ጆሽዋ የቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መ/የህብረት ሥራ ማህበር Joshua Saving & credit cooperative
905 subscribers
482 photos
4 videos
1 file
14 links
ማህበራችን የሚሰጣቸው አገልግሎቶች የቁጠባና የብድር እንዲሁም አነስተኛ የብድር መድህን
+251-11-558-4416/18
+251-11-558-29-70
+251-11-558-20-66
+251-11-470-72-11
+251-11-470-21-99
+251-11-557-40-92
+251-11-369-41-79
+251-11-666-11-02
09935315330 0930050687
www.joshuaet.com
Download Telegram
በህዳር 07 ቀን 2017 ዓ.ም ከተለያዩ ቅርንጫፎች ለተመረጡ የማህበሩ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የምክክር ጊዜ በማህበሩ ዋና ጽ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ተደርጓል፤

በዕለቱም የተገኙ አባላት ለማህበሩ መጠናከር እና መሻሻል የሚገባቸዉን አስተያየት እና ጥያቄ አቅርበዋል ፤ ከማህበሩም የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ እና ማብራርያ ተሰቷቸዋል፤

በተጨማሪም የዕጣ/አክሲዮን መጠናቸዉን፣ ቁጠባቸዉን ለመጨመርና ለሌሎች ሰዎች ወደ ማህበሩ እንዲቀላቀሉ ለመናገርና ለመጋበዝ ቃል በመግባት እንዲሁም በዕለቱም በገቡት መሰረት በመከፈል መልካም ጊዜ አሳልፈናል፡፡
ይህ ከአባላት ጋር የመገኛኘትና የመመካከር ሂደት በሌሎችም አባላቶች ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡
🙏7👍4🤝1
ከማህበሩ ቀደምት አባል ከሆኑት መምህር አለማየሁ አጋ ጋር የተደረገ የምስክርነት ቆይታ ፤
• መምህር አለማየሁ አጋ ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ የጆሽዋ ቁጠባና ብድር አባል ናቸዉ፤ሲቆጥቡ ሰንብተዉ ለትምህርት ቤታቸዉ ኡርጂ በሪ ኬጂ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፍያ እንዲሆን ብድር ጠየቁ፤ የሚያስፈልጋቸዉን ብድር ጆሽዋ ቁ/ብ/ኃ/የተ/መ/የህ/ሥራ ማህበር አቀረበላቸ እሳቸዉም፤ በታማኝነት በወቅቱ መለሱ፤ ቀጥለዉም በተደጋጋሚ እየተበደሩ መልሰዉ አሁን ላይ አንድ ሚሊዮን ብር ተበድረዉ በአግባቡ በመመለስ ላይ የሚገኙ ታታሪ ፣ ጠንካራ የሥራ ሰዉ ናቸዉ ፡፡
• መምህር አለማየሁ ትምህርት ቤታቸዉን ሲጀምሩ 22 ህጻናት በመያዝ ነበር በአሁኑ ወቅት ግን ትምህርት ቤቱን አስፋፍተዉ የተማሪዎቻቸዉ ቁጥር 477 አድርሰዋል ፤ ለወደፊቱም ከዚህ ለመጨመር ከጆሽዋ ጋር አብሮ ለመስራት ብዙ እቅድ አላቸዉ ፡፡
• በአሁኑ ወቅትም በኡርጂ በሪ ትምህርት ቤት 30 ለሚሆኑ መምህራንና የአስተዳደር ስራ የሚሰሩ ሠራተኞችን የሥራ ዕድል ፈጥረዉ በማስተዳደር ላይ ይገኛሉ፡፡
• በተጨማሪም ትምህርት ቤቱ በአከባቢዉ ለሚገኙ ማህበረሰብ እጅግ ከፍተኛ የሆነ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ በቦታዉ ተገኝተን መመልከት ችለናል፡፡
• መምህር አለማየሁ ስለ ጆሽዋ ቁጠባና ብድር ሲያብራሩ እጅግ ባለዉለታቸዉ እንደሆነ ከትንሽ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እያገዛቸዉ እንደሚገኝ ትናንት በእግራቸዉ እንደሚንቀሳቀሱ ዛሬ ግን መንቀሳቀሻ መኪና እንዳላቸዉ አብራርተዋል ፤ ለወገኖችም መልእክትም ሲያስተላልፉ ወደ ጆሽዋ ቁጠባና ብድር እንዲመጡና አባል በመሆን ቆጥበዉ በመበደር እራሳቸዉን ጨምሮ ለሌሎች መትረፍ እንዲችሉ አበረታታለዉ ብለዋል ፡፡

በተጨማሪ ከመምህር አለማየዉ አጋ አንደበት እንከታተል ፡፡

ምስክርነቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የጠዋት ገበያ ፕሮግራም ላይ ጥር 07 ቀን 2017 ዓ.ም የተላለፈ ነዉ ፡፡
👍51🤝1
ሁለተኛ እንግዳ ወ/ሮ ዋጋዬ አንባቸዉ ይባላሉ የጆሽዋ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መ/የህ/ሥራ ማህበር የረጅም ጊዜ አባልና የብድር ተጠቃሚ ናቸዉ ፤
• የሻሎም የመኪና እጥበት ድርጅት ባለቤት ናቸዉ፤ ድርጅቱ የከርሰ ምድር ዉሃ በማዉጣት ለመኪና ፣ ምንጣፍ እጥበት እንዲሁም ለግለሰብና ለድርጅት ዉሃ ማቅረብ ስራ ላይ የተሰማራ ነዉ፤
• ድርጅታቸዉን ሲጀምሩ በሦስት ሠራተኛ ነበረ ከጆሽዋ መቶ ሺህ በመበደር ማስፋፋት አሰቡ ተበደሩ እንዳሰቡትም አደረጉት ተሳካላቸዉ፤ ብድሩን ቀጥለዉም ሦስት መቶ ሺህ ተበድረዉ የበለጠ ስራቸዉን አጠናከሩበት፤ለወደፊቱም ብዙ እቅድ አላቸዉ ከአያያዛቸዉ እንደሚሳካላቸዉ ምንም ጥርጥር የለዉም ፡፡
• በአሁኑ ወቅት በሻሎም መኪና እጥበት 25 ሠራተኖች የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸዉ እየሰሩ ይገኛሉ፤
• ወ/ሮ ዋጋዬ በአሁኑ ወቅት ልጆቻቸዉን ለቁም ነገር አብቅተዉ ዉኃ ማመላለሻና መሸጫ እና መንቀሳቀሻ መኪና ባለቤትም ሆነዋል ፤ ለአከባቢዉ ማህበረሰብም ብዙ እገዛዎችን በማድረግ ላይ የሚገኙ እጅግ ብርቱ ሠራተኛ ናቸዉ ፡፡
• ወ/ሮ ዋጋዬ አንባቸዉ በመልእክታቸዉ በተለይ በተለይ ለሴት እህቶቻችን አርአያ እንደመሆናቸዉ መጠን ወደ እርሳቸዉ ቢመጡ ምክር እንደሚሰጡ፣ እንደሚያበረታቱ አበክረዉ ገልጸዋል ፤ መሻሻል ካሰቡ ጆሽዋ አባል ሆነዉ በመቆጠብ ተበድሮ እንደእሳቸዉ መለወጥ አልፎም ለሌሎች መትረፍ እንደሚቻል ገልጸዋል ፤የእሳቸዉ ምስክርነት ከበቂ በላይ መሆኑን በቦታዉ ተገኝተን ባደረግነዉ ቅኝት ለመረዳት ችለናል ፡፡

ተጨማሪዉን ከወ/ሮ ዋጋዬ አንባቸዉ አንደበት እንከታተል ፡፡

ምስክርነቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የጠዋት ገበያ ፕሮግራም ላይ ጥር 07 ቀን 2017 ዓ.ም የተላለፈ ነዉ ፡፡
👍7🙏1
በኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ለ11ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ለ4ኛ ጊዜ በጋራ የተዘጋጀዉ ኤግዚብሺንና ባዛር በአዲስ አበባ ኤግዚብሽን ማዕከል ዛሬ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተጀምሯል ፡፡
ጆሽዋ ቁጠባና ብድር ህ/ሥ ማህበር ተጋባዥ በመሆን እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
የተወደዳችሁ አባላት በማዕከሉ በመገኘት የዝግጅቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኃል ፡፡
🙏5🤝2
ማህበራችን ጆሽዋ ሲሳተፍበት የነበረዉ የኅብረት_ስራ_ኤግዚቢሽን-ባዛርና ሲምፖዚየም 2017 ዓ.ም ተጠናቀቀ።

በኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮምሽን እና በአዲስ አበባ ኅብረት ስራ ኮምሽን በጥምረት  ከ ጥር 28- የካቲት 3 ቀን 2017ዓ.ም የተዘጋጀው ኤግዚቢሽን፣ ባዛርና ሲምፖዚየም በስኬት ተጠናቋል።

በከተሞች አካባቢ በግብርና ምርቶችና ሸቀጦች ላይ ለሚፈጠረው ያልተገባ የዋጋ ንረት ኀብረት ሥራ ማህበራት አምራቾችን ከከተማ ሸማቾች ጋር በቀጥታ የግብይት ትስስር በመፍጠርና አላስፈላጊ የግብይት እሴት ሰንሰለቶችን በማስቀረት ምርቶችና ሸቀጦች ለዜጎች ፍትሃዊ በሆነ የገበያ ዋጋ ተደራሽ እንዲሆን ለማድረግ እያደረጉ ያሉት ጥረቶች ተጠቃሽ  መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮምሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ገልፀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ኅብረት ስራ ኮምሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በመዝጊያ  መርሀ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር ከ300 በላይ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለግብይት በመቅረብ  አምራችና ተጠቃሚን በቀጥታ አገናኝተዋል ሲሉ ተደምጠዋል።

በማጠቃለያም ለፕሮግራሙ መሳካት ከጎን ለሆኑ ልዩ ልዩ አጋር ድርጅቶች እና ማህበራት የምስጋና እና እውቅና በመስጠት መርሀ-ግብሩ በደማቅ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ተጠናቋል፡፡
👍8👏31