በሳዑዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ‘ከአረፋ በዓል በፊት’ ፍርዱ ይፈጸማል ተባለ
በሳዑዲ አረቢያ በናጂራኒ እስር ቤት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በሚቀጥለው ሳምንት ከሚከበረው የኢድ አል አረፋ በዓል በፊት ፍርዱ ተፈፃሚ እንደሚሆን እንደተነገራቸው ቤተሰቦቻቸው አስታወቁ።
ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ እንደዘገበው፣ በእስር ቤቱ የሞት ቅጣት የተፈፀመባቸውን ጨምሮ በአጠቃላይ 47 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ፍርድ ተወስኖባቸዋል። ቤተሰቦቻቸው የኢትዮጵያ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ህይወታቸውን እንዲታደግላቸው ጥያቄ እያቀረቡ ነው።
በሳዑዲ አረቢያ በናጂራኒ እስር ቤት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በሚቀጥለው ሳምንት ከሚከበረው የኢድ አል አረፋ በዓል በፊት ፍርዱ ተፈፃሚ እንደሚሆን እንደተነገራቸው ቤተሰቦቻቸው አስታወቁ።
ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ እንደዘገበው፣ በእስር ቤቱ የሞት ቅጣት የተፈፀመባቸውን ጨምሮ በአጠቃላይ 47 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ፍርድ ተወስኖባቸዋል። ቤተሰቦቻቸው የኢትዮጵያ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ህይወታቸውን እንዲታደግላቸው ጥያቄ እያቀረቡ ነው።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አምባሳደር ሪያድ ማንሱር አለቀሱ‼️
የፍልስጤም አምባሳደር ሪያድ ማንሱር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ትናንት ግንቦት 20 ምሽት በምክርቤቱ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ሲያለቅሱ ታይተዋል።
መናገር ሲያቅታቸው የተያዘው ቪደዬ የአለም ሚዲያዎችን ትኩረት ስቦ ውሏል።
የፍልስጤም አምባሳደር ሪያድ ማንሱር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ትናንት ግንቦት 20 ምሽት በምክርቤቱ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ሲያለቅሱ ታይተዋል።
መናገር ሲያቅታቸው የተያዘው ቪደዬ የአለም ሚዲያዎችን ትኩረት ስቦ ውሏል።
የሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ በቅርቡ እውቅና እንደሚሰጡ የሶማሊላንድ መሪ አስታውቀዋል።
የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሓመድ አብዲላሂን (ኢሮ) ዋቢ በማድረግ The Guardian በዛሬው እትሙ እንዳስነበበው ግጭት በበዛበት ቀጠና ሶማሊላንድ በምርጫ መንግስት በመቀየር ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ከማድረግ ባሻገር አሜሪካ በቻይና ተጽእኖ ስር በወደቀችው ጅቡቲ የሚገኘውን ወታደራዊ ሰፈሯን ወደ በርበራ ወደብ ለማዛወር አጥኝዎችን በመላክ ግምገማ እያደረጉ መሆኑን አትቷል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ በቅርቡ እውቅና እንደሚሰጡ የሶማሊላንድ መሪ አስታውቀዋል።
የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሓመድ አብዲላሂን (ኢሮ) ዋቢ በማድረግ The Guardian በዛሬው እትሙ እንዳስነበበው ግጭት በበዛበት ቀጠና ሶማሊላንድ በምርጫ መንግስት በመቀየር ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ከማድረግ ባሻገር አሜሪካ በቻይና ተጽእኖ ስር በወደቀችው ጅቡቲ የሚገኘውን ወታደራዊ ሰፈሯን ወደ በርበራ ወደብ ለማዛወር አጥኝዎችን በመላክ ግምገማ እያደረጉ መሆኑን አትቷል።
ዛሬ ያልተመዘገባችሁ ከግቢ ለቃችሁ ውጡ በተባልነው መሰረት አብዛኞቻችን የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ኢንተርን(Interns) and Residents ከጠዋት ጀምረን ጊቢ ተሰባስበን ነበረ::እኛም Interns ከተገናኘን ስለቆየን ሰላም እየተባባልን በየዶርሙ ትንሽ መጨዋወት ጀመርን:: ብዙም ሳንቆይ ሁላችንም እየተከታተልን ራይድ እና ፈርስ እየጠራን የነበረንን እቃ አየሸከፍን መውጣት ጀምረን:: ለአመታት እንደልጆቻቸው ተንከባክበው የመገቡን እናቶች ከማዳ' ቤት (Cafe) ወተው እንባ ባቀረር አይሮቻቸው ጥግ ላይ ቆመው አይን አይናችንን ያዩናል::
ከምሳ ሰዓት በኅላ የተሰጠን የጊዜ ገደብ ወደማለቅ ሲጠጋ በየጥጋጥጉ 3-4 እየሆኑ ሲቪል የለበሱ የደህንነት ሰዎች ተሰበሰቡ::እኛም ነገሩ ስለገባን ምክንያት ላለመስጠት በቀረችን ሰዓት ቶሎ ለማውጣት ስንሯሯጥ ጥጋጥግ ይዘው ያዩናል:: ከግቢ ለወጣ ስል ግን አንድ ሲቪል የለበሰ ተጠግቶኝ የጠየቀኝ ጥያቄ ግርምትን ጫረብኝ 😁
"ጥያቄዎቻችሁ ሁሉ ልክ እንደሆኑ አውቃለው ግን ከቅድም ጀምሮ ሁላችሁም ስትወጡ እያየዋቹ ነበረ አንዳችሁም ፊት ላይ ሀዘን አላየሁም... እንደውም ደስተኛ ሆናችሁ ትሳሳቃላችሁ... ለመመረቅ ጥቂት ወራት ቀርቷችሁ ጥላችሁ በመሄዳችሁ ትንሽ እንክዋን በውሳኔያቹ አትፀፀቱም?
ሳላውቀው በውስጤ ኩራት እየተሰማኝ... ወደን እኮ አይደለም ስለደከመን በዛውም ለእረፍት ወደቤት እየሄድን ስለሆነ ነው ብዬ ወሬ ሳላበዛ ከግቢ ወጣው::
በመንገድ ላይም የተሳፈርኩት የRide ሹፌር በኢትዮጵያ ታሪክ ትልልቅ ለውጦች የመጡት በተማሪዎች ንቅናቄ እንደሆነ ሲያስታውሰኝ፣ ከምን ጊዜውም በላይ ውሳኔያችን ልክ እንደሆነ እና ለቀጣይ ትውልድ ታሪክ በመፃፍ አሻራችንን አያስቀመጥን እንደሆነ ገባኝ::
ጉዞ ወደ ነፃነት
©EHPMOFFICIAL
ከምሳ ሰዓት በኅላ የተሰጠን የጊዜ ገደብ ወደማለቅ ሲጠጋ በየጥጋጥጉ 3-4 እየሆኑ ሲቪል የለበሱ የደህንነት ሰዎች ተሰበሰቡ::እኛም ነገሩ ስለገባን ምክንያት ላለመስጠት በቀረችን ሰዓት ቶሎ ለማውጣት ስንሯሯጥ ጥጋጥግ ይዘው ያዩናል:: ከግቢ ለወጣ ስል ግን አንድ ሲቪል የለበሰ ተጠግቶኝ የጠየቀኝ ጥያቄ ግርምትን ጫረብኝ 😁
"ጥያቄዎቻችሁ ሁሉ ልክ እንደሆኑ አውቃለው ግን ከቅድም ጀምሮ ሁላችሁም ስትወጡ እያየዋቹ ነበረ አንዳችሁም ፊት ላይ ሀዘን አላየሁም... እንደውም ደስተኛ ሆናችሁ ትሳሳቃላችሁ... ለመመረቅ ጥቂት ወራት ቀርቷችሁ ጥላችሁ በመሄዳችሁ ትንሽ እንክዋን በውሳኔያቹ አትፀፀቱም?
ሳላውቀው በውስጤ ኩራት እየተሰማኝ... ወደን እኮ አይደለም ስለደከመን በዛውም ለእረፍት ወደቤት እየሄድን ስለሆነ ነው ብዬ ወሬ ሳላበዛ ከግቢ ወጣው::
በመንገድ ላይም የተሳፈርኩት የRide ሹፌር በኢትዮጵያ ታሪክ ትልልቅ ለውጦች የመጡት በተማሪዎች ንቅናቄ እንደሆነ ሲያስታውሰኝ፣ ከምን ጊዜውም በላይ ውሳኔያችን ልክ እንደሆነ እና ለቀጣይ ትውልድ ታሪክ በመፃፍ አሻራችንን አያስቀመጥን እንደሆነ ገባኝ::
ጉዞ ወደ ነፃነት
©EHPMOFFICIAL
''አሜሪካ የድርሻዋን ትወጣ'' ህወሃት
የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ሃላፊነት የጎደለው እና ከፕሪቶሪያ ስምምነት ውጪ የሆነ ድርጊቱ ወጥቶ፣ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን አምስተኛውን ክረምት በአስከፊ ሁኔታ እንዳያሳልፉ ግዳጁን ሊወጣ ይገባል። የተፈናቃዮቹን ሁኔታ በአምባሳደርዋ፣ በተደራዳሪዋ እና በመላው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኩል የተከታተለችው አሜሪካ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ጊዜ የማይሽረው ቀውስ ተረድታ የድርሻዋን እንድትወጣ በድጋሚ እንጠይቃለን ሲል ህወሃት አዲስ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ሃላፊነት የጎደለው እና ከፕሪቶሪያ ስምምነት ውጪ የሆነ ድርጊቱ ወጥቶ፣ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን አምስተኛውን ክረምት በአስከፊ ሁኔታ እንዳያሳልፉ ግዳጁን ሊወጣ ይገባል። የተፈናቃዮቹን ሁኔታ በአምባሳደርዋ፣ በተደራዳሪዋ እና በመላው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኩል የተከታተለችው አሜሪካ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ጊዜ የማይሽረው ቀውስ ተረድታ የድርሻዋን እንድትወጣ በድጋሚ እንጠይቃለን ሲል ህወሃት አዲስ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሦስት ዓመታት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅነት የአገልግሎት ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ ሀገረ ስብከታቸው መመለሳቸውን ምክንያት በማድረግ በባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
በአቀባበሉ ከሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ጀምሮ የተለያዩ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ተገኝተዋል።
የአቀባበል ሥርዐቱ በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል መንበረ ጵጵስና የቀጠለ ሲሆን የተለያዩ መርሐ ግብራትን በማቅረብ እየተከናወነ ይገኛል።
ፈለገ ገነት ሚዲያ
በአቀባበሉ ከሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ጀምሮ የተለያዩ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ተገኝተዋል።
የአቀባበል ሥርዐቱ በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል መንበረ ጵጵስና የቀጠለ ሲሆን የተለያዩ መርሐ ግብራትን በማቅረብ እየተከናወነ ይገኛል።
ፈለገ ገነት ሚዲያ
"ህወሓት የትግራይን ችግርን የመመለስ አቅም የለውም" - አዲሱ የጌታቸው ረዳ ፓርቲ ስምረት
በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን የተመሰረተው ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ በይፋ ሥራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡
ስምረት ፓርቲ ትግራይ በአንድ ሃሳብ ብቻ የምትራመድ ሳትሆን፣ የተለያዩ ሃሳቦች የሚንጸባረቁባት ክልል እንድትሆን እንደሚሰራም ኃላፊው ገልፀዋል። አክለውም፤ "ፓርቲው በዋናነት ያለፉ ስህተቶችን የሚያርምና የነገዋ ትግራይ ላይ አተኩሮ የሚሰራ ነው" ብለዋል።
በአንድ ወር ከግማሽ ጊዜ ውስጥ በትግራይ የምስረታ ጉባኤ እንደሚኖርና የፓርቲው መቀመጫ መቀሌ እንደሚሆን አቶ ረዳኢ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። ፓርቲው በመጪው ምርጫ እንደሚሳተፍም ተጠቁሟል፡፡
በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ ቡድን የተመሰረተው ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ በይፋ ሥራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡
ስምረት ፓርቲ ትግራይ በአንድ ሃሳብ ብቻ የምትራመድ ሳትሆን፣ የተለያዩ ሃሳቦች የሚንጸባረቁባት ክልል እንድትሆን እንደሚሰራም ኃላፊው ገልፀዋል። አክለውም፤ "ፓርቲው በዋናነት ያለፉ ስህተቶችን የሚያርምና የነገዋ ትግራይ ላይ አተኩሮ የሚሰራ ነው" ብለዋል።
በአንድ ወር ከግማሽ ጊዜ ውስጥ በትግራይ የምስረታ ጉባኤ እንደሚኖርና የፓርቲው መቀመጫ መቀሌ እንደሚሆን አቶ ረዳኢ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። ፓርቲው በመጪው ምርጫ እንደሚሳተፍም ተጠቁሟል፡፡
" ጋሽ እሸቱ "
ሰሞኑን ኮሜዲያን እሸቱ በአንዳንድ ወላጆች ነቀፌታንም አድናቆትም እየተቸረው ይገኛል::
ጉዳዬ እንዲህ ነው ኮሜዲያን እሸቱ ጋሽ እሸቱ የሚል አዲስ የልጆች ፕሮግራም የጀመረ ሲሆን ብዙ ተመልካችም እያገኘ ይገኛል
ነገር ግን እሸቱ በአንድ ወቅት በpodcast ስለ ልጁ ይታባረክ እሸቱ ተጠይቆ
ልጄ ፊት ስልክ አይደለም መንካት ማውራትም አይፈቀድም ልጄ ምንም አይነት ስልክም ሆነ የቴክኖሎጂ ውጤት እንዲያይ አይፈቀድለትም አጠገቡ እንኳን ጌም የሚጫወት ልጅ ስልክ ይዞ ከታየ ወዲያው
ልጄን እንዲርቅ ይደርጋል ብሏል::
በዚህም ለልጁ ስልክ እና ቴሌቭዥን የከለከለ አባት ለሌሎች ልጆችስ ለምንድን ነው ስልክ እና ቴሌቪዥን እንዲያዩ ይህን ፕሮግራም በብዝ ድካም እና ጥረት ያቀርባው የሚሉ አካላት የበረቱ እና ለልጁ የማይፈልገው ነገር ለሌሎች ልጆች ማቅረብ አለበት ወይ የሚሉ ጠያቄ ወላጆችን ፈጥሯል?
እናንተስ በዚህ ላይ ምን አይነት አስተያያት አላችሁ
በጭዋነት አስፍሩት እስቲ ?
Via Gursha Page
ሰሞኑን ኮሜዲያን እሸቱ በአንዳንድ ወላጆች ነቀፌታንም አድናቆትም እየተቸረው ይገኛል::
ጉዳዬ እንዲህ ነው ኮሜዲያን እሸቱ ጋሽ እሸቱ የሚል አዲስ የልጆች ፕሮግራም የጀመረ ሲሆን ብዙ ተመልካችም እያገኘ ይገኛል
ነገር ግን እሸቱ በአንድ ወቅት በpodcast ስለ ልጁ ይታባረክ እሸቱ ተጠይቆ
ልጄ ፊት ስልክ አይደለም መንካት ማውራትም አይፈቀድም ልጄ ምንም አይነት ስልክም ሆነ የቴክኖሎጂ ውጤት እንዲያይ አይፈቀድለትም አጠገቡ እንኳን ጌም የሚጫወት ልጅ ስልክ ይዞ ከታየ ወዲያው
ልጄን እንዲርቅ ይደርጋል ብሏል::
በዚህም ለልጁ ስልክ እና ቴሌቭዥን የከለከለ አባት ለሌሎች ልጆችስ ለምንድን ነው ስልክ እና ቴሌቪዥን እንዲያዩ ይህን ፕሮግራም በብዝ ድካም እና ጥረት ያቀርባው የሚሉ አካላት የበረቱ እና ለልጁ የማይፈልገው ነገር ለሌሎች ልጆች ማቅረብ አለበት ወይ የሚሉ ጠያቄ ወላጆችን ፈጥሯል?
እናንተስ በዚህ ላይ ምን አይነት አስተያያት አላችሁ
በጭዋነት አስፍሩት እስቲ ?
Via Gursha Page
ዛሬ 23/ 09/2017 ዓም ከጎንደር ጭልጋ (አይከል ) መተማ መንገድ ሸቃጣሸቀጥ ጭኖ እየተጓዘ የነበረ የጭነት መኪና ሜዳ ላይ መኪናው ላይ በሚታየው መልኩ ተኩስ በመክፈት ሹፌሩን በ4 ጥይት በመምታት ረዳቱን ጨምሮ ሌሎች ሰወችን አፍነው ወስደዋል አሽከርካሪው በአይከል ሆስፒታል የህክምና እርዳታ አየተደረገለት ይገኛል።
ይህ አካባቢ በቅርብ አንድ በሬ የጫነ FSR ሹፌር ረዳት ሌሎች ሰወችን ጨምሮ በድምሩ 5 ሰወችን ማገታቸውን ገልፀን ሌላው መንገዱን ከመጠቀም እንዲታቀብ ጥሪ አቅርበን ነበር ሰሚ ባለመኖሩ እየሄደ ይታገታል ይመታል።
እንግዲህ የ Ethiopian Federal Police ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የሀገሪቱ መንገዶች ማንም ያለስጋት የሚንቀሳቀስባቸው እንዲሆኑ አድርገናል ያሉት በአሽከርካሪ ላይ ቀን በቀን በሚባል ደረጃ እገታ ጉዳት እየደረሰ ባለበት ሂደት ነው።
የሾፌሮች አንደበት
ይህ አካባቢ በቅርብ አንድ በሬ የጫነ FSR ሹፌር ረዳት ሌሎች ሰወችን ጨምሮ በድምሩ 5 ሰወችን ማገታቸውን ገልፀን ሌላው መንገዱን ከመጠቀም እንዲታቀብ ጥሪ አቅርበን ነበር ሰሚ ባለመኖሩ እየሄደ ይታገታል ይመታል።
እንግዲህ የ Ethiopian Federal Police ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የሀገሪቱ መንገዶች ማንም ያለስጋት የሚንቀሳቀስባቸው እንዲሆኑ አድርገናል ያሉት በአሽከርካሪ ላይ ቀን በቀን በሚባል ደረጃ እገታ ጉዳት እየደረሰ ባለበት ሂደት ነው።
የሾፌሮች አንደበት
ሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ14 ሀገራት ላይ የቪዛ እገዳ ጣለች!
ሳውዲ አረቢያ በድምሩ በ14 ሀገራት ዜጎች ላይ የብሎክ ቪዛ ማውጣትን በጊዜያዊነት ማገዷን አስታውቃለች።ከነዚህ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ ሀገራት ይገኙበታል።
ይህ የቪዛ እገዳ አዲስ የጊዜያዊ የሥራ ቪዛ ማመልከቻዎችን እና በመጠባበቅ ላይ ያሉትንም የሚመለከት ነው የተባለ ሲሆን በውጭ ዜጎች የሥራ ኃይል ላይ የተመሰረቱ የሳውዲ አረቢያ ዘርፎችን እንደሚጎዳ ተገልጿል።
በእገዳው ሰለባ ሆነዋል ከተባሉት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፣ ግብፅ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ ሱዳን፣ ቱኒዚያ እና ሞሮኮ ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ የመን፣ ህንድ፣ ፓኪስታን እና ባንግላዲሽ ተካትተዋል።እነዚህ ሀገራት ከሳውዲ አረቢያ ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍልሰትና የገንዘብ ዝውውር ስለሚያገኙ፣ እገዳው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያስከትል እንደሚችል ተዘግቧል።
የብሎክ ቪዛ የሳውዲ አረቢያ ቀጣሪዎች ቀድሞ በተፈቀደላቸው ኮታ የውጭ ሠራተኞችን እንዲቀጥሩ የሚያስችል ነው። የሳውዲ አረቢያ መንግስት የቪዛ እገዳውን የጣለበትን ዝርዝር ምክንያት ባይገልጽም፣ ይህ እርምጃ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ዕጣ ፈንታ አጣብቂኝ ውስጥ ሊጥል እንደሚችል ካፒታል ለመረዳት ችሏል።
Via Capital
ሳውዲ አረቢያ በድምሩ በ14 ሀገራት ዜጎች ላይ የብሎክ ቪዛ ማውጣትን በጊዜያዊነት ማገዷን አስታውቃለች።ከነዚህ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ ሀገራት ይገኙበታል።
ይህ የቪዛ እገዳ አዲስ የጊዜያዊ የሥራ ቪዛ ማመልከቻዎችን እና በመጠባበቅ ላይ ያሉትንም የሚመለከት ነው የተባለ ሲሆን በውጭ ዜጎች የሥራ ኃይል ላይ የተመሰረቱ የሳውዲ አረቢያ ዘርፎችን እንደሚጎዳ ተገልጿል።
በእገዳው ሰለባ ሆነዋል ከተባሉት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፣ ግብፅ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ ሱዳን፣ ቱኒዚያ እና ሞሮኮ ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ የመን፣ ህንድ፣ ፓኪስታን እና ባንግላዲሽ ተካትተዋል።እነዚህ ሀገራት ከሳውዲ አረቢያ ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍልሰትና የገንዘብ ዝውውር ስለሚያገኙ፣ እገዳው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያስከትል እንደሚችል ተዘግቧል።
የብሎክ ቪዛ የሳውዲ አረቢያ ቀጣሪዎች ቀድሞ በተፈቀደላቸው ኮታ የውጭ ሠራተኞችን እንዲቀጥሩ የሚያስችል ነው። የሳውዲ አረቢያ መንግስት የቪዛ እገዳውን የጣለበትን ዝርዝር ምክንያት ባይገልጽም፣ ይህ እርምጃ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ዕጣ ፈንታ አጣብቂኝ ውስጥ ሊጥል እንደሚችል ካፒታል ለመረዳት ችሏል።
Via Capital