Pattern Finance and Investment - ፋይናንስ
417 subscribers
590 photos
6 videos
51 files
34 links
Banking & FInance, Stock market, forex, Fintec and e-commerce
Download Telegram
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
ብሔራዊ ባንክ የRTGS የሥራ ሰዓት እንዲራዘም ወሰነ።

​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ ባንኮች መካከል የሚደረገውን ፈጣን የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት (RTGS) የሥራ ሰዓት እንዲራዘም መወሰኑን ለሁሉም የሥርዓቱ ተጠቃሚዎች በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል።

በዚህም አሁን ላይ በሳምንት 6 ቀን በቀን 9 ሰዓት ይሰራ የነበረው ሥርዓት በቀን ለሁለት ተጨማሪ ሰዓታት እንዲራዘም በማድረግ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጥ ተወስኗል።

ከፊታችን መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ የብሔራዊ ባንክ ውሳኔ የዘርፉ ተዋናዮች በተራዘመው ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ ወደ ባንኮች የሚገቡና የሚወጡ የገንዘብ ዝውውሮችን ያለምንም መስተጓጎል እንዲያከናወኑ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ/ም

Via @tikvahethmagazine