TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ባህርዳር

የባህር ዳር ከተማ የእስልምና ምዕመናን የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው የመስገጃ ቦታ ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱ ተሰማ።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ለእስልምና እምነት ተከታዮች ለመስገጃ የሚሆን 20 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ መሰጠቱን ዛሬ አስታውቋል።

የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ዛሬ የኢድ አልፈጥር በዓል በባህር ዳር ስታዲየም በሚከበርበት ወቅት ነው ይህንን የምስራች ለምዕመኑ ያበሰሩት።

ዶ/ር ድረስ ሳህሉ ምን አሉ ?

" ለብዙ ጊዜ ስትጠይቁት የነበረ የመስገጃ ቦታ አሁን በክልልም ፀድቆ የመጣ ስለሆነ ምናልባትም በሚቀጥለው ዓመት በደንብ ሰርታችሁት እዚህ ሳይሆን እዛው ከተፈቀደላችሁ ቦታ ላይ የምታከብሩት ይሆናል።

ክልሉ ያቀረባችሁትን ጥያቄ እኛ አፅድቀን ልከን ክልሉም ተቀብሎት 20 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ የኢድ አልፈጥር በዓል የምናከብርበት ቦታ ተፈቅዷል። "

ከንቲባው ይህንን ንግግራቸውን ሲያደርጉ የባህር ዳር ከተማ ሙስሊም ምእመን እጅግ በደስታ ስሜት " አላሁ አክበር ! አላሁ አክበር ! አላሁ አክበር ! " እያለ ድምፁን አሰምቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update RSF የግብፅ ወታደሮችን ለቀይ መስቀል አስረከበ። የሱዳን ጦርነት በጀመረበት ወቅት በጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደጋሎ የሚመራው የሱዳን ፋጥኖ ደራሽ (RSF) ኃይል እንደማረካቸው የገለፃቸውን የግብፅ ወታደሮችን ዛሬ ጥዋት ለዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ማስረከቡን አሳውቋል። RSF ለቀይ መስቀል ያስረከባቸው የግብፅ ወታደሮች በማራዊ ጦር ሰፈር የነበሩና ላለፉት 5 ቀናት ይዞ ያቆያቸው ናቸው…
#ሱዳን

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል / RSF የ72 ሰዓታት ተኩስ አቁም ማድረጉን አውጇል።

ይህን ያደረገው የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ እና ዜጎች ከግጭት ቀጠና እንዲወጡ የሰብዓዊ ኮሪደር ለማመቻቸት በተጨማሪም ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል።

ምንም እንኳን RSF ይህን ቢልም በሱዳን በተለይም በካርቱም በዛሬው የዒድ አልፈጥር በዓል ዕለት ግጭት መቀጠሉ ፣ ከተማዋ በከባባድ መሳሪያዎች ድምፅ እየተናወጠች ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

RSF የሱዳንን ጦር በአስከፊ ጥቃቶችን እየፈፀመ ነው በሚል ከሷል።

ከሱዳን ጦር በኩል በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተኩስ አቁም ለማድረግ ሃሳብ ይኖር እንደሆነ የታወቀ ነገር እንደሌለ አልጀዚራ ዘግቧል።

ባለፉት ቀናት ለሁለት ጊዜ ተኩስ አቁም ለማድረግ ተሞክሮ ምንም አልተሳካም።

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በከተሞች ውስጥ እየተደረገ በመሆኑ በርካቶች ከቤታቸው ለመንቀሳቀስ ተቸግረዋል።

@tikvahethiopia
#Update

አሜሪካ አንድ ዜጋዋ ሱዳን ውስጥ መገደሉን አስታወቀች።

አንድ የአሜሪካ ዜጋ ሱዳን ውስጥ እየተካሄደ ባለው ውጊያ መገደሉ ተሰምቷል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለፎክስ ኒውስ በሰጠው ቃል ፤ በሱዳን አንድ አሜሪካዊ ዜጋ መሞቱን አረጋግጧል።

መስሪያ ቤቱ ፤ ከሟች ቤተሰብ ጋር እየተገናኘ መሆኑንና በደረሰባቸው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን መግለፁን አመልክቷል።

" በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ለቤተሰብ ካለን አክብሮት የተነሳ ምንም የምንጨምረው ነገር የለም " ሲልም ስለ ሟች ዝርዝር መረጃ ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል።

በሌላ በኩል ፤ የአሜሪካ መከላከያ ጦር በአፍሪካ ኮማንድ በኩል በሱዳን ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ መሆኑን አሳውቋል።

የአሜሪካ ጦር ፤ በካርቱም የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲ ሰራተኞችን እና ዜጎችን ለማስወጣት የሚያስችለውን ተልዕኮ ለመፈፀም ተጨማሪ ኃይሎቹን ጅቡቲ ለማስቀመጥ ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ተሰምቷል።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስቀጠል በዝግጅት ላይ እንደሆነ ገልጿል።

በመሆኑም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ #የማይገኙ ሁሉም የዲግሪ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን፣ ክረምት) እንዲሁም የማስተርስ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን ፣ ክረምት) ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

ሊንክ ፦ http://196.190.28.50

ምዝገባው የሚያበቃበት ቀን ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ/ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ ዘውትር በየስራ ሰአት በሚከተሉት ቁጥሮች መወደወል ይቻላል ፦ 0914485592 / 0921990158

ከኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ #የራያ_ዩኒቨርሲቲም በጦርነት የተቋረጠውን መደበኛ ትምህርት ለማስቀጠል እየሰራ ይገኛል።

በዚህም ከ2ኛ እስከ 5ኛ ዓመት በራያ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የመማር እድል ያላገኙ ተማሪዎች ከ09/08/2015 ዓ/ም እስከ 13/08/2015 ዓ/ም ባሉ የስራ ቀናት እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

ተማሪዎች የሚመዘገቡት ለዩኒቨርስቲው ረጅስትራር እየደሉ ሲሆን የስልክ ቁጥሮቹ 0970140000፣ 0970240000 ፣ 0970230000 ናቸው። ተማሪዎች ዘውትር በስራ ሰዓት ብቻ እንዲደውሉ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሱዳን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል / RSF የ72 ሰዓታት ተኩስ አቁም ማድረጉን አውጇል። ይህን ያደረገው የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ እና ዜጎች ከግጭት ቀጠና እንዲወጡ የሰብዓዊ ኮሪደር ለማመቻቸት በተጨማሪም ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል። ምንም እንኳን RSF ይህን ቢልም በሱዳን በተለይም በካርቱም በዛሬው የዒድ አልፈጥር በዓል ዕለት ግጭት መቀጠሉ ፣ ከተማዋ…
#Update

የሱዳን ጦር በ72 ሰዓታቱ የተኩስ አቁም ተስማማ።

ጦሩ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀን ድረስ ዜጎች የኢድ አልፈጥር በዓልን እንዲያከብሩ፣ እና ለሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት መሳለጥ ሲባል የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማቱን ዛሬ ማምሻውን አሳውቋል።

በጄነራል ቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር " አማፂያን " ሲል የጠራቸው የRSF ኃይሎች የተኩስ አቁሙን እንዲያከብሩና ይህንን የሚያደናቅፉ ማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን እንደሚያቆሙ ተስፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

RSF ዛሬ ጥዋት ለዒድ አልፈጥር በዓል የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ማወጁ እና የሱዳን ጦር ሃሳብ ምን እንደሆነ እንዳልታወቀ መነገሩ ይታወቃል።

ምንም እንኳን የተኩስ አቁም እወጃዎች ቢኖሩም ሱዳን፣ በተለይ ካርቱም ዛሬ በውጊያ ስትናጥ ነበር የዋለችው።

@tikvahethiopia
#ትዊተር

ለጥንቃቄ ...

የትዊተርን አዲስ አሰራር ተከትሎ የበርካታ ታዋቂ ሰዎች እና ተቋማት #የማረጋገጫ_ምልክት ከትላንት ጀምሮ ተነስቷል።

ታዋቂው ቱጃር ኤሎን መስክ በ44 ቢሊዮን ዶላር ትዊተርን ከገዛው በኋላ በመተግሪያው ላይ የመጡ ለውጦች በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ እየሆኑ ይገኛል።

ከዚህም ውስጥ አንዱ ትዊተር ታዋቂ ግለሰቦች የሚሰጠውን የማረጋገጫ መልክት (Twitter verification) በክፍያ መጀመሩ ዋነኛው ነው።

ለግለሰብ በወር 8 ዶላር ለድርጅት ደግሞ 1000 ዶላር ማስከፈል የጀመረው መተግበሪያው ከትላንት ጀምሮ ክፍያ ያልፈጸሙ ያላቸውን አካውንቶች የማረጋገጫ ምልክታቸውን አንስቷል።

የማረጋገጫ ምልክታቸው የተነሳው በሀገራችን ጨምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ ታዋቂ ሰዎች ፣ የሚዲያ ተቋማት ፣ ትልልቅ የመንግስት እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ መስሪያ ቤቶች ነው።

በርካቶች ይሄንን ውሳኔ  በተመሳሳይ ስም የሚከፈቱ " የማረጋገጫ ምልክት " የሚኖራቸው አካውንቶች እንዲኖሩ እድሉን ይከፍታል በሚል የተቃወሙት ቢሆንም ውሳኔው ግን ተግባራዊ ተደርጓል።

ይህም ሀሰተኛ መረጃን ያባብሳል ተብሎ ተሰግቷል።

በተለይ አሁን ላይ የማረጋገጫ ምልክቱን በቀላሉ ማግኘት መቻሉ ለአጭበርባሪዎች (Scammers) በር በመክፈት በርካቶችን ሊጎዳ ይችላል።

የገጾችን ትክክለኛነት ለማሳየት የምንጠቀምበት ይህ የማረጋገጫ ምልክት ከዚህ በኋላ ለማረጋገጫነት ብዙም ጥቅም የሚኖረው አይመስልም።

የገጹ ተከታይ ብዛት እንደ ማረጋገጫ መውሰድ ብንችልም እንደ ሀገራችን የሀሰተኛው ገጽ ተከታይ ቁጥር ከትክክለኛው በሚበልጥበት ሁኔታ የገጹን ትክክለኛነት ለማረጋገጥም አዳጋች ያደርገዋል።

ከዚሁ ከትዊተር ማረጋገጫ ምልክት መነሳት ጋር በተያያዘ ጦርነት ውስጥ ባለችው ሱዳን የሆነ አንድ ጉዳይን እናጋራችሁ።

በጀኔራል መሐመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሄሜቲ) የሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ (RSF) የትዊተር አካውንት ያለው ሲሆን አካውንቱም 82.7K ተከታይ እና የሰማያዊ ማረጋገጫ ምልክት ነበረው።

ትዊተር ትላንት ይህንን የማረጋገጫ ምልክት ባነሳበት ሰዓታት ውስጥ የሰማያዊ ምልክት #የገዛ በተመሳሳይ በRSF ስም የተከፈተ 26 ሺ ተከታዮች ያሉት ገፅ ጄነራል መሀመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሄሜቲ) በጦርነቱ ላይ #እንደተሞቱ አድርጎ አንድ ፅሁፍ አስራጭቷል።

የዚህን የማረጋገጫ ምልክት ከትዊተር የገዛ ገፅ ያወጣውን ሀሰተኛ ፅሁፍ 1.7 ሚሊዮን ሰዎች አይተውታል ፤ ይህን ሀሰተኛ ፅሁፍ ያመኑም አልጠፉም።

ውድ ቤተሰቦቻችን በትዊተር አዲስ አሰራር ሁሉም ሰው ሰማያዊ የማረጋገጫ ምልክት እየገዛ በመሆኑ የሰማያዊ ምልክት ያላቸው አካላት ናቸው የሚያሰራጩት በማለት ሁሉንም የምታዩትን መረጃዎች አትመኑ፤ መረጃዎችን መርምሩ፣ አጣሩ። እናመሰግናለን !!

#TikvahFamily

@tikvahethiopia @tikvahethmagazine
#ምርጥ_ዕቃ

እርስዎን የሚመጥኑ ምርጥ የቤት ውስጥ መገልገያ ዕቃዎችን መግዛት ሲፈልጉ እኛ ጋር ይምጡ።

አድራሻ ፦ መገናኛ ዘፍመሽ ግራንድ ሞል 3ተኛ ፎቅ ከሊፍት ሲወርዱ ወደ ቀኝ ታጥፈው ቁጥር ፦ 376

ለበለጠ መረጃ፦ t.me/MerttEka / 0944-22-23-24
#MyWishEnterprise

DEVELON (ዲቬሎን) የሚለው አዲሱ የዶሳን ስያሜ የ Develop (“ማደግ”) እና Onward (“ወደፊት”) ቃላቶች ውህድ ሲሆን፤ በኮንስትራክሽን ማሽነሪ ዘርፍ ያሳረፍነዉን ትልቅ አሻራ በማጎልበት በጎ ነገሮችን ይዘን “ወደፊት ለማደግ” ያለንን ምኞት ያንፀባርቃል።

• ከአዲሱ የብራንድ ስያሜ ለዉጥ ውጭ ምንም አይነት ውጫዊ ገፅታም ሆነ ውስጣዊ የማሽኑ አካላት ላይ ለውጥ አልተደረገም።
 
• ኦርጅናል መለዋወጫ፣ አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና እና ተደራሽነት ያለው የጥገና አገልግሎት መለያችን ናቸው።

ማይ ዊሽ ኢንተርፕራይዝ ኃላ/የተ/የግ/ማ https://t.me/MYWISHENT
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የመታሰቢያ መርሃ ግብር ...

እሁድ ሚያዚያ 1 በቆቦ አካባቢ በተከሰተው ግጭት በሥራ ላይ ህይወታቸውን ላጡ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሁለት የሥራ ባልደረቦች የመታሰቢያ መርሃግብር ተካሄደ።

በግጭቱ ህይወታቸው ያለፉት አቶ ቾውል ቶንጎይክ እና አቶ አማረ ክንደያ ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ በሚጓዙበት ወቅት በመከላከያ ሰራዊት እና በአማራ ክልል ልዩ ኃይል መካከል በነበረ #የተኩስ_ልውውጥ ተመተው ህይወታቸው ማለፉን የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስታውሳለች።

አደጋው በተፈጠረበት ወቅት ቆቦ የሚገኙ የካፑቺን አባቶች በቦታው በመድረስ የሟቾቹን አስከሬን ወደቤታቸው በመውሰድ እና በማዘጋጀት ወደቤተሰቦቻቸው እንዲላክ ማድረጋቸውን ከቤተክርስቲያኗ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት ሚያዝያ 1 ቀን /2015 ዓ/ም ባስተላለፉት መልዕክት " ይህ ግጭት፣ ሰቆቃ፣ ስደት እና የእርስ በእርስ ጦርነት ሊቆም ይገባል። ችግሮችንም ሰከን ባለ መልኩ በውይይት ብቻ ልንፈታ ይገባል። ባለፉትም የነበሩትን ግጭቶች እና ጦርነቶች የፈታናቸው በውይይት ነው " ብለዋል። 

ብፁዕ ካርዲናል ለሟች ቤተሰቦች ሁሉ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ተመኝተው ለሞቱት ነፍሳቸውን በአብርሃም በይሳቅ በያዕቆብ አጠገብ እንዲያኖር ጸሎታቸውን አቅርበዋል።

ሚያዝያ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የካቶሊክ ተራዕዶ ድርጅት አቶ ቾውል እና አቶ አማረ  የመታሰቢያ መርሃግብር አዲስ አበባ በሚገኘው ጽ/ቤቱ ያካሄደ ሲሆን በዕለቱም የሟቾቹ ቤተሰቦች በተገኙበት የመታሰቢያ ጸሎት በብጹዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን መሪነት ተካሂዷል።

በተጨማሪም ድርጅት ከ4 አመት በፊት የኢትዮጵያ አየር መንገድ መከስከት ምክንያት ህይወታቸውን ያጡትን አራቱን ሠራተኞቹን በማስታወስ ጸሎት ተደርጓል።

ምንጭ፦ የአትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን

@tikvahethiopia
ወደ ትግራይ የየብስ ጉዞ ተጀመረ።

" ሰላም ባስ " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ / ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ሲሰጠው የነበረውና በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የትራንስፓርት አገልግሎት ጀምሯል።

ከሁለት ዓመታት በኋላ የሰላም ባስ የመንገድ ትራንስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ ጉዞ አድርጓል።

ከዚህ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት 51 ተጓዞችን በመያዝ ወደ አዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት ጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።

ድምፂ ወያነ ፤ አገልግሎት መጀመሩን ተከትሎ ትኬት ሲቆርጡ አገኘኃቸው ያላቸው ደንበኞች ፥ ወደ አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት በመጀመሩ ደስተኞች መሆናቸውን በመግለፅ ወደ ሌሎች አጎራባች ክልልሎችም ተመሳሳይ አገልግሎት ቢጀመር ሰላሙን ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ " ሰላም ባስ " የትራንስፖርት አገልግሎት ባገኘው መረጃ በየቀኑ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ እና ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ የተጀመረ ሲሆን ጉዞው የሚደረገው #በአፋር በኩል ነው።

ፎቶ፦ ሰላም ባስ / ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia