TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ታላቁ የህዳሴ ግድብ‼️

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድና ም/ጠ/ሚር ደመቀ መኮንን በተገኙበት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ወቅታዊ አቋም የሚቃኝ ግምገማ በተለያዩ ኮሚቴዎች ዛሬ ቀርቧል።

ግምገማውም፦

1. የታላቁ ህዳሴ ግድብ አሁን ያለበት ደረጃ፤
2. የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር፤
3. የአባይ ተፋሰስ ትብብር ማዕቀፍና
4. የግድቡ ሙሌት ደረጃን የሚያጠቃልል ነበር።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የታላቁ ህዳሴ ግድብን ወቅታዊ አቋም የሚቃኝ ግምገማ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ተደረገ፡፡ ግምገማው የተካሄደው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት ነው፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ትናንት በድረገጹ እንዳስነበበው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አሁን ያለበትን ደረጃ በተመለከተም የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ እንዳቀረቡት የሲቪል ምሕንድስና ሥራው ሰማንያ ሦስት በመቶ፣ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው ሃያ አምስት በመቶ፣ የብረታ ብረት ሥራው አሥራ ሦስት በመቶ በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ክንዋኔ ስልሳ ስድስት በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዕጣ የወጣባቸው #የኮዬ_ፈጬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚቀጥለው ሳምንት ለባለዕድለኞች ይተላለፋሉ‼️
.
.
#በድሃ ገንዘብ የተሠራ ነው፤ ቤቶቹን ባለዕድለኞች ከማስተለለፍ የሚያግደን ነገር የለም” - ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
.
.
በወሰን ይገባኛል ውዝግብ እጣ ለወጣላቸው ዕድለኞች ያልተላለፉት የኮዬ ፈጬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚቀጥለው ሣምንት ለባለዕድለኞች እንደሚተላለፉ ተገልጿል፡፡ 

ቤቶቹን ለማስተላለፍ አስቸጋሪ ሆኖ በቆየው የወሰን ይገባኛል ውዝግብ ጉዳይ የህግ ችግር አጥንቶ እንዲፈታ የተቋቋመው ኮሚቴ፤ ውሣኔውን ሰሞኑን ያሳውቃል ተብሎ የሚጠበቅ መሆኑን የገለፁት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር ሠናይት ዳምጤ፤ የኮሚቴውን ውሣኔ ተከትሎ ቤቶቹን በአንድ ሣምንት ጊዜ ውስጥ የማስተላለፍ ተግባር ይከናወናል ብለዋል፡፡ 

በም/ከንቲባ ኢ/ር #ታከለ_ኡማ የሚመራውና ከኮዬ ፈጬ ጋር ተያይዞ የተነሳውን የወሰን ጥያቄ ለመመለስና ዘላቂ መፍትሔ ለማስቀመጥ የተቋቋመው የአስተዳደር ወሰን አጣሪ ኮሚቴ ስራውን ባለመጨረሱ የቤት እጣ ከወጣ ጀምሮ መተላለፍ የነበረባቸው ቤቶች ለባለዕድለኞች ሳይተላለፉ መቆየታቸውን ኢ/ር ሰናይት ተናግረዋል፡፡
 
በቀጣይ የሚኖረውን እጣ አወጣጥ በተመለከተ የቤቱ ግንባታ 30% ከተጠናቀቀ በኋላ ዕጣውን በማውጣት ያላለቁ ግንባታዎች እንደሚሠሩ የገለፁት ኃላፊዋ፤ ይህ የሚደረገው ባለ ዕድሎች ቤታቸውን ተከታትለው የማየትና የመቆጣጠር ሃላፊነት እንዲኖራቸው ታስቦ ነው ብለዋል፡፡ 

መመሪያው የሚፈቅደው 80 በመቶ የሚሆነው ተጠናቆ ከተሰራ በኋላ ቢሆንም 30 በመቶ ላይ ሳለ እጣ አውጥቶ 80% ሲደርስ ግን ለባለዕድለኞቹ እንደሚያስተላልፉ ተናግረዋል፡፡  

አያይዘውም ቀደም ሲል ከባንክ ጋር ውል የመፈፀም ስራ ይከናወን እንደነበር ገልፀው፤ አሁን ግን በቤቶችና ልማት አስተዳደር የባንክ ሒሳብ ገቢ በማድረግ ውል ለመፈፀም የሚያስችል አሠራር ተዘርግቶ መጠናቀቁን ኃላፊዋ ገልፀዋል፡፡ 
ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሰጡት መግለጫ፤ ዕጣው ለባለ ዕድሎች እንዲተላለፍ ታስቦ የተሠራ በመሆኑና የተሰራውም በድሃው ገንዘብ በመሆኑ ከመተላለፍ መስተጓጐል እንደማይገባው ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም የአስተዳደር ወሰን ማጣራቱ ከግለሰቦች የዕጣ አወጣጥ ጋር እንደማይገናኝ ተናግረዋል፡፡ 

Via አዲስ አድማስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኮዬ ፈጬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚቀጥለው ሣምንት #ለባለዕድለኞች እንደሚተላለፉ ተገልጿል፡፡ #አዲስ_አድማስ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ:በትግራይ ክልል የጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር #ሓጎስ_ጎድፋይ የተመራው እና ለጌድዖ #ተፈናቃዮች እገዛ ለማድረግ ያቀደው የጤና ባለሙያዎች ልዑካን ቡድን👆ዶክተር ሃጎስ በትዊተር ገፃቸው "ሕዝባዊነት #ብሔርም #ድንበርም የለውም" ብለዋል። #ኢትዮጵያ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኮማንድ ፖስት...

በደቡብ ክልል ለአንድ ወር የሚቆይ #በመከላከያ_ሠራዊት የሚመራ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ከሳምንታት በፊት በምእራብ ወለጋ #ነጆ_ወረዳ ሁምና ዋቀዮ በሚባል አከባቢ በአሰቃቂ ሁኔታ 5 ሰዎች በኦነግ ታጣቂዎች በተባሉ ኃይሎች መገደላቸዉ ይታወሳል። ከተገደሉት የ2ቱ የውጪ ዜጎች ዉስጥ የሕንድ ዜግነት ያለዉ ግለሰብ አስከሬኑ ለቤተሰቦቹ የተላለፈ ሲሆን ነገር ግን #የጃፖን ዜግነት ያላት ሁለተኛዎ ሞች አስከሬን የመለየት ስራ #ችግር እንደገጠመዉ እና አስከሬኗ አሁንም ቅዱስ ፖዉሎስ ሆስፒታል እንደሚግኝ ለማወቅ ተችሏል።

Via ዳዊት እንደሻው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ስሙ ቆሼ እየተባለ በሚጠራው ሥፍራ በደረሰ የቆሻሻ ክምር መደርመስ አደጋ ጉዳቱ ላገኛቸው የተሰበሰበው ገንዘብ ጉዳይ #ውዝግብ አስነስቷል፡፡ በቆሼ ተጎጂዎች የተቋቋመው የጋራ ኮሚቴ ከተሰበሰበው ውስጥ አንድ ቢሊየን ብር በምን መንገድ እንደወጣ፣ የት እንደገባ ግልፅ እንዳልሆነላቸው ተናግረዋል፡፡ ኮሚቴው በተደጋጋሚ ስለአንድ ቢሊየን ብሩ ጉዳይ የከተማ አስተዳደሩን ቢጠይቅም መልስ እንዳላገኘ ተናግሯል፡፡

via Sheger
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Nia_Foundation🔝

አለም አቀፍ #የኦቲዝም ግንዛቤ ቀን በኒያ ፋውንዴሽ እየተካሄደ ይገኛል። ኑ ኦቲዝም ያለባቸውን ሰዎች አብረን እናክብር ድጋፋችንን እናሳይ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia