እውነት አርነት ያወጣል
2.63K subscribers
363 photos
68 videos
37 files
357 links
እውነት አርነት ያወጣል!!!
Download Telegram
እኛ እጅ ገብቷል

በቅርቡ ደግሞ እናንተ ጋር ይደርሳል
ለንባብ በቅቷል

ስታዲየም ያለው መሠረተ ክርስቶስ መጻሕፍት መደብር ይገኛል

ሼር አድርጉልኝ 🙏
ዛሬ ማርያም ለአባ ጊዮርጊስ ጽዋዕ ያጠጣችው ቀን ነው ተብሎ ይታሰባል። ታሪኩ የሚከተለውን ይመስላል፦

ከሰባት ቀናት የሱባዔ ቆይታ በኋላም፤ ‹‹እንደተለመደው በሥዕለ ማርያም ሥር ተደፍተው ሲያለቅሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ዑራኤልን አስከትላና ጽዋዓ እሳት አስይዛ መጥታ የሕይወት ጽዋዕ አጠጣቻችው፡፡ አባ ጊዮርጊስም የሕይወት ጽዋዕን ከጠጡ በኋላ የሰማይና የምድር ምስጢር ሁሉ ተገለጸላቸው››፡፡ ከዚህም በኋላ ከአርባ በላይ መጻሕፍትን ለመጻፍ ችሏል፡፡

የሕይወት ጽዋዕ›› የተባለውን መጠጥ በተመለከተ ገድሉ ላይ ‹‹የመረጥሁህና የልጄ ወዳጅ ጊዮርጊስ ብላ በስሙ ጠራችው፡፡ ከዕውቀት ወንዝ የመጣና ከጥበብ ምንጭ የተገኘ ከመለኮት ባሕር የተቀዳ ይህን ንጹሕ ጽዋ /እንካ/ ንሣ ጠጣ፡፡ ለስም አጠራርዋ ሰጊድ ይሁንና የዓለም ሁሉ ንግሥት እመቤታችን ያን ጊዜ በቀኝ እጅዋ ሰጠችው፡፡ ሳይጠጣውም ወደ ውስጡ ተመለከተ ይህን ጽዋ የጠጣ አይኰነንም ከሕይወት ባሕር ተቀድቶአልና የሚል መጽሐፍ አገኘ፡፡… ይህም በዮሴፍ ቤት በርሐ ጽዮን ሐዋርያት የጠጡት መንፈሳዊና ሰማያዊ መጠጥ ነው፡፡ በበዓለ ሃምሳ ከጠጡት ያልተለየ ነው፡፡ ይኸውም የሚናገር እሳት፣ የሚያድን እሳት መለኮታዊ እሳት ነው›› የሚል ተጽፎ ይገኛል (የደብረ ባሕርይ ጋስጫ አባ ጊዮርጊስና አቡነ በጸሎተ ሚካኤል አንድነት ገዳም፣ ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እና ገድለ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል - ግእዝና አማርኛ፤ (ታኅሣሥ 2004) ገጽ 34 - አጽንዖት የግል)፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ‹‹ሐዋርያት የጠጡት መንፈሳዊና ሰማያዊ መጠጥ ነው›› ተብሎ የተጠቀሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሁለት ላይ ‹‹በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው›› የተባለው ቅዱሱ መንፈስ ነው፡፡ ‹‹ማርያም›› ለአባ ጊዮርጊስ ያጠጣችው መንፈስ ቅዱስን እንደ ሆነ በገጽ 44 ላይ ‹‹እመቤታችን ማርያምም የገለጠችለት የመጻሕፍትን ዕውቀት ብቻ አይደለም፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ኀይልንም አለበሰችው እንጂ›› ተብሎ የተጻፈውን መመልከት ይቻላል፡፡ በገድሉ ትረካ መሠረት መንፈስ ቅዱስን የምትሰጠው ማርያም ናት ማለት ነው፡፡ በገድለ አባ ጊዮርጊስ እንደተጠቀሰው መንፈስ ቅዱስ ‹‹… ከዕውቀት ወንዝ የመጣና ከጥበብ ምንጭ የተገኘ…››፣ ‹‹… ከሕይወት ባሕር …›› የተቀዳ ሳይሆን ራሱ ዕውቀት ሰጪ፣ ራሱ የጥበብ ባለቤት የሆነና ራሱ የሕይወት ምንጭ የሆነ ቅዱስ መንፈስ ነው፡፡ በፍጡር እየተቀዳና በዕቃ እየተጨለፈ የሚወሰድ ሳይሆን እሱ በዓለሙ ሁሉ የመላ ለሁሉ እንደ ወደደ የሚሠራ ገናና አምላክ ነው፡፡
ከዛሬው ንባቤ ላቅምሳቹ ብዬ ነው

እስኪ ሐሳብ ስጡበት
እኔና እርሱ

ከአንድ ሰው ጋር የነበረኝ ውይይት በአጭሩ

እኔ፤ ስንት አዳኝ ነው ያለው?

እሱ፤ አንድ ብቻ እሱም ጌታችን ነው

እኔ፤ ማርያምስ መድኃኒት ተብላ ተጠርታ የለ? እሷስ አታድንም?

እሱ፤ የመድኃኒት እናት ስለሆነች ነው መድኃኒቱን የወለደችው እሷ ስለሆነች መድኃኒት እንላታለን

እኔ፤ መቼ ነው የወለደችው?

እሱ፤ (ይሄን አታውቅም? ከሚል ሳቅ ወይም ስላቅ በኋላ) ከዛሬ 2000 ዓመት በፊት

እኔ፤ ዛሬ ማርያም መድኃኒት ናት?

እሱ፤ አዎ ናት

እኔ፤ ለምን? አንድ አዳኝ ነው ያለው ብለኸኝ ነበርኮ

እሱ፤ ነገርኩህኮ መድኃኒቱን ስለወለደች ነው መድኃኒት የምትባለው አልኩህ አይገባህምንዴ?

እኔ፤ እሱ ገብቶኛል ስለወለደችው መድኃኒት የተባለችበት ምክንያት ነው ያልገባኝ እሱን ልታስረዳኝ ትችላለህ?

እሱ፤ ቆይ እኔ ልጠይቅህ ጌታችንን የወለደው ማነው?

እኔ፤ ማርያም

እሱ፤ በቃሃ ለዚህ ነው መድኃኒት የምትባለው

🤔😳🤔😳🤔😳🤔

እኔ ግራ ገባኝ የገባቹ አስረዱኝ አልገባኝም
የዚህ መጽሐፍ ዐላማ መምህራን ዐደራቸው ለቃለ እግዚአብሔርና ለቃሉ ባለቤት ለእግዚአብሔር በመኾኑ፣ ለሚያስተምሩት ትምህርት ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ማሳየትና ማሳሰብ ነው። ሕዝበ ክርስቲያኑ ጽሑፋችንን ቢያነብብና ስብከታችንን ቢሰማ፣ እኛን ፈልጎ ሳይኾን፣ እግዚአብሔርን ናፍቆ በመኾኑ ከቅዱሱ ቃል ሳንርቅ ታላቁን እግዚአብሔርን ብቻ ማሳየት ይኖርብናል። ስለ ኾነም አገልጋዮችን ‹‹ከተጻፈው አትለፍ›› ማለት ይገባል።
እግዚአብሔር ቢፈቅድ

በቅርብ ቀን
በጣም በቅርቡ
እኛ እጅ ገብቷል

በቅርቡ ደግሞ እናንተ ጋር ይደርሳል
በቅርብ ስርጭት ይጀምራል
በቅርብ ቀን