SIRARA
9.23K subscribers
3.96K photos
51 videos
2 files
666 links
ይህ ቻናል ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና የተረጋገጡ እና አዝናኝ የሆኑ መረጃዎች የሚቀርቡበት ነው!
ለማስታወቂያ እና ጥቆማ በዚህ ያናግሩን 👉 https://t.me/mo_anbesa
Download Telegram
ራስ ደስታ ሆስፒታል ትላንት እና ዛሬ በስራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙን ሁሉንም የጤና ባለሞያዎች ማሰናበቱን ገልጿል። በሌላ መልኩ ደግሞ የጤና ሚኒስትር ጡረታ ከወጡ ዶክተሮች ባለፈ ሥራ ላጡ ሐኪሞችም ጥሪ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ጠፈር ሊጓዙ ነው በሚል መሠረት ሚዲያ ያወጣው ዘገባ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጨ ይገኛል

መሠረት ሚዲያ ባወጣው መረጃ መሰረት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ጠፈር ለመጓዝ ማቀዳቸው የተገለጸ ሲሆን፣ የጉዞው ዋና ዓላማም ጠፈር ላይ ሆነው ለአለም ህዝብ የሰላም መልዕክት ለማስተላለፍ እንደሆነ ተጠቅሷል። ዘገባው ይህ ጉዞ ከተሳካ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የተጓዙ የመጀመሪያው የአለማችን መሪ እንደሚያደርጋቸውም አመላክቷል።

ታሪክን ስንመለከት፣ በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 ሲሆን፣ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ናቸው። በቅርብ ዓመታት ውስጥ ግን አንዳንድ ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል ለቱሪዝም ዓላማ ወደ ዝቅተኛው የምድር ምህዋር (low Earth orbit) ተጉዘዋል።
አሰልጣኝ አንጅ ፖስቴኮግሉ ቃላቸውን ጠብቀዋል

"በሁለኛ ዓመት ቆይታዬ ሁልጊዜም ዋንጫ አሸንፋለሁ"
ስፐርስ ከ 17ዓመታት በኋላ የዋንጫ ክብርን ተቀዳጅቷል። የዩሮፓ ሊጉ ዋንጫውን አሸናፊ ሁኗል። እንዲሁም በቀጣይ የውድድር ዓመት የሻምፒዮንስ ሊጉ ተሳታፊ።
"አሜሪካን ማን ፈቃጅ አደረጋት" አያቶላህ !

የኢራኑ ሁለንተናዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ "ቴህራን ኑክሌር ለማበልጸግ የማንንም ፈቃድ አትጠብቅም" ማለታቸው ተነግሯል። ይህ የአያቶላህ ንግግር ሁለቱ ሃገራት በኒውክሌር ልማት ላይ ሊያደርጉት ውይይት ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድር ተፈርቷል።
በአሜሪካ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ሁለት ሰራተኞች ተገደሉ

በአሜሪካ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ሰራተኞች የሆኑ ሁለት ግለሰቦች በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የአይሁድ ሙዚየም ደጃፍ ላይ መገደላቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል።
በትራንፕ ላይ ተሳለቁበት !
"እኔ እንግዲህ የምሰጥህ አውሮፕላን የለኝም "


ዋይት ሀውስ የሚገኙት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝደንት ራማፎሳ ከትራምፕ ጋር እየተወያዩ እያለ ። ትራምፕ ፡ በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ ነጮች ላይ ግፍና g*ድያ እንደተፈፀመ : የኦቫል ቢሮውን መብራት አጥፍተው ማረጋገጫ ነው ያሉትን ቪዲዮ እያሳዩ የደቡብ አፍሪካውን ፕሬዝደንት ሲወቅሷቸው ቆዩ ።
......
በዚህ መሀል አንድ ጋዜጠኛ ለትራምፕ ከኳታር መንግስት የተሰጣቸውን አውሮፕላን በተመለከተ ጠየቃቸውና ፡ ትራምፕ እያብራሩ እያለ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝደንት ጣልቃ ገብተው. .
" እኔ እንግዲህ ( እንደነኳታር ) የምሰጥህ አውሮፕላን የለኝም አዝናለሁ " 😉 ብለው ሲናገሩ ትራምፕ ቀበል አድርገው .....
" ኖሮህ ብትሰጠኝ ግን ፡ ካንተም እቀበል ነበር "... 🏃‍♂️👨‍🦽
Wasihune Tesfaye
ወደስራ ተመልሻለሁ
አርቲስት ይገረም ደጀኔ

ወዳጆቼ .....እኔ በጣም ደህና ነኝ ቅዳሜና እሁድ ትኩሳትና ሰውነቴን ጥሩ ስሜት ስላልተሰማኝ ወደሃኪም ቤት እሁድ እለት ሄጄ ለተወሰነ ሰዓት ኢመርጀንሲ ቆይቼ ህክምና አግኝቼ ሻል ሲለኝ ወደቤቴ ተመልሼ አንድ ሁለት ቀን እረፍት አድርጌ ወደስራዬ ተመልሻለሁ ።

          ይሄን ያልኩት የእኔን ቪዲዬ መልዕክት ተከትሎ ለእኔ በጎ በሚያስቡ በርካቶች መልካም ምኞት በማስተላለፋቸው መልዕክቱ እየሰፋ በርካቶች በስልክም በቴክስትም ጭንቀታቸውን እየገለፁ ነው ።

          በሶሻል ሚዲያም ፈጣሪ ይማርህ ብለው አብረውኝ ሆነዋል ...ለዚህም ትልቅ አክብሮት አለኝ ሁላችሁንም ፈጣሪ ያስባችሁ ሰላሙን ይስጣችሁ..

         በተረፈ ቪዲዬ ላይ እንደገለፅኩት በነበረቺኝ አጭር ቆይታ   ሆስፒታሉ ስላሳየኝ  በጎነት ፍቅርና እክብሮት ለማመስገን ነበር ብቅ ያልኩት እንጂ መታመሜ የሚወራ ሆኖ አይደለም  በጣምም ቀላል ስለነበር ።

        ፈጣሪ ሀገራችንንን ሰላም ያድርግልን !!
         ለሁላችንም  ያልተፈቱ ጥያቄዎቻችንን ይፍታልን !!
ክረምት እየድረሰ ነው ጓዶች፣ ወደ ጨረቃ ሳንሄድ አንሞትም. . .ለማንኛውም ችግኝ እያዘጋጃችሁ
SIRARA
ክረምት እየድረሰ ነው ጓዶች፣ ወደ ጨረቃ ሳንሄድ አንሞትም. . .ለማንኛውም ችግኝ እያዘጋጃችሁ
አንድ ሰው ወደ ጠፈር ጉዞ ሲያስብ
ምን ያስፈልገዋል ?
ISS- international Space Station-
1. ጉዞው ከመሬት ከ6 ስአት 24 ስአት ይፈጃል::
2. ትንሹ ጠረፍ ላይ ለመቀመጥ ከ8 እስከ 10 ቀን ሲሆን::
ትልቁ ደሞ 1 ወር ይሆናል ::
3.አሁን ላይ 4 ድርጅቶች ሰዎችን በቱሪስትነት ወደ ጠፈር እየወስዱ ይገኛል
እነሱም
* Axiom Space (USA)
* SpaceX (USA)
* Roscosmos (Russia)
* Space Adventures (USA)
ወደፊት ደሞ :-
* Blue Origin (USA – Jeff Bezos)
* Virgin Galactic (USA – Richard Branson )
ሰዎችን ለማጏጏዝ አስበዋል::
ወደ ዋናው ጥያቄ ስንገባ ስንት ብር ያስፍልጋል ወይንም እነዚህ ድርጅቶች ስንት ዶላር ተቀብለው ነው ሰውን ወደ ጠፈር የሚልኩት ሲባል ደሞ
* ከእነ ምግብ
* ትምህርቱ
* Medical cover
* ከእነ ሁሉም ነገር
* VIP treatment
አሁን ላይ ለአንድ ሰው (per person)
* 55 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን
ወደ ብር ሲመነዘር ደሞ በባንክ ምንዛሬ
6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ይሆናል
ነገር ግን እነ Elon Musk ወደፊት በአንድ ሰው ከ5 ሚሊዮን ዶላር እስከ 20 ሚሊዮን ዶላር ለማስከፈል ብዙ ሰራ እየሰሩ ሲሆን
ይህን ነገር እውን የሚሆነው በሚቀጥለው 10 ዓመት ወይንም ከዚህ ቀደም ባሉ ዓመታት ነውም ተብሏል::
ለ14 ቀን ወይንም ለ1 ወር ወደ ጠፈር 6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ከፍለው መሄድ ይፈልጋሉ
እንግዲያው ከላይ ያሉትን ድርጅቶች ያናግሩ::
መልካም ጉዞ::

ጉርሻ
መንግስት በራሱ ሕዝብ ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን እንዲያቆም አሜሪካ ጥሪ አድርጋለች።
‼️ የሞት ቅጣት‼️

እናቷም የእንጀራ አባቷም በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።
ወላጅ እናት ወ/ሮ ሀና በየነ ትባላለች የድሬዳዋ ከተማ ገንደቆሬ ሰፈር ነዋሪ ስትሆን ከቀድሞ ባሏ ጋር  የተፈታችው ይህቺ ሴት ከእሷ ጋር እየኖረ ባለው ሌላ ወንድ  ከአብራኳ የወጣችውን የገዛ ሴት ልጅዋ ተገዳ መደፈሯን ስታውቅ እጮኛዋን በወንጀል እንዲቀጣ ማድረግ ሲገባት የ11 ዓመት ልጇ ላይ ፈርዳ መረጃ ለማድበስበስ በማሰብ ልጇን ላይ ጫና በመፍጠር በድብደባ አካላዊ ጉዳት ከማድረስ በተጨማሪ ከ5ተኛ ክፍል የትምህርት ገበታ እና ከጎረቤቶቿ በመነጠል ከማንም ሰው ጋር ምንም ግንኙነት እንዳታረግ በማድረግ ለብዙ ጊዜ ቤት  ተዘግቶባት እና ስራ ቦታ ድረስ  ከስሯ ሳትነጥላት ብትንቀሳቀስም መረጃ ለመደበቅ በቂ ሆኖ ስላላገኘችው በመጨረሻ  በአብራኳ በወጣችው የገዛ ልጇ ላይ  የሰራችው ተደጋጋሚ የአረመኔ ሥራ  ሳያንሳት እጮኛዋን ከወንጀል ለማትረፍ መረጃ ለማጥፋት ህዳር 1 ቀን 2015 ዓም  ከእጮኛዋ ጋር በመተባበር ቀጥቅጠው ህፃን በአምላክ ግርማን ገደሏት።

***

በወላጅ እናቷ እና እንጀራ አባቷ  ሕይወቷ ያለፈው ሕፃን በአምላክ ግርማ አበጋዝ ጉዳይ ዛሬ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የቅጣት ውሣኔ ሰጥቷል።

ተከሳሾቹም

እናቷ ሀና በየነ በሞት እንድትቀጣ ተወስኗል::
እንጀራ አባቷ ብሩክ በሞት እንዲቀጣ ተወስኗል::

#ችሎት
5 የህክምና ዶክተሮች ከስራ ተሰናበቱ

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን የደብረታቦር አጠ/ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በስራ ማቆም አድማ ምክንያት በስራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ አምስት የህክምና ዶክተሮችን ከስራ ማሰናበቱን አሳውቋል።
#ስለ_3ዓመት_ታማኝ_ኖላዊነትዎ_
እናመሰግናለን 🙏

በዘር፣በሱሁት አስተምሕሮ እና በፓለቲካ ለምድ የተሸፈኑ ጠላቶቻችን ዝናራቸው አራግፈው ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ የወረወሩትን ቀስት ለመመከት ከሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነጳጳሳት ጋር ላደረጉት ተጋድሎ እናመሰግናለን።

ወጀብ በጸናብን ሰዓት እረኝነትዎ ባለመጣል ስላልታሙ እናመሰግናለን። በፈርዖን እና ቄሳር ፊት ግልገሎችን የመጠበቅ አደራዎትን ስላልጣለ እናመሰግናለን።
#የኛ_የሁላችንም_አባት_በቤተክርስቲያን ደማቅ አሻራቸውን ያሳረፉ ፣ቤተክርስቲያናችን በችግሯ እና በፈተናዋ ሰአት አለሁ ለቤተክርስቲያን እሞታለሁ ለሀይማኖቴ ምንም ይምጣ ምን አንገቴን እሰጣለሁ ብለው የዘመኑ ታላቅ ሀዋርያ የሆኑ ቤተክርስቲያኗ እስካሁኗ ሰአት ድረስ የሰጠቻቸውን ሀላፊነት በብቃት፣በንቃት፣በትጋት እንዲሁም በትኩረት የተወጡ ታላቅ አባት #ብፁዕ #አባታችን_አቡነ_አብርሃም_የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ የባህርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ እንኳን እግዚአብሄር በሰላም አስፈጸመዎት ታላቁ አባቴ እንዎደዎታለን እናከብረዎታለን ብራኬዎትም ጭምር አይለየን ብፁዕነተዎ🙏🙏
የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ

የቅዱስ #ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል፦

1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤
2. ብፁዕ አቡነ  ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ 
3. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን የሐዲያ ሀ/ስብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
4. ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዘኮሎራዶን የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤
5. ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሚኒሶታን እንደያዙ የኮሎራዶ ሀ/ስብከትን እንዲመሩ፤
6. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብ አፍሪካ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳ ጳስ፤
7. ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን የገዳማት መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ፤
8. ብፁዕ አቡነ ሙሴ አውስትራልያን እንደያዙ የግቢ ቅዱስ ገብርኤልና የበዐታ ለማርያም ገዳም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ ወስኗል።
ሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን እንዳይቀበል ተከለከለ


የትራምፕ አስተዳደር ሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን እንዳይቀበል ያገደ ሲሆን ይህም ከአሜሪካ አንጋፋው ዩኒቨርስቲ ጋር ያለውን አለመግባባት አባብሶታል።

የአገር ውስጥ ደህንነት መስርያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖኤም በኤክስ ገጻቸው ላይ እንደጻፉት አስተዳደሩ ሀርቫርድ "ተማሪዎች እና ስደተኛ ያልሆኑ ተማሪዎችን መቀበል የሚያስችለውን ዕድል ሕግን ማክበር ባለመቻሉ ምክንያት ተሰርዟል" ብለዋል።

"ይህ በመላው አገሪቱ ለሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እና የትምህርት ተቋማት እንደ ማስጠንቀቅያ ይሁናቸው" ሲሉ ሐሙስ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ልጥፍ ላይ ጽፈዋል።

ሀርቫርድ ውሳኔውን "ሕገ ወጥ" ሲል በመግለጫው አውግዞታል።

"ከ140 በላይ አገራት የመጡ እና ዩኒቨርሲቲውን እና ይህችን አገር በማይተመን መልኩ የሚያበለጽጉትን ዓለም አቀፍ ተማሪዎቻችንን እና ምሁራኖቻችንን ለማስተናገድ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኞች ነን" ሲል ዩኒቨርሲቲው በመግለጫው ላይ ምላሽ ሰጥቷል።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
«ደሃ ጥቁር ጉንዳን ነው» የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወዳጅና ተሸላሚ ዮናታን አክሊሉ ምን እያለን ነው??

90% ህዝቧ ደሃ በሆነባት እና 20 መንግስት ስራየ ብሎ በያዘው ጦርነት እና ሙሰኛ ባለጊዜ ሹማምንት በሚወስኑት ውሳኔና የሙስና ሰንሰለት በየቀኑ ሚሊዮን ንጹሃን ደሃ ሆነው በሚያድሩበት ሃገር እንዲህ ድሃን መጸየፍ ምንጩና ሊተላለፍ የፈለገው መልዕክትስ ምንድነው??
ብዙዎች "ያልተጠበቀ" ያሉትን የእነ አባ ሳዊሮስን ሹመት አንዴት ተመለከታችሁት?? እስኪ በጨዋነት ሃሳብ ሰጡበት
ኧረ ነገሩ እንዴት ነው??