ቴዎ ፍሎስ theophilus
219 subscribers
144 photos
7 files
7 links
" ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን::
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:5)
በዚህ ቻናል የተለያዩ ትምህርቶችና፡ ስብከቶች እንዲሁም ፡ስነ መለኮታዊ ይዘት ያላቸዉ አስተምሮቶች ይቀርበታል። በተጨማሪም ቅዱሳን በinbox ለሚጠይቁት ጥያቄ መልስን የሚያገኙበት መንፈሳዊ ቻናል ነዉ።


መንፈሳዊ ጥያቄን ለመጠየቅ inbox @tsedeM
Download Telegram
ሰላም ለእናንተ ተወዳጆች
ነገ በደረስንበት በሚል ርዕስ አዲስ ትምህርትን እንማራለን። ይጠብቁ
ሰይጣን ሰዉን ሀጢያት እንዲሰራ ይገፍፍና ሀጢአት ካሰራ በኃላ ደግሞ ለምን ሰራህ ብሎ ይከሳል።

ከፀደቀ መንፈሰ
ሁለት አመት የሞላዉ ይመስለኛል በአንድ እስር ቤት ዉስጥ ባለ አማኞች በሚሰበሰቡበት አዳራሽ የመስበክ እድል አጊንቼ ነበር: ስብከቴንም እንደጨረስኩ እድሜዉ በግምት ወደ 50 የሚጠጋ ተለቅ ያለ ሰዉ ፊቱ ላይ በሚነበብ ድንቅ በሆነ ፈገግታዉ አጥብቆ ሰላም አለኝ አጠገቡም ወዳለ ወንበር በመጠቆም ቁጭ እንድል ጋበዘኝ እኔም አንዳች ለእኔ ሊነግረኝ የፈለገዉ ነገር እንዳለ ስለገባኝ በደስታ ተቀመጥኩኝ።እርሱም ቀበል አድርጎ ትንሽ ደቂቃ ብትሰጠኝ እግዚአብሔር በህይወቴ የሰራዉን ስራ ላወራህ ፈልጌህ ነበር አለኝ እኔም በደስታ እንደምሰማው ገለፅኩለት:ያሳለፈዉ ህይወት ፊልም ወይም መፅሐፍ ሊሆን የሚችል ሚደንቅ ታሪክ ነዉ። እስር ቤት ከመግባቱ በፊት በጣም ሀብታም ነበር: የተለያዮ ድርጅቶችና መኪኖችም ነበሩት ሀብቱን ያጣበትንና እስር ቤት የገባበትን ምክንያት አጫወተኝ። በተስመጨረሻ ያለኝ ነገር ልቤ ዉስጥ ቀረ: ያለኝን ሀብት በአብዛኛዉ ከእጄ ላይ ተወስዶ ለእስር ተዳረኩ: እዚህ እስር ቤት ግን ኢየሱስ አገኘሁት: እርሱንም አወኩት እርሱ ደግሞ ትላንት በእጄ ላይ ካለዉ ሀብት እጅግ በለጠብኝ አሁን ገና ባለጠጋ ሆንኩኝ: ጳዉሎስን በደማስቆ ያገኘ ጌታ እኔን ደግሞ በእዚህ በእስር ቤት አገኘኝ። በኢየሱስ ያገኘሁት ነፃነትና ሰላም እስር ቤት ከመግባቴ በፊት ካለኝ ነፃነትና ሰላም በእጅጉን ይበልጣል። በእዚህ እስር ቤት ቃሉን እለት እለት አነባለሁ ሰፊ ሰዓትም እፀልያለሁ: አሁን እግዚአብሔር ይመስገን ከዚህ እስር ቤት ለመዉጣት ጥቂት ቀናቶች ነዉ የቀሩኝ ከዚህም በኃላ ባለኝ እድሜና ጉልበት ሁሉ የእግዚአብሔርንም መንግስት ለማገልገል ተዘጋጅቻለሁ አለኝ።ሲናገር ፊቱ ላይ የሚንፀባረቀዉ ደስታ ዋዉ.😮 የሚገርም ነዉ መዝናኛ እንጂ እስር ቤት ያለ አይመስልም: ንግግሩንም ሳይጨርስ የመዉጫ ሰዓታችን ስለደረሰ ለማቋረጥ ተገደድንና ተሰናበትኩት። ከዚህ ሰዉ ህይወት እግዚአብሔር ብዙ ነገር አስተማረኝ: ስለ እርሱም እግዚአብሔርን እያመሰገንኩ ተመለስኩ።

ተወዳጆች በኢየሱስ ያገኘነዉ ነፃነት በምንም ዋጋ የማናገኘዉ ማንም ደግሞ የማይሰጠን ትልቁ ሀብታችን ነዉ።

ኢየሱስ ማግኘት ምድር ላይ ካለ የትኛዉንም ሀብት ከማግኘት ይበልጣል።

ኢየሱስ በእዉነት ከሁሉ በላይ ነዉ።
ዘመኑ አስፈሪ ቢሆንም
የጌታ ፀጋ አላነሰንም
ዲያቢሎስ ቢራቀቅ ቢመጥቅ በእጥፍ
አይተኛም እኛን ሚጠብቅ

ዘማሪ #ደረጀ #ከበደ
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 1

የእግዚአብሔር ፅድቅ ክርስቶስ አጸደቀን

#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 24_06_2016