ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
27.7K subscribers
346 photos
9 videos
91 files
89 links
Join @Rovibook
😎
<|>
/\
👢👢

መካሪ ከተገኘ ህይወት ቀላል ነው!!
ለማንኛውም ማስታወቂያ ነክ ጉዳዮች @RASNAMRUD ያናግሩን
Download Telegram
እንደምን አመሻችሁ የመፅሐፍት ዓለም ቤተሰቦች
ለትረካ ስራ በአካል ተወዳዳሪዎች የነበራችሁ ስለመጣችሁ ሁላችሁንም ከልብ እናመሰግናለን አሁን ውጤቶችሁን የምንገለገልበት ስዓት ነው ከዛ በፊት 2ነገሮችን ልበል
1ኛ በሆንላይን(@heny10)ላይ ከአሜን ባሻገር ገፅ 33 እያነባችሁ የላካችሁልኝ ልጆች ውጤት ገና ነው ስለዚህም ይሄ ውጤት እናንተን አያካትትም
2ኛ በአካል ስቱዲዮ መጥታችሁ ድምፃችሁን ወስደን የዛሬው ውጤት ላይ ያላለፋችሁ ግን መተረክ እምትፈልጉ ልጆች ደስ እያለን እንቀበላቸዋለን (ክፍያ ለጊዜው ባይኖረውም የምንቀጥራቸው ልጆች በሌሉበት ሠዓት እናንተ በክፍያ ግን ትሰራላችሁ )
ስለዚህም ከዚ በታች ያላችሁ ልጆች ለቀጣዩ ለመጨረሻ ዙር አልፋችኋል
1ኛ ቤተሌሄም ይመር
2ኛ ሀይለሚካሄል ዳንሄል
3 ዮናስ አይናለም
4ኛ ታደለ ሽመልስ
5ኛ እየሩሳሌም ሰለሞን
6ኛ ምስክር አበራ
7ኛ ሳሙኤል ጌታቸዉ
8ኛ ሱራፌል ሙልዬ
9ኛ ትዕግሥት አበበ
10 ብሩክ ጫላ
እናመሰግናለን ሁላችንም ስለዚህ ከላይ ስማችሁ የጠቀስኩት ቀጣይ ፈተና ይኖራል ስለሁሉም ከልብ እናመሰግናለን ።
ለማንኛውም ጥያቄ
📞+251938753747
@heny10
ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹 pinned «☎️️ ምርትና አገልግሎታችሁን እንዲሁም አዲስ የከፈታችሁትን ቻናል ወይም ግሩፕ ማስተዋወቅ ለምትፈልጉ ማስታወቂያ ቻናላችን ላይ በታላቅ ቅናሽ እንሰራለን☎️0946900453 💢በሰአት 👇👇👇 🔆ለ1 ሰአት 👉 50ብር 🔆ለ2 ሰአት 👉 100ብር 🔆ለ4 ሰአት 👉 200ብር 🔆ለሙሉ ቀን 👉 300 ብር (ለ12ሰአት) * 🔆500 view 👉 100 birr 🔆1k view 👉 150 birr 🔆2k view…»
AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

#ስውር_አይን

የመርሐ ግብሩ መሪ እኒያን ሊቅ ሲያስተዋውቅ "በአይነ ሥውር አቅማቸው ይህን ሁሉ ትምህርት ተምረው ይህም ያህል ደቀ መዛሙርት አፍርተው.....እያለ በእርሱ አመለካከት ማድነቅ ያለውን ነገር አወረደው፡፡

ሊቁ ግን ሲነሱ:- "ይህ ወንድሜ ያለውን ሰምቻለሁ ፡፡ በዓይነ ስውር አቅማቸው.......ብሏል፡፡ ወንድሜ #አምፑል ተቃጠለ ማለት መብራት ሄደ ማለት አይደለም ዓይነ ስውር ማለት የሳሎኑን መብራት አጥፍቶ የጓዳውን አብርቶ የተቀመጠ ነው ብለዋል፡፡...."፡፡በእርግጥም ሊቅ ናቸው፡፡

የሚንከባለል ዓይን ያለው አብዛኛው ሰው የጓዳውን አጥፍቶ የሳሎኑን አብርቶ የተቀመጠ ነው፡፡

የላይኛው ዓይን አምፑል ነው፡፡ አምፑል የሚሰራው በራሱ አይደለም ዓይንም ያለ ልብ ከኃይል ምንጩ እንደተለያየ አምፑል ነው፡፡ ማስተዋል ከሌለ የላይኛው ዓይን ከጌጥነት አያልፍም፡፡ እግዚአብሔር የሠራውን ለማድነቅ የወደቁ ሰዎችን ለማንሳት ወዳጆችን በፍቅር ለመመልከት.....የሚያገለግለው የውስጥ ዓይን እንጂ የውጭ አይን አይደለም፡፡

ጌታችን ወደዚህ ዓለም የመጣው እያዩ የማያዩትን እናያለን እያሉ የማያስተውሉትን ሳያዩ እንመራለን የሚሉትን ለመውቀስ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚታየው እውነት የሚገኘው በውስጥ ዓይን እንጂ በላይ ዓይን አይደለም፡፡


ወደ ተመስጦ ስንገባ ዓይናችንን እንጨፍናለን፡፡ የላይኛው ዓይን ባካና ያደርጋል፡፡ ለኅሊና የቤት ስራ እየያዘ ይመጣል፡፡

የቀደሙት አባቶች የቋንቋ እውቀታቸው ይደንቃል፡፡ ሲሰይሙ "ዓይነ ስውር" ብለዋል፡፡ ሥውር አይን ያለው ማለት ነው፡፡ አንዱ የግልፅ አንዱ የውስጥ ዓይን ተደርጎለታል ማለት ነው፡፡ የላይኛው ዓይን ማጣት ሳይከለክላቸው ብዙ ታላላቅ ሥራ የሠሩ ሊቃውንትን ይቺህ ዓለም አስተናግዳለች፡፡

የላይኛውን ብርሃን ማጣት ኃጢያት አይደለም፡፡ በውስጥ ጨለማ ተዝናትቶ መቀመጥ ግን ሀጢያት ነው፡፡ የላይኛው በተዓምራት ይወገዳል የውስጥ ጨለማ ግን ያለትምህርትና እምነት አይወገድም፡፡

ዓይን ተመልሳ እራሷን አይታ አታውቅም፡፡ ሌሎችን ታያለች ራሷን ግን አታይም፡፡ ሌሎች ያጎደሉት ትገመግማለች የራሷን ግን አታውቀውም፡፡ የላኘኛዋ ዓይን ለሌሎች የሆነውን እያየች #ቅንዓትን የሌሎችን ሰላም እያየች #ምቀኘነት የሌሎችን መውደቅ እያየች #ፍርድን የሌሎች ርኩሰት እያየች #ውድቀትን ይዛ ትመጣለች፡፡

#በላይኛው_አይን_ብቻ_ማልቀስ_አይቻልም

በመንገድ ላይ እናቶቻችን "እያዩኘ ሰላም ሳችሉኘ አለፉ" ስንላቸው የተለመደ መልስ ይሰጣሉ፡- "አይ ልጄ የሚያየው ልብ እንጂ ዓይን መሰለህ?" ይላሉ፡፡

ትልቁ ብርሃን ያለው ልብ ላይ ነው፡፡ የልብ ብርሃን ከጨለመ የላይኛው አይቶ #መርገጥ አይቶ #መጠንቀቅ አይቶ #ማዘን አይችልም፡፡

ሥውር ዓይን ያስፈልጋል፡፡ ሥውር ዓይን ሲኖረን:-

✿ ያለንን እናውቃለን፡፡ ስለጎደለን የምንጨነቀው ያለንን በትክክል ስላላወቅን ነው፡፡

✿እግዚአብሔር ዛሬም በሥራ ላይ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ስለዚህ ተስፋችን ይታደሳል፡፡

✿ በአሁኑ ሁኔታ ሕይወትን አንመዝን፡፡ አሁን ያለው ደግም ይሁን ክፉ እርሱ መጨረሻችን አይደለም፡፡ #የሚመጣው_የሚልቀው_ነው፡፡

✿ ለጎዱን ሳይቀር በችግራቸው እንገኛለን፡፡

✿ በተገፉት ላይ አንጨክንም፡፡ ዓለም ተራ መሆኑ ይገባናል፡፡

✿ ለሌሎች ማካፈል አንረሳም፡፡ ሌሎች እኛ ጋ ድርሻ አላቸው፡፡

✿ አንደበታችንን እንገዛለን፡፡ መልካሙን ቀን ለማየት አንደበትን መቆጣጠር ያስፈልጋልና፡፡

እርሱ ሥውር አይን ይፍጠርልን🙏🙏🙏😊😊


@jahABP ነኘ ሳነብ ካገኘሁት መልካም ሰዎችን ይገልፃል ብዬ አሰብኩና እንዲህ አቀረብኩት፡፡

😍ክብር ይስጥልኘ🙏

አስተያየታችሁን አድርሱኘ፡፡

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

" #አትድገሙ

ክፉ ነገር በማሰብ ይጀምራል፡፡ በማድረግ ይደመደማል፡፡ ማሰብ ለክፋት ፅንሰቱ ማድረግ ልደቱ ነው፡፡ ክፉ ነገር በማድረግ እየተገለጠ ይመጣል፡፡ ክፉ ነገርን የጦር ኀይል የፍርድ ጽናት የቅጣት ብዛት አያስቆመውም፡፡ክፉ ማሰብ ባለቤቱን ይበክላል ክፉ መናገር የጎረቤትን ሰላም ያናጋል አዕምሮን ያቆሽሻል ክፉ ማድረግ ማድረግ ማህበረሰብን ይጎዳል ያፈናቅላል፡፡ ክፉን መድገም ያደነድናል፡፡

#ያለመውደቅን_ያህል_ወድቆ_መነሳት_ክብር_ነው፡፡

የማይወድቅ የለም መልዐክ ካልሆነ የማፀፀት የለም ሰይጣን ካልሆነ፡፡

መድገም ማስተጋባት ነው፡፡ የሌሎችን ክፋት ማወደስ ለክፋት በነፃ ማስታወቂያ መስራት ነው፡፡ ሳይከፍሉን በቅዱስ አደባባይ ርኩስ ማስታወቂያ መስራት ነው፡፡ አንድ ጊዜ ክፉ ነገርን ከሚፈፅሙለት ይልቅ ደግመው በሚያወሩለት ሰይጣን ይደሰታል፡፡ ኃጢያት በተግባር ከሚፈፅሙ በምኞትና በትዝታ የሚጨልጡ ይበዙለታል፡፡

ሰው ነንና ክፉ ነገር እናስብ ይሆናል አለመናገር መልካም ነው፡፡ ሰው ነንና ተናግረን ይሆናል አለማድረግ ግን የተሻለ ነው ሰው ነንና አድርገን ይሆናል አለመድገም ግን መልካም ነው፡፡ መድገም መስራት ብቻ ሳይሆን ማስተዋወቅም ነው፡፡ ነገሩን ደግሞ ማውራት አይገባም፡፡

አዝረከርካለው ያልነውን ጉዳይ አንሰራፍተነው ሊሆን ይችላል፡፡ መድገም ብዙ ደቀመዝሙርትን ያፈራል፡፡ "ክፉ ነገርን አትናገሩ ደግማችሁም አታውሩ" ለምን ስንል፡- ያደረገ ካለ ይደፍራል ያሰበ ካለይፈፅማል የጀመረ ካለ ብቻዬን አይደለሁም ይላል የፈራ ካለ ልብ ያገኛል አደራረጉ የጠፋው ካለ ስልቱን ያገኛል፡፡

ክፋ ነገርን እግዚአብሔር ይገስፅህ በማለት መቅበር ያስፈልጋል፡፡
ዝርዝር ማውራት ለሴጣን ስፖንሰር መሆን ነው፡፡ ይህን ለመገንዘብ መንፈሳዊ ሰው ብቻ ሳይሆን ጨዋ አስተዳደግም በቂ ነው፡፡

#እጅግ_ግልፅነት_እብደት_ነው፡፡

ሰይጣን ዋንኛ ስራ ጆሮን ማስለመድ ነው፡፡ ጆሮን ማስለመድ የፖለቲካ ትልቅ ስልት ነው፡፡ የክፉዎች ትልቅ መንገድ ነው፡፡ ጆሮ ከለመደው አፈፃፀሙ ቀላል ነው፡፡ የምንናገረውን ሰዎች ይለማመዱታል ማስደንበርን ነው የምንፈራው ከዛም የተለየ ነገር አለ፡፡

ብዙ ክፉ ድርጊቶች ሲወሩ ይብሳሉ፡፡
ዝርዝር የሚወራው የእግዚአብሔር ፍቅር ነው፡፡ ዛሬ ግን አጋንትን እያስለፈለፉ ትምህርት እንሰጣለን እየተባለ ነው፡፡ የሐሰት አባት ከተባለው የእውነት መረጃ እየተፈለገ ነው፡፡ ስብከት ሲያልቅብን ወደዚህ መግባታችን ያሳዝናል፡፡"

"መጥፎን ነገር እንደምንጠላ የሚያረጋግጥልን ስራችን ብቻ ነው" እና ከክፉ እንራቅ መልካምነትን እንዝራ እላለሁ

@jahABP ነኘ አሰተያየታችሁን አድርሱኘ መልካም ጊዜ ተመኘሁ፡፡
😍😁👍🙏

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

" #የተበላሸ_ማሞቂያ

ጨርሰው የማይሰሩ አሳሳቢ አይደሉም አይሰሩምና ብልሽት ያለባቸው ማሞቂያዎች ግን ሰውየው ሲሞክራቸው ይሰራሉ ልብሱን አውልቆ ሲገባ ያረጥባሉ፡፡ ዓይኑን መግለጥ ከመታጠቢያው መውጣት በማይችልበት ሰዓት ሙቀታቸቅን መስጠት ያቆማሉ፡፡

ሰውየው በአይኑ ሳሙና ገብቷልና ልብሱን ለመልበስ እንኳን ከውሃ ያለፈ ገላውም ሳሙና ብቻ ነውና ማሞቂያው ስለተበላሸ የፈራውን ቅዝቃዜ የፈራውን እንቅጥቅጥ በግድ ይጋፈጣል፡፡ በሙቀት ጀምሮ በቅዝቃዜ በመጨረሱ ይንቀጠቀጣል፡፡

የተበላሸ ማሞቂያ ሲገጥመን ሁል ጊዜ የወረት ያስታውሰናል በሙቀት ጀምሮ በቅዝቃዜ መጨረስ የዚህ ዓለም መገለጫ ሆኗል፡፡ በኡኡታ ሠርግ በግልግል ማሬ የሚለው ቃል እሬቴ በሚል....ይለወጣል፡፡

ጨርሰው ጨካኘ ፈጽመው ክፉ የሆኑትነ አንሞክራቸውም አንቀርባቸውም ብንቀርባቸውም ተጠንቅቀን ነውና አይጎዱንም፡፡

እነደተበላሸው ማሞቂያ በሙቀት ጀምረው በቅዝቃዜ የሚጨርሱ አረጋግተው ቀጥል የሚያንቀጠቅጡን ስሜት አልባ አድርገው ቀጥለው የሚያሳምሙ አስደስተው ቀጥሎ እትትትትት.....የሚያሰኙ ብዙዎች ናቸው፡፡


ፍፁም እስክንራቆት ያባበሉን ሌላ ማየት እስከማንችል ያወሩን በማይዘልቀው ሙቀታቸው ያታለሉን የትም መሄድ እንደማንችል ሲረዱ ይለዋወጣሉ፡፡ በረዶአቸውን ማዝነብ ይጀምራሉ፡፡

ስለተለወጡብን ሰዎች ከማሰብ ስለተለወጥንባቸው ማሰብ የተሻለ ነው፡፡ በሞቀው ሰላምታ ጀምረን ያኮረፍናቸው ፍፁም ሚስጥራቸውን ከሰማን በኀላ ገሸሽ ያልናቸው ሌላ ማየት ሲያቅታቸው አውረን የተለየናቸው አውላላ ሜዳ ላይ መሪ ፈልገው ሲንከራተቱ የሳቅንባቸው ሊኖሩ ይችላሉ፡፡

ምናልባት ዛሬ ሰው የማይወጣልን ሰው ገፍተን ሊሆን ይችላል፡፡ የዛሬውን የሚመጥነን ቅጣት ነውና በሚደርስብን ልንደሰት ይገባል፡፡

ትላንትን መልሰን መኖር ቢያቅተን በንሰሐ ማደስ እንችላለን፡፡ እነዚያንም ሰዎች መካስ እንችላለን፡፡
የንሰሐ የይቅርታ ዘመን ዕድል ነውና ሊያልፈን አይገባም፡፡

#ዛሬም_ከተለዋዋጭ_ማንነት_እንጠበቅ፡፡

#ሰው_እንጂ_አካባቢውን_የምንመስል_እስስት_አይደለንም፡፡

ጌታ ሆይ እውነተኛ ፍቅርን እንዳንገፋ እባክህን እርዳን፡፡ "

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ
መልካም ምሽት

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
AB PHOTOGRAPHY & GRAPHIC DESIGN

#እግር_በእግር

አንድ ቀን ሰይጣን በመንደሩ ወደሚፈሩት እና ወደ ሚከበሩት አስር አለቃ ደባልቄ ግዛው ቤት ሔደና ቀዳሚሚ ተከታይም ሳያደርግ "ደባልቄ!!" ብሎ በስማቸው ጠራቸው፡፡

አስር አለቃ ፊታቸውን በቁጣና በግርምት አኮማትረው ድምፁን ወደሰሙበት ዞር ቢሉ በአካባቢው ሰው የሚባል የለም፡፡ እዚህ ሰፈር አንድም ሰው የአስር አለቅነትን ማዕረጋቸው ሳያስቀድም የአባቻቸውን ስም ሳያስከትል እንዲህ ንፋስ እንዳነሳው ፌስታል ስማቸውን ለብቻው አንጠልጥሎ የሚነሳ ሰው የለም፡፡

እንኳን ሰው የዚህ ሰፈር ሰይጣን ቢሆን ራሱ እንደዚህ አስር አለቃን አቃሎ እና አበሻቅጦ ይጠራቸዋል ተብሎ አይታሰብም፡፡ እንዴት ሆኖ! ምን ሲደረግ...!

እንግዲህ አስር አለቃ የተጣሉ ባልና ሚስት አስታርቀው ገና መመለሳቸው ነበር፡፡ ልክ በራቸው ላይ ሲደርሱ ነው ሰይጣን የጠራቸው፡፡ ምን ይጠራቸዋል ያዋረዳቸው እንጂ! ቢሆንም 'ጆሮዬ ነው' ብለው ወደ ቤታቸው ግቢ ሊገቡ ርምጃ ሲጀምሩ፣

"አንተ ደባልቄ ! የሚደባልቅ ይደባልቅህ! ሲጠሩ አትሰማም!? ደንቆሮ!!" ብሏቸው እርፍ፡፡ በዚህ ቢበቃማ ጥሩ ነበር "ምን ያራሩጥሃል? ያቺ መንሽ እግር ሚስትህ እንደሆነች የትም አትሔድብህ ተወዝፋ ነው የምትጠብቅህ" ሲል ዘለፋቸው፡፡

አስር አለቃ መጀመሪያ በተናጋሪው ድፍረት ግርርርርርርርርምምምምምም አላቸው ቀጥሎ የንግግሩ ትርጉም አዕምሮአቸው ውስጥ ሲተረጎም ደማቸው ፈላ፡፡ ላለፉት አርባ ዓመታት እንዲህ ተንቀውም እንዲህ ደማቸው ፈልቶም አያውቅም፡፡ ከዘራቸውን ጠበቅ አድርገው ጨበጡና ድምፁን ወደሰሙበት ፎክረው ዞሩ፡፡

"ያንበሳው ግልገል!" በአካባቢው የሰው ዘር የለም!!

"እንኳን ፊቴ ያላገኘሁት ደመ ከልብ አድርጌው ዘብጥያ መውረዴ ነበር፡፡" አሉና ከዘራቸውን ወደ ግራ እጃቸው አጋብቸው ከዘራ በያዙበት እጃቸው አማተቡ፡፡

"ሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂ..." የሰይጣን የሚያበሳጭ እና የሚሰቀጥጥ ሳቅ ጆሮአቸው ሥር ተቅለጨለጨ.......

" ድሮም ከእግዜራችሁ በፊት ዱላችሁ ነው ትዝ የሚላችሁ....ነውጠኛ ሁሉ.... #የምትዠልጠው_ስታጣ_ታማትባለህ? አይሸፋፋው አስር አለቃ....ሂሂሂሂሂ ሁሁሁሁ ቂቂቂቂቂ..." አለ ሰይጣን ግቢ ግቢያቸው ውስጥ ቀድሞ ገብቶ #ካሉበት_አርባ_ክንድ_ርቆ ከቆመ በኀላ፡፡

አስር አለቃ ግራ ተጋቡ፡፡ ንዴታቸውን ዋጥ አድርገው እየተጣደፉ በቁጣ ወደ ቤታቸው በር ገሰገሱ፡፡

አስር አለቃ አቋማቸው እንደሰምበሌጥ ቀጥ ያለ ስፖርተኛ አቋም ነው፡፡ ሰው ሁሉ "አቤት ቁመና!!" ይላቸው፡፡ ሰይጣን ግን ወደ ቤታቸው ሲጣደፉ የሚያበሽቅ ንግግር

"ሸፋፋ ..ሸፋፋ ትላለህ! ሲራመዱ አይተህ...ደግሞ ወታደር ነኘ ይላል እንዴ? ይሄን ደጋን የመሰለ እግር ይዞ ሂሂሂሂሂሂ...እንኳን አገር ልትጠብቅ በዚህ ሸፋፋ እግርህ ሚስትህንም አትጠብቅ ተመልከት የእግርህን ክፍተት በልጅነትህ ፀሐይ አላሞቀችልህም ያቺ ጨብራራ እናትህ!!! ኪኪኪኪኪ..."

አስር አለቃ ከሳቸው አልፎ እናታቸው ማዋረዱ ቢያንገበግባቸውም የተናጋሪው ማንነት ስለገባቸው እንደገና አማተቡና

"የማርያምን ብቅል ፈጭቻለሁ ቱ! ቱ! ቱ! አንተ ፖለቲከኛ ሰይጣን!" ብለው ወደ መሬት አንዴ ወደሰማይ ትፍ! ትፍ! ቀጠል አድርገውም " አንተ ክፋ አውቄኻለው እንዲ አቅልሎ የሚጠራኘ እንዳንተ ያለው ቀላል እንጂ ሌላ እንደማይሆን መች አጣሁት?" ካሉ በኀላ ቆይ ላግኘህ ሚመስል ዛቻ ከዘራቸውን ነቀነቁና ነጠቅ ነጠቅ ብለው በመራመድ ወደቤታቸው ገቡ፡፡

ሰይጣንም አጀንዳውን ከፍቶ "አስር አለቃ ደባልቄ" በሚለው ፊት ለፊት በቀይ እስኪሪቢቶ 'ራይት' አደረገ፡፡ መንገዱንም ቀጠለ! እየሳቀ እና እያፏጨ...! ይሄ ሸፋፋ ለዛሬ ይበቃዋል ሲበሳጭ ይደር፡፡ ነገ ደሞ በተመቸኘ ሰዓት ብቅ ብዬ ነጅሼው እሔዳለሁ፡፡ አለና እየሳቀ መንገዱን ቀጠለ፡፡

አስር አለቃ ቤት ግራና ቀኘ ባሉት ጫት ቤቶች ተኮልኩለው ጫት የሚቅሙትን ወጣቶች በኩራት እየተመለከተ
"ርስቴ እየተስፋፋ ነው!" ብሎ እየኮራ ቁልቁቅል ወደ ወንዙ!

በእርግጥም ሰይጣን እንዳሰበው አስር አለቃ ሌሊቱን እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደረው፡፡ እንደዛ ያበሻቀጣቸው ሰይጣን ነው ለማለት ጥርጣሬ ገባቸው "እኔ የትኛው ቅድስና ኖሮኘ ሊፈትነኘ ይመጣል?"
አሉ ለራሳቸው፡፡ እንደውም አንዱ ጎረቤታቸው ተደብቆ እንደሰደባቸው ጠረጠሩ፡፡ "ማን ሊሆን ይችላል? ሌሊቱን ሙሉ ተብሰለሰሉ ፡፡

"ይች ጎረቤቴ የትነበርሽ ትሆን እንዴ? የለም ድምፁ የወንድ ነው፡፡ ግንበኛው አሰፋ መሆን አለበት እሱ ለካ ለሥራ ክፍለሃገር ከሄደ ሁለት ወሩ... እና ማናባቱ ነው...፡፡" ወደ ንጋቱ ላይ አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው፡፡ አረጋ!! ድንበር እየገፋ የበጠበጣቸው ጎረቤታቸው!! አረጋ! እሱስ ሚስታቸውን በምኞት ዓይኑ የሚቃኘ ጥጋበኛ ነው ድምፁ መጣላቸው ራሱ ነው!

"አገኘሁት ብለው ዘለው ከአልጋቸው ተነሱ፡፡ ሚስታቸው እማማ የውብዳር በአስር አለቃ አነሳስ ደንግጠው

"በስማም ምን ሆኑ? ሲሉ ጠየቁ

"ዝም በይ ሸፋፋ!" ሲሉ ሚስታቸውን ሰደቧቸው ከሰይጣን በተዋሷት ያደረች ስድብ፡፡ አስር አለቃ ከዛ በፊት ሚስታቸው ሰድበው አያውቁም ነበር፡፡ ልብሳቸውን ለባብሰው እየተጣደፉ ሲወጡ ሚስታቸው አልጋው ላይ ሆነው አሰቡ

"ይሔን ሁሉ ዘመን ዓይቶት የማያውቀውን የእግሬን መንሻፈፍ ዛሬ እንዴት ታየው? ምናልባት ወጣት ሴት ዓይቶ ይሆን? ማን ያውቃል ...? ባላቸውን ካገቧቸው ጀምሮ ዛሬ ገና ተጠራጠሩ፡፡

ልጃቸው ስንቄ እንደ ሁልጊዜው ከመኘታዋ ተነስታ እያንጎራገረች ነበር፡፡ ለሙዚቃ ከፍተኛ ፍቅር ያላት ስንቄ በተለይ የአስቴርን አወቀን ዘፈኖች ስትዘፍን ታስደምማለች፡፡ ዛሬ ግን እናቷ ድንገት አንባረቁባት

"ወዲያ ዝም በይ! ምን በጧቱ ታንቋርሪብኛለሽ!"

ስንቄ በእናቷ ንግግር ክፉኛ ተበሳጨች፡፡ እስከዛሬ ሲያንቋርር ነበር "የኔ ልጅ ድምጿ ብቻ የወፍ ዘር የሚያረግፍ..." እያሉ ዛሬ ታዲያ ምን ነካቸው? ስታምሰለስል ድንገት ጓደኛዋ ሊበን ደወለ፡፡

ዛሬ "ሰርፕራይዝ" ሊያደርጋት ጓደኞቹን አዘጋጅቶ እየጠበቃት ነው፡፡ እንድታገባው ሊጠይቃት ወስኗል ጓደኞቹ ጋር ቤቱ ቅልብጭ ያለ ፕሮግራም አዘጋችቶ ድንገት ሊነግራት የቃል ኪዳን ቀለበቱን አዘጋጅቶ በጉጉት እየጠበቃት ነው፡፡

"ሄሎ!" አለች እንደከፋት

"ሄሎ...! ምነው ድምፅሽ?" አላት እንባ ተናንቋት ስለተናገረች ድምጿ በእርግጥም ድክም ብሎ ነበር፡፡

"ድምፄ ምን ሆነ? ስትል ጠየቀችው፡፡

"ተንቋረረ ልበል?" አላት ፈገግ ብሎ፡፡ ስልኩን ጆሮው ላይ ጠረቀመችበት፡፡

ዘፋኘነትም ከዚህ በኀላ ዋጋ እንደሌለው ገባት፡፡ አርፋ የፀሀፊነት ሥራዋን ለመስራት ወሰነች፡፡ "አንቋራሪ ድምፅ " ያውም በእናቷና በምቶደው ፍቅረኛዋ የተመሰከረበት...፡፡ እስከዛሬ ሰው ፊት 'ስታንቋርር' ሁሌም ሲታዘባት በሹክሹክታ ሲቀልድባት እነንደኖረች ተሰማትና አፈረች!!

###
ኡኡኡኡኡኡኡኡኡ....ከወደውጪ ድምፅ ተሰማ...........

ክፍል ሁለት ይቀጥላል

#ካሉበት_አርባ_ክንድ_ርቆ ከቆመ በኀላ፡፡ እኔ እንደጨመርኩበት ልብ ይሏል

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ
😊😊😊😍😍🙏🙏
AB PHOTOGRAPHY


r.....for reflection

ምስሉን ተጭነው ይመልከቱ 📸📸 ቴክኖ ስፓርክ kb ወንድሜ ስልክህን እንዳነሳበት ስለሰጠኸኘ አመሰግናለሁ😍😍🙏🙏

@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
ክፍል 2

ኡኡኡኡኡኡኡኡኡ....ከወደውጪ ድምፅ ተሰማ፡፡ አስር አለቃ ጎረቤታቸውን በዱላ አናቱን ብለው በሩ ላይ ደፍተውት ነበር፡፡

ሰይጣን አጀንዳውን ይዞ አስር አለቃ ግቢ ሲደርስ ነገር ተደበላልቆ ጠበቀው፡፡ ጉዳዩን በጥንቃቄ አጣራና አጀንዳው ላይ እንዲህ ሲል ከተበ "የአስር አለቃው ጉዳይ ከእቅድ በላይ ተፈፅሟል፡፡"

ሦስት ፖሊሶች ኮሌታቸው ጨምድደው ወደያዟቸው አስር አለቃ ጆሮ ጠጋ አለና "አንተ ሸፋፋ! ስማ..! አሁን በግድያ ሙከራ ዘብጥያ ትወርዳለህ የተበደረው ጎረቤትህ ተሽሎት ወደ ቤቱ ይመለሳል..፡፡ ያች አንቋራሪ ልጅህም የትም ስታንቋር

ር ስለምትውል ቤትህ ሰው የለም፡፡ ሚስትህና ጎረቤትህ ብቻቸውን እዚህ ሰፊ ግቢ ራስህ አልጋ ላይ...ሂሂሂሂሂሂ ቂቂቂቂቂቂ አይ ሸፋፋው!!

ይልቅ ሚስትህን ዓይንህ እያየ ከምትወሰድ አንዱን ፖሊስ በካራቴ ድፋውና አምልጥ...ወታደር አይደለህ...? አስር አለቃ አይደለህ?.... ኮማንዶ ነኘ እያልክ በየጠላ ቤቱ ስታወራ አልነበር...? ወይስ ዝም ብለህ ስትወሽክ ነው...፡፡"

አስር አለቃ ቀስ ብለው ከጎናቸው የቆመውን ፖሊስ ተመለከቱት፡፡ክስት ያለ ነው...በዛ ላይ የያዘው መሳሪያ የከበደው ይመስላል፡፡ ሁለቱም ፖሊሶች ቢሆኑ ያን ያህል የሚስፈሩ አይደሉም ቀድረ ቀላል ነገር ናቸው፡፡ " ይሔኔንንስ መሣሪያውንም መንጠቅ አያቅተኘ " ሲሉ አሰቡ፡፡ ፖሊሶቹ አስር አለቃን እያጣደፉ ወደ ጣቢያ ወሰዷቸው፡፡

ዷ....! ዷ............መንደርተኛው ከሩቅ የተኩስ ድምፅ ሰማ

"ምንድነው....?"

"እስረኛ ሊያመልጥ ሞክሮ.....ፖሊሶቹ እግሩን ሰንክለው አቆሙት.....!

ሰይጣን በሳቅ ፍርስ አለ፡፡ እናም አጀንዳው ላይ እንዲህ ሲል ፃፈ "የእግሩ ጉዳይ አልቋል አሁን ነፍሱን ማንሻፈፍ ይቀረኛል!!"

ከዛም ሰይጣን ቀይ እስኪሪቢቶ አወጣና እየተፍነከነከ እንዲህ ሲል ፃፈ

"አስር አለቃ አምሳ አለቃ መቶ አለቃ ሻለቃ ጄነራል ሚኒስተር ...ጠቅላይ ሚኒስተር ሁሉም እግር አላቸው፡፡ እንኳን እነርሱ አገርም እግር አላት ስንፈልግ እናንሻፍፋታለን!!!"

ደራሲ #አሌክስ_አብርሃም
#ዙቤይዳ ከሚለው መፅሐፍ

#እግር_በእግር
ለንባብ እንዲመች ተደርጎ የተወሰደ

@jahABP ነኘ አስተያየታችሁን አድርሱኘ
😍😍😍🙏🙏🙏
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
@ABPGD @ABPGD @ABPGD
Forwarded from Bire
ድሳካር.pdf
77.4 MB
ድሳካር.pdf
ድሳካር.pdf


ምርጥ :ልብ አንጠልጣይ
:ፍቅርን
:ስለላን
:ሳይንስን
:ትንቤትን
:መድሃኒቶችን አጠቃሎ የያዘ!!!!

*እመኑኝ.አንዴ ከከፈታችሁ ሳትጨርሱ አታቆሙም!

*ኢትዮጵያን የሚወድ ያንብበው!!!
ብርሃኑ በቀለ ሰንዶታል!!!
*NB..የፈጠራ ክህሎት ያላችሁ ምናባችሁን ስለሚያሰፋው ሳታነቡት አትለፉ!!

*NB..ኢትዮጵያዊነት የሚያንገሸግሻችሁ አታንብቡት!!
ታሪኩ የሚጀመረው በ 2002 ዓ.ም ከቤሩት ወደ አዲስአበባ የሚበረውና ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አይር መንገድ የሆነው ቦይንግ 787 አውሮፕላን ተከስክሶ ከ90 ሰዎች ጋር ባሏ የሞተባት ሎዛ የተባለች ትንታግ ገፀ-ባህሪ የአደጋውን መንስዔ በራሷ መንገድ ለማጣራት የምታደርገውን ውጣ ውረድ በመተረክ ነው።
የሎዛ ይህ ድርጊት በኢትዮጵያና በሊባኖስ አይር መንገዶች አልተወደደላትም። እንዲያውም በግዙፉ ቦይንግ ካምፓኒ እንደ ጭራቅ እንድትታይና እሷን ማስወገድ የመጨረሻ አማራጫቸው አድርገው እንዲወስዱ አነሳሳቸው።

ሳታውቀው እንዲህ አይነት አጣብቂኝ ውስጥ የገባችው ሎዛ ገለልተኛ የአደጋው መንስኤ አጣሪ ኮሚቴ ያወጣውን ድምዳሜ ስታይ ይብሱኑ እንድትበሳጭና ነገሩን ገፍታበት ትክክለኛውን የአደጋውን መንስዔ በራሷ መንገድ ማጣራት በአደጋው ለተቀጨው ባሏ ጥልቅ ፍቅሩን የምትገልጽበት አይነተኛ ማካካሻ አድርጋ ወሰደችው።

ግን ደግሞ የውርደት ካባ ላለመከናነብ በመላው ዓለም የዕዝ ሰንሰለቱን የዘረጋው የቦይንግ ካምፓኒና ስሙ ምስጢራዊ የሆነ ድርጅት ሎዛን ለማስወገድ የመጨረሻ ካርዳቸውን መዘዋል--ግብግቡ የሚጀምረው እዚህ ጋ ነው እንግዲህ !

መጽሐፉ ልቦለዳዊ ቢሆንም የተከሰቱ እውነተኛ ሁነቶች ላይ ተንተርሶ የተጻፈ ነው(በ2002 ዓ.ም ከቤሩት አዲስአበባ በረራውን ያደረገ ቦይንግ 787 አውሮፕላን ተከስክሶ 90 ያህል ሰዎች እንደተቀጠፉ ልብ ይሏል )።

በተያያዘና ተመጋጋቢ በሆነ ሁኔታ የተማሩ የኢትዮጵያ ምሁራን ከዚህ በፊት ባልተካሄደበት መንገድ ኢትዮጵያን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ቁጥር አንድ ሀገር ለማድረግ እንቅስቃሴውን ሲያጧጥፉ መጽሐፉ ይተርካል። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን በቴክኖሎጂ ለማመንደግ የተነሳሱ ናቸው። ይህ ሁኔታ የእርዳታ ድርጓቸውን እየበተኑ ጥሬ እቃችንን በሚያጋብሱ ምዕራባውያን አልተወደደም--ሌላ ግብግብ!


በመጨረሻም ኢትዮጵያ በራሷ ባንዲራ ያጌጠች ሳታላይት ስታመነጥቅ የመጽሐፉ ሽፋን ላይ ይታያል።( ልብ በሉ! ይህን ሽፋን ይዞ መጽሐፉ የታተመው በ2008 ዓ.ም ነው)። ይህ ነገር መጽሐፉን ትንቢታዊ ያደርገዋል። ምክኒያቱም ከሁለት ዓመት በኋላ በቻይና ጀርባ አሳዝላም ቢሆን ኢትዮጵያ የራሷን ሳታላይት አመጥቃለች!


ሌላውን ከመጽሐፉ ......

መጽሐፉን በነጻ በ PDF ለማውረድ ከታች ያለውን link ተጠቀሙ!!!

ምርጥ :ልብ አንጠልጣይ
:ፍቅርን
:ስለላን
:ሳይንስን
:ትንቤትን
:መድሃኒቶችን አጠቃሎ የያዘ!!!!

*እመኑኝ.አንዴ ከከፈታችሁ ሳትጨርሱ አታቆሙም!

*ኢትዮጵያን የሚወድ ያንብበው!!!
ብርሃኑ በቀለ ሰንዶታል!!!
*NB..የፈጠራ ክህሎት ያላችሁ ምናባችሁን ስለሚያሰፋው ሳታነቡት አትለፉ!!

መልካም ንባብ
Kazin A better way to shop for health & beauty!We’re more than just your local pharmacy, we’re your friends we provide ur needs wz top secret,safe n deep down detail  personal advise.
A pharmacy for all of your needs only single prescription no worries we deliver it to ur home
A pharmacy your family can trust we r Always there to care,Caring beyond prescriptions.
Not just a pharmacy, but a family.
Look & feel better 4less!!

Address: saris addis sefer egregnia dildy sir ye hana maryam taxi meyazha gar

For any comments, call 0910551631 / 0912179203

@kazinpharm12 @kazinpharm12 @kazinpharm12
The secret of zion chalice
የጽዮናዊዝም ጸዋ ማህበር ሚስጥር!

ኢትዮጵያን ጨምሮ የ አለምን ታላላቅ ሚስጥራት ዶሴን በመሰብሰብ፣ በማጥናት፣ እንዲሁም በረቀቀ መንገድ የራስ ለማድረግ በተለያየ ዘመን እጂግ ሚስጥራዊ የስለላ ድርጅቶች እና የጸዋ ማህበራት ተመስርተዋል።
ከማህበራቱ ጥንክርና የተነሳ ለበርካታ መቶ አመታት ሰንሰለታቸው ሳይቋረጥ፣ ሚስጥራቸው ሳይገለጥ፣ ማንነታቸውም ይፋ ሳይወጣ፣ ዘመንን ያስረጁ፣ እጂግ ተጽኖ ፈጣሪ የስለላ ድርጅቶች ሁነ የጸዋ ማህበራት ይገኛሉ። ዛሬም ድርስ ጓዳችን የምትፈጸም እያንዳንዷን የሀገር ህልውና በቀላሉ ለማወቅ እጂግ ሚስጥራዊ በሆነ የስለላ መረብ ይጠቀማሉ ሀገራችን በዚህ ተንኮለ ከተጠለፈች ቆየች ።

በተለይ የጽዋ ማህበራት አንዳንዶቹ እጂግ በረቀቀ መልኩ ከመከናወናቸው የተነሳ ህልውናቸው ያለ እስከማይመስል ድረስ ህቡዕ ናቸው። ሚስጥራቸውም ከማህበራቸው የሚወጣው ከማህበሩ በድንገት አፈንግጦ የወጣ በሌሎች ማህበራት የተሰለበ ሰው ሲኖር ብቻ ነው ።

ከእኒህ ሚስጥራዊ የጽዋ ማህበራት አንዱ እና ዋናው የጽዮን የጽዋ ማህበራት ነው።
ጸዮናዊነት በሂብሪው እየሩሳሌም የሚል ትርጉም ሲኖረው ይህም ግንደ ቃሉ የተወረሰው ከመጻህፍ ቅዱስ ነው።
ይህ ሃይማኖታዊነቱ የገነነ፣ በፖለቲካውም ስር የሰደደ፣ እንቅስቃሴ በዘመናዊ መልክ በ19 ኛው ክፈለ ዘመን ቢቋቋምም ለበርካታ መቶ አመታት ከጀርባው ሚስጥራዊ እንቅስቃሴወችን ሲያከናውን የኖረ ማህበር ነው።
አሁን አሁን ይህንን ጽዮናዊነት መጠሪያ አለም እንዲረዳው የተደረገው በቋሚነት እስራኤላውያንን እንደ አሽዋ ከተበተኑበት አህጉራት ወደ አገራቸው ለመሰበሰብ የተቋቋመ ታላቅ ዝና ያለው ማህበር እንደሆነ ብቻ ነው።
ነገር ግን ይህ የጽዋ ማህበር እንደ አውሮፖ የዘመን ስሌት በ 1099 ወይም 11ኛው መቶ ክ/ዘመን በ አውሮፓ የተበተኑት ሊቃውነት በሚስጥር ተሰባስበው የመሰረተቱ የጽዮን ቤተ እምነት የተሰኘው ሃይማኖታዊ ተቋም በገሃዱ አለም የሚገኝ ሚስጥራዊ የሆነ ድርጂት ነው።

በ1975 በፖሪስ ብሄራዊ ቤተ መዛግብት (ቢብልዮቴክ ናስዮናስ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው ና ሚስጥራዊው ሰነድ( ሌ ዶስዮ ስክሬ) ተብሎ የሚታወቀው የብራና ጽሁፍ እንደ ሰረ አይዛክ ኒውተን፣ ሳንድሮ ቦቲቼሊ፣ ቪክቶር ሂዩጎ፣ እና ገናናው ሊኦናርዶ ዳ ቬንች፣ ያሉ በርካታ በርካታ የጽዮን ቤተ እምነት አባላትን ስም ይፍ አድርጓል።

እኒህ አለም ላይ በዘመናቸው ገናና የነበሩ ሰወች ከተመሰረተበት ከ1099 እስከ 21ኛው ክ/ዘመን በተለያየ ዘመናት ተጽኖ ፈጣርያን ግለ ሰቦች የሆኑ የሚስጥሩ የጽዮን ማህበር መሪወችም ነበሩ።

ይህ ማህበር ለ900አመታት አካባቢ ሚስጥሩ እንደ ተጠበቀ፣ ህቡዕ እንቅስቃሴው እንደ ቀጠል ፣ አለም ላይ የነበሩ ሚስጥራዊ ኩነትና ታቦተ ጽዮንን ጨምር የቅዲስ ጽዋውን ቅርሶችን እንቅስቃሴወችን ሲመረምሩ ለመውሰድም ሲጥሩ እና ፍላጎታቸውን በስውር ሲያስፈጸሙ ኑረዋል።

ይህ ህቡዕ ድረጂት ሚስጥሩ በፖሪሱ ቢብልዮቴክ ናስዮናል ሚስጥራዊ ሰንድ እስከተጋለጠ ድረስ በርካታ እንቅስቃሴወቹን ከውኗል።

የእስራኤሉ የስለላ ድረጂት ሞሳድ ን ጨምሮ የጽዮን ፕሮቶኮሎች ከፍተኛ የመንግስት አካላት ና ፖለቲከኞች ጭምር ያሉበት አይሁዳውያኑ ስብስብ ወደ ፊት ክርስቶስ ይወለዳል በሚል አሁን በቅረብ የሰሎሞን ቤተ መቅደስን ገንበተው የሰሎምንን ታቦት የጽዮንን ጽላት ይጠባበቃሉ።

በእርግጥ የሌዋዊው ሙሴ ጽዮን፣ የሰሎሞን መጽናኛ ታቦተ ጽዮን፣ ከ እስራኤም ምድር ወደ ኢትዮጵያ ከመጣች እንሆ ሶስት ሺ አመታትን ስላስቆጠረች በረከት ከ እስራኤል ምድር ጸጋም ከእየሩሳሌም ተነስቷል...ወደ ሀገሯ ትመለስ ዘንድ የቅዱስ ሰሎሞን ምኞቱም ነበረች!
በሰሎሞን ስረወ መንግስት ከመነበሯ የተነሳችውን ጸዮን ወደ ፊት ይወለዳል በሚሉት በመሲሁ ኢየሱስ ትመለሳለች ብለው በቀቢጸ ተስፋ ቤተመቅደሱን አንጸው ጽዮንን ከመነበሯ ኢየሱስን ከዙፋኑ እስኪ መጡ ይጠበቃሉ።

ይህ ታቦተ ጽዮንን ከ ኢትዮጵያ ለመውስድ በተለያዩ አዝማናት ቢሞከርም ከመንበሯ ትነሳ ዘንድ ፈቃደ እግዚአብሔር አይደለምና ፈጽሞ ሊያገኟት አልተቻላቸውም።
በተለይ እስራኤል ከተበታተነችበት አገግማ በ1948 እንደ ሃገር ከተመሰረተች ወዲህ የጽዮን ጽዋ ማህበር ጨምሮ ሞሳድና የተለያዩ ሚስጥራዊ ተቋማት እንደ ኦፐስ ዴይ ያሉ የቫቲካን የካቶሊክ ሚስጥራዊ ማህበር እምነትን ከመመረዝ አንስቶ ታቦተ ጽዮንን ለመውስድ ቢታሰብም ታቦተ ጽዮን የነበረችበት፣ ያለችበት፣ ወደ ፊትም የምትኖርበት፣ ሁኔታ እጂግ መግነጢሳዊ ሃይሏ በጊዜ የሚገለጥ ሚስጥር ነው እንዳሉት አበው ተሰውራባቸዋለች።

እንዲሁም በዚህ ዘመኝ በረካታ ሚስጥራዊ እቃወችን እንዲሁም የአዳምን ኤዶም ''ቅዱሱን ምድር '' ለመውረስ ይሞክራሉ.. .. ግን አይችሉም ።
ይህ የታቦተ ጽዮን ሁነት ለሁለት ሶስት ሽ አመታት ለኢትዮጵያ ፈተና የሆነባት ነገር ቢሆንም አሁን ላይ አላማና ግቡ ተጠምዞ የፖለቲካ አሰላለፉ ተቀይሮ ኢትዮጵያ ለሽ ዘመናት ያጸናትን የወጠራትን ጂማት ለመበጣጠስ እጂግ አሳዘኝ በሆነ ሴራ ተጠልፋለች።
ባልተፈጠርኩ የሚያስብለውን ይህን እለት ይህን ዘመን ይህ ክስተት ሀገሪቱን ሊያፈርስ ህዝቦቿን ሊያጠፋ የመጣብን ውስብስብ ሴራ በእውኑ ያልፍልን?
@ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
@ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
@ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
@RASNAMRUD
የሀገሯ ~  ገመገም
ከጥርሶቿ ~ ግርግም፣
ሳቋ ~ ሲያፍገመግም
ሳልፍና ~ ሳገድም።

አማትሬ ~ ባየው:
ተሰትረው ~ ኑረው
የቅርብ ሩቅ ~ ሆነው።

ኩንስንስ  አመሏ
ጵስጡቂስ ጠረኗ
ኑረት   አኳኃኗ፣            

ዘንጠፍጠፍ እያለ 
ቀልብ እያዋለለ:

የገዛ ጥላዋ 
ብርቅርቅ ገላዋ:

ውልብ ይልብኛል...
የድምጿ ሲርሲርታ
ያቃጭልብኛል።

እናማ......

ምናብ ሀሳብ ሲምስ
ሲያወጣ ሲመልስ፣

ጣዕሙን ሊያጣጥም
ምላስ ሲፈረጥም፣

እፀበሉ ግርጌ
ነጠላ አደግድጌ፣

ስለቴን ላስገባ
በእግዜሩ ሙሀባ፣

መጣሁ ከአድባርሽ
እቤተስኪያን ቅጥርሽ፣

የኔ እንዲያ መዋተት
ደርሶ መንከራተት፣

የኔ እንዲያ መውተረተር
ካንቺ ለመሰተር።

እነሆ አካሏን ጎብኝቶ ጠረኗን በምናቡ ምጎ ካጣጣመ በኃላ በዕውኑ አለም ፍለጋውን ማነፍነፉን ቀጠለ።
አንቺ ሆዬ ወዴት አለሽ?

@ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
@ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹
https://t.me/Rovibookben
ርዕስ:-ሽሽት 🏃‍♀️

አብረንሽ  እንሁን
እንስጥሽ ደስታን
ተንከባካቢሽ እንሁን
ታማኞች እኮ ነን....
ፍቅራችን ከልብ ነው
ሀሰት  የማያውቀው
ንፁህ ልብ ነው ያለን
ምስክሮች  አሉን...
.
.
ብለውኝ ሲቀርቡኝ
ደግሞ ሲጠጋጉኝ
እኔ ሸሻለውኝ.....
እኔ ሮጣለውኝ.....
.
.
ሮጬ ሳበቃ
ሸሽቼ  ሳበቃ
.
.
ስጋት  ይወርሰኛል
ፍርሀት ይገባኛል
ቆይ ቆይ ቆይ...
ይሄን ሁሉ አፍቃሪ
መውደዱን ሁልጊዜ  ነጋሪ
ዕለት ዕለት አውሪ
ደጋግሞ መስካሪ
ገፍቼ  ገፍቼ
ሸሽቼ ሸሽቼ
ማን ላይ እደርስ ይሆን?
ማን ላይ ልወድቅ ይሆን?

ብዬ አስባለው💭
አወጣ  አወርዳለው...
ግን ደግሞ ሃሳቤ ሳይቋጭ
ውስጤም ገና ሳይል ረጭ
መልሴንም ሳላገኝ
መልሴንም ሳላገኝ
ሌላ ሌላ  ወደድኩሽ ባይ
ያላንቺ  እኔ አልኖርም ባይ
ደጃፌ ላይ  ቆሞ
እበሬ ላይ ቆሞ
በሬን ሲያንኳኳ ባይ
በሬን ሲመታ  ባይ
ደጋሚ ለመሮጥ
ደግሞ ለመሯሯጥ
አኮበኩብ ጀመር
እነሳሳ ጀመር


@ከመጻሕፍት ዓለም 🇪🇹

@geez6789
✍️በግዕዛዊት ✨️