TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DrAbiyAhmed

ዛሬ ከሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን በአጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ መክሯል።

እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን ያለበትን ደረጃ አንስቷል።

በተጨማሪም የ2015 የበጀት ዓመት ዕቅድ የትኩረት አቅጣጫን መቃኘቱን የጠ/ሚ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ዶ/ር ዐቢይ ስብሰባውን በተመለከተ ፤" ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም፣ ቀጥተኛ የውጭ ሙዓለ ነዋይ ፍሰት መጨመር ታይቷል። ባለፉት ሁለት ወራት የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ ከፍተኛ የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን፣ የበጎ ፈቃደኝነት ተግባራት፣ የሬሚታንስ ጭማሪ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥራ ክንውን የተመዘገቡበት እንደ ሆነ አረጋግጠናል። በዚህ ዓመት የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ መቀጠል በእጅጉ አስፈላጊ ነው። " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝታቸውን አጠናቀው ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል። የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና በሀገሪቱ የስልጣን እርከን ሶስተኛ ሰው የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን ጎብኝተዋል። ትላንት ታይዋን ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ብዙ ሲባልለት የነበረ እና በአሜሪካ እና ቻይና መካከል የፈጠረው ከፍተኛ ውጥረት ዓለምን ያሰጋ ነበር። ቻይና ፔሎሲ ወደታይዋን እንደሚመጡ…
#US #CHINA

" ቻይና ማንንም መከልከል አትችልም " - ፔሎሲ

" ሀገሬን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ " - ቻይና

በአሜሪካ በስልጣን እርከን 3ኛዋ ሰው ናንሲ ፔሎሲ ከታይዋን ጉብኝታቸው በኋላ " ቻይና የዓለም መሪዎችን ወይም ማንንም ወደ ታይዋን እንዳይጓዙ መከልከል አትችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

ቻይና ፤ ከፔሎሲ ጉብኝት በፊት ጉብኝቱ እንዳይደረግ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያና ዛቻ ብታሰማም ፔሎሲ ወደ ታይዋን ገብተው ፤ ጉብኝት አድርገው ባለስልጣናትን አነጋግረው ሄደዋል።

ምንም እንኳን የፔሎሲ ጉብኝት ቢጠናቀቅም በቻይና እና አሜሪካ መካከል ያለው ውጥረት የቀጠለ ሲሆን ቻይና " ሀገሬን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ " ስትል ዝታለች።

በሌላ በኩል ወደ ታይዋን ትልክ የነበረውን የተፈጥሮ አሸዋ መላክ ያቆመች ሲሆን ፍራፍሬና የዓሣ ምርቶችን ከታይዋን ማስገባት አቁማለች።

ታይዋን አካባቢ አሁንም የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴ መቀጠሉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#China

ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?

#ኢትዮጵያ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።

አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።

አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።

#ሱዳን

ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።

ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።

#ኤርትራ

ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።

የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።

ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።

#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GurageZone የጉራጌ ዞን መንግስት የኮሚኒኬሽን እና ሚዲያ ቡድን መሪ አቶ ፈቃዱ ዘለቀ ለብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ሬድዮ ጣቢያ የተናገሩት ፦ " ... የጉራጌ ዞን በክልልነት ለመዋቀር ለፌደሬሽን ም/ቤት የቀረበውን ጥያቄ ምላሽ በመጠባበቅ ላይ ነው። የህዝቡ ጥያቄ በክልልነት ለመዋቀር ነዉ ይሄንንም ለፌደሬሽን ምክር ቤት አቅርበናል ምላሹን እየጠበቅን ነው። የዞኑ ም/ቤት እስካሁን በአዲሱ አደረጃጀት…
" ማንኛውንም ኢ-መደበኛና ህገወጥ እንቅስቃሴ አልታገስም " - የደቡብ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ

የደቡብ ክልል መንግስት ከአደረጃጀት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የሚፈፀም ማንኛውንም ኢ-መደበኛና ሕገ -ወጥ እንቅስቃሴን አልታገሰም ሲል አስጠነቀቀ።

ጉራጌ ዞንን የሁከትና የብጥብጥ ቀጠና ለማድረግ የሚደረገውን እንቅስቃሴን መንግስት አይታገስም ብሏል።

ዛሬ በጉራጌ ዞን ወቅታዊ ፀጥታ ሁኔታ ላይ የክልሉ የፀጥታ ሴክተር፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት አመራርና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በወልቅጤ ከተማ ውይይት አድርገው ነበር።

በዚህም ወቅት በደቡብ ክልል በምክትል ርዕሠ መስተዳድር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ፥ በጉራጌ ዞን የሕዝብን የመዋቅር ጥያቄ ሽፋን በማድረግ የሚደረግ ኢ-መደበኛ እንቅስቃሴ ተቀባይነት የለውም፤ ይህንኑ ሕገ ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በዛሬው መድረክ ፤ ሁሉም አካባቢዎች በክልል ለመደራጀት ጥያቄዎችን ማቅረባቸው ተገልጾ " ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን ባገናዘበና የሕዝብን የአብሮነት፣ የልማትና የጋራ ተጠቃሚነት ብሎም በሁሉም ዘርፍ በቅርበት ለሕብረተሰቡ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ መዋቅሩ እየተሰራ ይገኛል " ተብሏል።

የጉራጌ ዞንም ከሌሎች አጎራባች ወንድም ሕዝቦች ጋር ለሀገር ግንባታ፣ ለኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለጋራ ብልፅግና እንዲያመች በአንድ ላይ መሆን እንደሚገባው በመድረኩ ተጠቁሟል።

ለዚህም አመራሩ ሕብረተሰቡን በቅርበት በማወያየትና ከአደረጃጀት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በዞኑ የሚፈጠር ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር እንዳይኖር በከፍተኛ ትኩረት መስራት ይኖርበታል ተብሏል።

ያንብቡ : telegra.ph/Gurage-Zone-08-03

@tikvahethiopia
ክረምት በመጣ ቁጥር በሌላም ጊዜ በተመቻቸ መንገድ እጦት ምክንያት የሚሰቃዩ፣ ስራቸው የሚስተጓጎል፣ ለክህምና ቶሎ መድረስ ሳይችሉ ቀርተው ህይወታቸው አደጋ ላይ የሚወድቅ ዜጎች ብዙ ናቸው።

ከዚህም በተጨማሪ በሀገር ኢኮሮኖሚ እና በዜጎች ኑሮ መሻሻል ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖም ከባድ ነው።

በሀገራችን በርካታ መንገዶች ቢገነቡም ገና እጅግ ብዙ መስራት ይቀራል። ብዙ ሊታዩ የሚግባቸው እጅግ በጣም ወሳኝ ቦታዎችም አሉ።

በተለይም ከፍተኛ የሰዎች እንቅስቃሴ ባሉባቸው አካባቢዎች በመንገድ እጦትና ብልሽት ብዙ እንግልት ይፈጠራል።

የሚሰሩ መንገዶች መጓተት፣ የጥራት ጉድለት ፣ በጊዜው አለማለቅ፣ ሲበላሽ አለመጠገን፣ ወሳኝ ቦታዎች ላይ የመንገዶችን አለመስራት ችግሮች በመንገድ ምክንያት ለሚፈጠረው እንግልት እንደምክንያት ይጠቀሳሉ።

ከላይ በፎቶ እና ቪድዮ የተያያዘው ከኦሮሚያ ክልል (ከቲክቫህ አባላት)ና ከአማራ ክልል (ከአሚኮና አዊ ኮሚኒኬሽን) የተገኙ ሲሆን ብዙ ቦታ የለውን የመንገድ ችግር ማሳያ ነው።

በዚሁ አጋጣሚ፦

ከከሳ- ግምጃቤት - አምበላ የጠጠር መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል ተብሏል። ጥገናውን መንገዱን ወደ አስፋልትነት ለማሳደግ የተረከበው የቻይናው ccecc ተቋራጭ እያከናውነው መሆኑን ተገልጿል።

የወልድያ-ጋሸና መንገድም ጥገናውን ለማክናወን (1.1 ቢሊዮን ብር) የተቋራጭነት ስራው በአማራ መንገድ ሥራዎች ኢንተርፕራይዝ ተይዞ የነበረ ሲሆን ስራው እየተሰራ በጦርነት ሳቢያ ተቋርጦ ነበር ተብሏል።

ተቋራጩ ያቀረባቸው ንብረቶች በመዘረፉ ወደ ስራ ለመግባት አስቸጋሪ እንደነበር ተገልጾ አሁን ላይ የመንገዱ አገልግሎት እንዳይቋረጥ የሚያስችል ጥገና ለማድረግ ስምምነት ላይ መደረሱን አሚኮ ዘግቧል።

ፎቶ /ቪድዮ ፡ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት፣ አሚኮ፣ አዊ ኮሚኒ.

@tikvahethiopia
#GujiZone

• " እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ባለው ጊዜ የ12 ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ ቁጥሩ ግን ሊጨምር ይችላል " - የሰባ ቦሩ ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ

• " የሞቱት ዜጎች ምናልባት በፀጥታ ችግር ምክንያት ሊሆን ይችላል " - የጉጂ ዞን ኮሚኒኬሽን

በኦሮሚያ ክልል፣ በጉጂ ዞን ፤ ሰባ ቦሩ ወረዳ በድርቅ ምክንያት የወገኖቻችን ህይወት እያለፈ መሆኑ ተገለፀ።

በኦሮሚያ ክልል፣ በጉጂ ዞን በሰባ ቦሩ ወረዳ ረሃብ ተከስቶ 12 ሰዎች መሞታቸውን የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ቢሮው፤ እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ዓ/ም ባለው ጊዜ ብቻ የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉን ገልጾ ቁጥሩ ግን ሊጨምር እንደሚችል አሳውቋል።

በወረዳው 35,442 ዜጎች አስቸኳይ ምግብ እርዳት ያስፈልጋቸዋል የተባለ ሲሆን እነዚህ ዜጎች በንሳ ፣ በደጋላልቻ ፣ ሰባሎሌማሞ ፣ በኡቱሉ፣ ኦዴ ፣ ሀራጌሳ ቀበሌዎች ያሉ ናቸው ተብሏል።

የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት መኮና ሀጤሳ ፤ ለወረዳው አልፎ አልፎ የምግብ እርዳታ ቢመጣም ምግብ ከሚያስፈልጋቸው ዜጎች ጋር የሚመጣጠን አይደለም ብለዋል።

በወረዳው የሟቾች ቁጥር በየቀኑ #እየጨመረ ሲሆን ባለፉት 2 ወራት የምግብ እና መሰል እርዳታቸዎች መቋረጣቸው ማህበረሰሙ ለከፋ የምግብ እጥረት መጋለጡን ገልፀዋል።

የጉጂ ዞን የኮሚኒኬሽን ቢሮ በበኩሉ ፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች 5 ወረዳዎች ድርቅ ተከስቷል ብሏል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ኦልኮ፤ " በረሃብ ምክንያት ስለሞቱ ሰዎች መረጃ የለኝም " ብለዋል። ነገር ግን " በአካባቢው የፀጥታ ችግር አለ " ሲሉ መግለፃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Guji-Zone-08-04

@tikvahethiopia
#ሀዋሳ #ድሬዳዋ #ባህርዳር

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የማለዳ በረራ ጀመረ።

አየር መንገዱ ከሀዋሳ ፣ ከድሬዳዋ እና ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ማለዳ 1:00 የሚነሱ እለታዊ በረራዎች መጀመሩን አሳውቋል።

#EthiopianAirlines

@tikvahethiopia