እንደው በፈጣሪ እናት፤ በአመ አምላክ ይሁንባችሁ ወድ የዚህ ቻነልና ግሩጵ ወንድሞቼ እህቶቼ እስስኪ ከላይ ያለችዋን ሶስት ነጠብጣብ ስትነኩት add member የሚል ይመጣል contact ውስ የሏችሁ ዘመድ ጓደኞችና ቤተሰብን add እናድርግ እንመማር 🤲🙏?
❤1
☞ትድረስ ለሰሜናውያን ክርስቲያኖች!
❖ከየኔታ (መምህር) ገብረ መድኅን እንየው
"በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።" (ኤፌ 4፥3)
አክሱም ጽዮን መሳለም እና ክርስቲያን ወገኖቸን ማየት ናፍቆኛል።በሕይወት ያሉት መጠየቅ ለረፉት ማልቀስ ይገባኛል።
ደብረ ዳሞም ናፍቆኛል በገመዱ ተንጨዋልየ ወጥቸ የማገኘው በረከት ናፍቆኛል ።ሁሉም የበረከት እና የታሪክ ቦታዎች ገዳማት ናፍቀውኛል።እናንተስ??ግሸን፣ ላሊበላ..መጥታችሁ አብረን ታቦቱን ስናከብር ባንዲት ቅዳሴ አሜን ስንል ትዝ አይላችሁም??
የማውቃቸውም በስም የማላውቃቸውም ኦርቶዶክሳውያን ናፍቀውኛል። በቃ የሆነውን ሳስበው ልቤን ያርደኛል።ይህንን ስጽፍ እያለቀስሁ ነው።
ሰሜናውያን ወንድሞቸ እህቶቸ ያረፋችሁ ነፍሳችሁን ይማር ፦ በሕይወት ያላችሁ እደምን አላችሁ???
ከአሁን በፊት በሥሁት ፖለቲካ ሊሆን የማይገባው ሁኗል።
ይሁንም እንጂ እስከ አሁን ከሆነው ወደፊት የሚሆነው ይበልጣል። አሁንም በሥሁት ፖለቲካ መጋደል ነው የሚሻለው???
መፍትሄው ግን ከራሳችን ነው።
ምን አልባትም መረዳት ካልቻልን ከሁለት አሥርታት ዓመታት በኋላ በምሥራቅ አፍሪክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ላይኖር ይችላል።የላይ ፈሪ የታች ፈሪ እያላችሁ ማዶ እና ማዶ ሁናችሁ ክርስትና እንዳይኖር ነው የምትፈልጉት???
ዋዜማው የሚሸተው እና የሚያሳየው እንደዚያ ነው።
ለዚህ ደግሞ ብዙ መማር አይጠይቅም የምናየው እና የምንሰማው ብቻ ሊሆን የታሰበውን ይነግረናል።
በተለይም ሰሜኑ ክፍል የትናንት መሠረት የታሪክ እንብርት እንደመሆኑ መጠን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ አይፈለግም።መከራው የጠናበትም አንዱ ለዚህ ነው።
#መፍትሄ አንድ፦
#ክርስቲያን መሆን፦ መምሰል ሳይሆን መሆን መሆን መሆን፦ኦርቶዶክስ ስንሆን፦የአንድ ግንድ ቅርንጫፎች እንሆናለን፣አንድ አካል ህዋሳት እንሆናለን፣የአንድ መስቀል ተሸካሚዎች እንሆናለን፣የአንድ ማህፀነ ዮርዳኖስ ልጆች እንሆናለን፣አንድ ሰርግ ቤት ተጠርተን እንዴት እንባላለን? እንኳን ለምድራዊ መሬት ገና በሰማይ ተስፋ አለን ብለን እንጠብቅ የለምን??
#መፍትሄ ሁለት፦
የሥሁት ፖለቲካ መርዝን መትፋት። ኋላ ቀር የዘር ፖለቲካ የለከፈው አእምሮ ክርስቲያናዊ ሀሳብ ማሰብ አይችልምና።ይሄ መርዘኛ ተንኮል አሳነሰን እነጂ አላበዛንም። አዋረደን እንጂ አላከበረንም ።አስኮነነን እንጂ አላጸደቀንም።በታተነነን እንጂ አላዋሐደንም።በኦርቶዶክሳዊት ልብ መግባባት፦በዐይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ መናበብ ይጠበቅብናል፡፡
#በየግላችን የሰማነውን፣የተባለውን፣የተማርነውን ሥሁት ሀሳብ አውልቀን መጣል እና በኦርቶዶክሳዊነት መሙላት።
በእግዚአብሔር አምሳል መሳል ሁነን መሥራት።
የሚሠራ ሰው ከአንድ የግል ፍላጎት ሰይጣን ጋር ይዋጋል።
የማይሠራ ሰው ግን ከሺህ የፍትወት ሰይጣናት ጋራ ይዋጋል።
#መፍትሄ ሦስት፦
ለተፈጠሩ ችግሮች ሁሉ ኦርቶዶክሳዊ ህዝባዊ መፍትሄ መፈለግ፦በዓላማ ያጋደሉን ፍጹም ዕርቅ አያመጡልንም።
በትርክት ጅራፍ እየተጋረፍን መፍትሄ አይመጣም ኦርቶዶክሳዊነት ግን እውነት እና ሕይወት መፍትሄም ነው።
#መፍትሄ አራት፦
ገዳማዊ እና ሊቃውንታዊ መፍትሄን መጠቀም፦
ከሥሁት ፖለቲካ የተላቀቁ በገዳም ያሉ አባትች እና ሰላማውያን የቤተ ክርስቲያን መምህራን በፊት ቢቀድሙልን የተሻለ ነው።
የተሰበረ የእውነት ልብን ማግኘት አለብን እና ሁነው እንድንሆን የሚያደርጉን፣በጸሎት የሚያጸድቁ በትምህርታቸው የሚያስታርቁን ከፊት ይቅደሙን።
#መፍትሄ አምስት፦
ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በተለይም በሰሜኑ ያለን፣በሀገር ውስጥ እና በሀገር ውጭ ያለን የሚድያ አንድነት መፍጠር፦ መንፈሳዊነታችንን መንፈስ ማድረግ ይጠበቅብናል።
አብዛኛውን የጥላላቻው መርዝ የሚረጨው በሚድያ ስለሆነ አንቲ ባይረስ ሁነን ማስቀረት ይቻላል።
#መፍትሄ ስድስት፦
በሆነው ልክ ለመፍትሄ መሆን፦
መፍትሄው በተዘረጋው ልክ መዘርጋት። በረዘመው ልክ መርዘም።በሥሩ ልክ ሥር መስደድ።
ይበለጠው ግን፦ትንሽ መናገር ።ብዙ መሥራት ነው።
የነፋስ መንፈስ፣የውኀ መፍሰስ፣የብርሃን መመላለስ...የማይከለክለው ኦርቶዶክሳዊ ተግባር።
#መፍትሄ ሰባት፦
እያንዳንዳችን የቤተ ክርስቲያን ችግር ከመሆን መዳን።
የችግራችን ይበልጡን ችግሮች እኛው ነን ። ሌላው በክርስቲያናዊ አንድነታችን ላይ በሴራ ቢሠራ ለዓላማው ነው ። እኛው ግን የምንታረድበትን ቢላዋ እየላስን ነው ችግር የሆነው።
ከሥሁታን መነጠል እና ለመፍትሄ ራሳችንን መስጠት
ችግር ለመፈታፍታት ብለው ራሳቸዉ ችግር የሆኑ ብዙዎች አሉና።
ከአእላፋት ቅዱሳን ኅብረት ጋር እየኖሩ ባዶነት ጽኑ ደዌ ነው።
#መፍትሄ ስምንት
በገባን እና ሊሆን በሚገባው ልክ አሁን ጀምረን መሥራት
ከኦርቶዶክሳውያን ኅብረት መከራ ይልቅ የአልጋ ቁራኛ የደዌ ዳኛ መሆን ይቀላል፡፡
በጽኑ ቆስለናል ።፦ቁስሉም ፈውስ ይፈልጋል ፡፡ ፈውሱም ከአምላካችን እና ከእኛ ብቻ ነው ያለው፡፡
ቁጭ ብሎ ከማንጋጠጥ ለፈውስ መላላጥ ይሻላል፡፡
ችጥሩ አቆሰለን እኛ ግን በዚያው ቆስለን መቅረት የለብንም ፡፡
ቁስላችንንን ለመድኃኒት፦
ምታችንን ለትንሣኤ ፦
መገፋፋታችንን ለእረፍት፦እናድርገው።
ግድ ችግሬን አርቁልኝ አይባልም እንዲርቅ ሠርቶ መገኘት።
መሆን ያለብንን ሳንሆን መሆን ያለበት እንዲሆንልን የምንፈልገው አንድነት አይሆንምና፡፡
#መፍትሄ ዘጠኝ፦
በዚህ ውስጥ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ፦
1.አንድ ሃይማኖት ያለው መሆን አለበት
2.ለአንዲት ሃይማኖቱ ዕውቀት ያለው መሆን አለበት
3.ለኦርቶዶክሳዊት ዕውቀቱ መረዳት ያለው መሆን አለበት
4.በክርስቲያናዊ መረዳቱ ላይ እምነት ያለው መሆን አለበት
5. በኦርቶዶክሳዊ እምነቱ ላይ ተግባር ያለው መሆን አለበት
6.በኦርቶዶክሳዊት ቅዱስ ተግባሩ ላይ ኅብረት ያለው መሆን አለበት
7.በኦርቶዶክሳዊት አሀቲ ኅብረቱ ላይ ለትውልድ የሚተርፍ ዓለማ ያለው መሆን አለበት
8.በኦርቶዶክሳዊት ዓላማው ላይ የመንግሥተ ሰማይ ተስፋ ያለው መሆን አለበት
9.በሰማያዊት ተስፋው ላይ የጸጋ ውሕደት ያለው መሆን አለበት
10.በጸጋ ውሕደቱ አንድ አድራጊ የሁሉም ህሊና መዳረሻ ተዋሕዶተ መንፈስ ቅዱስን የሚናፍቅ መሆን አለበት።
ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ድርሻን ለመወጣት በቅድሚያ በዓላማው አካል መሆን ይጠይቃል።
ለሌላው መትረፍ የሚቻለው መሆን ባለብን መጠን ስንከዎን ነው።
ነው።
#መፍትሄ አሥር፦
ዋናው የሁሉም መፍቻ የማይረሳው።፦ኦርቶዶክሳዊ ኅብረት፦
የኦርቶዶክሳዊነት መገለጫው መንፈሳዊ ህብረት ነው። ኅብረቱም ረቂቅ ኅብረት ነው። አካሉ አንድ ህዋሱ ብዙ የሆነለት
የግዘፍ ህብረት ቢሆን ኑሮ ነፋስ በየት በነፈሰ ውኀ በየት በፈሰሰ ነበር። ክርስቶስ የገነባው ይሄን ኅብረት ነው።
አንድ መንፈስን ተዋህደን ነው ማኅበር የሆነው።ግለኝነት የካፒታሊዝም ሥርዓት ነው።የህብረት ማሳያው መለያው ፍቅር ነው።ዓለምን በክርስትና የሠራት ያ ህብረት ነው፡፡መንፈሳዊ ኅብረት የመንፈስ ስበት ነው፡፡በኅብረት ቢጸልዩ ጸሎቱ እግዚአብሔርን ይቀሰቅሳል፡፡በኅብረት ቢሠሩ ለውጥ ይመጣል፡፡
❖ከየኔታ (መምህር) ገብረ መድኅን እንየው
"በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።" (ኤፌ 4፥3)
አክሱም ጽዮን መሳለም እና ክርስቲያን ወገኖቸን ማየት ናፍቆኛል።በሕይወት ያሉት መጠየቅ ለረፉት ማልቀስ ይገባኛል።
ደብረ ዳሞም ናፍቆኛል በገመዱ ተንጨዋልየ ወጥቸ የማገኘው በረከት ናፍቆኛል ።ሁሉም የበረከት እና የታሪክ ቦታዎች ገዳማት ናፍቀውኛል።እናንተስ??ግሸን፣ ላሊበላ..መጥታችሁ አብረን ታቦቱን ስናከብር ባንዲት ቅዳሴ አሜን ስንል ትዝ አይላችሁም??
የማውቃቸውም በስም የማላውቃቸውም ኦርቶዶክሳውያን ናፍቀውኛል። በቃ የሆነውን ሳስበው ልቤን ያርደኛል።ይህንን ስጽፍ እያለቀስሁ ነው።
ሰሜናውያን ወንድሞቸ እህቶቸ ያረፋችሁ ነፍሳችሁን ይማር ፦ በሕይወት ያላችሁ እደምን አላችሁ???
ከአሁን በፊት በሥሁት ፖለቲካ ሊሆን የማይገባው ሁኗል።
ይሁንም እንጂ እስከ አሁን ከሆነው ወደፊት የሚሆነው ይበልጣል። አሁንም በሥሁት ፖለቲካ መጋደል ነው የሚሻለው???
መፍትሄው ግን ከራሳችን ነው።
ምን አልባትም መረዳት ካልቻልን ከሁለት አሥርታት ዓመታት በኋላ በምሥራቅ አፍሪክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ላይኖር ይችላል።የላይ ፈሪ የታች ፈሪ እያላችሁ ማዶ እና ማዶ ሁናችሁ ክርስትና እንዳይኖር ነው የምትፈልጉት???
ዋዜማው የሚሸተው እና የሚያሳየው እንደዚያ ነው።
ለዚህ ደግሞ ብዙ መማር አይጠይቅም የምናየው እና የምንሰማው ብቻ ሊሆን የታሰበውን ይነግረናል።
በተለይም ሰሜኑ ክፍል የትናንት መሠረት የታሪክ እንብርት እንደመሆኑ መጠን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ አይፈለግም።መከራው የጠናበትም አንዱ ለዚህ ነው።
#መፍትሄ አንድ፦
#ክርስቲያን መሆን፦ መምሰል ሳይሆን መሆን መሆን መሆን፦ኦርቶዶክስ ስንሆን፦የአንድ ግንድ ቅርንጫፎች እንሆናለን፣አንድ አካል ህዋሳት እንሆናለን፣የአንድ መስቀል ተሸካሚዎች እንሆናለን፣የአንድ ማህፀነ ዮርዳኖስ ልጆች እንሆናለን፣አንድ ሰርግ ቤት ተጠርተን እንዴት እንባላለን? እንኳን ለምድራዊ መሬት ገና በሰማይ ተስፋ አለን ብለን እንጠብቅ የለምን??
#መፍትሄ ሁለት፦
የሥሁት ፖለቲካ መርዝን መትፋት። ኋላ ቀር የዘር ፖለቲካ የለከፈው አእምሮ ክርስቲያናዊ ሀሳብ ማሰብ አይችልምና።ይሄ መርዘኛ ተንኮል አሳነሰን እነጂ አላበዛንም። አዋረደን እንጂ አላከበረንም ።አስኮነነን እንጂ አላጸደቀንም።በታተነነን እንጂ አላዋሐደንም።በኦርቶዶክሳዊት ልብ መግባባት፦በዐይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ መናበብ ይጠበቅብናል፡፡
#በየግላችን የሰማነውን፣የተባለውን፣የተማርነውን ሥሁት ሀሳብ አውልቀን መጣል እና በኦርቶዶክሳዊነት መሙላት።
በእግዚአብሔር አምሳል መሳል ሁነን መሥራት።
የሚሠራ ሰው ከአንድ የግል ፍላጎት ሰይጣን ጋር ይዋጋል።
የማይሠራ ሰው ግን ከሺህ የፍትወት ሰይጣናት ጋራ ይዋጋል።
#መፍትሄ ሦስት፦
ለተፈጠሩ ችግሮች ሁሉ ኦርቶዶክሳዊ ህዝባዊ መፍትሄ መፈለግ፦በዓላማ ያጋደሉን ፍጹም ዕርቅ አያመጡልንም።
በትርክት ጅራፍ እየተጋረፍን መፍትሄ አይመጣም ኦርቶዶክሳዊነት ግን እውነት እና ሕይወት መፍትሄም ነው።
#መፍትሄ አራት፦
ገዳማዊ እና ሊቃውንታዊ መፍትሄን መጠቀም፦
ከሥሁት ፖለቲካ የተላቀቁ በገዳም ያሉ አባትች እና ሰላማውያን የቤተ ክርስቲያን መምህራን በፊት ቢቀድሙልን የተሻለ ነው።
የተሰበረ የእውነት ልብን ማግኘት አለብን እና ሁነው እንድንሆን የሚያደርጉን፣በጸሎት የሚያጸድቁ በትምህርታቸው የሚያስታርቁን ከፊት ይቅደሙን።
#መፍትሄ አምስት፦
ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በተለይም በሰሜኑ ያለን፣በሀገር ውስጥ እና በሀገር ውጭ ያለን የሚድያ አንድነት መፍጠር፦ መንፈሳዊነታችንን መንፈስ ማድረግ ይጠበቅብናል።
አብዛኛውን የጥላላቻው መርዝ የሚረጨው በሚድያ ስለሆነ አንቲ ባይረስ ሁነን ማስቀረት ይቻላል።
#መፍትሄ ስድስት፦
በሆነው ልክ ለመፍትሄ መሆን፦
መፍትሄው በተዘረጋው ልክ መዘርጋት። በረዘመው ልክ መርዘም።በሥሩ ልክ ሥር መስደድ።
ይበለጠው ግን፦ትንሽ መናገር ።ብዙ መሥራት ነው።
የነፋስ መንፈስ፣የውኀ መፍሰስ፣የብርሃን መመላለስ...የማይከለክለው ኦርቶዶክሳዊ ተግባር።
#መፍትሄ ሰባት፦
እያንዳንዳችን የቤተ ክርስቲያን ችግር ከመሆን መዳን።
የችግራችን ይበልጡን ችግሮች እኛው ነን ። ሌላው በክርስቲያናዊ አንድነታችን ላይ በሴራ ቢሠራ ለዓላማው ነው ። እኛው ግን የምንታረድበትን ቢላዋ እየላስን ነው ችግር የሆነው።
ከሥሁታን መነጠል እና ለመፍትሄ ራሳችንን መስጠት
ችግር ለመፈታፍታት ብለው ራሳቸዉ ችግር የሆኑ ብዙዎች አሉና።
ከአእላፋት ቅዱሳን ኅብረት ጋር እየኖሩ ባዶነት ጽኑ ደዌ ነው።
#መፍትሄ ስምንት
በገባን እና ሊሆን በሚገባው ልክ አሁን ጀምረን መሥራት
ከኦርቶዶክሳውያን ኅብረት መከራ ይልቅ የአልጋ ቁራኛ የደዌ ዳኛ መሆን ይቀላል፡፡
በጽኑ ቆስለናል ።፦ቁስሉም ፈውስ ይፈልጋል ፡፡ ፈውሱም ከአምላካችን እና ከእኛ ብቻ ነው ያለው፡፡
ቁጭ ብሎ ከማንጋጠጥ ለፈውስ መላላጥ ይሻላል፡፡
ችጥሩ አቆሰለን እኛ ግን በዚያው ቆስለን መቅረት የለብንም ፡፡
ቁስላችንንን ለመድኃኒት፦
ምታችንን ለትንሣኤ ፦
መገፋፋታችንን ለእረፍት፦እናድርገው።
ግድ ችግሬን አርቁልኝ አይባልም እንዲርቅ ሠርቶ መገኘት።
መሆን ያለብንን ሳንሆን መሆን ያለበት እንዲሆንልን የምንፈልገው አንድነት አይሆንምና፡፡
#መፍትሄ ዘጠኝ፦
በዚህ ውስጥ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ፦
1.አንድ ሃይማኖት ያለው መሆን አለበት
2.ለአንዲት ሃይማኖቱ ዕውቀት ያለው መሆን አለበት
3.ለኦርቶዶክሳዊት ዕውቀቱ መረዳት ያለው መሆን አለበት
4.በክርስቲያናዊ መረዳቱ ላይ እምነት ያለው መሆን አለበት
5. በኦርቶዶክሳዊ እምነቱ ላይ ተግባር ያለው መሆን አለበት
6.በኦርቶዶክሳዊት ቅዱስ ተግባሩ ላይ ኅብረት ያለው መሆን አለበት
7.በኦርቶዶክሳዊት አሀቲ ኅብረቱ ላይ ለትውልድ የሚተርፍ ዓለማ ያለው መሆን አለበት
8.በኦርቶዶክሳዊት ዓላማው ላይ የመንግሥተ ሰማይ ተስፋ ያለው መሆን አለበት
9.በሰማያዊት ተስፋው ላይ የጸጋ ውሕደት ያለው መሆን አለበት
10.በጸጋ ውሕደቱ አንድ አድራጊ የሁሉም ህሊና መዳረሻ ተዋሕዶተ መንፈስ ቅዱስን የሚናፍቅ መሆን አለበት።
ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ድርሻን ለመወጣት በቅድሚያ በዓላማው አካል መሆን ይጠይቃል።
ለሌላው መትረፍ የሚቻለው መሆን ባለብን መጠን ስንከዎን ነው።
ነው።
#መፍትሄ አሥር፦
ዋናው የሁሉም መፍቻ የማይረሳው።፦ኦርቶዶክሳዊ ኅብረት፦
የኦርቶዶክሳዊነት መገለጫው መንፈሳዊ ህብረት ነው። ኅብረቱም ረቂቅ ኅብረት ነው። አካሉ አንድ ህዋሱ ብዙ የሆነለት
የግዘፍ ህብረት ቢሆን ኑሮ ነፋስ በየት በነፈሰ ውኀ በየት በፈሰሰ ነበር። ክርስቶስ የገነባው ይሄን ኅብረት ነው።
አንድ መንፈስን ተዋህደን ነው ማኅበር የሆነው።ግለኝነት የካፒታሊዝም ሥርዓት ነው።የህብረት ማሳያው መለያው ፍቅር ነው።ዓለምን በክርስትና የሠራት ያ ህብረት ነው፡፡መንፈሳዊ ኅብረት የመንፈስ ስበት ነው፡፡በኅብረት ቢጸልዩ ጸሎቱ እግዚአብሔርን ይቀሰቅሳል፡፡በኅብረት ቢሠሩ ለውጥ ይመጣል፡፡
❤4