲያዙ በ72 ሰዓት ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማ በተመችዎት ቦታ ካርድዎን እናደርስሎታለን።

መተግበሪያውን ኣውርደው ካርድዎን ይዘዙ።

https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo

#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የተደረገው የዲጅታል የነዳጅ ግብይት ከነገ ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በመላ_ሀገሪቱ ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል።

ነገ በመላው ሀገሪቱ በሚጀምረው የዲጂታል የነዳጅ ግብይት በሁሉም ክልሎች ያሉ ነዳጅ ማደያዎች ቅድመ ዝግጅት ሲያደርጉ ነበር።

የዲጂታል ነዳጅ ግብይት ከነገ ጀምሮ በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ ይሆናል።

እንዴት በዲጂታል መንገድ የነዳጅ ግብይት ማካሄድ ይቻላል ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ አብሯቸው ከሚሰራቸው ኢትዮ ቴሌኮም / ቴሌብር ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ኤግል ላይን ቴክኖሎጂ / ነዳጅ / በኩል የነዳጅ ግብይቱን በተመለከተ ተከታዩን መልዕክት ያስተላልፋል።

#ቴሌብር

- በቴሌ ብር ነዳጅ ለመቅዳት ወደ ነዳጅ ማደያ ስትሄዱ በቅድሚያ ፤ የቴሌብር ሱፐርአፕን ከ onelink.to/75zfa5 በማውረድ ወይም *127# በመደወል የቴሌብር አካውንት በቀላሉ ክፈቱ፤

- ከቴሌብር ጋር በተሳሰሩ 20 ባንኮች ከሚገኝ የባንክ አካውንታችሁ፤ በየነዳጅ ማደያዎቹ በተመደቡ የቴሌብር ወኪሎች ወይም የአገልግሎት ማዕከሎች አማካኝነት ገንዘብ ወደ ቴሌብር አካውንትዎ ማስተላለፍ ይችላሉ፤

- የነዳጅ ማደያ ሠራተኞች ስልክ ቁጥርና የሚከፍሉትን የገንዘብ መጠን ሞልተው ሲጨርሱ በስልክዎ በሚደርስዎ የማረጋገጫ መልዕክት ላይ የገንዘብ መጠኑ ትክክል መሆኑን በማየት የሚስጥር ቁጥር ማስገቢያ ሳጥኑ ውስጥ የሚስጥር ቁጥር (ፒን) በማስገባት ያረጋግጡ፡፡

በመጨረሻም ክፍያው መፈጸሙን የሚያረጋግጥ አጭር መልዕክት የሚደርስዎ ሲሆን ከቴሌብር ሱፐርአፕም ደረሰኝ ማግኘት ይችላሉ፡፡

#ነዳጅ_መተግበሪያ

በነዳጅ ከነገ ጀመሮ በመላ ሐገሪቱ በሚገኙ 1100 በላይ የነዳጅ ማድያዎች ነዳጆን መቅዳት ይችላሉ።

- አንድ ጌዜ በሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ  አካውንቶን Link አርገው የሚጠቀሙበት፤

- በነዳጅ STANDBY( ፈጣን) ፈጣን አግልግሎት የሚያገኙበት ነው።

ከPLAY STORE እና APP STORE አውርደው ፣ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ አካውንትዎ ጋር ያስተሳስሩ ፦

For Android: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj

For iOS:
https://apps.apple.com/us/app/nedaj/id1639807926

#CBE_BIRR

በሲቢኢ ብር ነዳጅ ሲቀዱ ሁለት አማራጮች አሉ።

የመጀመሪያው ፦

ራስዎ ወደ ሲቢኢ ብር መተግበሪያዎ ‘Quick Pay’ በመግባት ‘Fuel Payment’ የሚለውን የአገልግሎት አማራጭ መርጠው አስፈላጊውን መረጃ በማስገባት ክፍያ ፈጽመው ነዳጅ የሚቀዱበት ነው፡፡

ሁለተኛው ፦

ለነዳጅ ቀጂ ባለሙያው ሲቢኢ ብር የተመዘገቡበትን ስልክ ቁጥር ߹ የሰሌዳ ቁጥርዎን እና የሚቀዱትን ነዳጅ የገንዘብ መጠን አሳውቀው በሚደርስዎት አጭር መልእክት መሠረት የገንዘብ መጠኑን ትክክለኛነት አረጋግጠው ክፍያውን በመፈፀም ነዳጅ የሚቀዱበት አማራጭ ነው።

የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለመጫን ወይም ለማዘመን ፦

ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

ለአፕል ስልኮች ፦
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፤ " የጋፋት የህዋ ምህንድስ እና ልማት ማዕከል " ከ20 ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ መጓዝ የሚችል ሮኬት አስወንጭፏል።

ዩኒቨርሲቲው " አፄ ቴዎድሮስ 2015 " የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሮኬት ከ20 ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ በማስወንጨፍ ስኬታማ ሙከራ ማድረጉን አሳውቋል።

" የጋፋት የህዋ ምህንድስና ልማት ማዕከል " ከዚህ ቀደምም ተመሳሳይ ሙክራ ያደረገ ሲሆን ይኸኛው ሙከራ ግን ከዚህ በፊት ከተደረጉ ሙከራዎች የተሻለ ምርምር የተደረገበት መሆኑን አሳውቋል።

ቪድዮ ፦ አሚኮ

#ደብረታቦር_ዩኒቨርሲቲ #አፄቴዎድሮስ2015

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USEmbassyAA

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ለDV (ዲቪ) መመረጥ ለቪዛ ወይም ለቃለ መጠይቅ ዋስትና እንደማይሰጥ አስገንዝቧል።

ካለፈው ቅዳሜ ምሽት አንስቶ የ2024 የDV ተመራጮች የታወቁ ሲሆን ለዚህ ዕድል ያመለከቱ በድረገፅ ow.ly/rJuC50OhWuz ላይ በመግባት የማረጋገጫ ቁጥር በማስገባት መመረጥ አለመመረጣቸውን ማወቅ ይችላሉ።

ይህ ብቸኛው የማወቂያው መንገድ መሆኑን ኤምባሲው ገልጿል።

በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ፥ የዲቪ (DV) ተመራጭ መሆን ለቪዛ ወይም ለቃለመጠይቅ ዋስትና እንደማይሆን አስገንዝቧል።

እንደ ኤምባሲው ማብራሪያ ፤ የዲቪ (DV) ሎተሪ ተመራጭ መሆን የቪዛ ጥያቄ ለማቅረብ የመጀመሪያው መስፈርት ሲሆን በቀጥታ ለቪዛ ወይም ለቃለመጠይቅ ዋስትና አይሰጥም።

@tikvahethiopia
#big5construct

በዐዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ዕውቅ መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት አቶ አየነው ይሁኔ በዌብ ላይ የተመሠረተ ሲስተም በመጠቀም የጂኦቴክኒካል መረጃ አስተዳደርን እንዴት ማከናወን እንደሚቻል በጥናት ላይ የተመሠረተ እጅግ ጠቃሚ ንግግር ያደርጋሉ።

ይህ፣ የጂኦቴክኒካል መረጃ አስተዳደር ሂደቶቻቸውን ለማመቻቸት ለሚፈልጉ የግንባታው ዘርፍ ባለሙያዎች ሁሉ እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ በተሳታፊነት ለመመዝገብ እና የሲፒዲ ነጥቦችን ለማግኘት (መስፈንጠሪያውን በመከተል) ይመዝገቡ https://bit.ly/3oI8P6L

የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል መስፈንጠሪያውን ይከተሉ: https://t.me/big5ethiopia
#ነዳጅ

የነዳጅ ግብይት #በመላው_ሀገሪቱ  በ " ዲጅታል " መንገድ ብቻ እንዲሆን በተላለፈው ውሳኔ መሰረት ዛሬ ግንቦት 1/2015 ተግባራዊ መሆን ጀምሯል።

በክልሎች የነዳጅ ጉዳይ ከተነሳ አይቀር ...

በክልል ከተሞች ላይ #ነዳጅ በተለይም ቤንዚን እንደልብ ማግኘት የማይታሰብ ነው። ነዳጅ ሲገኝም ለሰዓታት ረጃጅም ሰልፍ መሳለፍ እና መንገላታት አይቀሬ ነው።

እንደ #ሀዋሳ ያሉ ትልቅ ከተሞች ውስጥ ነዳጅ በወረፋ ብቻ ሳይሆን በሳምንት ለተወሰነ ቀን ብቻ ነው መቅዳት የሚቻለው (ለከተማው ነዋሪ - በኩፖን) ። ይህም የሚከናወነው በታርጋ " #ሙሉ እና #ጎዶሎ ቁጥር " ነው የሚከናወነው። ማደያዎችም ከተመደበላቸው ተሽከርካሪ ውጭ ማስተናገድ አይችሉም።

" እንግዳ ነኝ ፤ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ አይደለሁም " ለሚሉት ደግሞ የነዳጅ ማደያዎች የሚኖሩበትን ከተማ የነዋሪ #መታወቂያ በማየት እንደሚቀዱ ለመረዳት ተችሏል።

ከምንም በላይ የሚገርመው እጅግ በርካታ ማደያዎች ባሉበትና አሁንም እየተሰሩባት ባለው ከኢትዮጵያ ግዙፍ ከተሞች አንዷ ሀዋሳ በየዕለቱ ነዳጅ የሚሸጡት እጅግ ውስን ቁጥር ያላቸው ማደያዎች ናቸው።

ይህ በእንዲህ እያለ ግን በከተማው ነዳጅ በጥቁር ገበያ ከፍ ባለ ብር እንደጉድ ነው የሚቸበቸበው። ሀዋሳ ብቻ ሳይሆን በሀዋሳ ዙሪያ ጭምር ነው ይህ የሚሆነው።

የከተማው የአስተዳደር አካላት ይህንን እያወቁ መፍትሄ እየሰጡ እንዳልሆነ ከተገልጋዮች ቅሬታ ይቀርባል።

እጅግ በጣም ብዙ ተሽከርካሪዎች በሌሉበት እና በርካታ ማደያዎች ባሉበት ከተማ ነዳጅ ለማግኘት በዚህ ደረጃ መቸገር ከምን የመጣ ነው ?

ከሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ ስላለው የነዳጅ ግብይት ጉዳይ የሲዳማ ክልል ንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በድሶ አዲሳ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

አቶ በድሶ አዲሳ  ፦

" ችግሩ አለ ፤ ይህ የሆነው በቀን ከ3 ሚሊዮን ሊትር የማይበልጥ ቤንዚን ስለሚቀርብ በአገር ደረጃ የቤንዚን እጥረት በመኖሩ ነው።

ለዚህም ሲባል ተሸከርካሪዎችን በየቀኑ በተለያዩ የነዳጅ ማደያ ጣቢያዎች መድበን ነው እንዲቀዱ የምናደርገው።

ችግሩ ያለው ቤንዚን ላይ ነው የነዳጅ ማደያዎችም ቤንዚን ለማግኘት አንድ ወር ይጠብቃሉ።

ነዳጅ በጥቁር ገበያ ሀዋሳ ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባም ይሸጣል ፤ ለዚህ ተብሎ ከሌላ ቦታ የሚገባ ነዳጅ አለ።

እንደዚህ ዓይነት ተግባር የሚፈጽሙ የተወሰኑ ማደያዎች መኖራቸው ታውቆም እርምጃ የተወሰደባቸው አሉ።

ግብይቱ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት ሲሆን ችግሩ ይቀረፋል። "

ነዳጅ ለማግኘት የመቸገር ጉዳይ በሀዋሳ ብቻ ሳይሆን በጎረቤት ሻሸመኔ፣ በሌሎችም ከተሞች ያለ ጉዳይ ነው።

እንደ ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን መረጃ ከሆነ " በሀገር ውስጥ በቂ የሆነ የነዳጅ አቅርቦት አለ " ነገር ግን በክልል ከተሞች ያለው ነዳጅ ለማግኘት የመቸገር ጉዳይና የጥቁር ገበያው ነገር መፍትሄ የሚያሻው ነው።

@tikvah_eth_BOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከቀናት በፊት የብልፅግና ፓርቲ የወረዳ አመራር በተገደሉበት ወቅት #ወንድማቸውን ጨምሮ ሌሎችም የመኪና አሽከርካሪዎች መገደላቸውን አንድ ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ የሰጡ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ተናግረዋል።

ከቀናት በፊት ከአዳማ ወደ አዋሽ በሚወስደው መንገድ ላይ በተከፈተ ተኩስ በአፋር ክልል በገቢ ረሱ የሓንሩካ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡመር ለማ መገደላቸውን የአፋር ክልል የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ማሳወቁ ይታወሳል።

ቃላቸውን የሰጡት የከባድ መኪና አሽከርካሪው፥ ጥቃቱ ወለንጪቱ አካባቢ መሰንዘሩን አመልክተው አቶ ዑመር ለማን ጨምሮ 7 ሰዎች ናቸው የተገደሉት ብለዋል።

" አሽከርካሪዎች ሰላማዊ መንገድ ነው ብለው በሰላም እየተጓዙ እያለ በአጋጣሚ በወለንጪቲ እንደውም ከድሮው የዘረፋ ቦታ በተለየ መልኩ በጣም ለወለንጪቲ ቅርብ ከ5 ኪ/ሜ ባልበለጠ ርቀት ውስጥ መጥተው ነው ዘረፋውንም አካሂደው አሽከርካሪዎችን ገድለው እንዳለ የነበረ ንብረት ዘርፈው የሄዱት።

ሰባት አካባቢ የሞቱ አሉ ከዛ መካከል በአጋጣሚ የአፋር ክልል የብልፅግና የወረዳ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑ ገለሰብ ከነወንድማቸው ተገድለዋል፤ 5ቱ አሽከርካሪዎች ናቸው። የሞቱ አሽከርካሪዎች ቢያንስ የዜና ሽፋን አላገኙም፤ የተረፉ አሽከርካሪዎችም አሉ።

ጥቃቱ በተለያዩ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው የተሰነዘረው አይሱዙ አለ፣ ሱኖትራክ ተሳቢ የሌላቸው አሉ፣ የቤት መኪኖች አሉ፣ ፒካፕ፣ ቦቴ አለ እንደውም ቦቴው በጥይት ተመቶ ነዳጅ ሲፈስ ነበር "

ከዚሁ ጥቃት ጋር በተያያዘ የገቢ ረሱ ዞን 3 ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃሰን ዲን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ማብራሪያ አቶ ኡመር ለማ አባታቸውን አዲስ አበባ አሳክመው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ መገደላቸውን ገልጸዋል።

ጥቃቱ ምሽት ላይ መፈፀሙን ያስታወሱት አቶ ሃሰን ወለንጪቲ አካባቢ ባልታወቁት ታጣቂዎች በተከፈተው ተኩስ ነው አቶ ዑመር የተገደሉት ብለዋል።

እንደ ኃላፊው ገለፃ፥ የአቶ ዑመር ወንድም መሐመድ ለማ አብረው ሲገደሉ መኪና ውስጥ የነበሩት አባታቸውን ጨምሮ ሌላ ወንድማቸውን (ዓሊ ለማ) ጨምሮ ተርፈዋል።

" እዛ አካባቢ ያለውን ሰላም መጠበቅ እንዳለብንና መስራት እንዳለብን ነው የሚያሳወው " ያሉት አቶ ሃሰን " የኦሮምያ አመራሮችም አከባቢዎችን ቅኝት በማድረግ ዜጎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ የማድረግ ሁኔታን መፍጠር ይገባል በዚህ ላይ ተባብረን መስራት አለብን " ብለዋል።

ከጥቃቱ የተረፉት የአቶ ዑመር ወንድም ዓሊ ለማ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ ጥቃት ያደረሱት 30 የሚጠጉ የቀድሞውን የመከላከያ ልብስ የሚመስል ዩኒፎርም የለበሱ ታጣቂዎች ናቸው ብለዋል።

አቶ ዑመር ለማ ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበሩ፤ የአቶ ዑመር እንዲሁም የወንድማቸው ስርዓተ ቀብር በአዋሽ ተፈፅሟል።

ጥቃት በተፈፀመበት የአዳማ - አዋሽ ቀጠና እጅግ የለየለት የወንጀል ተግባር በታጠቁ አካላት እንደሚፈፀም ሲገለፅ እንደነበር ይታወሳል።

በዚሁ መስመር ታጣቂዎች እንደሚንቀሳቀሱና ከተማዎች ውስጥ በመግባት ጭምር ሰላማዊ ሰዎችን መግደል፣ በየመንገዱ ሰላማዊ ሰዎችን እያገቱ ከፍተኛ ገንዘብ የመጠየቅ፤ በአጠቃላይ በቀጠናው ወጥቶ ለመግባት ከፍተኛ ስጋት የመፍጠር እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ሲገለፅ ቆይቷል።

በሌላ በኩል፤ በዛው በኦሮሚያ ባለፈው ሳምንት ሚያዚያ 26 ምሽት ከአዲስ አበባ ወደ ባቱ - ሀዋሳ በሚወስደው ፈጣን መንገድ ላይ በዓለምጤና እና ቆቃ መሀል ዝርፊያ እና የመኪና ማቃጠል ተግባር መፈፀሙን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም በዚሁ መስመር ግድያን ጨምሮ የንብረት ዘረፋ ፣ መኪና ማቃጠል መፈፀሙ የሚዘናጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
#EthioTelecom

ከዛሬ ጀምሮ በሃገራችን ሁሉም አካባቢዎች የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ብቻ የሚፈጸም በመሆኑ ለተግባራዊነቱ በሁሉም የነዳጅ ማደያዎች በቂ ዝግጅት ማድረጋችንን እየገለጽን፤

ውድ ደንበኞቻችን ነዳጅ ለመቅዳት ወደ ነዳጅ ማደያ ከማምራታችሁ በፊት በቅድሚያ የበኩላችሁን ቅድመ-ዝግጅት እንድታደርጉ ለማስታወስ እንወዳለን

⛽️ የቴሌብር አገልግሎት ተጠቃሚ ካልሆኑ ቴሌብር ሱፐርአፕን ከ onelink.to/75zfa5 በማውረድ ወይም *127# በመደወል ይመዝገቡ

⛽️ ከቴሌብር ጋር ከተሳሰሩ 20 ባንኮች በሞባይል ባንኪንግ፣ በቴሌብር ወኪሎች እና በኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች ነዳጅ ለመቅዳት የሚያስፈልግዎን ገንዘብ ወደ ቴሌብር ሂሳብዎ ያስተላልፉ

⛽️ ለተጨማሪ ድጋፍ ወደ 127 ይደውሉ ወይም በጽሁፍ ወደ 126 ወይም የቴሌብር ማህበራዊ ገጾቻችን ጥያቄዎን ይላኩ

ማስታወሻ: የነዳጅ ክፍያዎን በቴሌብር ሲፈጽሙ ምንም አይነት ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ አይጠየቁም

ለተጨማሪ መረጃ bit.ly/3V3wjPF
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የሚሰጥባቸውን ቀናት ይፋ አደርጓል።

የ8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀ ዲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ ከከተማና ክፍለ ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን የሞዴል ፈተናዎችን እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በ2015 ዓ.ም 75,100 የ8ኛ እንዲሁም 75,078 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተናውን ይወስዳሉ።

@tikvahethiopia
#EOTC

የቅዱስ ሲኖዶስ የግንቦት የርክበ ካህናትጉባኤ ነገ ግንቦት 2 ቀን 2015  ዓ/ም ይከፈታል።

በአሁን ሰዓት የግንቦት 2015 ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ሥነሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመካሔድ ላይ ነው።

ፎቶ ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

@tikvahethiopia