TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ ፦ የፌዴራል መንግስት እና ህወሃት በስምምነቱ መሰረት የከባድ መሳሪያዎችን  መረካከብ ጀምረዋል።

በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል በደቡብ አፍሪካ እና በኬኒያ የተደረሰዉን ስምምነት ተከትሎ በትላንትናዉ ዕለት የመጀመሪያ ዙር ከባድ መሳሪያ ርክክብ መደረጉ ተገልጿል።

ርክክቡ ከመቐለ ከተማ 36 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አጉላ ካምፕ የተከናወነ ሲሆን በርክክቡ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ ታዛቢዎች ተገኝተው እንደነበር ተገልጿል።

በቀጠናው የተሰማራው የሰራዊት አመራር ሌተናል ኮሎኔል አለሜ ታደለ ፤ " በመንግስታችንና በህዋሃት አመራሮች መካከል በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት የተለያዩ ዓይነት ከባድ መሳሪያዎችን ተረክበናል " ብለዋል።

ህወሃት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያስረከባቸዉ የመሳሪያ ዓይነቶች፦

-  ብረት ለበስ ታንኮች፤
- የተለያዩ ሚሊ ሜትር መድፎች፤
- ሮኬቶች፤
- ዙዎች፤
- ሞርተሮች እና ፐምፐን ያጠቃለለ መሆኑን ሌተናል ኮሎኔል አለሜ ታደለ ተናግረዋል፡፡

የርክክብ ስነ-ስርዓቱን ለመታዘብ የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ አረካካቢ ኮሚቴዎች የተገኙ ሲሆን ከአረካካቢዎች መካከል ብርጋዴር ጄኔራል አድዋ ልቡካን ፒተር በሁለቱም ወገኖች በኩል እየተደረገ ያለዉ የከባድ መሳሪያ ርክክብ የተጀመረዉን የሰላም ጉዞ የሚያጠናክር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

" በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐፕሊክ መንግስትና በህወሃት  መካከል የተደረሰው ሰላምን የማስፈን ተግባር ዓለምን የሚስደንቅ ስለሆነ ለመላው ህዝብና ስምምነቱን ተግባራዊ እያደረጉ ላሉ አካላት ምስጋናዬን አቀርባለሁ " ብለዋል፡፡

Credit : የሀገር መከላከያ ሰራዊት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የፌዴራል መንግስት እና ህወሃት በስምምነቱ መሰረት የከባድ መሳሪያዎችን  መረካከብ ጀምረዋል። በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል በደቡብ አፍሪካ እና በኬኒያ የተደረሰዉን ስምምነት ተከትሎ በትላንትናዉ ዕለት የመጀመሪያ ዙር ከባድ መሳሪያ ርክክብ መደረጉ ተገልጿል። ርክክቡ ከመቐለ ከተማ 36 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አጉላ ካምፕ የተከናወነ ሲሆን በርክክቡ የተለያዩ ሀገራት…
ስለ ከባድ መሳሪያ ርክክብ ማን ምን አለ ?

የትግራይ ኃይሎች ተወካይ የሆኑት ሙልጌታ ገብረክርስቶስ ፦

"  በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት መሬት ላይ ወርዶ ተፈፃሚ ሊሆን የሚገባው ትጥቅ የመፍታት ሂደት በይፋ ተጀምሯል።

በዓጉላ ተከማችቶ የነበረውን የከባድ መሳሪያ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ተግባራዊ አድርገነዋል።

ሰላማዊ የሆነ የርክክብ እና የመተጋጋዝ ሂደት ነበር። ወደፊትም ይሄ ትጥቅ የመፍታት ሂደት በሌሎችም ካምፖች ተጠናክሮ ይቀጥላል። "

የሀገር መከላከያ ተወካይ ኮሎኔል አለሜ ታደለ ፦

" የተለያዩ ሀገራት ሳይሆን አንዲት ኢትዮጵያ ነን። ከዚህ በመነሳት ሁለቱም የታጠቀው ኃይል የጋራ ስምምነት አድርጎ ትጥቆች መፈታት አለበት ብሎ በውሉ መሰረት በተግባባነው መሰረት እኛም ካለንበት የመከላከል ቀጠና ፤ ቲዲኤፍም (TDF) ምሽግ ከያዘበት በሰላም ፣ በመግባባት፣  በፍቅር ወደ ዓጉላ መጥተናል።

በዓጉላ የከባድ መሳሪያዎች በተሰበሰቡበት ቦታዎች ተገናኝተን ትጥቆችን ቆጥረን ተረክበናል።

የከባድ መሳሪያዎችን ትጥቆች ስንረከብ ዝርዝር ሁኔታዎችንና የቴክኒክ ሁኔታዎችን ቀጣይ የምናያቸውና የምናረጋግጣቸው ይሆናል፤ ሆኖም ግን በውላችን መሰረት ትጥቁን በሰላም ፣ በፍቅር ከቲዲኤፍ (TDF) ተወካዮች ተረክበናል። የአፍሪካ ህብረቶችም በሰላም አስረክበውናል።

እኛ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በማናቸውም ጊዜ ለህዝብ እስከቆምን ድረስ የትግራይም ህዝብ ህዝባችን ነው ሌላውም ህዝብ ህዝባችን ነው በሰላም በጋራ ከዚህ በፊት እንደነበርነው አብረን ሰላማችንን ጠብቀን አብረን የመኖርና አብረን የማደግ ፣ አብረን የመበልፀግ አንድ ህዝብ እስከሆንን ድረስ በፍቅር ተባብረን ሰላማችንን መጠበቅ አለብን። "

@tikvahethiopia
#ነዳጅ #Update

ወደ ትግራይ ክልል #ነዳጅ መግባት መጀመሩን የክልሉ የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ፤ ወደ መቐለ 10 ቦቴ ነዳጅ መግባቱን ያመለከተ ሲሆን ወደ ኩዊኃ እና ዓጉላም ነዳጅ መግባት መጀመሩን ጠቁሟል።

ከፌዴራል መንግስት ጋር ጥሩ ትብብር እየተደረገ ነው ያለው ቢሮ " እናተ ጋር ካለው ችግር አንፃር ቅድሚያ እንሰጣለን " ተብለናል ሲል ገልጿል።

ጦርነት ለመፈጠሩ በፊት በወር 12 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ ይገባ እንደነበር የገለፀው ቢሮው አሁን እየገባ ያለው ነዳጅ ከሚፈለገው አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው ብሏል።

መቐለ ውስጥ ካሉት 15 ማደያዎች ነዳጅ የገባው በ4ቱ ላይ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል።

ነዳጅ ለማግኘት እነማን ቅድሚያ አላቸው ?

አሁን እየገባ ያለው ነዳጅ በተወሰነ መልኩ ስለሆነ ፦

- አምቡላንስ
- እሳት አደጋ
- ውሃ አቅራቢ ቦቴዎች
- የመንግስት ተሽከርካሪዎች
- የእርዳታ አከፋፋይ አካላት
- ባንክ፣ ቴሌ፣ መብራት ኃይል
- በትራንስፖርት ቢሮ ታሪፍ የወጣላቸው ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ቅድሚያ እንደሚያገኙ ተመላክቷል።

የፋይናንስ እጥረት በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እንዳይገባ እንቅፋት መሆኑን ያሳወቀው ቢሮው ችግሩን ለማፍታት ከባንክ ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

ቤንዚን እና ናፍጣ ስንት እየተሸጠ ነው ?

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከፌዴራል መንግስት ለክልሉ እንደተላከ ለመረዳት ተችሏል።

በመቐለ #ቤንዚን በሊትር 60 ብር ከ57 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን #ናፍጣ 66 ብር ከ58 ሳንቲም እየተሸጠ መሆኑን ከክልሉ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

Photo Credit : Tigrai Television

@tikvahethiopia
በደቡብ ክልል፤ ወላይታ ዞን ዉስጥ በጤና ስርዓት ላይ ያለው ችግር እንዲፈታ የፌደራል መንግስት አስቸኳይ የእርምት እርምጃ ይውሰድ ሲሉ የጤና ባለሞያዎች ጠየቁ።

ባለሞያዎቹ ይህን የጠየቁት ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት የፅሁፍ መልዕክት ነው።

መልዕክታቸውን የላኩ የጤና ባለሞያዎች፤ በዞኑ የጤና ዘርፍ ላይ ያሉ አመራሮች ቸልተኝነት የተነሳ የህክምናዉን አገልግሎት እንደ ሌሎች አካባቢዎች ግዜዉን የሚመጥን አልሆነም ብለዋል።

ባለሞያዎቹ እንደሚሉት የደንገተኛ ቀዶ ህክምና ከአንድ ሆስፒታል (ኦቶና) ዉጭ ማግኘት የማይታሰብ ሆኗል።

መድኃኒት፣ የምርመራ መሳሪያ እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶች በበቂ ሁኔታ የለም የሚሉት ባለሞያዎቹ፤ ባልተሰራ ነገር "የዉሸት ሪፖርት" እንድናቀርብም እንገደዳለን ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላው ባለሙያዎች የሰሩበት #ደመወዝ እና #ጥቅማጥቅም ባለማግኘታቸዉ ችግር እያጋጠማቸው እንደሆነ ጠቁመዋል።

በዞኑ የተለያዩ ሆስፒታሎች የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች ከደመወዝና ጥቅማጥቅም ጋር በተያያዘ ስራ ለመስራት ስለመቸገራቸውም አስረድተዋል።

ያለውን ችግር ለበላይ አካላትና ለሚዲያ እንዳይገለፅ ጫና እንደሚደርስ እንዳንድ ባለሞያዎችንም እስከ ማሰር የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዋል።

በዞኑ የፋይናንስ ችግር ሳይሆን የመልካም አስተዳደር ችግር ጎልቶ እንደሚታይ አሳውቀዋል።

የጤና ሚኒስቴር፤በዞኑ የሚታየው ችግር እንዲፈታ፣በተለይም በወላድ እናቶች ላይ እያደረሰ ያለው ችግር እንዲቀረፍ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል።

በዞኑ አብዛኞቹ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ላይ ችግሩ አለ ያሉት የጤና ባለሞያዎቹ በዚህም ስራ መስተጓጎሉን አመልክተዋል።

ስለጉዳዩ ከዞን ጤና መምሪያ ምላሽ እና ማብራሪያ ለማግኘት ለአንድ አመራር ስልክ ብንደውልም ስልኩ አልተነሳም።

@tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሲሚንቶ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በልሁ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ስለሆነው የሲሚንቶ ስርጭትና ግብይት መመሪያ ምንድነው ያሉት ? አቶ ተሻለ በልሁ ፦ " ... አዲሱ መመሪያ አንደኛ የቀየረው ሲሚንቶ በገበያ ስርዓት ይመራ ነው። በገበያ የሚመራ ሲባል ምን ማለት ነው አከፋፋዮቻቸውን ፤ ቸርቻሪዎቻቸውን የመምረጥ ነፃነት #የፋብሪካዎች ነው። እስከዛሬ ማን ነበር የሚመርጥላቸው ?…
መመሪያ ቁጥር 940/2015

የሲሚንቶ #ግብይት እና #ስርጭትን ለመቆጣጠር የወጣው መመሪያ ቁጥር 908/2014 ተሽሮ መመሪያ ቁጥር 940/2015 መፅደቁ ታውቋል።

አዲሱ መመሪያ ምን ይላል ?

- በኬላዎች አከባቢ ሲሚንቶ ምርት ላይ የሚደረግ ማንኛውም ቁጥጥር ተነስቷል።

- ቸርቻሪዎችን እና አከፋፋዮችን መምረጥ የፋብሪካዎች ሃላፊነት እንዲሆን ተደርጓል።

- ያለደረሰኝ ምንም አይነት ግብይት እንዳይካሄድ ተደርጓል።

- ከፋብሪካዎች የሚወጣ ማንኛውም የሲሚንቶ ምርት በቂ ሰነድ ሊኖረው ይገባል።

ይኸው መመሪያ የሲሚንቶ ጅምላ እና ቸርቻሪ ነጋዴዎች ግዴታ እንዳለባቸው የሚደነገግ ሲሆን ግዴታዎቹም ፦

👉 የሲሚንቶ ጅምላ ነጋዴ ሲሚንቶ የሚገዛውን ቸርቻሪ ድርጅት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በመመዝገብ በህጋዊ የረሰኝ ሽያጭ የማከናወን ግዴታ አለበት።

👉 በግዥ የተረከበውን ሲሚንቶ በተቀመጠው የዋጋ ጣሪያ መሠረት ለማንኛውም ተጠቃሚ የመሸጥ ግዴታ አለበት።

👉 ሲሚንቶን ከህጋዊ መስመር ውጭ አላግባብ አከማችቶ መያዝና ከተተመነው የዋጋ ጣሪያ በላይ ያለመሸጥ ግዴታ አለበት።

👉 የሲሚንቶ ቸርቻሪ ነጋዴ የያዘውን የሲሚንቶ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በንግድ  መደብሩ በግልፅ በሚታይ ቦታ ላይ የመለጠፍ ግዴታ አለበት።

👉 ማንኛውም ሲሚንቶ ገዢና ሻጭ የንግድ እንቅስቃሴውን መረጃ በአግባቡ የመያዝ እና  በተቆጣጣሪ አካላት ሲጠየቅም የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡

ምንጭ፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጉዳዩ እንዲህ ነው ፦ የአቶ ሙላቱ ጉጆ የወንድሙ ልጅ በሁላ ወረዳ ጫልቤሳ ተብሎ በሚጠራ አከባቢ አግብታ ሄዳለች። በሲዳማ ባህል መሰረት ሴት ልጅ አግብታ ከአከባቢ ከሄደች በኃላ የልጅቷ ቤተሰብ የዘመድ ልጆችን እና የልጅቷን ጓደኞች ሰብስቦ የተዳረችውን ልጅ ጥየቃ ፤ የሚበላ ነገር አስይዞ ይልካል። በዚህ መሰረት የአቶ ሙላቱ ጉጆ ልጅ የአጓቷ ልጅ አግብታ ወደሄደችበት በቀን 11/03/15 ዓ.ም ከቤተሰብ…
#Update

15 ዓመት ተፈርዶበታል !

ከሁለት ሳምንት በፊት በሲዳማ ክልል ፤ " የሁላ ወረዳ ፍርድ ቤት " አንዲት የ13 አመት ታዳጊን የደፈረ ግለሰብ ላይ የ3 አመት ከ9 ወር የፍርድ ውሳኔ መስጠቱ #ብዙዎችን_ያስቆጣ እንደነበር አይዘነጋም።

የተበዳይ ቤተሰቦች ባቀረቡት ይግባኝ መሰረት ባንሳ አከባቢ ተዘዋዋሪ ምድብ ችሎት ዛሬ ጥር 3 ቀን 2015 በይርጋለም የቀረበውን አቤቱታ በመመርመር የቀድሞውን ውሳኔ በመሻር አጥፊው በ15 አመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ማስታወሻ : https://t.me/tikvahethiopia/75508

Credit : Ermias Elias (HO)

@tikvahethiopia