Tesfa
6.25K subscribers
949 photos
51 videos
2 files
875 links
አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው?
እግዚአብሔር አይደለምን?
Download Telegram
ቶማስ ሌሎች ደቀ መዛሙርት ኢየሱስን እንዳዩ ሲነግሩት አላመነም ነበር ፤ ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ተገለጠለት።

ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው። ቶማስ አይቶ አመነ፤ ነገር ግን ሳያዩ የሚያምኑ ይበልጥ ብፁዓን ናቸው።

የትንሣኤው እውነቱ በምስክርነት ተረጋግጧል፤ ኢየሱስ ከሞት ተነስቷል።

#በደም_የተጻፈ_ፍቅር #tesfa #hope

Follow tesfa on Telegram

Also follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
33
እነዚህ ሁለት ሰዎች ኢየሱስ ሞቶ ተስፋ ቆርጠው ነበር። ነገር ግን እነርሱ ሳያውቁት እርሱ ራሱ ከእነርሱ ጋር ነበር፤ በመንገድ ላይ መጻሕፍትን ከፍቶ ሲያስረዳቸው ልባቸው በውስጣቸው ይቃጠል ጀመር፤ ነገር ግን ገና አላወቁትም ነበር።

እንጀራውን በቈረሰ ጊዜ ግን ዓይኖቻቸው ተከፈቱ፤ በዚያ ጊዜ አወቁት፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ።

እውነቱ ይህ ነው!
ኢየሱስ አሁን ሕያው ነው።

ትንሣኤው የጠፋውን ተስፋ ዳግመኛ አድሷል።

ሉቃስ 24:32 እርስ በርሳቸውም፡— “በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን?” ተባባሉ።


#በደም_የተጻፈ_ፍቅር #tesfa #hope

Follow tesfa on Telegram

Also follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
47
ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ አንድ ግልጽ ትእዛዝ ሰጥቷቸዋል::

ሂዱ የትንሣኤውን ዜና ወደ ዓለም ሁሉ ውሰዱ ደቀ መዛሙርትም አድርጓቸው።

በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዲያጠምቋቸው እና በክርስቶስ ውስጥ ያለን አዲስን ሕይወት እንዲያስጀምሯቸው ነግሯቸዋል።

በዚህ ትእዛዝ ውስጥ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሆን የዘላለም ህይወት ተስፋ አለ።

ማቴዎስ 28:19—20 “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”


#በደም_የተጻፈ_ፍቅር #tesfa #hope

Follow tesfa on Telegram

Also follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
23
ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከመውጣቱ በፊት ለደቀ መዛሙርቱ የሰጠው ተስፋ እና ተልዕኮ ነው።
“መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ ሲወርድ ኃይል ትቀበላላችሁ" ብሎ።
እግዚአብሔር የሚሰጠው ኃይል፤
የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነው!
ለመናገር፣ ለመቆም፣ ለመመስከር የሚያበረታ ኃይል ነው።
ትንሳኤውን፣ የማዳኑን ሀይል በዙሪችን ላሉ፣ለማናውቃቸውም
እስከ ምድር ዳር ዓለም ሁሉ ነው።
እግዚአብሔር ኃይሉን ሰጥቶ ልኮናል።
መንፈስ ቅዱስም ከእኛ ጋር ነው።

ሐዋ. ሥራ 1:8 ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ።”


#በደም_የተጻፈ_ፍቅር #tesfa #hope

Follow tesfa on Telegram

Also follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
21👍7🔥4
የፍጥረት ሁሉ ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
በሰማይ በክብር በአባቱ ቀኝ ያለው እርሱ፣ ሕይወትን የሚሰጥ፣ ነፍስን የሚያድን ጌታ፣ እንደተናገረው እንዲሁ ይመጣል!
ይህ የተስፋ ፍጻሜ ነው፤
በእርሱ ያመኑትን ወደ ክብሩ ለመውሰድ ይመጣል።
ስለዚህ ዛሬ ወደ ሕይወት እንጠራሀለን:
ጌታ ኢየሱስን ተቀበል።
እርሱ በደጅ ነው፤ መምጫው ቅርብ ነው። በእርሱ በማመን
ከሞትና ከጥፋት መዳን ትችላለህ፤ ወደ ዘላለም ሕይወት መግባት ትችላለህ።
ኢየሱስ ሲመጣ ያመኑትን በምሕረቱ ይዞ ወደ ዘላለም ክብር ይወስዳል።
ህያው ተስፋችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል።

ሐዋ. ሥራ 1:11 ደግሞም፡— “የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ስማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል፡” አሉአቸው።


#በደም_የተጻፈ_ፍቅር #tesfa #hope

Follow tesfa on Telegram

Also follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
🔥256
በብዙ ነገር ጠንካራ እና ባለጠጋ የሚመስሉ ሰዎችም እንኳ ብዙ ጉድለት ሊያጋጥሟቸው ይችላል። ነገር ግን እግዚአብሔርን በእውነት የሚፈልጉ ሰዎች ከሚያስፈልጋቸው መልካም ነገር አይጎድሉም።

እግዚአብሔርን መፈለግ፤ ከእርሱ ጋር መቀራረብ፣ እርሱን መታመን፣ በየቀኑ በእርሱ ላይ መደገፍ ነው። እርሱም የሚያደርግልህ ነገር ሁሉ ለአንተ የሚሻል ነው! ሁልጊዜ የሚያስፈልግህን ይሰጥሀል።

ወንድሜ፡ ዛሬ ሁኔታዎች እንኳ ያልተረጋጉ ቢመስሉ፣ ቢከብዱህ: እግዚአብሔር ያውቅሀል። እርሱን በእውነተኛ ልብህ ስትፈልገው ሰላም፣ ኃይል፣ ደስታን እና የሚያስፈልግህን ሁሉ ይሰጥሀል።

መዝሙር 34:10 ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉትን ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም።


Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
28🔥7👍2🤩1
እውነተኛ ሙላት ከውጫዊ ነገር አይመጣም፤
እግዚአብሔርን በሙሉ ልብ ስትፈልግ ነው።
በመከራ ውስጥ እያለፍክ እንኳ በእግዚአብሔር ላይ መታመን ትልቅ ጥበብ ነው፤
ምክንያቱም እርሱን ስትፈልግ ከመልካም ነገር አያጎድልህም።
ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ህብረት ስታደርግ በአስቸጋሪ ሁኔታ እንኳን ሰላምን እና እረፍትን ይሰጥሀል!

መዝሙር 63:1 አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች፡ እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ።


Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
33🔥5👍2
እግዚአብሔር በሕይወትህ ያደረገውን ሁሉ ማሰብ እና ማስታወስ ያስፈልጋል።
በእርሱ መመረጥህን፤
የእርሱ ሕዝብ ተደርገህ መጠራትህን፤
በሕይወትህ ውስጥ ያደረገውን ልታስብ እና ልታመሰግነው ይገባል!
በችግኝ ጊዜ ያገዘህን፣ ጸሎት የመለሰልህን፣
ያልተገባህን ጸጋ ያበዛልህን 🙏
እርሱ በህይወትህ ትናንት ታማኝ ነበር ፣
ዛሬም በታማኝነቱ የሚመራህን እርሱ ነው።

መዝሙር 105:5-6 ባሪያዎቹ የአብርሃም ዘር፥ ለእርሱም የተመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፥ የሠራትን ድንቅ አስቡ፥ ተአምራቱን የአፉንም ፍርድ።


Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
29🔥3
እግዚአብሔር ትልቅ ነው፤ ከመታውቅ ያልፋል።
ሁሉም ለእርሱ በእርሱ ተፈጥሯል።
የፍጥረት ሁሉ መገኛ ነው፤ ከእያንዳንዱ ፍጥረት ህልውና ጀርባ የመኖራቸው ዋስትና እግዚአብሔር ነው። ትልቅ የሆነውን  ለመኖርህ የሚያስፉልግህን የአጥናፍ አለሙ ሁሉ መገኛ የሆነውን እግዚአብሔር ወደህይወትህ ልትጋብዝ ትፈልጋለህ?

እግዚአብሔር ትልቅ ነው፤ በአምላካችን ከተማ በተቀደሰ ተራራ ምስጋናው ብዙ ነው።
መዝሙረ ዳዊት 48፡1


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
25🔥2
በድካምህ የሚያግዝህ፣ ስትደክም የሚያበረታህ፣ ስትወድቅ የሚያነሳህ፣ ጉልበት እና አቅም የሚሆንህ፤ በመንፈሳዊም ሆነ በስጋዊ ህይወትህ ሁሌም ሊለውጥህ፣ ሊሰራህ፣ ሀይልህን ሊያድስ አቅምን ሊሰጥህ፣ ሀይሉን በድካምህ ሊገልጥ ቸሩ እግዚአብሔር ሁሌም ይጠራሀል::
ምላሽህን ልትሰጥ ፈቃደኛ ነህ? ልንረዳህ ዝግጁ ነን::

ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል። - ትንቢተ ኢሳይያስ 40:29



መልካም ሳምንት ይሁንላችሁ!
#tesfa #hope #brightmonday

#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
32🔥6👍2
እረፍት ሚታረፈው በሕይወት እያለህ ነው ዛሬ! ህያው ሆንህ ያልጀመርከውን እረፍት እንዴት ትቀጥለዋለህ? ማረፍ ያለብህ በሞትህ ሳይሆን ዛሬ ህያው ሆንህ ነው። ለዛም ነው ጌታችን እና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” ብሎ የተናገርው::
ና! ወደዚህ ጌታ መምጣትና ማረፍ ትወዳለህ? በህይወት እያለህ ወደ ሚያሳርፍህ ጌታ መቅረብ ትወዳለህ?
ልንረዳህ በዚህ አለን::
ኢየሱስ የህይወት እረፍት ነው!

እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።
የማቴዎስ ወንጌል 11:28


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
45👎2🔥1
በህይወት ምልልስ ውስጥ ብዙ ኃላፊነቶች፣ ፈተናዎች ሊገጥምህ ይችላል።
እግዚአብሔር ግን በራስህ ብቻ እንድንተማመን አይፈልግም።
ክርስቶስ ለሚገጥም ማንኛውም ነገር ሁሉ ኃይልን ይሰጥሀል።

ሁሉን መቻል ማለት የፈለከውን ሁሉ በራስህ ኃይል ታደርጋለህ ማለት አይደለም። ይልቁንም በክርስቶስ ኃይል ፈተናን ማለፍ፣ ታማኝ ሆኖ መኖር ማለት ነው።

ዛሬ የሳምንቱን ስትጀም በፍርሃት ወይም በጭንቀት ሳይሆን ክርስቶስ ከአንተ ጋር እንዳለ በመታመን ጀምር። ምንም ዓይነት ሸክም ወይም ፈተና ቢመጣ ብቻህን አይደለህም።

ፊልጵስዩስ 4:13 ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
🔥2216👍1😢1
ሕይወት ብዙውን ጊዜ የፍርሃት፣ የጥርጣሬ እና የድክመት ጊዜያትን እንድታልፍ ታስገድድሀለች። ነገር ግን ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው።

የእግዚአብሔር መገኘት ከሚገጥምህ ከማንኛውም ችግር ይበልጣል።

እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 41:10


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
17🔥6👍1
የእስራኤል ሕዝብ በመከራና በስደት ውስጥ ባሉበት ጊዜ እግዚአብሔር ግን ለእነርሱ ያለውን ፍቅር እና መልካም ዕቅድ ነግሯቸዋል።
እነርሱ ተስፋ ቢቆርጡም እግዚአብሔር ግን እኔ ስለእናንተ መልካም አሳብ አለኝ ብሎ ተስፋን እንደሰጣቸው፤ ይህ ቃል ዛሬም ለአንተ ህይወት ይሰራል፡፡ ለህይወትህም ትልቅ መጽናናት ነው።
አንዳንድ ጊዜ ሕይወት ግራ ሊያጋባህ ይችላል፤ ፈተና፣ መዘግየት ወይም ያልተጠበቀ ነገር ሲመጣ እግዚአብሔር እንደረሳህ እና እንደተወህ ሊሰማን ይችላል።
ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ አንተ ያለው አሳብ የሰላም፣ የተስፋ እና የመልካም ፍጻሜ ነው።
እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው የመጨረሻው ታሪክህም በእርሱ በእጁ ነው።

ዛሬ በምንም ዓይነት ግራ መጋባት እና በጭንቀት ብታልፍ፣ እግዚአብሔር ስለ አንተ ያለው ዕቅድ መልካም መሆኑን አስታውስ። እርሱ ተስፋ የሚሰጥ አምላክ ነው፤ ወደፊትህም በእጁ ውስጥ ነው።

ኤርምያስ 29:11 ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።

#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
17🔥6
በጣም ከባድ ጊዜያቶችን በምታሳልፍበት ጊዜ እንኳን እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው። ዳዊት ብዙ ጦርነት፣ ፍርሃት እና አደጋ አጋጥሞት ነበር፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር አብሮነት ላይ ሙሉ በሙሉ ይተማመን ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ ባለ ጊዜ እንኳ እንደማይተወው ስለሚያውቅ ነው።

ዛሬ ምንም አይነት ጭንቀት ቢገጥምህ፣ ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው፣ እርሱም ሰላምን ይሰጥሃል።


መዝሙር 23:4 በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ፡ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።

#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
41🔥3
እግዚአብሔር በሰው ህይወት ውስጥ የሚፈቅደውን ሁሉ ነገር ለበጎ ይለውጠዋል። ዛሬ የምታልፍበትን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይቀይረዋል።

አንዳንድ ጊዜ የምታልፍበት ነገር ለምን እንደሚሆን ላይገባህ ይችላል፤ ህመም፣ መዘግየት፣ ችግር ወይም ውድቀት ቢኖርም በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እግዚአብሔር እየሠራ ነው።
እርሱ ከባድ ነገሮችን እንኳ ለመልካም ያደርጋቸዋል።
ዛሬ ያልገባህ ሁኔታ ቢኖርም ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር ከህይወትህ አንድም ክፍል አይለይም። እርሱ እያንዳንዱን ነገር ለመልካም ፍጻሜ እያዘጋጀህ ነው።


ሮሜ 8:28 እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
34🔥9👍1
በዚህ ቃል መሰረት ፈተና ወይም ፍርሃት ቢኖር እግዚአብሔር ከአንተ ጋር መሆኑን ይነግርሀል። ብቻህን አይደለህም፤ እርሱ ይመራህል፣ ያጽናናሀል፣ ኃይልም ይሰጥሀል።
በምታልፍበት ሁኔታ ሳይሆን በእግዚአብሔር ህልውና ታመን። እርሱ በምትሄድበት ሁሉ ከአንተ ይሆናል። ፍርሃትህን አስወግደህ፤ በእግዚአብሔር ብቻ ታምነህ ምትኖርበትን ህይወት ዛሬ ወስን!

"በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?” ኢያሱ 1፥9


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
🔥2120
እግዚአብሔር በማንኛውም የሕይወት ሁኔታ ውስጥ ለልጆቹ ቅርብ ነው። ከአደጋ ምትሸበት እና የምትጠለልበት መጠጊያ ቦታ ነው። እግዚአብሔር በድካምህ ጊዜ የሚያበረታህ ኃይልህ ነው። አንዳንድ ጊዜ በሕይወትህ የምታልፍበት ነገር ከአቅምህ በላይ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በዚያ ጊዜ ውስጥ እንኳ የሚያጸናህ እና እንድትቀጥል የሚያደርግ ኃይል ይሰጥሀል። እግዚአብሔር አምላክ በችግርህ ጊዜ ከአንተ ጋር ያለ፣ የሚረዳ፣ የሚያጽናና እና ተስፋ የሚሰጥ አባት ነው።

ዛሬ በሕይወትህ ውስጥ ድካም፣ ፍርሃት ወይም ጭንቀት ካለ፣ ብቻህን አይደለህም። እግዚአብሔር መጠጊያህ፣ ኃይልህ እና ረዳትህ ነው። ወደ እርሱ በጸሎት ብትቀርብ ሰላሙን ይሰጥሃል፣ ልብህንም ያበረታል።

መዝሙር 46:1 አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው።


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
19🔥4
እውነተኛ እረፍትና እፎይታ የሚገኘው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።
በሀጢያት ወይም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ደክመሀል? ኢየሱስ ወደ እኔ ና፤ እረፍት እሰጥሃለሁ ብሎ ይጠራሀል።
እርሱ የሚሰጠው እረፍት: ከሀጢዓተኝነት እና ከበድለኝነት ነፃ የሚያወጣ እረፍት፣ ከጭንቀትና ከፍርሃት ነፃ የሚያወጣ እረፍት፣ በልብ ውስጥ የተረጋጋ ሰላምና እፎይታ የሚሰጥ እረፍት፣ የዘላለም ሕይወት የሚገኝበት እውነተኛ እረፍት ነው።
ዛሬ ወደዚህ እረፍት ተጠርተሀል!

ማቴዎስ 11:28 እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።


#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
27👍2
እግዚአብሔር የልጆቹን ጩኸት ይሰማል። አንዳንድ ጊዜ በችግር፣ በሀዘን ወይም በጭንቀት ውስጥ ልታልፍ ትችላለህ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ጸሎትህን ይሰማል፣ የምታልፍበትንም ያውቃል፤ ደርሶም በጊዜው ይረዳሀል።
እግዚአብሔር ቅርብ ነው፣ የሚሰማ እና የሚያድንም አምላክ ነው።
ዛሬ በጭንቀት ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር ጩኸትህን ይሰማል፤ በጊዜውም ይደርስልሀል።

“ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።”— መዝሙር 34፥17

#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
16🔥5