الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
21.8K subscribers
374 photos
17 videos
7 files
913 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞ትዳር በኢስላም☜ ክፍል ሶስት/ ③ =>ከአንድ በላይ ሚስት በቀደምት ነብያት..      ....በዚህም ምክንያት ሳራም ነብዩላህ ኢብራሂም አሰ ልጅ ይወልዱ ዘንድ #ሀጀርን ዳረቻቸው።ሀጀርን አግብተው ነብዩላህ ኢስማኢልን አሰ ከወለዱ በኃላ #ሳራ የቅናት_መንፈስ አደረባት። ኢብራሂም አሰ ሚስታቸውን ሀጀርን እና ልጃቸውን ኢስማኢልን ከአጠገቧ እንዲያርቁላት ሳራ ጠየቀች። ይግን ጉዳይ ኢብራሂም አሰ ወደ #አላህ…
☞ትዳር_በኢስላም.☜

  ክፍል~አራት /④ት

=>ከአንድ በላይ ሚስት በቀደምት ነብያት..

 
#ነብዩላህ_ያዕቁብ_እና_ሌሎችም

   ነብዩ ያዕቁብ አሰ በአንድ ጊዜ 4 ሚስቶች ያገቡ ሲሆን እንደመፅሀፍ ቅዱስ ገለፃ ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፣

1/
#ሊያ
2/
#ራሄል
3/
#ባላ
4/
#ዘለፋ ናቸው።

  ☞ ከእነዚህ አራት ሴቶች 12 ልጆችን ያገኙ ሲሆን ከሚስቶቻቸው በጣም ተወዳጅ የነበረችው
#የነብዩ_ዩሱፍ_እናት_ራሄል ነበረች።
እሷም ነብዩ ዩሱፍን እና ታላቅ ወንድማቸውን ቢኒያሚኒን ወልዳላቸዋለች ይላል መፅሀፍ ቅዱስ

     
#ነብዩ ሙሳ..

    ሙሳ 4 ሚስቶች እንደነበሯቸው የቀደምት መፅሀፍት ያረጋግጣሉ።ስማቸውም እንደሚከተለው ተጠቅሷል..
1/
#ሰፉራህ ይቺ ሚስታቸው ከእሳቸው 2 ልጆች ያላት ሲሆን ስማቸውም #ጀሱንና_አዚር ናቸው።

2/
#ጀብሻህ
3/
#የቀይኑይ_ልጅ
4/
#የሃባብ_ልጅ ናቸው።
     ይህ መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የሰፈረ ነው።

        /ነብዩ.ዳውድ

     እንደቀደምት መፅሀፍት(መፅሀፍ ቅዱስ እና ሌሎችም) የነብዩ ዳውድ ሚስቶች በርካታ ከመሆናቸው አንፃር ቁጥራቸው በትክክል ለማወቅ ያዳግታል።በአንዳንድ ዘገባዎች #29 ሚስቶች እና #40 ሴት ባሮች እንደነበራቸው ይነገራል። ቁጥራቸው  ብዙ ስለሆነ ስማቸው በውል አይታወቅም ይላል።በሌሎች ዘገባዎች ደግሞ የዳውድ ሚስቶች ዘጠኝ ብቻ ናቸው የሚልም አለ..

☞ነብዩ ሱለይማን..

   በመፅሀፍ ቅዱስ እንደተጠቀሰው ከሆነ ነብዩ ሱለይማን
#ከ1000 በላይ ሴቶች እንዳላቸው እና ከእነዚህ ውስጥ 700 ጨዋ ሚስቶቻቸው ሲሆኑ 300 ደግሞ ሴት ባሮቻቸው እንደነበሩ ተነግሯል።ከብዛታቸው የተነሳ ስማቸውን በውል ለማወቅ አልተቻለም ይላሉ የመፅሀፉ ባለቤቶች።ነገር ግን እኛ ሙስሊሞች የምናምነው በቁርአን እና በሀዲስ የተረጋገጠውን ብቻ ነው። በኢስላም የሚታወቀው የነብዩላህ ሱለይማን  ሚስቶች #100 ብቻ ናቸው የሚለው ነው። መቀበልም ያለብን ይህን ብቻ ነው። ምክንያቱም ይህ እውነታ በነብዩ ሰአወ የተነገረ ነው..
   
#ያላገቡ.ነብያት
☞ መልእክተኛ ሆነው ከተላኩ ነብያቶች ውስጥ ያገቡ  ነብያቶች እንዳሉ ከላይ አሳልፈና። 1 ሚስት ብቻ ያገቡም ነበሩ ለምሳሌ
#ዩሱፍ ያገቡት አንድ ብቻ ነበር፣በአንፃሩ ምንም ያላገቡ የአላህ መልእክተኞች የነበሩ ሲሆን በውል የሚታወቁት ሁለት ብቻ ነበሩ፣ እነሱም #ነብዩላህ የህያ እና ነብዩላህ ኢሳ ናቸው..

   ☞እዚህ ጋር ማስታወስ የምፈልገው ነገር አለማግባት የታላቅነት መገለጫ እንዳልሆነ ሊሰመርበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ነው። አንዳንድ የሌላ እምነት ተከታይዎች ነብዩላህ ኢሳ ባለማግባታቸው አንዱ የታላቅነት መገለጫ አድርገው ሲቆጥሩት ይስተዋላሉ።ጉዳዩ ሴት አለማግባት ከሆነ ታዲያ ነብዩላህ የህያ የንግስናው እና የገድሉ ባለቤት ለምን አላደረጓቸውም..
   ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት በነብዩ ሰአወ ጊዜ የተደነገገ አስመስለው እሱንም እንደታላቅ ነውር በመቁጠር ሲያራግቡት እና ጥላሸት ሲቀቡ እስልምና ሃቅ ፈላጊ በሆኑ ሰዎች ተቀባይነት እንዳያገኝ በር ላይ ቁመው ሰዎችን ሲያስበረግጉ ይስተዋላሉ። ከዚህም በከፋ ሁኔታ መፅሀፍ ቁዱስ ከአንድ በላይ አግብተዋል ያላቸውን ነብያቶች በተመለከተ የተፃፈውን ነገር መሰረዝ ስለማይችሉ በምትኩ እንደእነሱ አባባል የኦሪት እና የመዝሙር ባለቤት የሆኑትን ነብዩ ሱለይማንን እና ነብዩ ዳውድን መናፍቃን ሆነው ነው ብዙ ሚስት ያገቡት እያሉ ሲጠሯቸው የያዙትን እምነት እየተቹ  መሆናቸው ያልገባቸው ሊሆኑ ይችላሉ ብለን ድምዳሜ ለመስጠት ተገደናል። እነዚህ ነብያቶች ከአንድ በላይ ያገቡት መናፍቅ ሆነው ፣ተሳስተው ወይም ተገደው ነው ብለው ያስባሉ።
#እውነታው ግን ነብይ መናፍቅ ፈፅሞ ሊሆን አይችልም.

     ☞ እውነታው ኢስላም ከአንድ በላይ ሚስት እንደ አዲስ የደነገገ ሳይሆን ገደብ ያጣውን የሴቶችን ያለገደብ በአንድ ወንድ ቁጥጥር ስር የመሆንን ጭቆና ከላያቸው ላይ ገፎ በፍትህ ማኖር የሚችል ሰው ከአራት በላይ እንደማይፈቀድለት አጥብቆ እርምት የሰጠ ሀይማኖት ነው.።

      ከአንድ በላይ ሚስት በገደብ መሆን እንዳለበት ከሰማይ ወርዶ የተደነገገበት ብቸኛው ሀይማኖት ኢስላም ብቻ ነው..
        የአይሁዳውያን ሀይማኖት ከአንድ በላይ ሚስት የሚፈቀድበት ሆነ ነገር ግን የቁጥር ገደብ ያልተቀመጠለትና ስለፍትህ ያልተወራበት ሆኖ እናገኘዋለን።የኃላ ኃላ የአይሁድ እምነት አዋቂነን ባይዎች በራሳቸው ስልጣን የሚስትን ቁጥር #4 እንዲሆን ተስማሙ።ይህ ስምምነት ሰው ሰራሽ እንጂ በተውራት ያልወረደ እና ያላስተማሩት ስለሴቶች መብትና ፍትህ ያልተወራበት ጎደሎ ድንጋጌ ነው።

#ከአንድ_በላይ_ሚስት_በቀደምት_ሀይማኖቶች

⇡ይቀጥላል ..

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam